ru
Feedback
ወድሰኒ ​​

ወድሰኒ ​​

Открыть в Telegram

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ⛪️የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የመዝሙሮች ግጥሞች ከነ ዜሞቻቸው ለማግኘት ወደ ቻናላችን ይቀላቀሉ⛪️ YouTube https://youtube.com/@enamsgn?si=LYkrdnXK7rL--cMv የመዝሙር ግጥም መላክ ወይም ሀሳብ አስተያየት ጥቆማ ካሎት በ @Slamanshdngl ላይ ያድርሱን

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала ወድሰኒ ​​

Канал ወድሰኒ ​​ (@enamsgn) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 22 357 подписчиков, занимая 3 446 место в категории Религия и духовность и 1 516 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 22 357 подписчиков.

Согласно последним данным от 27 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -485, а за последние 24 часа — -28, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 4.19%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 1.30% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 936 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 291 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 6.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ⛪️የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የመዝሙሮች ግጥሞች ከነ ዜሞቻቸው ለማግኘት ወደ ቻናላችን ይቀላቀሉ⛪️ YouTube https://youtube.com/@enamsgn?si=LYkrdnXK7rL--cMv የመዝሙር ግጥም መላክ ወይም ሀሳብ አስተያየት ጥቆማ ካሎት በ @Slamanshdngl ላይ ...

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 28 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

22 357
Подписчики
-2824 часа
-1437 дней
-48530 день
Архив постов
​​​​👆የቀጠለ እኒኽም ቅዱሳን ይኽንን በሚነጋገሩበት ጊዜ በውስጡ አንገትን የሚቆለምም ልብንም የሚያቀልጥ ሆድን የሚሰነጥቅ ሥርን የሚበጣጥስ መሳሪያ ካለበት የብረት ጋን ውስጥ ጨመራቸው፡፡ ከዚህ በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደና የብረቱን ጋን እሳት አጠፋው፡፡ ከቅዱሳኑም አንዳቸውንም ሳያቃጥላቸው የብረቱ ጋር ማቃጠሉና መፍላቱ ጸጥ አለ፡፡ ወንድሞቻችን ሆይ እንግዲህ በጭንቃቸው ጊዜ ገድላቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ይህ መልአክ ከሰማእታትና ከጻድቃን ጐን እንደማይለይ እወቁ ለኃጥአንም ኃጢአታቸውን ይቅር ይላቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ይጸልይላቸዋል፡፡ እኛም የዚህ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓሉን እያከበርን አማላጅና ወዳጅ እናድርገው። በዚህም በሚመጣውም ዓለም ሊረዳን ይችላልና፡፡ ዳግመኛም መስፍኑ ሐሳቡ ሳይሳካለት ስለቀረ 14 የሾሉና የጋሉ የብረት ችንካሮች አምጥተው ሰባቱን በእናቱ በኢየሉጣ አካል ሰባቱን በራሱ በቂርቆስ አካል ማለት ሁለቱን በጆሮዎቹ ሁለቱን በዐይኖቹ ሁለቱን በአፍንጫዎቹ አንዱን በልቡ ይቸነክራቸው ዘንድ ጭፍሮቹን አዘዘ፡፡ ዳግመኛም የህፃኑን የእራስ ቆዳ ገፈው እሳት ውስጥ ይጨምሩ ዘንድ አዘዘ፡፡ አሁንም መልአኩ መጥቶ ይህንን መከራ ከእርሱ አራቀለት፡፡ ቀጥሎም በመቃን ውስጥ ጨምረው በገመድ እንዲጎትቱት አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ መልአኩ አዳነው፡፡ ሕዝቡም ይህንን ሁሉ ተአምር ባዩ ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገኑት ቅዱስ ገብርኤልንም አከበሩት፡፡ ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት እየሉጣ ብዙ መከራ ከተቀበሉ በኋላ ጥር 15 በሰይፍ ተመትተው ስማትነትን ተቀብለዋል። የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል ፣ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት እየሉጣ ተራዳኢነት ጸሎት አይለየን። ከዚህ በኋላ ሕፃኑን አስፈልገው ቢጠይቁት ነቢዩ ዳዊት የተናገረው ኃይለ ቃል መንፈስ ቅዱስ ተገልጾለት፤ ‹‹የአሕዛብ ጣዖታት የወርቅና የብር የሰው እጅ ሥራዎች ናቸው፡፡ የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ›› መዝ. ፻፴ በማለት ሲዘልፏቸው አገር ገዥው ሰምቶ ተቆጣና የብረት ጋን አስመጥቶ ውኃ ሞልቶ ከዕቶን እሳት ላይ ጥዶ ልዩ ልዩ ማገዶዎች በመጨመር ነበልባሉ ከመጠን በላይ ሆነ፡፡ የብረት ጋኑም ድምፅ እንደ ክረምት መብረቅና ነጎድጓድ እስኪያስፈራ ድረስ አስነድዶ ሕፃኑን ከነእናቱ ወስዳችሁ ጨምሩአቸው ብሎ አዘዘ፡፡ በዚህ ጊዜ ቅድስት ኢየሉጣ በጣም ፈራች፡፡ የእግዚአብሔር ሥራ እፁብ ድንቅ ግሩም ረቂቅ ነው፡፡ ገና አፉን ያልፈታ የሦስት ዓመት ሕፃን ‹‹እናቴ ሆይ! ገድላችን እንፈጽም ዘንድ ጨክኝ በርቺ›› አላት፡፡ ቅድስት ኢየሉጣም ‹‹ልጄ የነፍስ አባት ሁነኝ›› አለችው፡፡ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ከዘመናቸው ሳይደርስ፣ ታሪካቸውን ሳይማር የሠለስቱ ደቂቅን ታሪክ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ‹‹አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል›› ቢላት ፍርሃቱ ሊለቃት ባለመቻሉ፣ ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ጸለየ፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ! የወይኑን ፍሬ ስትሻ ግንዱን ታጠፋለህን? እንደዚህስ ሁሉ እኔን አድነህ እናቴን ታጠፋታለህን?›› ብሎ በጸለየጊዜ መንፈስ ቅዱስ አደረባትና መንግሥተ ሰማያትን በዓይነ ሥጋ እንድታይ አደረጋት፡፡ ከዚህ በኋላ ፍርሃቱ ለቀቃትና ‹‹ልጄ ሆይ! ከዛሬ ጀምሮ መምህሬ፣ አባቴ፣ መካሪዬ እልሃለሁ እንጂ ልጄ አልልህም›› ብላ በጭካኔ ከልጅዋ ጋር ወደ ፈላው የብረት ጋን ገባችበት፡፡ በዚህ ጊዜ ሕፃኑ ቂርቆስ አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል ያለውን ቃል ለመፈጻም እግዚአብሔር አምላክ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው፡፡ መልአኩም በትእምርተ መስቀል እሳቱን ቢባርከው እንደ በረዶ ቀዝቅዞላቸዋል፡፡ በመልካቸውም እንደ ፀሐይ አበራ፡፡ ከእግር ጥፍራቸው እስከ ራስ ጠሩራቸው አንድም ሳይጎዳቸው በደህና ወጡ፡፡ በመጨረሻም ሕፃኑ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ እንዲህ አለ፡፡ ይህን ያህል ገድል ተጋድዬ ምን ዋጋ ትሰጠኛለህ ቢለው፣ ጌታ በልብህ ያለውን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው፡፡ ዳግመኛም ሥጋህ በምድር ላይ እንዳይፈርስ እንዳይበሰብስ በኤልያስ ሠረገላ ላይ አኖርሃለሁ አለው፡፡ ስለሆነም በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያናችን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለእናታችን ለቅድስት ኢየሉጣ እና ለሕፃኑ ለቅዱስ ቂርቆስ ያደረገውን ይህን ታላቅ ተአምር ድንቅ ሥራ በማሰብ ከዋዜማው ጀምራ እግዚአብሔርን ስታመሰግን ትውላለች ታድራለች፡፡ የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል በረከት ተራዳኢነት ከሁላችን ጋር ይኑር አሜን፡፡

