en
Feedback
ወድሰኒ ​​

ወድሰኒ ​​

Open in Telegram

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ⛪️የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የመዝሙሮች ግጥሞች ከነ ዜሞቻቸው ለማግኘት ወደ ቻናላችን ይቀላቀሉ⛪️ YouTube https://youtube.com/@enamsgn?si=LYkrdnXK7rL--cMv የመዝሙር ግጥም መላክ ወይም ሀሳብ አስተያየት ጥቆማ ካሎት በ @Slamanshdngl ላይ ያድርሱን

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ወድሰኒ ​​

Channel ወድሰኒ ​​ (@enamsgn) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 22 911 subscribers, ranking 3 383 in the Religion & Spirituality category and 1 456 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 22 911 subscribers.

According to the latest data from 22 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -570 over the last 30 days and by -12 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 3.79%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 1.05% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 868 views. Within the first day, a publication typically gains 241 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 7.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ⛪️የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የመዝሙሮች ግጥሞች ከነ ዜሞቻቸው ለማግኘት ወደ ቻናላችን ይቀላቀሉ⛪️ YouTube https://youtube.com/@enamsgn?si=LYkrdnXK7rL--cMv የመዝሙር ግጥም መላክ ወይም ሀሳብ አስተያየት ጥቆማ ካሎት በ @Slamanshdngl ላይ ...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 23 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

22 911
Subscribers
-1224 hours
-1227 days
-57030 days
Posts Archive
​​​​ሰኔ 12 #የቅዱስ_ሚካኤል ዓመታዊ በዓል! እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለእናታችን ቅድስት አፎሚያ አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ። ሰኔ 12 ቅዱስ ሚካኤል እናታችን ቅድስት አፎሚያን ከጠላት ዲያብሎስ እጅ ያዳነበት ፣ እናታችን ቅድስት አፎሚያ እረፍቷ ነው ።እግዚአብሔር ከቅዱሱ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ፣ ከእናታችን ቅድስት አፎሚያ በረከት ተካፋይ ያድርገን ። 👉 በወርኃ ሠኔ መታሰቢያ ከሚደረግላቸው ቅዱሳን መካከል እግዚአብሔርን የሚፈራ የአስተራኒቆስ ሚስት የሆነች የቅድስት አፎምያን ታሪክ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡ ቅድስት አፎምያ በትዳር በነበረችባቸው ዘመናት እግዚአብሔርን ከሚወድ ባለቤቷ ጋር እግዚአብሔርን ስታገለግለው የኖረች ሴት ነበረች፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ እንደነበር ታሪካቸው ይነግረናል፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጉል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡ ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፡፡ የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ ባያት ጊዜ ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ፣ ሌላ ባል አግብታ፣ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡ ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ፤ እነሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ፤ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡ በሠኔ ፲፪ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ሞከረ፡፡ ሰይጣን አስቀድሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንቶስ መጻሕፍትን እየጠቀሰ እንደተፈታተነው ሁሉ ቅድስት አፎምያንም ለማሳመንም አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዳዊትን የመሳሰሉ ደጋግ አባቶችን ታሪክ እየጠቀሰ ወደ ትዳር እንድትገባ ደጋግሞ ወተወታት፡፡ ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና “የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?” በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡ ለጊዜው “በኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም” ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ፡፡ ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን “ድረስልኝ” እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሠኔ ፲፪ ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡ ይህች የታመነች ቅድስት አፎምያ በሰላም እስክታርፍ ጊዜ ድረስ የተጓዘችበትን መንፈሳዊ ጎዳና አስተውለን ይሆን? አስቀድማ ከባሏ ጋር አንድ ሆና በታማኝነት ፈጣሪዋን አገለገለችው፡፡ በኋላም የባሏን ኑዛዜ አክብራ ምንም እንኳን ኃጢአት ባይሆንባትም በሁለተኛ ትዳር ራስዋን ማጠላለፍ አልፈለገችም፡፡ በጎ ሥራ አብልጣ በመሥራት እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ተፋጠነች እንጂ፡፡ ሰይጣን ልጅ አለመውለዷን ተጠቅሞ ያቀረበላትን የጋብቻ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ “መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ መናፍስት ከእግዚአብሔር እንደሆኑ መርምሩ” ተብሎ በቅዱሳት መጻሕፍት የታዘዘውን መመሪያ ተጠቅማ ሰይጣንን በተወክሎ እግዚአብሔር ተቃውማ አሸነፈችው፡፡ የቅዱስ ሚካኤልን ርዳታ ያገኘችውና በሰላም ዐርፋ ወዳገለገለችው እግዚአብሔር በክብር የሔደችው በጽናት ተጋድላ ነው፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በጸሎቷ ይማረን፤ የቅዱስ ሚካኤል የረድኤቱ ኃይል ሁላችንንም ይጠብቀን፣ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

የአፎምያ እረዳት ✞ የአፎምያ እረዳት ነህ ሚካኤል❨፪×❩ ቅሩበ እግዚአብሔር የልዑል ፈጥነህ ድረስልን ስንጠራህ ሚካኤል ፊት ለፊታችን አምላክ ሠደደህ አቀናህልን መንገዱን ጠርገህ የቤንሆርን ምክር አፈረስክ ከልጆችህ ጋር ከነዐን ደረስክ ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን እንጠራሀለን ሚካኤል ብለን        /አዝ = = = = = በቃዲስ ክንፍህ ተዘርግቶልን ደመናው በአንተ ተጋረደልን አብረኸን ልትሆን ጌታ የላከህ አንተ ሚካኤል ታዳጊያችን ነህ ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን እንጠራሀለን ሚካኤል ብለን        /አዝ = = = = = ሙሴ ሲለየን ደጉ አባታችን ሚካኤል ነበር ከላይ መሪያችን የማንነቱ ጉዞ እስኪያበቃ እጅግ እረዳን የኛ ጠበቃ ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን እንጠራሀለን ሚካኤል ብለን        /አዝ = = = = = ሳጥናኤል መክሮን የሀሰት ምክር ሊወስደን ሻተ ሙሴ መቃብር ስለማይጠቅመን አንተ ሠወርከው ምክሩን በታትነህ አስጎነበስከው ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን እንጠራሀለን ሚካኤል ብለን #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።  ╔✞════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

