የጌታ ባሪያ የሲሳይ አበበ ገጽ
Kanalga Telegram’da o‘tish
ይህ የቴሌግራም ቻናል ልዩ ልዩ መልእክቶችን እና ትምህርቶችን ማስተላለፊያ ገፅ ነው፡፡
Ko'proq ko'rsatish490
Obunachilar
-224 soatlar
-57 kun
-2030 kun
Postlar arxiv
አብድዩ 1:1-21
1 ጌታ እግዚአብሔር ስለ ኤዶም እንዲህ ይላል፤
ከእግዚአብሔር ዘንድ መልእክት ሰምተናል፤
መልእክተኛውም ወደ አሕዛብ ተልኮ እንዲህ
ብሏል፤
“ተነሡ፤ እርሷን ለመውጋት እንውጣ።”
2 “እነሆ፤ በአሕዛብ መካከል ታናሽ አደርግሃለሁ፤
እጅግ የተናቅህ ትሆናለህ።
3 አንተ በሰንጣቃ ዐለት ውስጥ
የምትኖር፣
መኖሪያህንም በከፍታ ስፍራ ያደረግህ፣
ለራስህም፣
‘ማን ወደ ምድር ሊያወርደኝ ይችላል?’ የምትል፣
የልብህ ትዕቢት አታልሎሃል።
4 እንደ ንስር መጥቀህ ወደ ላይ ብትወጣ፣
ጐጆህንም በከዋክብት መካከል ብታደርግ፣
ከዚያ አወርድሃለሁ”
ይላል እግዚአብሔር።
5 “ሌቦች ወደ አንተ ቢመጡ፣
ዘራፊዎችም በሌሊት ቢገቡ፣
የሚሰርቁት የሚፈልጉትን ያህል ብቻ አይደለምን?
ወይን ለቃሚዎች ወደ አንተ ቢመጡ፣
ጥቂት ቃርሚያ አይተዉምን?
አንተ ግን ምንኛ ጥፋት ይጠብቅሃል!
6 ዔሳው ግን እንዴት ተዘረፈ?
የሸሸገውስ ሀብት ምንኛ ተመዘበረ!
7 ወዳጆችህ ሁሉ ወደ ድንበር ይገፉሃል፤
ጓደኞችህ ያታልሉሃል፤ ያሸንፉህማል፤
እንጀራህን የበሉ ወጥመድ ይዘረጉብሃል፤
አንተ ግን አታውቀውም።
8 “በዚያ ቀን ጥበበኛ ሰዎችን ከኤዶም፣
አስተዋዮችንም ከዔሳው ተራሮች አልደመስስምን?”
ይላል እግዚአብሔር።
9 “ቴማን ሆይ፤ ተዋጊዎችህ ይደነግጣሉ፤
በዔሳውም ተራሮች ያለ ሁሉ፣
ተገድሎ ይጠፋል።
10 በወንድምህ በያዕቆብ ላይ ስላደረግኸው ግፍ፣
በዕፍረት ትሸፈናለህ፤
ለዘላለምም ትጠፋለህ።
11 እንግዶች ሀብቱን ዘርፈው ሲሄዱ፣
ባዕዳንም በበሮቹ ሲገቡ፣
በኢየሩሳሌምም ላይ ዕጣ ሲጣጣሉ፣
በዚያ ቀን ገለልተኛ ሆነህ ተመለከትህ፣
አንተም ከእነርሱ እንደ አንዱ ሆንህ።
12 ክፉ ቀን በገጠመው ጊዜ፤
በወንድምህ ሥቃይ መደሰት አልነበረብህም፤
በጥፋታቸው ቀን፣ የይሁዳ ሕዝብ ሲያዝኑ
ሐሤት ማድረግ አልነበረብህም፤
በጭንቀታቸውም ቀን፣
በትዕቢት ልትናገር አይገባህም ነበር።
13 በጥፋታቸው ቀን፣
በሕዝቤ በር መግባት የለብህም ነበር፤
በጥፋታቸው ቀን፣
በጭንቀታቸው መደሰት አልነበረብህም፤
በጥፋታቸው ቀን፣
ሀብታቸውን መዝረፍ አይገባህም ነበር።
14 ስደተኞቻቸውን ለመግደል፣
በመንታ መንገድ መጠባበቅ አይገባህም ነበር፣