​​ሐምሌ 19 ቅዱስ ገብርኤል እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!! በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በዓል ነው፡፡ ይህ ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ቅዱስ ቂርቆስን ከሞት አደጋ እንደታደገበት የሚታሰብበት ዕለት ነው። የሐምሌ 19 ስንክሳርና የሐምሌ ወር ድርሳነ ገብርኤል እንዲህ ተርከውታል፡፡ በዘመነ ሰማእታት ከሐድያን ነገሥታትና መኳንንት በክርስቲያኖች ላይ መከራ አጽንተውባቸው ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ብዙዎች ሰማእትነትን ሲቀበሉ የተቀሩት አገር ጥለው ተሰደዱ። እየሉጣም የሦስት ዓመት ህፃን የነበረውን ቅዱስ ቂርቆስን ይዛ ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኮንን አገኘችው ሰዎችም ነገር አሰሩባት ወደእርሱ አስቀረባት እና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኮንን ሆይ ዕድሜው ሦስት አመት የሆነው ህፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እሱን ጠይቅ አለችው፡፡ ህፃኑም ወዳለበት ጭፍራውን ልኮ ወደእርሱ አስመጣው ህፃኑም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ህፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው፡፡ ህፃኑም መልሶ አዎ ለኔ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ሐዘንና ለቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው፡፡ መጻሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏል እና አለው፡፡ እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስካስደነገጣቸው ድረስ ንጉሱን መኳንንቱንና ጣኦታቱን ረገማቸው፡፡ከብርታቱም የተነሳ አደነቁ፡፡ መኮንኑም በአፈረ ጊዜ በያይነቱ በሆነ ስቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ስቃይን አሰቃየው እናቱንም ከእርሱ ጋር አሰቃያት፡፡ እግዚአብሔርም ያለ ምንም ጉዳት ያነሳቸው ነበር፡፡ ብዙዎች አህዛብም ይኸንን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማእትነት አረፉ፡፡ የሰማእትነትንም አክሊል ተቀበሉ፡፡ በህፃኑም ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት፡፡ ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው፡፡ መስፍኑም በውስጡ ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ የዶሮ ማር፣ እርሳስ፣ ብረት፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል ጨምራችሁ ታላቅ የብረት ጋን አንጡልኝ ብሎ ጭፍሮቹን አዘዛቸው፡፡ ጭፍሮቹም እንዳዘዛቸው ካአደረጉ በኋላ ያዘዝከንን ሁሉ ፈጽመን እሳቱ ነዶ ፈልቷል፡፡ ድምፁ እንደነጐድጓድ ይጮኸል ወላፈኑም እንደጸሐይ ነጸብራቅ በሩቁ ይጋረፋል፡፡ የፍላቱም ኃይል በ14 ክንድ ያኽል ከፍታ ወደ ላይ ይዘላል፡፡ እንግዲህ በውስጡ የሚጣሉትን እዘዝ አሉት በዚህ ጊዜ ህፃን ቂርቆስና እናቱ እየሉጣ በክርስቶስ ስም ስለሚያምኑ አስረዋቸው ነበርና ከፍላቱ ሊጨምሯቸው ከእስር ቤት አወጧቸው፡፡ በዚያም ፍላቱ ወደላይ በሚዘል ብረት ጋን ውስጥ ለመጨመር ሲወስዷቸው የነዚህን ቅዱሳን አሟሟት ያዩ ዘንድ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲሰበሰቡ አዘዛቸው፡፡ በዚህን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ የፍላቱን ጩኸት በሰማችና ባየች ጊዜ ተሸበረች፡፡ ተዘጋጅቶላት ከነበረው ክብር ልታፈገፍግ ሞከረች፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ግን እናት ሆይ ከዚህ የብረት ጋን ግርማ የተነሳ አትፍሪ ድንጋጼም አይደርብሽ አናንያንና አዛርያን ሚሳኤልንም እግዚአብሔር ከእቶነ እሳት እንዳወጣቸው ሁሉ እኛንም ከዚህ ከብረት ጋን ሊያወጣን ችሎታ ያለው መሆኑን አትጠራጠሪ፡፡ እናት ሆ ከዚህ ከሚያልፈው ዓለም ጭንቅና መከራ ለመዳን ስትይ በማያልፈው ዘላለማዊ እሳት ለመቀጣት ትመርጫለሽን ይኽስ አይሆንም ይቅርብሽ፡፡ በአሁኑ ጊዜ እግዚአብሔር በመካከላችን አለና ይረዳናል፡፡ እናት ሆይ ሶስናን ከእደ ረበናት /መምህራነ አይሁድ/ ዳንኤልን ከአፈ አናብስት ያዳነ እርሱ እኛንም ከጋን ፍላት ያወጣናል፡፡ ይልቁንም እግዚአብሔር በዚህ የብረት ጋን ውስጥ ግዳጃችንን ልንፈጽም ፈቅዶ ከሆነ ኢዮብ ንብረቱንና ገንዘቡን ልጆቹንና ሚስቱን በመጨረሻም የተፈጥሮ አካሉን ባሳጣው ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ እግዚአብሐር ሰጠ እግዚአብሔር ነሳ እግዚአብሔርም እንደወደደ አደረገ ከማለት በስተቀር ምንም የተናገረው ነገር እንደሌለ ሁሉ እኛም የሱን ዓላማ በመከተል ይኽንን መከራ ልንታገስ ይገባናል፡፡ ነገር ግን እናቱ በዚህ ምክር ልትጽናና ባለመቻሏ ቅዱስ ቂርቆስ ዐይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ አቤቱ አምላክ ሆይ ይችን ባሪያህን ከርስትህ የምትለያት ከሆነ ከባለሟልነትህ መጽሐፍ ፋቀኝ፤ አቤቱ አዝመራውን አቃጥለ ፍሬውን ልትባርክ ትወዳለህን ይኽን እንዳታደር ግን ቸርነትህ ትከለክልኸለች አቤቱ እንጨቱን ቆርጣችሁ አንድዱት ቅጠሉን ግን ጠብቁት ብለኽ ልታዝ መለኮታዊ ባሕሪህ አይደለም፡፡ ነገር ግን እንጨቱንም ቅጠሉንም በአንድ ጠብቁት ብለኽ ታዝዛለኽ እንጂ፡፡ እንግዲህ በዚህ ምክንያት ይኽንን ያየ ሁሉ ማዳን የሚችል አምላክ ቢኖራቸውስ ኖሮ ከእሳት ባልሸሹም ነበር ብሎ አይጠራጠር፡፡ አቤቱ ዲያብሎስም ከባለስልጣኑ ይልቅ እኔ በረታሁ ቅዱሳኖቹንም ድል ነሳኋቸው ብሎ እንዳይመካ ከመንጋውም አንድ በግ ቀማው በማለት እንዳይደነፋ ለእናቴ ጽኑ የሆነ ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ስጣት ብሎ በጸለየ ጊዜ ዲያብሎስ ከእየሉጣ አጠገብ ብን ብሎ ጠፋ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ በሰማያዊ መንግሥት አባት የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታኽ ኃይልን ሰጥቶኛልና የሚጠብቀንን ገድላችንን ፈጽመን ድል እናድርግ እነሆ በብረት ጋን ውስጥ የሚነደውን እሳት በማይበት ጊዜ በለምለም /በምንጭ/ ላይ እንደሚወርድ ጠል ሆኖ አይቸዋለሁና አለችው፡፡

