en
Feedback
ወድሰኒ ​​

ወድሰኒ ​​

Open in Telegram

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ⛪️የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የመዝሙሮች ግጥሞች ከነ ዜሞቻቸው ለማግኘት ወደ ቻናላችን ይቀላቀሉ⛪️ YouTube https://youtube.com/@enamsgn?si=LYkrdnXK7rL--cMv የመዝሙር ግጥም መላክ ወይም ሀሳብ አስተያየት ጥቆማ ካሎት በ @Slamanshdngl ላይ ያድርሱን

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ወድሰኒ ​​

Channel ወድሰኒ ​​ (@enamsgn) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 21 655 subscribers, ranking 3 546 in the Religion & Spirituality category and 1 602 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 21 655 subscribers.

According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -503 over the last 30 days and by -11 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 3.25%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 0.99% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 704 views. Within the first day, a publication typically gains 215 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 5.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ⛪️የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የመዝሙሮች ግጥሞች ከነ ዜሞቻቸው ለማግኘት ወደ ቻናላችን ይቀላቀሉ⛪️ YouTube https://youtube.com/@enamsgn?si=LYkrdnXK7rL--cMv የመዝሙር ግጥም መላክ ወይም ሀሳብ አስተያየት ጥቆማ ካሎት በ @Slamanshdngl ላይ ...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

21 655
Subscribers
-1124 hours
-1197 days
-50330 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
September '26
September '260
in 0 channels
August '260
in 0 channels
Get PRO
July '26
+1
in 1 channels
Get PRO
June '260
in 2 channels
Get PRO
May '260
in 5 channels
Get PRO
April '260
in 3 channels
Get PRO
March '26
+1
in 3 channels
Get PRO
February '260
in 5 channels
Get PRO
January '26
+1
in 5 channels
Get PRO
December '250
in 5 channels
Get PRO
November '250
in 3 channels
Get PRO
October '25
+1 007
in 0 channels
Get PRO
September '25
+923
in 2 channels
Get PRO
August '25
+1 142
in 5 channels
Get PRO
July '25
+1 043
in 8 channels
Get PRO
June '25
+1 060
in 5 channels
Get PRO
May '25
+804
in 8 channels
Get PRO
April '25
+1 447
in 7 channels
Get PRO
March '25
+2 101
in 10 channels
Get PRO
February '25
+1 849
in 6 channels
Get PRO
January '25
+1 813
in 7 channels
Get PRO
December '24
+2 114
in 10 channels
Get PRO
November '24
+2 259
in 14 channels
Get PRO
October '24
+2 119
in 10 channels
Get PRO
September '24
+1 281
in 9 channels
Get PRO
August '24
+1 754
in 19 channels
Get PRO
July '24
+1 167
in 14 channels
Get PRO
June '24
+1 096
in 8 channels
Get PRO
May '24
+1 395
in 11 channels
Get PRO
April '24
+2 300
in 19 channels
Get PRO
March '24
+3 411
in 12 channels
Get PRO
February '24
+3 726
in 12 channels
Get PRO
January '24
+218
in 21 channels
Get PRO
December '23
+176
in 4 channels
Get PRO
November '23
+122
in 5 channels
Get PRO
October '23
+94
in 5 channels
Get PRO
September '23
+134
in 0 channels
Get PRO
August '23
+90
in 0 channels
Get PRO
July '23
+98
in 0 channels
Get PRO
June '23
+82
in 0 channels
Get PRO
May '23
+120
in 0 channels
Get PRO
April '23
+92
in 0 channels
Get PRO
March '23
+66
in 0 channels
Get PRO
February '23
+64
in 0 channels
Get PRO
January '23
+101
in 0 channels
Get PRO
December '22
+130
in 0 channels
Get PRO
November '22
+94
in 0 channels
Get PRO
October '22
+79
in 0 channels
Get PRO
September '22
+66
in 0 channels
Get PRO
August '22
+97
in 0 channels
Get PRO
July '22
+68
in 0 channels
Get PRO
June '22
+54
in 0 channels
Get PRO
May '22
+30
in 0 channels
Get PRO
April '22
+39
in 0 channels
Get PRO
March '22
+42
in 0 channels
Get PRO
February '22
+39
in 0 channels
Get PRO
January '22
+41
in 0 channels
Get PRO
December '21
+56
in 0 channels
Get PRO
November '21
+98
in 0 channels
Get PRO
October '21
+121
in 0 channels
Get PRO
September '21
+137
in 0 channels
Get PRO
August '21
+202
in 0 channels
Get PRO
July '21
+194
in 0 channels
Get PRO
June '21
+162
in 0 channels
Get PRO
May '21
+91
in 0 channels
Get PRO
April '21
+66
in 0 channels
Get PRO
March '21
+72
in 0 channels
Get PRO
February '21
+76
in 0 channels
Get PRO
January '21
+125
in 0 channels
Get PRO
December '20
+814
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
07 September0
06 September0
05 September0
04 September0
03 September0
02 September0
01 September0
Channel Posts
እጅግ አሳዛኝ ክስተት እጅግ አሳዛኝ ክስተት በጅጅጋ ከተማ የሃይማኖት እኩልነትና ነጻነት በተረጋገጠባት ሀገራችን፤ ዛሬ በጅጅጋ ከተማ ያልተጠበቀና አሳዛኝ ድርጊት ተፈጽሟል። በከተማው አዲስ የተገነባው የመድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን መፍረሱ ታውቋል። ይህ ድርጊት በአካባቢው ምዕመናን ዘንድ ከፍተኛ ሀዘንን የፈጠረ ሲሆን፣ የሚመለከታቸው አካላት ስለዚህ ድርጊት አስቸኳይ ህጋዊ ማጣራት እንዲያደርጉ ማህበረሰቡ እየጠየቀ ይገኛል። © ሶማሌ ሀገረ ስብከት

