Gulele inspection Directorate
1 372
Subscribers
No data24 hours
+197 days
+2530 days
Posts Archive
ማሳሰቢያ ፡- በጉለሌ ክ/ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ስር ለምትገኙ የጉድኝት ማዕከል ሱ/ቫይዘሮች በሙሉ፡፡
እንደሚታወቀው የ2016 በጀት ዓመት የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት የስታንዳርድ ኢንስፔክሽን የደረጃ ፍረጃ ስራ ከታህሳስ ወር ጀምሮ እንደሚሰራቀደም ብለን ያሳቅን መሆኑ ይታወቃል ፡፡
በመሆኑም በመመሪያው መሰረት ሱ/ቫይዘሮች ተቋማት ያለባቸውን ክፍተቶች ተረድተው አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ በቃል ግብረመልስ ላይ መገኘት እንዳለባቸው አውቃችሁ በተላከው የታህሳስ ወር የትምህርት ተቋማት የኢንስፔክሽን መርሀግብር መሰረት በየጉድኝት ማዕከላችሁ ስር በሚገኙ ትምህርት ተቋማት የቃል ግብረመልስ ላይ በመገኘት የተለመደው ቅንጅታዊ ስራችን እንዲጠናከር ከታላቅ አክብሮት ጋር እናሳስባለን ፡፡
ከሰላምታ ጋር
ማሳሰቢያ ፡- በጉለሌ ክ/ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ስር ለምትገኙ የጉድኝት ማዕከል ሱ/ቫይዘሮች በሙሉ፡፡
እንደሚታወቀው የ2016 በጀት ዓመት የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት የስታንዳርድ ኢንስፔክሽን የደረጃ ፍረጃ ስራ ከታህሳስ ወር ጀምሮ እንደሚሰራቀደም ብለን ያሳቅን መሆኑ ይታወቃል ፡፡
በመሆኑም በመመሪያው መሰረት ሱ/ቫይዘሮች ተቋማት ያለባቸውን ክፍተቶች ተረድተው አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ በቃል ግብረመልስ ላይ መገኘት እንዳለባቸው አውቃችሁ በተላከው የታህሳስ ወር የትምህርት ተቋማት የኢንስፔክሽን መርሀግብር መሰረት በየጉድኝት ማዕከላችሁ ስር በሚገኙ ትምህርት ተቋማት የቃል ግብረመልስ ላይ በመገኘት የተለመደው ቅንጅታዊ ስራችን እንዲጠናከር ከታላቅ አክብሮት ጋር እናሳስባለን ፡፡
ከሰላምታ ጋር
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የመምህርነት የስራ ቅጥር ማስታወቂያ!
(ህዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም)
ለመመዝገብ ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdxUL1wAfiSGg1hOhpblCLTOqFHFBu3Iu2nx-R401Opy8525g/viewform
ማሳሰቢያ
ምዝገባ በአካል የማይከናወን ሲሆን ከላይ በተገለፀው ማስፈንጠሪያ ላይ ብቻ የሚፈፀም ይሆናል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- [email protected]
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
ጥብቅ ማሳሰቢያ ፡- በአራዳ ፣ቂርቆስ እና ጉለሌ ክ/ከተማ አስተዳደር ለምትገኙ የ አጫጭር ማሰልጠኛ ተቋማት በሙሉ ፡፡
እንደሚታወቀው ከመስከረም 22 ጀምሮ ለእያንዳንዱ ተቋም በወጣለት መርሀ ግብር መሰረት የስታንዳርድ (የውጭ) ኢንስፔክሽን የደረጃ ፍረጃ ስራ እየተሰራ መሆኑ ይታወቃል ፡፡ በነገር ግን በአብዛኞቹ ተቋማት አመራሮች ለስራው ቀና ትብብራቸውን በማሳየት ስራው በተያዘለት መርሀ ግብር መሰረት እየተሰራ ያለ ቢሆንም ጥቂቶቹ ደግሞ አሳማኝ ያልሆኑ የተለያዩ ምክንያቶችን በመደርደር በግዴለሽነት ባለሙያዎችን ያለአግባብ ከማንገላታታቸውም በተጨማሪ ስራውን እያስተጓጎሉ ይገኛሉ ፡፡
በመሆኑም እስከአሁን ችግሩን የፈጠሩ ተቋማት በመመሪያው መሰረት ተጠያቂ የምናደርግ መሆኑን እያሳሰብን በቀጣይ ቀሪ የተቋማት አመራሮች ከዚህ ትምህርት በመውሰድ በወጣላችሁ መርሀግብር መሰረት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ በተቋማችሁ ተገኝታችሁ ተግባራዊ እንድታደርጉ በጥብቅ እናሳስባለን ፡፡
ማሳሰቢያ ፡- ለአራዳ ፣ቂርቆስ እና ጉለሌ ክ/ከተማ አስተዳደር ቴ/ሙያ ትምህርትና ስልጠና ጽ/ቤት ፡፡