ገብርኤል ስሙ ገብርኤል ስሙ ዘአምኃ ለማርያም ዘበትርጓሜሁ አምላክ ውእቱ(፪×) ይበል ይበል አቅዲሙ ዜነዋ ለደብረ ልዑል ኢየሩሳሌም አምኃሁ ለዘይመጽዕ ዓቢይ ኖላዊ ኖላዊ(፪×) ይበል ይበል የፈላው ጋኑን--ገብርኤል ስሙ አቀዝቅዞት----ገብርኤል ስሙ ቂርቆስንና----ገብርኤል ስሙ እናቱን አዳነ---ገብርኤል ስሙ ዘአምኃ ለማርያም ዘበትርጓሜሁ አምላክ ውእቱ ይበል ይበል ሠለስቱን ሕፃናት--ገብርኤል ስሙ ያዳናቸው እርሱ---ገብርኤል ስሙ እኛንም ያድነን----ገብርኤል ስሙ ከሚነደው እሳት---ገብርኤል ስሙ ዘአምኃ ለማርያም ዘበትርጓሜሁ አምላክ ውእቱ ይበል ይበል መልአከ ራማ-----ገብርኤል ስሙ እኛን ይወደናል----ገብርኤል ስሙ ሃያሉ አባት--------ገብርኤል ስሙ ሊቀ መልአኩ------ገብርኤል ስሙ ዘአምኃ ለማርያም ዘበትርጓሜሁ አምላክ ውእቱ ይበል ይበል 👉ዘማሪት ቤርሲ ሰላም #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

ለገብርኤል የነገርኩት በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ለገብርኤል የነገርኩት ያስጨነቀኝ ታላቅ ድንጋይ ተንከባሎ በዓይኔ አየሁት ከአይን ጥቅሻ ቀድመህ ፈጥነህ ትደርሳለህ በምልጃህ ፀሎትህ ከእኔ ጋር አለህ ገብርኤል ገብርኤል ገብርኤል የምለው እጄን ስዘረጋ ብዙ ሰጥተኸኝ ነው        /አዝ = = = = = የደስታን ዜና ይዘዋል እጆችህ የአምላክ ውዳሴ ተሞልቷል ከንፈርህ ችግሬን አትሻም አትፈቅድም ጥፋቴን እንዳይሰናከል አቁመሀል እግሬን        /አዝ = = = = = በእሳቱ መሀል ምስጋና አስተምረኝ በእቶንም መካከል ውዳሴን አሳየኝ እንዳላጉረመርም በሆነው በአልሆነው ገብርኤል አሳየኝ አመስግኜ እንዳልፈው        /አዝ = = = = = ሲራቅና ሚሳቅ አብድናጎን ሆነው በሚነደው እሳት ከእቶን ተጥለው ገብርኤል ደረሰ ሊነግራቸው ዜና ችግር እንደሚርቅ በብዙ ምስጋና 👉 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ እና ዘማሪት መቅደስ ማርዬ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