በጭንቀታቸው ቀን፣
የተረፉትን አሳልፈህ መስጠት አልነበረብህም።
15 “በአሕዛብ ሁሉ ላይ፣
የእግዚአብሔር ቀን ደርሷል፤
አንተ እንዳደረግኸው፣ በአንተም ላይ ይደረጋል፤
ክፉ ሥራህም በራስህ ላይ ይመለሳል።
16 እናንተ በቅዱሱ ተራራዬ እንደ ጠጣችሁ፣
አሕዛብ ሁሉ ዘወትር ይጠጣሉ፤
ይጠጣሉ፤ አብዝተውም ይጠጣሉ፤
ከዚህም በፊት እንዳልሆኑት ይሆናሉ።
17 ነገር ግን በጽዮን ተራራ ነጻ መውጣት ይሆናል፤
የያዕቆብ ቤትም እርሷ የተቀደሰች ትሆናለች፤
ርስታቸውን ይወርሳሉ።
18 የያዕቆብ ቤት እሳት፣
የዮሴፍም ቤት ነበልባል ይሆናል፤
የዔሳው ቤት ገለባ ይሆናል፤
ያቃጥሉታል፤ ይበሉትማል፤
ከዔሳው ቤት የሚተርፍ አይኖርም።”
እግዚአብሔር ተናግሯል።
19 የኔጌብ ሰዎች፣
የዔሳውን ተራራ ይይዛሉ፤
ከተራራው ግርጌ ያሉ ሰዎችም፣
የፍልስጥኤማውያንን ምድር ይወርሳሉ፤
የኤፍሬምንና የሰማርያንም ዕርሻ ይይዛሉ፤
ብንያምም ገለዓድን ይወርሳል።
20 በከነዓን ያለው ይህ የእስራኤል ስደተኞች ወገን፣
እስከ ሰራጵታ ያለውን ምድር ይወርሳል፤
በሰፋራድም ያሉ የኢየሩሳሌም ስደተኞች፣
የኔጌብን ከተሞች ይወርሳሉ።
21 የዔሳውን ተራሮች ለመግዛት፣
ነጻ አውጪዎች ወደ ጽዮን ተራራ ይወጣሉ፤
መንግሥቱም የእግዚአብሔር ይሆናል።
አብድዩ 1:1-21
1 ጌታ እግዚአብሔር ስለ ኤዶም እንዲህ ይላል፤
ከእግዚአብሔር ዘንድ መልእክት ሰምተናል፤
መልእክተኛውም ወደ አሕዛብ ተልኮ እንዲህ
ብሏል፤
“ተነሡ፤ እርሷን ለመውጋት እንውጣ።”
2 “እነሆ፤ በአሕዛብ መካከል ታናሽ አደርግሃለሁ፤
እጅግ የተናቅህ ትሆናለህ።
3 አንተ በሰንጣቃ ዐለት ውስጥ
የምትኖር፣
መኖሪያህንም በከፍታ ስፍራ ያደረግህ፣
ለራስህም፣
‘ማን ወደ ምድር ሊያወርደኝ ይችላል?’ የምትል፣
የልብህ ትዕቢት አታልሎሃል።
4 እንደ ንስር መጥቀህ ወደ ላይ ብትወጣ፣
ጐጆህንም በከዋክብት መካከል ብታደርግ፣
ከዚያ አወርድሃለሁ”
ይላል እግዚአብሔር።
5 “ሌቦች ወደ አንተ ቢመጡ፣
ዘራፊዎችም በሌሊት ቢገቡ፣
የሚሰርቁት የሚፈልጉትን ያህል ብቻ አይደለምን?
ወይን ለቃሚዎች ወደ አንተ ቢመጡ፣
ጥቂት ቃርሚያ አይተዉምን?
አንተ ግን ምንኛ ጥፋት ይጠብቅሃል!
6 ዔሳው ግን እንዴት ተዘረፈ?
የሸሸገውስ ሀብት ምንኛ ተመዘበረ!
7 ወዳጆችህ ሁሉ ወደ ድንበር ይገፉሃል፤
ጓደኞችህ ያታልሉሃል፤ ያሸንፉህማል፤
እንጀራህን የበሉ ወጥመድ ይዘረጉብሃል፤
አንተ ግን አታውቀውም።
8 “በዚያ ቀን ጥበበኛ ሰዎችን ከኤዶም፣
አስተዋዮችንም ከዔሳው ተራሮች አልደመስስምን?”