ከሚካኤል በቀርከሚካኤል በቀር የሚያፅናናኝ የለም እረዳቴ እርሱ ነው በመከራዬ ቀን/፪/ ሀዘኔ እጅግ በዝቶ ከሚካኤል በቀር የሚረዳኝ ሳይኖር በስደቴ ዘመን ሰላም ከእኔ እርቆ ከሚካኤል በቀር ጭንቀት አስቸገረኝ በዙሪያዬ ከቦኝ ዛሬ ግን አፅናኜ ከሚካኤል በቀር ሚካኤል ደርሰ ጠላቴ አፈረልኝ ሚካኤል ነው የዳዊት እረዳት ከጎሊያድ ያዳነው ሚካኤል ነው መንፈሳዊ ብርታት ሀይልንም የሰጠው/፪/         /አዝ = = = = = ቃልኪዳኑ ብሩህ ከሚካኤል በቀር ዝክሩን ለዘከሩት ስሙንም ለጠሩት አጋንት አትቀርቡም ከሚካኤል በቀር ስእሉ ባለበት ድርሳኑን ቢደግሙት በረከት ይገኛል ከሚካኤል በቀር በርሱ ቢማፀኑት ከለመኑት በእውነት ሚካኤል ነው በትረ መስቀል ይዞ የሚጠብቀኝ ሚካኤል ነው ከአንበሶች መንጋ የሚታደገኝ/፪/ /አዝ = = = = = በኑሮአችን ሁሉ ከሚካኤል በቀር እርሱ ይመራናል ፈጥኖ ይረዳናል ፈርኦንን ድል ነስቶ ከሚካኤል በቀር ከግብፅ አውጥቶናል በብርሃን መርቶናል የኤርትራን ባህር ከሚካኤል በቀር ከፍሎ እንዳሻገረ ከነአን ደርሰናል ሚካኤል ነው ከበልአም እርግማን እስራኤልን ያዳነ ሚካኤል ነው ዛሬም በአዲስ ኪዳን ክብሩ የገነነ /፪/ ዘማሪ አረጋይ ገ/መድህን          እና ዘማሪት ፀዳለ ጎበዜ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።  ╔✞════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

ልጁ ነኝ ✞ ልጁ ነኝ የሚካኤል ልጁ በቤቱ ያደኩኝ በደጁ የልቤ ብዬ የምጠራው ሚካኤል ለኔ አባቴ ነው❨፪❩ በክንፉ እኔን በእጁ ሰይፍ ይዟል ሚካኤል ሊረዳኝ ቆሟል እንዳስፈሪ እንደ ንጉስ ሠራዊት በቀኜ ነው በቀንና በሌሊት   ሚካኤል አባቴ ለዚ እኮ ነው መመካቴ   ሚካኤል አባቴ ጋሻ ክብሬ ነው ማለቴ   ሚካኤል አባቴ ጎኔ ቆመኽ እንዳቆምከኝ   ሚካኤል አባቴ እኔ ለአለም ምስክር ነኝ      /አዝ = = = = = ልናገር ላውራ ላዚም ልዘምር ከፍ አርጌ ልመስክር መች ይረሳል ልጅነቴ ያሳደገኝ እቅፍ አርጎ በክንፎቹ የከለለኝ   ሚካኤል አባቴ እስከዛሬ ያላልኩትን   ሚካኤል አባቴ በልቤ ውስጥ ያኖርኩትን   ሚካኤል አባቴ ዛሬ ላውራው በአደባባይ   ሚካኤል አባቴ ረድቶኛል ከአባቴ ጋር      /አዝ = = = = = ከተኛሁበት ከእንቅልፌ አንቅቶ ነጻ አወጣኝ እስሬን ፈቶ በጨለማ በወኅኒ ቤት በእስር አብሮኝ ነበር ጠባቂዬ ሚካኤል   ሚካኤል አባቴ በክፉ ቀን ያለ ጎኔ   ሚካኤል አባቴ ያልተለየኝ በድካሜ   ሚካኤል አባቴ ሰው የሚወድ የማይንቅ   ሚካኤል አባቴ በጌታ ፊት ሚያስታርቅ      /አዝ = = = = = ብርቱ እና ኃያል ጽኑ ነው ስሙ ሚካኤል ሞገስ የሆነው ምን ይሆናል ሚካኤልን የያዘ ሰው ምግቡ መና ደመና ነው ሚጋርደው   ሚካኤል አባቴ የአባቶቼ መንገድ መሪ ሚካኤል አባቴ በእኔም ህይወት ታምር ሰሪ   ሚካኤል አባቴ በመንገዴ ቀድሞ ፊቴ   ሚካኤል አባቴ ይስበኛል ወደ ርስቴ 👉ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።  ╔✞════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

✟ተነሳ ህዝቤ ተነሳ✟
📣📣📣" አዋጅ አዋጅ"📢"ያልሰማህ ስማ የሰማህ አሰማ እነዚህ መናፍቃን ከውጭ ሆነው ቤተክርቲያንን መዋጋት ሲያቅታቸው ውስጥ በመግባት በኛ ቆብ በኛ ቀሚስና በኛ መስቀል ኑፋቂያቸዉን እየዘሩ ዶግማችንንና ቀኖናችንን ስርአታችንንና ትሁፊታችንን ለመለወጥ እንቅስቃሴ እያደረጉ እንደሆነ መረጃ ደርሶናልና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ  ምዕመናን በሀገርም በውጪም ያላችሁ ይህንን በመገንዘብ እራሳችሁን እንድጠብቁ ቤተክርስቲያን መልዕክቷን ታስተላልፋለች።"
  ተነሳ ህዝቤ ተነሳ ተነሳ ወገን ተነሳ የጥንቱ እንዳይረሳ የቀድሞ እንዳይረሳ ባገርም በውጪም በየትም ያላችሁ የተዋህዶ ፍቅር ያለ በልባችሁ በሉና ተነሱ ታሪካችሁ ይብራ ምድረ ተሀድሶ ምድረ ሃራትካ          /አዝ = = = = = መጥቷል በኢየሱስ ስም ትጥቅህን ሊያስፈታህ በልና መልሰው የለም አዲስ ጌታ አንዲት ጥምቀትና አንዲት ሃይማኖት አለች ተዋህዶ የተረከብናት          /አዝ = = = = = በነዮዲት ጉዲት በግራኝ አህመድ ገዳም ሲፈርስ አየሁ ካህን ሲታረድ ትላንት የሆነብን ሳይወጣ ቁጭቱ ዳግም ተነሱባት ጡቷን የጠቡት          /አዝ = = = = = በረት ቢያስገቡንም የኤል ልጅ ዝምታ እውነትን ለመግለጥ አንደበት ቢገታ የእውነት ሠይፍ ይዞ የሚፈርድልን እውነተኛው ዳኛ ይምጣ ሰሎሞን        /አዝ = = = = = ከእኛ የሚመስሉ ግን ከእኛ ያልሆኑ አሉ በጥፋት ሀይል የሚሰለጥኑ መክረን አስተምረን እንድትመለስ እድሜ ከሀለውጉስ ከመአርዮስ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