እንደሚታወቀው ከመስከረም 22 ጀምሮ በቴ/ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የስታንዳርድ ኢንስፔክሽን የደረጃ ፍረጃ ስራ እየተሰራ መሆኑ ይታወቃል ፡፡ በመሆኑም በመመሪያው መሰረት ሱ/ቫይዘሮች ተቋማት ያለባቸውን ክፍተቶች ተረድተው አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ በቃል ግብረመልስ ላይ እንዲገኙ ያሳወቅን ቢሆንም እስከአሁን ድረስ እየተገኙ ስላልሆነ የቡድን መሪዎችና አመራሮች በየወሩ በቴሌግራም እየለቀቅን ባለው የተቋማት የኢንስፔክሽን መርሀግብር መሰረት ሱ/ቫይዘሮችን በመመደብ በየክ/ከተማችሁ በሚገኙ ማሠልጠኛ ተቋማት የቃል ግብረመልስ ላይ እንዲገኙ በማድረግ ቅንጅታዊ ስራችን እንዲጠናከር ከታላቅ አክብሮት ጋር እናሳስባለን ፡፡
ከሰላምታ ጋር
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
ጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት
Repost from N/a
Photo unavailableShow in Telegram
ጥንቃቄ ለወላጆች!
15 አመቱ ነው።ሳቢር ሬድዋን። አጋቾች ከቤት አባብለው አውጥተውት ካገቱት በኋላ ቤተሰቡን ከፍተኛ ብር ጠይቁ። ገዳዮቹ ገንዘብ እንኳን እስኪሰበሰብ አልጠበቁም። በአሰቃቂ ሁኔታ ገድለውት ሲያበቁ በሸገር - ጣዊል ሪልስቴት አካባቢ ቆሻሻ መጣያ ገንዳ ውስጥ ጥለውት ተሰውረዋል።
ሟች ተማሪ ሳቢር ሬድዋን ከአንዲት ሴት በተደጋጋሚ ስልክ ሲደወልለት እንደነበር። ደዋይዋ ደብዳቤ ልታደርስልኝ ስለምፈልግ ስልክህን ይዘህ ውጣ እንዳለችው ታውቋል፡፡ ሳቢር ስልክ ሳይዝ ደዋይዋ ወዳለችበት ቦታ መሄዱንና እዚያው መታገቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡
እንዲህ አይነቱ ወንጀል ተስፋፍቶ የስራ እድል እስከመሆን ስለደረሰ ወላጆች ከባድ ጥንቃቄ ሊያርጉ ይገባል።
(Zehabesha)
በ2016 በጀት ዓመት በህዳር ወር የስታንዳርድ ኢንስፔክሽን የሚሰራላቸው የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ዝርዝር የተሸሻለ
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የሥራና ክህሎት ሚንስቴር በ2016 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ገብተው በተለያዩ የሙያ መስኮች ስልጠና የሚወስዱ ተማሪዎች የመግቢያ ነጥብ ይፋ አድርጓል፡፡
(ህዳር 6/2016 ዓ.ም) የሥራና ክህሎት ሚንስቴር በ2016 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ገብተው በተለያዩ የሙያ መስኮች ስልጠና የሚወስዱ ተማሪዎች የመግቢያ ነጥብ ይፋ አድርጓል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒሰትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የመቁረጫ ነጥቡን ይፋ ለማድረግ በተዘጋጀው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳስታወቁት፣ ዜጎች ወደ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የሚመጡት መሄጃ ስላጡ ሳይን ያላቸውን እምቅ አቅም አውጥተው መጠቀም እንዲችሉ ነው፡፡ ይህም የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለዜጎች ዕድል ፈጣሪ አቅሞች እና ተጨማሪ አማራጭ የሚሰጡ ተቋማት ያደርጋቸዋል ብለዋል፡፡
ከባለፈው ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ባለው አዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ መሰረት ከዚህ ቀደም እስከ ደረጃ 5 ብቻ ተገድቦ የነበረው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የእድገት መሰላል እስከ ደረጃ 8 ድረስ እዲሆን ተደርጓል፡፡ ይህም ፖሊሲው ደረጃ ስድስትን ከመጀመሪያ ድግሪ፣ ደረጃ ሰባትን ከማስተርስ እንዲሁም ደረጃ ስምንትን ከዶክትሬት ዲግሪ ትይዩ እንዲሆን አድርጓል፡፡ ስለሆነም በዚህ ዓመት የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ መግባት ቢፈልጉ በደረጃ 6 ገብተው መሰልጠን እንደሚያስችላቸው አመላክተዋል፡፡
Repost from Addis Ababa Education Bureau
ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በደረጃ 6 የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች እንደሚስተናገዱ የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር በዚህ ዓመት በተቀመጠው መስፈርት መሰረት በክልሎች አማካኝነት የሰልጣኞች ምደባ ይካሄዳል ብለዋል፡፡ በዚህም በተያዘው የሥልጠና ዘመን 632 ሺህ በላይ ተማሪዎች የሥራ ገበያውን የሰው ሀይል ፍላጎት መሠረት ባደረገ መልኩ ከደረጃ 1-ደረጃ 5 እንደ ውጤታቸው ተመድበው እንደሚሰለጥኑም ነው ክብርት ሚኒስትር የገለጹት፡፡
በወጣው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ደረጃ አንድ እና ሁለት 110,015 ፤ በደረጃ ሦሰት እና አራት 412,557 እንዲሁም በደረጃ አምስት 110,015 እንደሚሳተፉ የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር በረደጃ ስድስት ደግሞ 2000 የሚሆኑ ሰልጣኞችን ለቀመበል ዝግጅት መደረጉን አመላክተዋል፡፡
የ2016 የስልጠና ዘመን የተዘጋጀው መቁረጫ ነጥብ የ2015 ትምህርት እና የ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12 ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ላይ ተግባራዊ ይሆናል፡፡ ከ2014 ዓ.ም በፊት ለነበሩ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ደግሞ በስልጠና ዘመኑ በነበረው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ይስተናገዳሉ፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ያዘጋጀው የመግቢያ ነጥብ ከዚህ በታች ባለው ሰንጠረዥ ቀርቧል፡፡
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- [email protected]
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
To all government school principals(one from each school)and cluster supervisors coordinators we have orientation on government school evaluation checklist since lisencing ev.will began on Monday
The orientation will be held on Friday at Gulele branch Daki bu.3rd floor at 2:30 in z morning
The orientation will be held on Friday at Gulele branch Daki bu.3rd floor at 2:30 in z morning
Repost from የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
30/2/2016
የጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት በኢንስፔክሽን መመሪያ፣ማዕቀፍ፣በስታንዳርድ እና ቼክሊስት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡
የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት በትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት ለሁለት ቀን ባዘጋጀው ስልጠና ላይ በ2016 በጀት አመት የውጭ ስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ለሚካሄድባቸው አጠቃላይ የትምህርት ተቋማት በኢንስፔክሽን መመሪያ፣ ማዕቀፍ፣ ስታንዳርድ ቼክሊስት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት የጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት የትምህርት ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ክፍሌ ተሻለ ሲሆኑ በስልጠናው ላይ ከግብአት ከሂደት ከውጤት እንዴት እንደሚመዘኑ እና እስታንዳርዱ ምን ምን ይዘት እንደሚያካትት በስልጠናው ላይ በዝርዝር ቀርቧል፡፡
የኢንስፔክሽን መመሪያ እና በቼክሊስት መሰጠቱ ተቋማት ራሳቸውን ቀድመው በማዘጋጀት ለመማር ማስተማሩ ብቁ እንዲሆን ለማስቻል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
Repost from የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