ይላል እግዚአብሔር።
9 “ቴማን ሆይ፤ ተዋጊዎችህ ይደነግጣሉ፤
በዔሳውም ተራሮች ያለ ሁሉ፣
ተገድሎ ይጠፋል።
10 በወንድምህ በያዕቆብ ላይ ስላደረግኸው ግፍ፣
በዕፍረት ትሸፈናለህ፤
ለዘላለምም ትጠፋለህ።
11 እንግዶች ሀብቱን ዘርፈው ሲሄዱ፣
ባዕዳንም በበሮቹ ሲገቡ፣
በኢየሩሳሌምም ላይ ዕጣ ሲጣጣሉ፣
በዚያ ቀን ገለልተኛ ሆነህ ተመለከትህ፣
አንተም ከእነርሱ እንደ አንዱ ሆንህ።
12 ክፉ ቀን በገጠመው ጊዜ፤
በወንድምህ ሥቃይ መደሰት አልነበረብህም፤
በጥፋታቸው ቀን፣ የይሁዳ ሕዝብ ሲያዝኑ
ሐሤት ማድረግ አልነበረብህም፤
በጭንቀታቸውም ቀን፣
በትዕቢት ልትናገር አይገባህም ነበር።
13 በጥፋታቸው ቀን፣
በሕዝቤ በር መግባት የለብህም ነበር፤
በጥፋታቸው ቀን፣
በጭንቀታቸው መደሰት አልነበረብህም፤
በጥፋታቸው ቀን፣
ሀብታቸውን መዝረፍ አይገባህም ነበር።
14 ስደተኞቻቸውን ለመግደል፣
በመንታ መንገድ መጠባበቅ አይገባህም ነበር፣
በጭንቀታቸው ቀን፣
የተረፉትን አሳልፈህ መስጠት አልነበረብህም።
15 “በአሕዛብ ሁሉ ላይ፣
የእግዚአብሔር ቀን ደርሷል፤
አንተ እንዳደረግኸው፣ በአንተም ላይ ይደረጋል፤
ክፉ ሥራህም በራስህ ላይ ይመለሳል።
16 እናንተ በቅዱሱ ተራራዬ እንደ ጠጣችሁ፣
አሕዛብ ሁሉ ዘወትር ይጠጣሉ፤
ይጠጣሉ፤ አብዝተውም ይጠጣሉ፤
ከዚህም በፊት እንዳልሆኑት ይሆናሉ።
17 ነገር ግን በጽዮን ተራራ ነጻ መውጣት ይሆናል፤
የያዕቆብ ቤትም እርሷ የተቀደሰች ትሆናለች፤
ርስታቸውን ይወርሳሉ።
18 የያዕቆብ ቤት እሳት፣
የዮሴፍም ቤት ነበልባል ይሆናል፤
የዔሳው ቤት ገለባ ይሆናል፤
ያቃጥሉታል፤ ይበሉትማል፤
ከዔሳው ቤት የሚተርፍ አይኖርም።”
እግዚአብሔር ተናግሯል።
19 የኔጌብ ሰዎች፣
የዔሳውን ተራራ ይይዛሉ፤
ከተራራው ግርጌ ያሉ ሰዎችም፣
የፍልስጥኤማውያንን ምድር ይወርሳሉ፤
የኤፍሬምንና የሰማርያንም ዕርሻ ይይዛሉ፤
ብንያምም ገለዓድን ይወርሳል።
20 በከነዓን ያለው ይህ የእስራኤል ስደተኞች ወገን፣
እስከ ሰራጵታ ያለውን ምድር ይወርሳል፤
በሰፋራድም ያሉ የኢየሩሳሌም ስደተኞች፣
የኔጌብን ከተሞች ይወርሳሉ።
21 የዔሳውን ተራሮች ለመግዛት፣
ነጻ አውጪዎች ወደ ጽዮን ተራራ ይወጣሉ፤
መንግሥቱም የእግዚአብሔር ይሆናል።
የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል። 2ጢሞ. 3፥16-17
የእግዚአብሔር ሰው የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት ቃል ያስፈልገዋል።
ሰውየው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ ነው።
መጽሐፉ ደግሞ የእግዚአብሔር እስትንፋስ አለበት።
እስትንፋሱ ስላለበት ሕይወት አለው። ሕያውና የሚሠራ ነው።
መጽሐፉ ደግሞ መጽሐፍ የተባለው በመላው ነው።
ለብዙ ነገሮች ይጠቅማል።
ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል።
"ሰው ሆይ፤ መልካም የሆነውን አሳይቶሃል፤ እግዚአብሔር ከአንተ የሚፈልገው ምንድን ነው? ፍትሕን ታደርግ ዘንድ፣ ምሕረትንም ትወድድ ዘንድ፣ በአምላክህም ፊት በትሕትና ትራመድ ዘንድ አይደለምን?"
(ሚክ 6፥8 አመት)
Repost from የጌታ ባሪያ የሲሳይ አበበ ገጽ
"...ኖኅ በዘመኑ ከነበሩት ሰዎች ሁሉ ይልቅ ጻድቅና ነቀፋ የሌለበት ሰው ነበር፤ አካሄዱንም ከእግዚአብሔር ጋራ አደረገ።"
(ዘፍ 6፥9 አመት
እግዚአብሔርን አስቆጥቶ ከሚጠፋ ሕዝብ ጋራ ተነጻጽሮ ጻድቅ ሆኖ መገኘት አንድ ነገር ነው። በእግዚአብሔር መለኪያ ላይ ከፍ ብሎ መገኘት ደግሞ ሌላ፤ “ኖኅ በዘመኑ ከነበሩት ሰዎች ሁሉ ይልቅ ጻድቅና ነቀፋ የሌለበት ሰው ነበር፤ አካሄዱንም ከእግዚአብሔር ጋራ አደረገ” (ዘፍ 6፥9)። ኖህ፣ ተለክቶና ተለይቶ የተገኘ ብቻ ሳይሆን፣ የልኬቱን ደረጃ አምላኩን በመከተል ያጸና ነበር። ዓለምን የኮነነው እምነቱ ባካሄዱ ታየ። አካሄዱም መርከቡ ላይ አውጥቶ ሸሸገው።
"...ኖኅ በዘመኑ ከነበሩት ሰዎች ሁሉ ይልቅ ጻድቅና ነቀፋ የሌለበት ሰው ነበር፤ አካሄዱንም ከእግዚአብሔር ጋራ አደረገ።"
(ዘፍ 6፥9 አመት)