መድኃኔዓለም በማን እንመስልህ መድኃኔዓለም በማን እንመስልህ ቃል አጣን አንተን ሚመጥንህ ቢነገር ቢዘመርልህ ያንተን ነው ላንተ የምንሰጥህ❨፪×❩ መንገድ የምትመራኝ ልታይልኝ አይኔ የልቤ አብርሆት ማያዬ ብርሃኔ ጉዞዬን ያቀናህ ሰላሜ መድህኔ ክበር በአዲስ ዜማ ክበር በአዲስ ቅኔ መድሃኔአለም በሰማይ ዜማ ላንተእልል እልል  '' እንዘምራለን ቀን በቀን ለስምህ '' ክብርህ የቃኘው አዲስ ልዩ ዜማ  '' ለዘለአለም አይቆምም ላንተማ       /አዝ = = = = = ስከፋ ስቸገር አትርቅም ከጎኔ እንደ እናት እንደአባት ታስባለህ ለኔ የማይነጋ ለሊት ማያልፍ የመሰለኝ እንደ ጥላ አለፈ ስምህ ሲከተለኝ መድኃኔዓለም ታማኝ ወዳጅ ነህ ቀርበህ የማትሸሽ '' '' ቀን የከፋለት አትሄድም ሲመሻሽ '' '' መንገደኛ ነኝ ኤማሁስ ምድር '' '' ግባ ከቤቴ ስሰማህ ልደር       /አዝ = = = = = ወዳጄ ሲከዳኝ ጊዜ ሲለውጠው አንተ ግን አንተ ነህ አይደለህ እንደሰው ፈዋሽ ባለዘይት አባቴ ሃኪሜ ስትነካው ሳቅ ሆነ ስቃይና ህመሜ መድኃኔዓለም የምታስብልኝ አባቴ የልቤ '' '' ሁሉን ፈፀምከው ቀድመህ ሃሳቤ '' '' ይኖራል ላንተ ልቤ እየዘመረ '' '' ዝምታ አይችልም ካንተ እየተማረ        /አዝ = = = = = አላጉረመርምም ይህ ቀርቶኛል ብዬ የማያልቅ እንጀራ ከእጅህ ተቀብዬ የልቤን የውስጤን ፈፀምከው በሙሉ አመስጋኝ ነኝ እኔ በሆነልኝ ሁሉ መድኃኔዓለም በሰማይ ዜማ ላንተ እልል እልል '' '' እንዘምራለን ቀን በቀን ለስምህ '' '' ክብርህ የቃኘው አዲስ ልዩ ዜማ '' '' ለዘለአለም አይቆምም ላንተማ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።  ╔✞════●◉❖◉●════✞╗ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

#ተዝካረ_በዓላ_ለማርያም_በደብረ_ምጥማቅ ግንቦት 21 ከሠላሳ ሦስቱ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ደብረ ምጥማቅ ነው፡፡ ደብረ ምጥማቅ ግብጽ ውስጥ በገምኑዲ አቅራቢ የምትገኝ ገዳም ናት፡፡ እመቤታችን ል
#ተዝካረ_በዓላ_ለማርያም_በደብረ_ምጥማቅ ግንቦት 21  ከሠላሳ ሦስቱ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ደብረ ምጥማቅ ነው፡፡ ደብረ ምጥማቅ ግብጽ ውስጥ በገምኑዲ አቅራቢ የምትገኝ ገዳም ናት፡፡ እመቤታችን ልጇን ይዛ በስደት ሳለች ጌታ ‹‹በዚህ ቦታ በስምሽ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ይታነጻል ስሙንም ደብረ ምጥማቅ ይሉታል›› ብሎ ትንቢት ነግሯት ነበር፡፡ ጊዜው ሲደርስም በዚሁ ቦታ በእመቤታችን ስም ቤተ ክርስቲያን ታንጾ ስሙ ደብረ ምጥማቅ ተብሏል፡፡ #በዚህ ቦታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የክርስትናን ሃይማኖት ለመግለጽ ለ5 ቀናት ለክርስቲያኑም ለአረማዊውም በገሀድ ታይታለች፡፡ በዚህም ዕለት በልጇ የመለኮት ብርሃን ከፀሐይ ሰባት እጅ አሸብርቃ መላእክት፣ሊቃነ መላእክት፣ኪሩቤና ሱራፌል ከበዋት ነቢያት፣ሐዋርያት፣ሰማዕታት፣ደናግልና መነኰሳት ሄሮድስ ያስፈጃቸው ሕፃናት ሁሉ ይመጣሉ፡፡ ሱራፌል ማዕጠንት ይዘው እያመሰገኑ ያጥኑ ነበር፡፡ ከሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በነጭ ፈረስ ቅዱስ መርቆሬዎስ በጥቁር ፈረስ በየተራ እየመጡ ይሰግዱላታል፡፡ በዚህም ጊዜ ከቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ ሆና በግልጽ ለሁሉ ትታይ ነበር፡፡ ከፊቷ ብርሃን የተነሣ አምስት ቀን ሌሊቱና ቀኑ አይታወቅም ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ልብሳቸውን ወደ ላይ ሲወረውሩላት የፈቀደችውን ተቀብላ ትልክላቸዋለች፤ ለበረከት ይካፈሉታል፡፡ ከተሰበሰቡትም የሞተ ዘመድ ያላቸው አስነሺልን ሲሏት አስነሥታ በሕይወተ ሥጋ ታሳያቸው ነበር፡፡ እንዲህ እየሆኑ በፍጹም ደስታ አምስቱን ቀን ሰንብተዋል፡፡ ወደ ቤታቸውም ለመኼድ ሲሹ በፊቷ ሰግደው ይሰናበቷታል እርሷም ትባርካቸዋለች፡፡ የበዓሉ መታሰቢያ ከግንቦት 21 እስከ 25 ቀን ነው፡፡ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷ ይደርብን አሜን! ወስብሐት ለእግዚአብሔር! ምንጭ፦መድበለ ታሪክ ፣መዝገበ ታሪክ፣ስንክሳር

ጻድቃኔ ማርያም ✞ ጻድቃኔ ማርያም ደጓ እናቴ መጣው ከደጅሽ አንቺን ብዬ ያጥያቴን ገመድ ፈታሽልኝ የውስጤን ብሶት ተረዳሽኝ ወዳለሽበት ወደ ደጅሽ ስንቄን ሰንቄ ስጓዝ ልጅሽ እንግድነቴን ተቀበልሽኝ ልዩ ፍቅርሽን ገለጥሽልኝ ውስጤ ቢቆሽሽ መች ተፀየፍሽኝ ባዛኙ ልብሽ ይህው ቀረብሽን❨፪×❩ /አዝ = = = = = የተጠማውት አንቺን ነበር እናቴ ፍቅርሽ አሸነፈኝ እራሴን ዳብሰሽ አጽናናሽኝ ብሶቴን ሁሉ አራቅሽልኝ እናትህ አለው አትዘን ብለሽ ተረድተሽኛል ችግሬን አይተሽ❨፪×❩       /አዝ = = = = = የውስጤን ብሶት ስነግርሽ እግርሽ ስር ሆኛ ሳዋይሽ ዝም አላልሽኝም እመቤቴ ቃል ገባሽልኝ ለሂወቴ የጨለመውን ተስፋ አብርተሽ ሰው አርገሽኛል ጤናዬን ሰተሽ❨፪×❩       /አዝ = = = = = የሚገባኝን አርገሽልኝ የተስፋ ስንቄን አሲዘሽኝ ሸኝተሽኛል ወደቤቴ ሁሉን አድራገሽ እመቤቴ ደጅሽ ስመጣ መቼ አፈርኩኝ ምልጃሽ ጎብኝቶኝ ደስታ አገኘሁኝ❨፪×❩ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።  ╔✞════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