ሰኔ ፴ /30/ አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሠላሳ በዚች ዕለት ነቢይ ሰማዕትና ሐዋርያ የሆነ መጥምቁ ዮሐንስ ተወለደ። ይህም በእናቱ ማኅፀን ውስጥ ሳለ ለእግዚአብሔር ልጅ የሰገደው ነው። ይህም በመድኅን ክርስቶስ ራስ ላይ እጁን ጭኖ በውኃ ያጠምቀው ዘንድ የተገባው ነው። በቅዱስ ወንጌል እንደ ተነገረ ወንድ ልጅን ትወልድ ዘንድ የኤልሳቤጥ የፅንሷ ወራት በተፈጸመ ጊዜ ወንድ ልጅን ወለደች። ዘመዶቿና ጐረቤቶቿ እግዚአብሔር ቸርነቱን እንዳበዛላት በሰሙ ጊዜ ስለርስዋ ደስ አላቸው። በስምንተኛውም ቀን ሊገዝሩት መጡ በአባቱ ስም ዘካርያስ ብለው ጠሩት። እናቱ ግን አይሆንም ዮሐንስ ይባል አለች። ከዘመዶችሽ ስሙ እንዲህ የሚባል የለም አሏት ። አባቱንም ጠቅሰው ማን ሊባል ትወዳለህ አሉት። እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ ዮሐንስ ይባል ብሎ ጻፈ ። ሁሉም አደነቁ። ያን ጊዜም አንደበቱ ከድዳነት ተፈትቶለት ተናገረ እግዚአብሔርንም ፈጽሞ አመሰገነው። ስለ ልጁና ስለ መድኃኒታችን መምጣት ልጁ ዮሐንስም የልዑል ነቢይ እንደሚባልና በእግዚአብሔርም ፊት እንደሚሔድ ትንቢት ተናገረ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑርለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር

ዝግጅት አለዎት? ጭንቀቱን ለእኛ ይተውት! "ቤተ ብርሃን ዲኮር" አዲስ ስራ፣ አዲስ ውበት! ከቀላል የቤት ውስጥ ዝግጅት.. እስከ ታላላቅ መድረኮች፣ ቦታዎን በብርሃን እና በውበት ለመሙላት ተዘጋጅተና
ዝግጅት አለዎት? ጭንቀቱን ለእኛ ይተውት! "ቤተ ብርሃን ዲኮር" አዲስ ስራ፣ አዲስ ውበት! ከቀላል የቤት ውስጥ ዝግጅት.. እስከ ታላላቅ መድረኮች፣ ቦታዎን በብርሃን እና በውበት ለመሙላት ተዘጋጅተናል። እይታን የሚቀይር... ጥራቱ የማይነካካ፣ ቤተ ብርሃን ከመጣ... የውበት ጥማትዎ ይረካ! አሁኑኑ ይደውሉልን፣ ዝግጅትዎን በብርሃን እንሙላው!

የልቤ ዜማ የልቤ ዜማ ነሽና ሰላም ነው ያንቺ ምስጋና ሞገሴ ነው ስምሽ ለኔ ስላለሽ ማርያም ከጎኔ በመገፍት ብኖር እምነቴን አፀናለሁ በጣቶችሽ  ተይዤ አዲሱ ቀን አያለሁ❨፪×❩ ስማፀን ደጅሽ መጥቼ ተመለሰኩ ተረጋግቼ እንደምን አንቺን እረሳለሁ በምልጃሽ ተፈውሻለሁ        /አዝ = = = = = የጠላቶቼን አራስ የሚቀጠቅጠው የአብራክሽን ፍሬ ተስፍዬን አበራው❨፪×❩ የድኅነት ምክንያት አርጎሻል ለአዳም ዘር ትምክህት ሆነሻል የልቤ ብርሃን ፋና አዛኝት ባንቺ ልፅናና          /አዝ = = = = = የአፌን እንጉርጉሮ ምስጋናዬ ወርሶታል እግሬ ከእረግረግ ወጥቶ በሰገነት ተተክሏል ❨፪×❩ ሐዘኔን የምሻገረው ስምሽን እየጠራሁ ነው አገኘው ደስታ ሰላም ጠርቼ ብዬ ማርያም  👉ዘማሪ ዲያቆን እንዳለ ደረጀ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

ትምክህተ ዘመድነ ትምክተ ዘመድነ❨፪×❩ ማርያም ዕምነ ማርያም ትምክህተ ዘመድነ የድነታችን አርማ የነፃነታችን የህይወት መሰረት ነሽ ድንግል እናታችን አንቺን ለኛ ዘርን ባያስቀር እንደጥንቱ እንደ ሰዶም ምድር ሁላችን በጠፋን ነበር        /አዝ = = = = = የአብርሀም ድንኮን ነሽ አምላክ ያደረብሽ የጌድዮንም ፀምር ለይቶ ያከበረሽ የኛ ቤዛ በጉ የተያዘብሽ የዋህ ርግብ  ከ አበውስር የተገኘሽ እፀሳቤቅ የህይወት ሀረገ ነሽ        /አዝ = = = = = አምላክ ከሰማይ ሆኖ ይችን አለም ሲቃኝ ንፅህይት ቅድስት ሁነሽ ማርያም አንቺን ቢያገኝ ትህትናሽን ሂወትሽንም ወዶ ቃል ሰው ሆነ ከሰማያት ወርዶ አከበረሽ በፋፁም ተዋህዶ        /አዝ = = = = = የመዳናችን ምክንያት የሰው ልጆች ሰላም ከሀጢያት ከመርገም የዳነብሽ አለም አምስት ሺ አምስት መቶ ዘመን በሲኦል ውስጥ ተግዘን የኖርን ድንግል ባንቺ ነፃነት አገኘን #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

እመቤቴ የአምላክ እናት እመቤቴ የአምላክ እናት ላመስግንሽ ቀን ከሌሊት ለልጅሽም ክብር ውዳሴ ታቀርባለች ዘወትር ነፍሴ❨፪×❩ ልቤ ተነሳሳ ተቀኘ ለክብርሽ በፍጹም ትህትና ሊያመሰግንሽ ጽዮን መጠጊያ ነሽ የአብርሃም ድንኳን የታጠረች ተክል እመ ብርሃን        /አዝ = = = = = የለመለመች መስክ አምላክ የመረጣት የጽላቱ ኪዳን  ታቦቱ ድንግል ናት የሰማይ የምድር ንግሥት ናትና ክብር ይገባታል ዘወትር ጠዋት ማታ        /አዝ = = = = = አደራሽን ማርያም የሁሉ እናት በምልጃሽ አስቢኝ ኋላ ስራቆት ያንን የእሳት ባሕር አሻግርኝ ድንግል ሆይ እንዳልወድቅ እንዳልሞት ከቶ እንዳላይ ስቃይ 👉ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