የቅ/ጽ/ቤት ኢንስፔክሽን ቡድን መሪ አቶ መስፍን አበራ በበኩላቸው እንደገለጹት ስልጠናው ለመንግስትና ለግል 50 ተቋማት ከቅድመ አንደኛ እስከ መካከለኛ ደረጃ ላሉ የትምህርት ተቋማት ሲሆን በቀጣይ ተቋማቱ በስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ላይ የደረጃ ፍረጃ ከመካሄዱ በፊት ከግበአት ከሂደት ከመረጃ ስብስብና ከውጤት አንፃር ያሉባቸውን ክፍተቶች ለመሙላት የታሰበ ስልጠና መሆኑን ገልጸዋል፡፡
እንደዚህ አይነት ስልጠናዎች መሰጠቱ ተቋማቱ ያሉባቸውን ክፍተቶች አሻሽለው መማር ማስተማሩ ላይ ተግባራዊ ለውጥ እዲያመጡ እና በስታንዳርዱ መሰረት ያሉባቸውን ክፍተቶች እንዲያዩ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡
በስልጠናው ላይ ርዕሰነ መምህራን፣ሱፐርቫይዘሮች፣የክ/ከተማና ወረዳ ቅ/ጽ/ቤት ቡድን መሪዎች እና የትምህርት ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
Repost from የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
የቅ/ጽ/ቤት ኢንስፔክሽን ቡድን መሪ አቶ መስፍን አበራ በበኩላቸው እንደገለጹት ስልጠናው ለመንግስትና ለግል 50 ተቋማት ከቅድመ አንደኛ እስከ መካከለኛ ደረጃ ላሉ የትምህርት ተቋማት ሲሆን በቀጣይ ተቋማቱ በስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ላይ የደረጃ ፍረጃ ከመካሄዱ በፊት ከግበአት ከሂደት ከመረጃ ስብስብና ከውጤት አንፃር ያሉባቸውን ክፍተቶች ለመሙላት የታሰበ ስልጠና መሆኑን ገልጸዋል፡፡
እንደዚህ አይነት ስልጠናዎች መሰጠቱ ተቋማቱ ያሉባቸውን ክፍተቶች አሻሽለው መማር ማስተማሩ ላይ ተግባራዊ ለውጥ እዲያመጡ እና በስታንዳርዱ መሰረት ያሉባቸውን ክፍተቶች እንዲያዩ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡
በስልጠናው ላይ ርዕሰነ መምህራን፣ሱፐርቫይዘሮች፣የክ/ከተማና ወረዳ ቅ/ጽ/ቤት ቡድን መሪዎች እና የትምህርት ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
Repost from inspection_MoE
Photo unavailableShow in Telegram
የ2015 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ተፈታኞች አቅም ማሻሻያ (Remedial Program) መከታተያ የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ።
==============//==
ጥቅምት 23/2016 ዓ .ም (ትምህርት ሚኒስቴር ) በ2015 የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎች የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም መከታተያ መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆኗል።
የከፍተኛ ትምህርት የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር ) እንደገለጹት በ2016 በግልና የመንግስት ተቋማት የአቅም ማሻሻያ /Remedial Program / የሚከታተሉ ተማሪዎች መቁረጫ ነጥብ እንደተፈተኑት የትምህርት ዓይነት ብዛት 30% እና ከዚያ በላይ ሆኗል ።
በዚህም መሠረት በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር የመቁረጫ ነጥብ የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች 255 የተፈጥሮ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች 234 መሆኑን አስታውቀዋል።
የማህበራዊ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች 218 የማህበራዊ ሳይንስ ለመደበኛና የማታ ሴት ተማሪዎች 200 መሆኑን ተናግረዋል።
ታዳጊ ክልሎች የተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 224 ታዳጊ ክልሎች ተፈጥሮ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 210 መሆኑን ተናግረዋል።
ታዳጊ ክልሎች የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች መግቢያ 192 ታዳጊ ክልሎች ማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች መቁረጫ180 መሆኑን አመልክተዋል።