ይነበብ ገድሉ ይነበብ ገድሉ ይውጣ ታምሩ ድውይ ይፈወስ ይቀደስ ምድሩ ተክለሃይማኖት አማላጃችን አለ ከእኛ ጋር መሀከላችን አይለወጥም   ተክለሃይማኖት ያለህ ቃል ኪዳን      ተክለሃይማኖት ተክልዬ ስምህ    ተክለሃይማኖት ዛሬም ይሰራል    ተክለሃይማኖት ከተግባር ቤትህ   ተክለሃይማኖት ተሰልፈናል   ተክለሃይማኖት ዳቤህን በልተን   ተክለሃይማኖት ተፈውሰናል     ተክለሃይማኖት          /አዝ = = = = = እጅህ ያለብሰናል   ተክለሃይማኖት የክብር ካባ    ተክለሃይማኖት ከመታሰቢያው   ተክለሃይማኖት መቅደስ እንግባ   ተክለሃይማኖት ስራው ይነገር     ተክለሃይማኖት ለዓለም ሁሉ   ተክለሃይማኖት ታላቅ ነው እና    ተክለሃይማኖት ተክልዬ ገድሉ   ተክለሃይማኖት          /አዝ = = = = = ኢትዮጵያ በራች   ተክለሃይማኖት በስብከትህ   ተክለሃይማኖት ተጠብቀናል   ተክለሃይማኖት በፀሎትህ   ተክለሃይማኖት የአምላክ አገልጋይ   ተክለሃይማኖት ወንጌል ያዘለ   ተክለሃይማኖት በቅዱስ ስሙ   ተክለሃይማኖት ጠላት ቆሰለ   ተክለሃይማኖት         /አዝ = = = = = ጠጣን ፀበሉን   ተክለሃይማኖት ታሸን በእምነቱ   ተክለሃይማኖት ስሙ ሲነሳ    ተክለሃይማኖት ጠፉ አጋንንቱ    ተክለሃይማኖት ኢየሩሳሌም    ተክለሃይማኖት ሆነች ምድራችን   ተክለሃይማኖት ክብራችን በዛ   ተክለሃይማኖት ስለ አባታችን    ተክለሃይማኖት #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

✞ ክርስቶስ ሰምራ ✞ ክርስቶስ ሰምራ ትጉህ መናኝ ነሽ ለሙሽራነት በላይ የታጨሽ ሀብት ትዳርሽን ሁሉንም ትተሽ መናኝ ሁነሻል አምላክ በልጦብሽ ክርስቶስ ሰምራ ልጆቼን ትዳሬን ክርስቶስ ሰምራ ንብረቴን ሳትዪ ክርስቶስ ሰምራ መናኝ አደረገሽ ክርስቶስ ሰምራ ፍቅሩ የአዶናይ ክርስቶስ ሰምራ በቤቱ መጣልን ክርስቶስ ሰምራ አምላክን ብለሽ ክርስቶስ ሰምራ የሞቀ ቤትሽን ክርስቶስ ሰምራ እሱን አስናቀሽ        /አዝ = = = = = ክርስቶስ ሰምራ ዲያቢሎስ ከአምላኩ ክርስቶስ ሰምራ ቢታረቅ ብለሽ ክርስቶስ ሰምራ ከሲኦል ሂደሻል ክርስቶስ ሰምራ እሱን ፈልገሽ ክርስቶስ ሰምራ ትዕቢቱ በልጦበት ክርስቶስ ሰምራ ከሲኦል ጣለሽ ክርስቶስ ሰምራ ሚካኤል ደርሶልሽ ክርስቶስ ሰምራ ከጥልቅ አወጣሽ        /አዝ = = = = = ክርስቶስ ሰምራ ፀሎት ስታደርሺ ክርስቶስ ሰምራ ከባህር ውስጥ ሁነሽ ክርስቶስ ሰምራ ይመላለሳሉ ክርስቶስ ሰምራ አሳዎች በአካልሽ ክርስቶስ ሰምራ ለአስራ ሁለት አመት ክርስቶስ ሰምራ በውስጡ ፀለይሽ ክርስቶስ ሰምራ ሰላም በዓለም ላይ ክርስቶስ ሰምራ ይሁን እያልሺ 👉ዘማሪ አሸናፊ ዘለቀ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

📍ዜናዋን ሰማን ዜናዋን ሰማን ሰማን ዜናዋ የክርስቶስ ሰምራ ፅኑ ተጋድለዋ ቅድስት እናት ናት ንፅሕት እጅግ ያስገርማል የገድልዋ ፅናት አስራ ሁለት ዓመት ስትፀልይ ኑራ ሞገስ አግኝታለች ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ እንናገራለን እኛስ ልእልናዋ እንመሰክራለን የሰማን ዜናዋ     /አዝ = = = = = ያላትን ሁሉትታ ከቤቷ ስትወጣ ከሃብትና ንብረት ቅድስና መርጣ በፅኑ ስራዋ አክሊል ተጎናፅፋ ክብርን ተቀዳጀች መከራውን አልፋ     /አዝ = = = = = እንኳንና ሰው የተማፀናት አጋዥ መከታ ያደረጋት ለዲያብሎስ እርቅን ለምናለች እና ለክርስቶስ ሰምራ ይድረሳት ምስጋና /አዝ = = = = = በቃል ኪዳንዋ የታመነ በአፀድዋ ገብቶ እርሷን ለለመነ በመንግስተ ሰማይ ይኖራል ተከብሮ በክብር በልዕልና ከርሷ ጋር አብሮ 👉ዘማሪ ዲ/ን ፀሐዩ ንጉስ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