​​​​ሰኔ 12 #የቅዱስ_ሚካኤል ዓመታዊ በዓል! እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለእናታችን ቅድስት አፎሚያ አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ። ሰኔ 12 ቅዱስ ሚካኤል እናታችን ቅድስት አፎሚያን ከጠላት ዲያብሎስ እጅ ያዳነበት ፣ እናታችን ቅድስት አፎሚያ እረፍቷ ነው ።እግዚአብሔር ከቅዱሱ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ፣ ከእናታችን ቅድስት አፎሚያ በረከት ተካፋይ ያድርገን ። 👉 በወርኃ ሠኔ መታሰቢያ ከሚደረግላቸው ቅዱሳን መካከል እግዚአብሔርን የሚፈራ የአስተራኒቆስ ሚስት የሆነች የቅድስት አፎምያን ታሪክ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡ ቅድስት አፎምያ በትዳር በነበረችባቸው ዘመናት እግዚአብሔርን ከሚወድ ባለቤቷ ጋር እግዚአብሔርን ስታገለግለው የኖረች ሴት ነበረች፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ እንደነበር ታሪካቸው ይነግረናል፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጉል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡ ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፡፡ የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ ባያት ጊዜ ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ፣ ሌላ ባል አግብታ፣ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡ ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ፤ እነሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ፤ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡ በሠኔ ፲፪ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ሞከረ፡፡ ሰይጣን አስቀድሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንቶስ መጻሕፍትን እየጠቀሰ እንደተፈታተነው ሁሉ ቅድስት አፎምያንም ለማሳመንም አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዳዊትን የመሳሰሉ ደጋግ አባቶችን ታሪክ እየጠቀሰ ወደ ትዳር እንድትገባ ደጋግሞ ወተወታት፡፡ ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና “የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?” በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡ ለጊዜው “በኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም” ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ፡፡ ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን “ድረስልኝ” እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሠኔ ፲፪ ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡ ይህች የታመነች ቅድስት አፎምያ በሰላም እስክታርፍ ጊዜ ድረስ የተጓዘችበትን መንፈሳዊ ጎዳና አስተውለን ይሆን? አስቀድማ ከባሏ ጋር አንድ ሆና በታማኝነት ፈጣሪዋን አገለገለችው፡፡ በኋላም የባሏን ኑዛዜ አክብራ ምንም እንኳን ኃጢአት ባይሆንባትም በሁለተኛ ትዳር ራስዋን ማጠላለፍ አልፈለገችም፡፡ በጎ ሥራ አብልጣ በመሥራት እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ተፋጠነች እንጂ፡፡ ሰይጣን ልጅ አለመውለዷን ተጠቅሞ ያቀረበላትን የጋብቻ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ “መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ መናፍስት ከእግዚአብሔር እንደሆኑ መርምሩ” ተብሎ በቅዱሳት መጻሕፍት የታዘዘውን መመሪያ ተጠቅማ ሰይጣንን በተወክሎ እግዚአብሔር ተቃውማ አሸነፈችው፡፡ የቅዱስ ሚካኤልን ርዳታ ያገኘችውና በሰላም ዐርፋ ወዳገለገለችው እግዚአብሔር በክብር የሔደችው በጽናት ተጋድላ ነው፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በጸሎቷ ይማረን፤ የቅዱስ ሚካኤል የረድኤቱ ኃይል ሁላችንንም ይጠብቀን፣ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

የአፎምያ እረዳት ✞ የአፎምያ እረዳት ነህ ሚካኤል❨፪×❩ ቅሩበ እግዚአብሔር የልዑል ፈጥነህ ድረስልን ስንጠራህ ሚካኤል ፊት ለፊታችን አምላክ ሠደደህ አቀናህልን መንገዱን ጠርገህ የቤንሆርን ምክር አፈረስክ ከልጆችህ ጋር ከነዐን ደረስክ ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን እንጠራሀለን ሚካኤል ብለን        /አዝ = = = = = በቃዲስ ክንፍህ ተዘርግቶልን ደመናው በአንተ ተጋረደልን አብረኸን ልትሆን ጌታ የላከህ አንተ ሚካኤል ታዳጊያችን ነህ ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን እንጠራሀለን ሚካኤል ብለን        /አዝ = = = = = ሙሴ ሲለየን ደጉ አባታችን ሚካኤል ነበር ከላይ መሪያችን የማንነቱ ጉዞ እስኪያበቃ እጅግ እረዳን የኛ ጠበቃ ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን እንጠራሀለን ሚካኤል ብለን        /አዝ = = = = = ሳጥናኤል መክሮን የሀሰት ምክር ሊወስደን ሻተ ሙሴ መቃብር ስለማይጠቅመን አንተ ሠወርከው ምክሩን በታትነህ አስጎነበስከው ከኛ ጋር ነበርክ አርባውን ዘመን እንጠራሀለን ሚካኤል ብለን #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።  ╔✞════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

ከሚካኤል በቀርከሚካኤል በቀር የሚያፅናናኝ የለም እረዳቴ እርሱ ነው በመከራዬ ቀን/፪/ ሀዘኔ እጅግ በዝቶ ከሚካኤል በቀር የሚረዳኝ ሳይኖር በስደቴ ዘመን ሰላም ከእኔ እርቆ ከሚካኤል በቀር ጭንቀት አስቸገረኝ በዙሪያዬ ከቦኝ ዛሬ ግን አፅናኜ ከሚካኤል በቀር ሚካኤል ደርሰ ጠላቴ አፈረልኝ ሚካኤል ነው የዳዊት እረዳት ከጎሊያድ ያዳነው ሚካኤል ነው መንፈሳዊ ብርታት ሀይልንም የሰጠው/፪/         /አዝ = = = = = ቃልኪዳኑ ብሩህ ከሚካኤል በቀር ዝክሩን ለዘከሩት ስሙንም ለጠሩት አጋንት አትቀርቡም ከሚካኤል በቀር ስእሉ ባለበት ድርሳኑን ቢደግሙት በረከት ይገኛል ከሚካኤል በቀር በርሱ ቢማፀኑት ከለመኑት በእውነት ሚካኤል ነው በትረ መስቀል ይዞ የሚጠብቀኝ ሚካኤል ነው ከአንበሶች መንጋ የሚታደገኝ/፪/ /አዝ = = = = = በኑሮአችን ሁሉ ከሚካኤል በቀር እርሱ ይመራናል ፈጥኖ ይረዳናል ፈርኦንን ድል ነስቶ ከሚካኤል በቀር ከግብፅ አውጥቶናል በብርሃን መርቶናል የኤርትራን ባህር ከሚካኤል በቀር ከፍሎ እንዳሻገረ ከነአን ደርሰናል ሚካኤል ነው ከበልአም እርግማን እስራኤልን ያዳነ ሚካኤል ነው ዛሬም በአዲስ ኪዳን ክብሩ የገነነ /፪/ ዘማሪ አረጋይ ገ/መድህን          እና ዘማሪት ፀዳለ ጎበዜ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።  ╔✞════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

ልጁ ነኝ ✞ ልጁ ነኝ የሚካኤል ልጁ በቤቱ ያደኩኝ በደጁ የልቤ ብዬ የምጠራው ሚካኤል ለኔ አባቴ ነው❨፪❩ በክንፉ እኔን በእጁ ሰይፍ ይዟል ሚካኤል ሊረዳኝ ቆሟል እንዳስፈሪ እንደ ንጉስ ሠራዊት በቀኜ ነው በቀንና በሌሊት   ሚካኤል አባቴ ለዚ እኮ ነው መመካቴ   ሚካኤል አባቴ ጋሻ ክብሬ ነው ማለቴ   ሚካኤል አባቴ ጎኔ ቆመኽ እንዳቆምከኝ   ሚካኤል አባቴ እኔ ለአለም ምስክር ነኝ      /አዝ = = = = = ልናገር ላውራ ላዚም ልዘምር ከፍ አርጌ ልመስክር መች ይረሳል ልጅነቴ ያሳደገኝ እቅፍ አርጎ በክንፎቹ የከለለኝ   ሚካኤል አባቴ እስከዛሬ ያላልኩትን   ሚካኤል አባቴ በልቤ ውስጥ ያኖርኩትን   ሚካኤል አባቴ ዛሬ ላውራው በአደባባይ   ሚካኤል አባቴ ረድቶኛል ከአባቴ ጋር      /አዝ = = = = = ከተኛሁበት ከእንቅልፌ አንቅቶ ነጻ አወጣኝ እስሬን ፈቶ በጨለማ በወኅኒ ቤት በእስር አብሮኝ ነበር ጠባቂዬ ሚካኤል   ሚካኤል አባቴ በክፉ ቀን ያለ ጎኔ   ሚካኤል አባቴ ያልተለየኝ በድካሜ   ሚካኤል አባቴ ሰው የሚወድ የማይንቅ   ሚካኤል አባቴ በጌታ ፊት ሚያስታርቅ      /አዝ = = = = = ብርቱ እና ኃያል ጽኑ ነው ስሙ ሚካኤል ሞገስ የሆነው ምን ይሆናል ሚካኤልን የያዘ ሰው ምግቡ መና ደመና ነው ሚጋርደው   ሚካኤል አባቴ የአባቶቼ መንገድ መሪ ሚካኤል አባቴ በእኔም ህይወት ታምር ሰሪ   ሚካኤል አባቴ በመንገዴ ቀድሞ ፊቴ   ሚካኤል አባቴ ይስበኛል ወደ ርስቴ 👉ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።  ╔✞════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

✟ተነሳ ህዝቤ ተነሳ✟
📣📣📣" አዋጅ አዋጅ"📢"ያልሰማህ ስማ የሰማህ አሰማ እነዚህ መናፍቃን ከውጭ ሆነው ቤተክርቲያንን መዋጋት ሲያቅታቸው ውስጥ በመግባት በኛ ቆብ በኛ ቀሚስና በኛ መስቀል ኑፋቂያቸዉን እየዘሩ ዶግማችንንና ቀኖናችንን ስርአታችንንና ትሁፊታችንን ለመለወጥ እንቅስቃሴ እያደረጉ እንደሆነ መረጃ ደርሶናልና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ  ምዕመናን በሀገርም በውጪም ያላችሁ ይህንን በመገንዘብ እራሳችሁን እንድጠብቁ ቤተክርስቲያን መልዕክቷን ታስተላልፋለች።"
  ተነሳ ህዝቤ ተነሳ ተነሳ ወገን ተነሳ የጥንቱ እንዳይረሳ የቀድሞ እንዳይረሳ ባገርም በውጪም በየትም ያላችሁ የተዋህዶ ፍቅር ያለ በልባችሁ በሉና ተነሱ ታሪካችሁ ይብራ ምድረ ተሀድሶ ምድረ ሃራትካ          /አዝ = = = = = መጥቷል በኢየሱስ ስም ትጥቅህን ሊያስፈታህ በልና መልሰው የለም አዲስ ጌታ አንዲት ጥምቀትና አንዲት ሃይማኖት አለች ተዋህዶ የተረከብናት          /አዝ = = = = = በነዮዲት ጉዲት በግራኝ አህመድ ገዳም ሲፈርስ አየሁ ካህን ሲታረድ ትላንት የሆነብን ሳይወጣ ቁጭቱ ዳግም ተነሱባት ጡቷን የጠቡት          /አዝ = = = = = በረት ቢያስገቡንም የኤል ልጅ ዝምታ እውነትን ለመግለጥ አንደበት ቢገታ የእውነት ሠይፍ ይዞ የሚፈርድልን እውነተኛው ዳኛ ይምጣ ሰሎሞን        /አዝ = = = = = ከእኛ የሚመስሉ ግን ከእኛ ያልሆኑ አሉ በጥፋት ሀይል የሚሰለጥኑ መክረን አስተምረን እንድትመለስ እድሜ ከሀለውጉስ ከመአርዮስ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