የከበረ ዮሐንስም ንጉሥ ሆይ እንዲህ አትበል እንዲህ አንተ እንደምትለው አይደለም የከበረች ድንግል እመቤታችንስ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሆድዋ ውስጥ በነበረ ጊዜ የእርሱ ኅብረ መልክ በሚለዋወጥ ጊዜ ከእርሱ ጋር መልኳ ይለወዋወጥ ነበር። በንጹሕ ብርሌ ውስጥ ውኃ በጨመሩ ጊዜ ውኃ መስሎ እንደሚታይ ወይን ጠጅም ቢጨምሩ ያንኑ መስሎ እንደሚታይ ወይም ከውስጡ በተጨመረው ቀይም ቢሆን ቀልቶ እንደሚታይ ቅጠልያም ቢገባበት ቅጠልያ መስሎ እንደሚታይ። ድንግልም በሆድዋ ውስጥ የልጅዋ መልክ በሚለዋወጥ ጊዜ ከእርሱ ጋራ መልኳ ይለዋወጥ ነበር። እንደ ሮማን አበባ የምትቀላበት ጊዜ አለ እንደናርዶስም የምታብለጨልጭበት ጊዜ አለ የለመለመ ቅጠል የምትመስልበትም ጊዜ አለ ከወለደች በኋላ ግን አልተለወጠችምና ዮሴፍ በአንድ በቀድሞው ኅብረ መልኳ ተወስናለት መልኳን ተረዳ ማለት ነው አለው። በዚያን ጊዜ በንጉሥ አዳራሽ ውስጥ ከወርቅ የተሠራ የእመቤታችን አምላክን የወለደች የድንግል ማርያም ሥዕል ነበረችና አፈ ወርቅ ዮሐንስ ልሳነ ወርቅ ዮሐንስ አፈ በረከት ዮሐንስ መልካም ተናገርክ የሚል ቃል ከእርሷ ወጣ። ንጉሡና ከእርሱ ጋር ያሉት በሰሙ ጊዜ እጅግ አደነቁ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት በዚያን ጊዜ ንጉሥ አዝዞ ወርቅ ሠሪ አስመጥቶ ለከበረ ዮሐንስ የወርቅ ልሳን አሠርቶ ለሚያየው ሁሉ መታሰቢያ ምልክት ሊሆን አምላክን ከወለደች ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ሥዕል ዘንድ ሰቀለው። ቅዱስ ዮሐንስንም ከዚያች ቀን ወዲህ ልሳነ ወርቅ ብሎ ጠራው አፈ ወርቅም ተብሎ እስከዛሬ ተጠራ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሱ ጸሎትና ምልጃ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። (#ስንክሳር_ዘወርኀ_ግንቦት)

#ግንቦት_12 #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ በዚህችም ዕለት የዓለሙ ሁሉ መምህር የሆነ የከበረ አባት ዮሐንስ አፈወርቅ አረፈ፡፡ ይህም አባት ከእስክንድርያ አገር ሰዎች ወገን ነው የአባቱም ስም አስፋኒዶስ የእናቱም ስም አትናሲያ ነው እሊህም እጅግ ባለጸጎች ነበሩ ይህንንም ልጃቸውን በመልካም አስተዳደግ አሳደጉት ትምህርትንና ጥበብንም ሁሉ አስተማሩት እርሱ ወደ አቴና ሒዶ በመምህራን ቤት ተቀምጦ ትምህርትን ሁሉ ተምሮ በዕውቀቱ ከብዙዎች በላይ ከፍ ከፍ ብሏልና። ከዚህም በኋላ ገና በታናሽነቱ መነኰሰ የዚህንም የኃላፊውን ዓለም ጣዕም ንቆ ተወ ከእርሱም ቀድሞ በዚሁ ገዳም ቅዱስ ባስልዮስ መንኵሶ ነበር በአንድነትም ተስማምተው ብዙ ትሩፋትን ሠሩ ወላጆቹም በሞቱ ጊዜ ከተውለት ገንዘብ ምንም ምን አልወሰደም ለድኆችና ለምስኪኖች ሰጠ እንጂ ከዚያም በምንኵስና ሥራ በመጠመድ ፍጹም ገድልን እየተጋደለ ኖረ። በዚያም ገዳም ሶርያዊ ጻድቅ ሰው ስሙ ሲሲኮስ የሚባል መነኰስ ነበረ እርሱም ወደፊት የሚሆነውን በመንፈስ ቅዱስ ያይ ነበር በአንዲት ሌሊትም ለጸሎት እየተጋ ሳለ ሐዋርያትን ጴጥሮስንና ዮሐንስን አያቸው ወደ ዮሐንስ አፈወርቅ ገብተው ጴጥሮስ መክፈቻ ሰጠው ወንጌላዊ ዮሐንስም ወንጌልን ሰጠው እንዲህም አሉት በምድር ያሠርከው በሰማይ የታሠረ ይሆናል በምድርም የፈታኸው ደግሞ በሰማያት የተፈታ ይሆናልና በውስጥህ መንፈስ ቅዱስ ያደረብህ አዲስ ዳንኤል ሆይ የክብር ባለቤት ከሆነ ከታለቅ መምህር ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ወደ አንተ ተልከናልና ዕወቅ እኔም የመንግሥተ ሰማያት መክፈቻ የተሰጠኝ ጴጥሮስ ነኝ። ሁለተኛውም እኔም በመጀመሪያው ስብከቴ በከበረ ወንጌል ቃል አስቀድሞ ነበረ ያልኩ ይህም ቃል በጠላት ላይ የእሳት ሰይፍ የሆነ ዮሐንስ ነኝ። ለአንተም ከክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ወገኖችህ ምእመናንን በቀናች ሃይማኖት ታሳድጋቸው ዘንድ ዕውነተኛ አእምሮ ደግሞ ተሰጥቶሃል። ጻድቅ ሲሲኮስም ይህን ራእይ በአየ ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ ቸር ታማኝ እረኛ ሁኖ እንደሚሾም ዐወቀ። ከዚህም በኋላ በቅዱስ ዮሐንስ ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ በላዩ ወርዶ አደረበትና ብዙ ድርሳናትንና ተግሣጻትን ደረሰ ዲያቆን ሁኖ ሳለም የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍት ብሉያትንና ሐዲሳትን ተረጐመ። በአንዲት ሌሊትም ቅዱስ ዮሐንስ ሲጸልይ የእግዚአብሔር መልአክ በድንገት እንደ በረድ ነጭ በሆነ ልብስ ተገለጠለት ቅዱስ ዮሐንስም ሲያየው ደንግጦ በምድር ላይ ወደቀ መልአኩም አርአያውን ለውጦ እንደ ሰው ሁኖ ታየው ወዳጄ አዲስ ዳንኤል ሆይ አትፍራ ተነሣ አለው የቅዱስ ዮሐንስም ልቡ ተጽናንቶ ጌታዬ አንተ ማነህ ግርማህ አስፈርቶኛልና አለው የእግዚአብሔር መልአክም ትሠራው ዘንድ የሚገባህን ልነግርህ ወዳንተ የተላክሁ ነኝ። አሁንም እግዚአብሔር አምላክ ያዘዘህን ለመሥራት ልብህን አበርታ ቃልህ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ በአራቱ ማእዘን ይደርሳልና እልፍ አእላፋትም ትምህርትህን ተቀብለው ትእዛዝህን ሰምተው ወደ ፈጣሪያቸው እግዚአብሔር ተመልሰው ይድናሉና በእግዚአብሔር መንግሥትም ውስጥ የጸና የብርሃን ዐምድ ትሆናለህና። እነሆ የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አንተ ይመጣል ከእርሱም ጋራ ሁሉም ካህናትና ዲያቆናት በየማዕረጋቸው የሚያዝህንም አድርግ የእግዚአብሐር ትእዛዝ ነውና ልትተላለፍ አይገባህም አለው። ከዚህም በኋላ ያ መልአክ ለአባ ፊላትያኖስ ተገልጦ ቅዱስ ዮሐንስን ቅስና እንዲሾመው አዘዘው በማግሥቱም ሊቀ ጳጳሳቱ መጣ ከርሱ ጋራም ካህናት አሉ ይህን ቅዱስ ዮሐንስንም ይዞ ቅስና ሾመው። የቍስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳትም በአረፈ ጊዜ ንጉሥ አርቃድዮስ ልኮ አስመጥቶ ቅዱስ ዮሐንስን በቍስጥንጥንያ ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾመው አባቶቻችን ሐዋርያት እንደሚአደርጉት በሊቀ ጵጵስናው ሥራ ላይ ጸና ሕይወትነት በአላቸው ትምህርቶችና ተግሣጾች ሕዝቡን ሁልጊዜ የሚአስተምር ሆነ። ከኤጲስቆጶሳትም ሆነ ከመንግሥት ወገን ሕግን የሚተላለፉትን ሁሉ ይገሥጻቸዋል ማንንም አይፈራም ፊት አይቶም አያደላም። የንጉሥ አርቃድዮስ ሚስት አውዶክስያም ገንዘብ ወዳጅ ስለሆነች የአንዲት ድኃ መበለት ቦታዋን በግፍ ወሰደች ያቺ መበለትም ወደ ቅዱስ ዮሐንስ መጥታ ንግሥት አውዶክስያ ቦታዋን እንደነጠቀቻት ነገረችው እርሱም የደኃዋን ቦታዋን መልሺላት ብሎ ከብዙ ምክር ጋር እንድትመልስላት ንግሥት አውዶክስያን ለመናት እርሷ ግን እምቢ በማለት አልታዘዘችለትም ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብታ ሥጋውን ደሙን እንዳትቀበል አውግዞ ለያት። ቍጣንና ብስጭትንም ተመልታ ስለ ክፉ ሥራቸው ከሹመታቸው እርሱ የሻራቸውን ኤጲስቆጶሳት ሰበሰበች እነርሱም ንግሥቲቱን ስለ ተቃወመ ስደት እንደሚገባው በእርሱ ላይ ተስማምተው ጻፉ እርሷም አጥራክያ ወደ ሚባል ደሴት ሰደደችው። ከዚያም በደረሰ ጊዜ የዚያች ደሴት ሰዎች በክፉ ሥራ ጸንተው የሚኖሩ ከሀድያን ሁነው አገኛቸው ቅዱስ ዮሐንስም አስተማራቸው ገሠጻቸውም በፊታቸው ስለ አደረጋቸው ድንቆች ተአምራት ወደ ቀናች ሃይማኖት አስገባቸው። የሮሜ ንጉሥ አኖሬዎስና ሊቀ ጳጳሳቱ ዮናክኒዶስ ስለ ቅዱስ ዮሐንስ ስደት በሰሙ ጊዜ እጅግ አዘኑ በንጉሥ አርቃድዮስ ላይም በመቆጣት እንዲህ የሚል ደብዳቤ ጽፈው ላኩ ከዚህ ከክፉ ሥራ ተጠበቅ ትእዛዛችንንም ተቀብለህ የከበረ ዮሐንስን ከስደቱ ከአልመለስከው በአንተና በእኛ መካከል ሰላም አይኖርም። መልእክታቸውንም በአነበበ ጊዜ እጅግ አዘነ ሚስቱንም አግዶ ልኮ ቅዱስ ዮሐንስን ከስደቱ መለሰው በተመለሰ ጊዜም የቍስጥንጥንያ ሰዎች በመመለሱ ታላቅ ደስታ አደረጉ። ከጥቂት ቀኖች በኋላም ንግሥቲቱ ወደ ክፋቷ ተመልሳ ሁለተኛ ወደ አጥራክያ ደሴት ሰደደችውና በዚያው አረፈ። ንጉሥ አኖሬዎስና ሊቀ ጳጳሳት ዮናክኒዶስም በሰሙ ጊዜ መልእክትን ላኩ ሊቀ ጳጳሳቱም የከበረ ዮሐንስን ከስደቱ እስከምትመልሰው ድረስ ሥጋውንና ደሙን እንዳትቀበል አውዶክስያን አወገዛት። ከዚህም በኋላ የከበረ ዮሐንስን ይመልሱት ዘንድ ንጉሥ ላከ ግን ሙቶ አገኙት ሥጋውንም ተሸክመው ወደ ቊስጥንጥንያ ከተማ አደረሱት። የከበረ ዮሐንስም በተሰደደበት አገር እንደአረፈና ሥጋውንም ወደ ቍስጥንጥንያ ከተማ እንደአመጡ ወደ አባ ዮናክኒዶስ መልእክት ጽፈው አስረዱት። ሁለተኛም የሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብታ ሥጋውንና ደሙን እንዳትቀበል ልኮ አውድክስያን አወገዛት እየለመነችውም ስምንት ወር ያህል ኖረች በብዙ ልመናም ፈታት። ነገር ግን ጭንቅ በሆነ ደዌ እግዚአብሔር አሠቃያት ያድኗት ዘንድ ገንዘቧን ለባለ መድኃኒቶች ጥበበኞች እስከ ሰጠች ድረስ ግን አልዳነችም ወደ ቅዱስ ዮሐንስ መቃብርም ሔዳ በእርሱ ላይ ያደረገችውን በደል ይቅር ይላት ዘንድ እየሰገደችና እያለቀሰች ለመነችው እርሱም ይቅር አላት ከደዌዋም ፈወሳት። ጌታችንም ከሥጋው ታላላቅ ድንቆች ታአምራትን ገለጠ። ስለርሱም እንዲህ ተባለ በአንዲት ዕለትም ከንጉሥ አርቃዴዎስ ጋር ተቀምጦ ሳለ ንጉሡ እንዲህ አለው አባቴ ሆይ ስለ አንድ ቃል እንድታስረዳኝ እለምንሃለሁ። ይህም ቃል ከብዙ ጊዜ ጀምሮ በልቤ ውስጥ ይመላለሳል ወንጌላዊ ማቴዎስ ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያምን የበኵር ልጅዋን እስከ ወለደች ድረስ ዮሴፍ አላወቃትም ስለምን አለ ወንዶች ሴቶችን እንደሚአውቋቸው ዮሴፍ አወቃትን አለው።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! 🕯 #ፍልሰተ_ሥጋሁ_ለአቡነ_ተክለ_ሃይማኖት    የአባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት የዕረፍቱ መታሰቢያ ነሐሴ 24 ቀን ሲኾን ሥጋው/ዐፅሙ የፈለሰበት ደግሞ ግንቦት 12 ቀን ነው፡፡ ይህም እግዚአብሔር ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት ‹‹ደቀ መዛሙርትህ ቤተ ክርስቲያን ሠርተው ሥጋህን ያፈልሱታል›› ብሎ የተስፋ ቃል ነግሯቸው ነበር፡፡ ጊዜው ሲደርስ ባረፉ በ56ኛው ዓመት ለሦስተኛው ዕጨጌ ለአበ ምኔቱ ለአባ ሕዝቅያስ ተገልጠው ‹‹እግዚአብሔር የነገረኝ ተስፋ ሊፈጸም ነውና ደቀ መዛሙርቱን ሰብስበህ በግንቦት 12 ሥጋዬን አፍልሱ፡፡ ከቅዱስ ሚካኤል ጋር እመጣለሁ፤ ምልክት ይሆንህ ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ ስትገባ መብራቱን አጥፋ እኛ ስንመጣ ይበራልሃል›› አሉት፡፡     አባ ሕዝቅያስ መነኮሳቱን ሰብስቦ በደብረ አስቦ (ደብረ ሊባኖስ) ሥጋው ካረፈበት ዋሻ ገቡ፤ መዐዛውም እንደ ሽቱ አምሮ አገኙት፡፡ ተሸክመውም ወደ ቤተ ክርስቲያን አስገቡት፡፡ ከዚያም አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅዱስ ሚካኤል መጥተው ከመንበሩ ተቀመጡ፤ የጠፋው መብራትም በራ፡፡ ዐፅሙንም ከመንበሩ ሥር ግንቦት 12 ቀን በእልልታና በደስታ አስቀምጠውታል፡፡ ‹‹ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ እስመ በውስቴታ ተገብረ ፍልሰተ ሥጋሁ ወዐፅሙ›› ትርጓሜውም ‹‹ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ ታመሰግነዋለች  የሥጋውና የዐፅሙ ፍልሰት በውስጧ ተደርጓልና›› እንዲል፡፡ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት በረከታቸው ይደርብን አሜን!        ወስብሐት ለእግዚአብሔር! ምንጭ፦ መድበለ ታሪክ ፣ መዝገበ ታሪክ ፣ አውሎግሶን   