መድኃኔዓለም በማን እንመስልህ መድኃኔዓለም በማን እንመስልህ ቃል አጣን አንተን ሚመጥንህ ቢነገር ቢዘመርልህ ያንተን ነው ላንተ የምንሰጥህ❨፪×❩ መንገድ የምትመራኝ ልታይልኝ አይኔ የልቤ አብርሆት ማያዬ ብርሃኔ ጉዞዬን ያቀናህ ሰላሜ መድህኔ ክበር በአዲስ ዜማ ክበር በአዲስ ቅኔ መድሃኔአለም በሰማይ ዜማ ላንተእልል እልል  '' እንዘምራለን ቀን በቀን ለስምህ '' ክብርህ የቃኘው አዲስ ልዩ ዜማ  '' ለዘለአለም አይቆምም ላንተማ       /አዝ = = = = = ስከፋ ስቸገር አትርቅም ከጎኔ እንደ እናት እንደአባት ታስባለህ ለኔ የማይነጋ ለሊት ማያልፍ የመሰለኝ እንደ ጥላ አለፈ ስምህ ሲከተለኝ መድኃኔዓለም ታማኝ ወዳጅ ነህ ቀርበህ የማትሸሽ '' '' ቀን የከፋለት አትሄድም ሲመሻሽ '' '' መንገደኛ ነኝ ኤማሁስ ምድር '' '' ግባ ከቤቴ ስሰማህ ልደር       /አዝ = = = = = ወዳጄ ሲከዳኝ ጊዜ ሲለውጠው አንተ ግን አንተ ነህ አይደለህ እንደሰው ፈዋሽ ባለዘይት አባቴ ሃኪሜ ስትነካው ሳቅ ሆነ ስቃይና ህመሜ መድኃኔዓለም የምታስብልኝ አባቴ የልቤ '' '' ሁሉን ፈፀምከው ቀድመህ ሃሳቤ '' '' ይኖራል ላንተ ልቤ እየዘመረ '' '' ዝምታ አይችልም ካንተ እየተማረ        /አዝ = = = = = አላጉረመርምም ይህ ቀርቶኛል ብዬ የማያልቅ እንጀራ ከእጅህ ተቀብዬ የልቤን የውስጤን ፈፀምከው በሙሉ አመስጋኝ ነኝ እኔ በሆነልኝ ሁሉ መድኃኔዓለም በሰማይ ዜማ ላንተ እልል እልል '' '' እንዘምራለን ቀን በቀን ለስምህ '' '' ክብርህ የቃኘው አዲስ ልዩ ዜማ '' '' ለዘለአለም አይቆምም ላንተማ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።  ╔✞════●◉❖◉●════✞╗ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

#ተዝካረ_በዓላ_ለማርያም_በደብረ_ምጥማቅ ግንቦት 21 ከሠላሳ ሦስቱ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ደብረ ምጥማቅ ነው፡፡ ደብረ ምጥማቅ ግብጽ ውስጥ በገምኑዲ አቅራቢ የምትገኝ ገዳም ናት፡፡ እመቤታችን ል
#ተዝካረ_በዓላ_ለማርያም_በደብረ_ምጥማቅ ግንቦት 21  ከሠላሳ ሦስቱ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ደብረ ምጥማቅ ነው፡፡ ደብረ ምጥማቅ ግብጽ ውስጥ በገምኑዲ አቅራቢ የምትገኝ ገዳም ናት፡፡ እመቤታችን ልጇን ይዛ በስደት ሳለች ጌታ ‹‹በዚህ ቦታ በስምሽ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ይታነጻል ስሙንም ደብረ ምጥማቅ ይሉታል›› ብሎ ትንቢት ነግሯት ነበር፡፡ ጊዜው ሲደርስም በዚሁ ቦታ በእመቤታችን ስም ቤተ ክርስቲያን ታንጾ ስሙ ደብረ ምጥማቅ ተብሏል፡፡ #በዚህ ቦታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የክርስትናን ሃይማኖት ለመግለጽ ለ5 ቀናት ለክርስቲያኑም ለአረማዊውም በገሀድ ታይታለች፡፡ በዚህም ዕለት በልጇ የመለኮት ብርሃን ከፀሐይ ሰባት እጅ አሸብርቃ መላእክት፣ሊቃነ መላእክት፣ኪሩቤና ሱራፌል ከበዋት ነቢያት፣ሐዋርያት፣ሰማዕታት፣ደናግልና መነኰሳት ሄሮድስ ያስፈጃቸው ሕፃናት ሁሉ ይመጣሉ፡፡ ሱራፌል ማዕጠንት ይዘው እያመሰገኑ ያጥኑ ነበር፡፡ ከሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በነጭ ፈረስ ቅዱስ መርቆሬዎስ በጥቁር ፈረስ በየተራ እየመጡ ይሰግዱላታል፡፡ በዚህም ጊዜ ከቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ ሆና በግልጽ ለሁሉ ትታይ ነበር፡፡ ከፊቷ ብርሃን የተነሣ አምስት ቀን ሌሊቱና ቀኑ አይታወቅም ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ልብሳቸውን ወደ ላይ ሲወረውሩላት የፈቀደችውን ተቀብላ ትልክላቸዋለች፤ ለበረከት ይካፈሉታል፡፡ ከተሰበሰቡትም የሞተ ዘመድ ያላቸው አስነሺልን ሲሏት አስነሥታ በሕይወተ ሥጋ ታሳያቸው ነበር፡፡ እንዲህ እየሆኑ በፍጹም ደስታ አምስቱን ቀን ሰንብተዋል፡፡ ወደ ቤታቸውም ለመኼድ ሲሹ በፊቷ ሰግደው ይሰናበቷታል እርሷም ትባርካቸዋለች፡፡ የበዓሉ መታሰቢያ ከግንቦት 21 እስከ 25 ቀን ነው፡፡ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷ ይደርብን አሜን! ወስብሐት ለእግዚአብሔር! ምንጭ፦መድበለ ታሪክ ፣መዝገበ ታሪክ፣ስንክሳር

ጻድቃኔ ማርያም ✞ ጻድቃኔ ማርያም ደጓ እናቴ መጣው ከደጅሽ አንቺን ብዬ ያጥያቴን ገመድ ፈታሽልኝ የውስጤን ብሶት ተረዳሽኝ ወዳለሽበት ወደ ደጅሽ ስንቄን ሰንቄ ስጓዝ ልጅሽ እንግድነቴን ተቀበልሽኝ ልዩ ፍቅርሽን ገለጥሽልኝ ውስጤ ቢቆሽሽ መች ተፀየፍሽኝ ባዛኙ ልብሽ ይህው ቀረብሽን❨፪×❩ /አዝ = = = = = የተጠማውት አንቺን ነበር እናቴ ፍቅርሽ አሸነፈኝ እራሴን ዳብሰሽ አጽናናሽኝ ብሶቴን ሁሉ አራቅሽልኝ እናትህ አለው አትዘን ብለሽ ተረድተሽኛል ችግሬን አይተሽ❨፪×❩       /አዝ = = = = = የውስጤን ብሶት ስነግርሽ እግርሽ ስር ሆኛ ሳዋይሽ ዝም አላልሽኝም እመቤቴ ቃል ገባሽልኝ ለሂወቴ የጨለመውን ተስፋ አብርተሽ ሰው አርገሽኛል ጤናዬን ሰተሽ❨፪×❩       /አዝ = = = = = የሚገባኝን አርገሽልኝ የተስፋ ስንቄን አሲዘሽኝ ሸኝተሽኛል ወደቤቴ ሁሉን አድራገሽ እመቤቴ ደጅሽ ስመጣ መቼ አፈርኩኝ ምልጃሽ ጎብኝቶኝ ደስታ አገኘሁኝ❨፪×❩ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።  ╔✞════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

ይነበብ ገድሉ ይነበብ ገድሉ ይውጣ ታምሩ ድውይ ይፈወስ ይቀደስ ምድሩ ተክለሃይማኖት አማላጃችን አለ ከእኛ ጋር መሀከላችን አይለወጥም   ተክለሃይማኖት ያለህ ቃል ኪዳን      ተክለሃይማኖት ተክልዬ ስምህ    ተክለሃይማኖት ዛሬም ይሰራል    ተክለሃይማኖት ከተግባር ቤትህ   ተክለሃይማኖት ተሰልፈናል   ተክለሃይማኖት ዳቤህን በልተን   ተክለሃይማኖት ተፈውሰናል     ተክለሃይማኖት          /አዝ = = = = = እጅህ ያለብሰናል   ተክለሃይማኖት የክብር ካባ    ተክለሃይማኖት ከመታሰቢያው   ተክለሃይማኖት መቅደስ እንግባ   ተክለሃይማኖት ስራው ይነገር     ተክለሃይማኖት ለዓለም ሁሉ   ተክለሃይማኖት ታላቅ ነው እና    ተክለሃይማኖት ተክልዬ ገድሉ   ተክለሃይማኖት          /አዝ = = = = = ኢትዮጵያ በራች   ተክለሃይማኖት በስብከትህ   ተክለሃይማኖት ተጠብቀናል   ተክለሃይማኖት በፀሎትህ   ተክለሃይማኖት የአምላክ አገልጋይ   ተክለሃይማኖት ወንጌል ያዘለ   ተክለሃይማኖት በቅዱስ ስሙ   ተክለሃይማኖት ጠላት ቆሰለ   ተክለሃይማኖት         /አዝ = = = = = ጠጣን ፀበሉን   ተክለሃይማኖት ታሸን በእምነቱ   ተክለሃይማኖት ስሙ ሲነሳ    ተክለሃይማኖት ጠፉ አጋንንቱ    ተክለሃይማኖት ኢየሩሳሌም    ተክለሃይማኖት ሆነች ምድራችን   ተክለሃይማኖት ክብራችን በዛ   ተክለሃይማኖት ስለ አባታችን    ተክለሃይማኖት #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

✞ ክርስቶስ ሰምራ ✞ ክርስቶስ ሰምራ ትጉህ መናኝ ነሽ ለሙሽራነት በላይ የታጨሽ ሀብት ትዳርሽን ሁሉንም ትተሽ መናኝ ሁነሻል አምላክ በልጦብሽ ክርስቶስ ሰምራ ልጆቼን ትዳሬን ክርስቶስ ሰምራ ንብረቴን ሳትዪ ክርስቶስ ሰምራ መናኝ አደረገሽ ክርስቶስ ሰምራ ፍቅሩ የአዶናይ ክርስቶስ ሰምራ በቤቱ መጣልን ክርስቶስ ሰምራ አምላክን ብለሽ ክርስቶስ ሰምራ የሞቀ ቤትሽን ክርስቶስ ሰምራ እሱን አስናቀሽ        /አዝ = = = = = ክርስቶስ ሰምራ ዲያቢሎስ ከአምላኩ ክርስቶስ ሰምራ ቢታረቅ ብለሽ ክርስቶስ ሰምራ ከሲኦል ሂደሻል ክርስቶስ ሰምራ እሱን ፈልገሽ ክርስቶስ ሰምራ ትዕቢቱ በልጦበት ክርስቶስ ሰምራ ከሲኦል ጣለሽ ክርስቶስ ሰምራ ሚካኤል ደርሶልሽ ክርስቶስ ሰምራ ከጥልቅ አወጣሽ        /አዝ = = = = = ክርስቶስ ሰምራ ፀሎት ስታደርሺ ክርስቶስ ሰምራ ከባህር ውስጥ ሁነሽ ክርስቶስ ሰምራ ይመላለሳሉ ክርስቶስ ሰምራ አሳዎች በአካልሽ ክርስቶስ ሰምራ ለአስራ ሁለት አመት ክርስቶስ ሰምራ በውስጡ ፀለይሽ ክርስቶስ ሰምራ ሰላም በዓለም ላይ ክርስቶስ ሰምራ ይሁን እያልሺ 👉ዘማሪ አሸናፊ ዘለቀ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ

📍ዜናዋን ሰማን ዜናዋን ሰማን ሰማን ዜናዋ የክርስቶስ ሰምራ ፅኑ ተጋድለዋ ቅድስት እናት ናት ንፅሕት እጅግ ያስገርማል የገድልዋ ፅናት አስራ ሁለት ዓመት ስትፀልይ ኑራ ሞገስ አግኝታለች ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ እንናገራለን እኛስ ልእልናዋ እንመሰክራለን የሰማን ዜናዋ     /አዝ = = = = = ያላትን ሁሉትታ ከቤቷ ስትወጣ ከሃብትና ንብረት ቅድስና መርጣ በፅኑ ስራዋ አክሊል ተጎናፅፋ ክብርን ተቀዳጀች መከራውን አልፋ     /አዝ = = = = = እንኳንና ሰው የተማፀናት አጋዥ መከታ ያደረጋት ለዲያብሎስ እርቅን ለምናለች እና ለክርስቶስ ሰምራ ይድረሳት ምስጋና /አዝ = = = = = በቃል ኪዳንዋ የታመነ በአፀድዋ ገብቶ እርሷን ለለመነ በመንግስተ ሰማይ ይኖራል ተከብሮ በክብር በልዕልና ከርሷ ጋር አብሮ 👉ዘማሪ ዲ/ን ፀሐዩ ንጉስ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