በዚህም ተደስታ ልብሰ ምንኲስናዋን ይዛ፣ የመጨረሻውን የሦስት ዓመት ሕፃን ልጇን አዝላ ከሞት የተነሳችውን አገልጋይዋን አስከትላ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ሄዳ አስቀድማ ያዘጋጀችውን ልብሰ ምንኲስና ለብሳ ከሴቶች ገዳም ገባች፡፡ ይዛው የተሰደደችው ሕፃን ግን ወንድ ስለሆነ ከገዳሙ ውጭ አስቀምጣው ስለገባች ሕፃኑ አምርሮ ማልቀሱን የተመለከተች ከመነኰሳቱ አንዲቷ ሲያለቅስ ከሚያድር ብላ ወደ በዓቷ ልታስገባው ስትል ቅዱስ ሚካኤል ነጥቆ ወስዶ በገነት አስቀመጠው፤ ታኅሣሥ 29 ቀን ተወልዶ በሦስት ዓመቱ ታኅሣሥ 12 ቀን ብሔረ ሕያዋን አስገብቶታል፡፡    ከዕለታት በአንደኛው ቀን ቅዱስ ሚካኤል ካለችበት በዓት አውጥቶ በክንፉ ወደ ጣና (ጓንጉት) ደሴት አደረሳት፤ በዚያም ሰውነቷ ተበሳስቶ ዓሣ ሰውነቷን መመላለሻ እስኪያደርጋት ድረስ ለ12 ዓመት በባሕሩ ውስጥ ቁማ ስትጸልይ ኖራለች፡፡ እግዚአብሔርም ከመከራዋ ብዛት ከገድሏ ጽናት የተነሣ 6 የጸጋ ክንፍ ሰጥቷታል፡፡ እግዚአብሔር ‹‹ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ምን እንዳደርግልሽ ትፈልጊያለሽ?›› ብሎ በጠየቃት ጊዜ ‹‹ደቂቀ አዳምን እንዳያስታቸው ዲያብሎስን ማርልኝ›› አለችው፡፡ ‹‹እርሱ ምሕረት አይሻም እንጂ ከወደደ ጥሪው›› ብሎ ቅዱስ ሚካኤልን ረዳት አድርጎ ወደ ሲዖል ላካት፡፡ በዚያም ዲያብሎስን በስሙ ጠርታ ‹‹ፈጣሪ ምሮሃልና ና ውጣ›› አለችው፡፡ ዲብሎስም ‹‹አስቀድሜ ስፈልግሽ እኖር ነበር አሁን አጠገቤ መጣሽልኝ›› ብሎ ጎትቶ ወደ ሲዖል ጣላት፡፡ ከዚያም ቅዱስ ሚካኤል የብርሃን ሰይፉን መዞ ሲዖልን ቢመታት ታላቅ ንውጽውጽታ ሆነ፤ ሲዖልም ብርሃን ለበሰች፡፡ ወዲያው ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ነጥቆ ሲያወጣት በተሰጣት የጸጋ ክንፍ እጅግ የበዙ ነፍሳትን ማርካ ወጥታለች፡፡ ከዚህ በኋላ በጾም በጸሎት ተወስና ስትኖር እግዚአብሔር ‹‹ቅዱስ ሚካኤልን ባልደረባ ሰጥቼሻለሁ፤ ክብረ በዓልሽም በየወሩ ከሚካኤል ጋር ይታሰባል›› ብሎ ቃል ገብቶላታል፡፡ ከዚህም የተነሣ በየዓመቱ ግንቦት 12 ቀን በደማቅ ክብረ በዓል ትታሰባለች፡፡ የዕረፍቷ መታሰቢያ ነሐሴ 24 ቀን ነው፡፡ በረከቷ ለሁላችን ይድረሰን አሜን!          ወስብሐት ለእግዚአብሔር! ምንጭ፦ መድበለ ታሪክ ፣ መዝገበ ቅዱሳን   

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! 🕯 #ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ በኢትዮጵያ ቡልጋ አካባቢ ልዩ ስሙ ቅዱስ ጌዬ በሚባል ቦታ የተወለደችው ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ከአባቷ ደረሳኒ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!         🕯 #ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ    በኢትዮጵያ ቡልጋ አካባቢ ልዩ ስሙ ቅዱስ ጌዬ በሚባል ቦታ የተወለደችው ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ከአባቷ ደረሳኒ ከእናቷ ዕሌኒ ግንቦት 12 ቀን ተወለደች። ወላጆቿ የእግዚአብሔርን ሕግጋትና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን በማስተማር አሳደጓት፤ ለዐቅመ ሔዋን በደረሰች ጊዜም ለሠምረ ጊዮርጊስ ዳሯት፤ ካገባትም በኋላ ካህን ሆነ፤ 12 ልጆችንም (ዐሥር ወንዶችና ሁለት ሴቶች) ወለዱ። ቅድስት ክርስቶሰ ሠምራ እግዚአብሔርን የምትፈራ፣ በጾምና በጸሎት ተወስና የምትኖር ደግ ሴት መሆኗን የሰማው በዘመኑ የነበረው ንጉሥ ዓፄ ይስሐቅ (የንግሥና ስሙ ንጉሥ ዓፄ ገብረ መስቀል) እንዲያገለግሏት 174 አገልጋዮችን ‹‹በጸሎትሽ አስቢኝ›› ብሎ ላከላት፡፡ ከአገልጋዮቿ መካከል አንዷ ምግባሯ አስቸጋሪ በመሆኑ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን በጣም ታበሳጫት ነበር። ይህችው አገልጋይ ከዕለታት አንድ ቀን ስታስቸግራት ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የእሳት ትንታግ አንስታ በአገልጋይዋ አፍ አደረገችባትና ወዲው ሞተች፡፡ በዚህም ክርስቶስ ሠምራ ደነገጠችና ወደ ሰማይ አንጋጣ  ‹‹እኔ ክርስቲያንና የካህን ሚስት ስሆን ነፍሰ ገዳይ ሆንኩ፤ ወዮልኝ ነፍሴን ምን እላታለሁ? ልሸከማት የማልችል ኃጢአት አገኘችኝ›› እያለች ፈጣሪዋን ትማጸን ጀመር፤ ዳግመኛም ‹‹ይህችን ነፍስ ከሥጋዋ አዋሕደህ ብታስነሣልኝ ልጆቼን፣ ቤቴን፣ ንብረቴንና ሀብቴን ትቼ አንተን እከተላለው›› ብላ ስዕለት ተሳለች፡፡ ‹‹አቤቱ ጸሎቴን ስማኝ ጩኸቴም ወደ አንተ ይድረስ በመከራዬ ቀን ፊትህን ከእኔ አትመልስ›› (መዝ 101፥1-2) እንዲል ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ ክርስቶስ ሠምራም ይህንኑ መዝሙር ስትዘምር የሞተችዋን አገልጋይ አግዚአብሔር አስነሣላት።

ያከብርዋ ለሰንበት ያከብርዋ ለሰንበት መላእክት በሰማያት ጻድቃን በውሰተ ገነት ወኲሉ ፍጥረት አሣት ወአናብርት እለ ውሰተ ደይን ያዕረፉ ባቲ እስመ ባቲ አዕረፈ እምኲሉ ግብሩ ያከብሯታል ሰንበትን መላእክት በሰማያት ጻድቃን በገነት ፍጥረታት በሙሉ አሳዎች እና አንበሪዎች በመቃብር ያሉ ያከብሯታል አምላክ በእርሷ እንዳረፈ ከሥራ ኹሉ ሰማይና ምድር ቀላያት አብርህት ሰውና እንስሳ ቅዱሳን መላዕክት ፈጥሮ ያረፈበትን ቅዱሱን ሰንበትን ሁላችንም እናክብር ሆነን በአንድነት       /አዝ = = = = = አንዱን ቀን እረፍ ስድስቱን ቀን ስራና አምላክህን አክብር አብዛለት ምስጋና ለስጋዊ ደስታ ለማይጠቅም ትርፍ ህጉን አትጣስ ሰንበትን ዕረፍ       /አዝ = = = = = በያሬድ ዝማሬ በዳዊት በገና በዕዝራ መሰንቆ በታላቅ ምስጋና ጭንቁን አውጁለት አለም እንዲሰማ ሰንበትን በማክበር ደስ በሚል ዜማ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

እሰይ ነጋ እሰይ ነጋ እሰይ ነጋ ላመሰግንህ ነው አይኔን የከደንኩት አንተን አምኜ ነው አይኔን የከደንኩት አንተን አምኜ ነው        /አዝ = = = = = በበደሌ ሳትፈርድ ትጠብቀኛለህ ከእኔ በላይ ለእኔ ታስብልኛለህ የማታንቀላፋው ቸሩ እረኛዬ ብርሃኑን ያየሁት ባንተ ነው ጌታዬ        /አዝ = = = = = ቀናቶቼን ሰጠሁ ላንተው አሳልፌ በሰላም እተኛለሁ በክንድህ አርፌ ተመስገን ማለትን በብርሃን ጨለማ ታስተምረኛለህ በወፎቹ ዜማ       /አዝ = = = = = ትናንትናን ታልፎ ስላየሁ አዲስ ቀን ከእንቅልፌ ስነቃ እላለሁ ተመስገን አንተ ባታነጋው የጨለመውን አልኖርም ነበረ ዛሬ ባልኩት ቀን        /አዝ = = = = = ሁሉም የሚሆነው እንደየሥራቱ በአንተ ብቻ እኮ ነው መጨለም መንጋቱ ስለ አደረክልኝ ምኔን ልክፈልህ ተመስገን ብቻ ነው ሥላሴ ዋጋህ       /አዝ = = = = = በብርሃን ተተካ አስፈሪው ጨለማ እንደኔማ ሳይሆን ምህረትህ ቀድማ የእኔ ያልኳት ዛሬ ነግታ የምትመሸው በጥበቤ አይደለም በበጎነትህ ነው 👉ሊቀ መዘምር ቴድሮስ ዮሴፍ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

✞ ዮም ፍስሐ ኮነ ✞ ዮም /ፍስሐ ኮነ/(፪) በእንተ ልደታ ለማርያም በባርነት ሳለን - - -  ፍስሐ ኮነ ኃጢአት በአለም ነግሳ - - - ፍስሐ ኮነ በድንግል መወለድ - - - ፍስሐ ኮነ ቀረልን አበሳ - - - ፍስሐ ኮነ እግዚአብሔር መረጠሸ - - - ፍስሐ ኮነ ልትሆኚው እናቱ - - -  ፍስሐ ኮነ ይኸው ተፈፀመ - - - ፍስሐ ኮነ የዳዊት ትንቢቱ - - - ፍስሐ ኮነ          /አዝ===== የሔዋን ተስፋዋ - - - ፍስሐ ኮነ የአዳም ዘር ህይወት - - - ፍስሐ ኮነ የኢያቄም የሐና - - - ፍስሐ ኮነ ፍሬ በረከት - - - ፍስሐ ኮነ ምክንያተ ድኂን - - - ፍስሐ ኮነ ኪዳነምህረት - - - ፍስሐ ኮነ ድንግል ተወለደች - - - ፍስሐ ኮነ የጌታዬ እናት - - - ፍስሐ ኮነ          /አዝ===== በሔዋን ምክንያት - - - ፍስሐ ኮነ ያጣነውን ሰላም - - - ፍስሐ ኮነ ዛሬ አገኘነው - - - ፍስሐ ኮነ በድንግል ማርያም - - - ፍስሐ ኮነ የምስራች እንበል - - - ፍስሐ ኮነ ሀዘናችን ይጥፋ - - - ፍስሐ ኮነ ተወልዳለችና - - - ፍስሐ ኮነ የአለም ሁሉ ተስፋ - - - ፍስሐ ኮነ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።         ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖   ❖ @enamsgn @enamsgn ❖         ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