2
✞ ደስተኛ ነኝ እኔ ✞ ደስተኛ ነኝ እኔ በሕይወቴ ስላለኸኝ ውዴ አብረሆቴ ዓይምሮን የሚያልፈው የአንተ ምህረት በልቤ ይፈሳል እንደ ጅረት ለመቅደሱ ሰሪ ሆንኩለት መቅደስ የሚባርከውን ስሙን ልቀድስ ችሎ ባይክስህም የዓንደበቴ ዜማ አልውልም አላደርም ሳልጠራህ እኔማ        /አዝ = = = = = አላወርድም ሙሾ አይወርድም ክራሬ ስለሚያልፈው ኑሮ አይተባም ብዕሬ መኖሪያዬ ክብሬ በሰማይ ነውና ኢየሱስ ብቻ ነህ የአንደበቴ ቃና        /አዝ = = = = = ጎተራዬ ቢጎድል ወይኔም ባያፈራ ሠላም አለው ውስጤ በሰራኸው ስራ ክብርህን ያውጃል የእንባዬ ጅረቱ ስለረሰረሰች ነፍሴ ከሙላቱ        /አዝ = = = = = ስላሸበረቀ መቃኔ በአንተ ደም መዝሙሬ ዜማዬ ሆኗል የዘላለም አላንጎራጉርም ለሚያልፈው መሻቴ የዘላለም አምላክ ስላለ በቤቴ 👉ዘማሪት ትርሀስ ገ/እግዚአብሔር #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ
813
3
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!         🕯 #ፍልሰተ_ሥጋሃ_ለእግዝእትነ_ማርያም    እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በ64 ዓመቷ ጥር 21 ቀን ከዚህ ዓለም ድካም ማረፏን ‹ዕረፍታ ለእግዝእትነ ማርያም› በሚለው በጥር 21 የጽሑፍ ዝግጅታችን መጻሕፍትን ጠቅሰን ማቅረባችን ይታወሳል፡፡ ሐዋርያትም ሥጋዋን በክብር ለማሳረፍ ወደ ጌቴሴማኒ ይዘዋት ሲሄዱ አይሁድ በምቀኝነት ተነሳስተው ሥጋዋን ከሐዋርያት እጅ ነጥቀው ሊያቃጥሉት ሲሄዱ ታውፋንያ የተባለው መሪያቸው የአልጋውን ሸንኮር ቢይዘው የታዘዘ መልአክ ሁለቱን እጁን ቆርጦ የእመቤታችንን አስከሬን ከወንጌላዊው ዮሐንስ ጋር ነጥቆ ገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር እንዳኖረው ‹ጸመ ፍልሰታ ለማርያም› በሚለው ጽሑፋችን ገልጸን ነበር፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላም ቅዱስ ዮሐንስ ተመልሶ ሲመጣ በገነት ዕፀ ሕይወት ሥር መኖሯን ለሐዋርያት ነገራቸው፡፡ እነርሱም እንደ ዮሐንስ ባለማየታቸው ሲያዝኑ ዓመት ከተቀመጡ በኋላ ምን እናድርግ ብለው መክረው ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ሁለት ሱባዔ ያዙ፤ በሁለተኛው ሱባኤ መጨረሻ (ነሐሴ 14 ቀን) መልአክ የእመቤታችንን ሥጋ ከገነት ዕፀ ሕይወት ሥር አምጥቶ ሰጣቸውና ወደ ጌቴሴማኒ ወስደው ቀበሯት፡፡ የእመቤታችንን ሥጋ በሚቀብሩበት ጊዜ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ቅዱስ ቶማስ በአገልግሎት ምክንያት ወደ ሀገረ ስብከቱ (ሕንድ) ሄዶ ነበር፡፡ እርሱ ከአገልግሎት በደመና ሲመለስ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስታርግ አገኛት፡፡ ቅዱስ ቶማስ ያን ጊዜ ሌሎች አይተው ለእርሱ የቀረበት መስሎት ‹‹ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ ዛሬ ደግሞ ያንችን ትንሣኤ ሳላይ›› ብሎ ከደመናው ተወርውሮ ሊወድቅ ፈለገ፡፡ እመቤታችንም አጽናንታው እርሱ ብቻ እንዳያት አስረድታ ለምልክት የተገነዘችበትን ሰበን ሰጥታ ሰደደችው፡፡    ቅዱስ ቶማስ ከሐዋርያቱ ዘንድ በደረሰ ጊዜ ዐውቆ ነገሩን ደብቆ ‹‹የእመቤታችን ነገር እንዴት ሆነ?›› ብሎ ቢጠይቃቸው ‹‹አግኝተን ቀበርናት እኮ›› አሉት፤ ቶማስም ‹‹አይሆንም ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር ለሰሚም አያምርም›› አላቸው፡፡ ከዚያ ‹‹ቀድሞ የጌታችንን ትንሣኤ ተጠራጠርክ፤ አሁን ደግሞ አታምንም›› ብለው በቅዱስ ጴጥሮስ መሪነት ወደ መካነ መቃብሯ ይዘውት ሄደው መቃብሩን ከፍተው ቢያጧት ደንግጠው ቆመው ሳለ ቶማስ ‹‹አታምኑኝም ብዬ ነው እንጅ ተነሥታ ዐርጋለች›› ብሎ የቀበሩበትን ሰበን አሳያቸው፤ እነርሱም ትንሣኤና ዕርገቷን አምነው ሰበኑን ለበረከት ተከፋፍለውታል፡፡    ከዚህ በኋላ በመንፈሳዊ ቅንዓት ‹‹ቶማስ አይቶ እኛ ትንሣኤዋን ዕርገቷን ለምን አናይም?›› ብለው ትንሳኤዋን ዕርገቷን እንዲያሳያቸው በዓመቱ ነሐሴ 1 ቀን ሱባዔ ገቡ፡፡ ሁለተኛው ሱባዔ ነሐሴ 14 ቀን ተጠናቅቆ ከሁለት ቀን በኋላ በተነሣችበት ነሐሴ 16 ቀን ሐዋርያትን ሰብስቦ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሠራዒ ካህን፣ ቅዱስ ጴጥሮስን ተራዳኢ ካህን፣ እስጢፋኖስን ደግሞ ሠራዒ ዲያቆን አድርጎ፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን መንበር አድርጎ ቀድሶ አቍርቧቸው ትንሣኤዋንና ዕርገቷን አሳይቷቸዋል፡፡ ለእመቤታችንም ‹‹በዚህች ቀን ሥጋዬንና ደሜን የሚቀበል፣ ለተቸገረ የሚሰጥ ኃጢአቱን ይቅር እልለታለሁ፤ መንግሥተ ሰማያትንም አወርሰዋለሁ›› ብሎ ቃል ኪዳን ሰጥቷታል፡፡ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃና ጸሎት አይለየን አሜን!              ወስብሐት ለእግዚአብሔር! ምንጭ፦ ነገረ ማርያም ፣ ስንክሳር ዘነሐሴ 16 ፣ መድበለ ታሪክ
789
4
✞ እመቤታችን ✞ እመቤታችን በቀኝ ቆማለች የብርሐን ልብሷን ተጎናጽፋለች ሠዓሊተ ምሕረት መዝገበ ጸሎት አቁራሪተ መዓት የጌታዬ እናት/2/ እመቤታችን *** የብርሐን ልብስሽን እመቤታችን *** ነይ ተጎናጽፈሽ እመቤታችን *** ሠዓታቱን ሥናደርስ እመቤታችን *** ንዒ ሥንልሽ እመቤታችን *** በሠጠሽ ቃል ኪዳን እመቤታችን *** እንድታስምሪን እመቤታችን *** እንለምንሻለን እመቤታችን *** ከእግርሽ ሥር ወድቀን         /አዝ = = = = = እመቤታችን *** ከኪሩቤል ድንግል እመቤታችን *** አንቺ ትበልጫለሽ እመቤታችን *** ከሦስቱ አካል አንዱን እመቤታችን *** ወልድን ሥለ ወለድሽ እመቤታችን *** ስለእዚህ ድንግል ሆይ እመቤታችን *** እንወድሻለን እመቤታችን *** ዘወትር ጠዋት ማታ እመቤታችን *** እንማልዳለን         /አዝ = = = = = እመቤታችን *** ለሥም አጠራሩ እመቤታችን *** ክብር ይግባውና እመቤታችን *** እናት እንድትሆኚኝ እመቤታችን *** ሸልሞኛልና እመቤታችን *** ሥምሽን ሥጠራ እመቤታችን *** ሠዎች ያዝኑልኛል እመቤታችን *** ሞገሴ ነሽና እመቤታችን *** ይድረስሽ ምሥጋና         /አዝ = = = = = እመቤታችን *** ድንቅ ድንቅ ነገር እመቤታችን *** ነብያት ተናገሩ እመቤታችን *** ሐገረ እግዚአብሔር እመቤታችን *** ድንግል ናት እያሉ እመቤታችን *** ሁለተኛው አዳም እመቤታችን *** ከአንቺ ተወለደ እመቤታችን *** የተዘጋው ደጃፍ እመቤታችን *** በአንቺ ተከፈተ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗         ✞✞ ✞✞ ✞✞ ✞✞ ✞✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖         ✞✞ ✞✞ ✞✞ ✞✞ ✞✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ
534
5
✞ ማርያም አርጋለች ✞ ማርያም አርጋለች ወደ ገነት /2/ የሰማይ መላእክት እያረጓጓት እሷም እንደ ልጇ ተነስታለች የአባቷ ዳዊት ትንቢት ልትፈፅም ወርቁን ተጎናፅፋ በቀኙ ልትቆም ወደ አምላክ ማደሪያ ወደ ሰማያት አረገች በእልልታ ድንግል የኛ እናት አርጋለች ማርያም ማርያም ተነስታለች /አዝ===== ሰማያት ይከፈት ደመናም ይዘርጋ ዝምታም አይኖርም እመ አምላክ አርጋ አንደበት ይከፈት ማርያምን ያመስግን ከዘላለም ጥፋት በምልጃዋ እንድንድን አርጋለች ማርያም ተነስታለች /አዝ===== የአምላክ ማደሪያ ያ ቅዱስ ስጋሽ አምላክን ያቀፉ እነዚያ እጆችሽ ሙስና መቃብር ይዞ አላስቀራቸው ተነስተዋል በክብር በእምነት አየናቸው አርጋለች ማርያም ተነስታለች /አዝ===== ሃዋርያት አበው እንኳን ደስ አላችሁ በክብር አረገች ማርያም ሞገሳችሁ ወደ አለምም ውጡ ሰበኗን ይዛችሁ የድንግል እርገቷን ንገሩ ተግታችሁ አርጋለች ማርያም ተነስታለች /አዝ===== ማርያም አርጋለች ወደ ገነት /2/ የሰማይ መላእክት እያረጓጓት እርሷም እንደ ልጇ ተነስታለች #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።         ✞✞✞✞✞✞✞✞✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖   ❖ @enamsgn @enamsgn ❖         ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
538
6
✞ ድንግል ወላዲተ ቃል ✞ ድንግል❨፪×❩ ወላዲተ ቃል ❨፪×❩ አሟሟትሽ በጥር ነሃሴ መቃብር ድንግል ያንቺ ለብቻ ነው ትንሳኤሽ ሲነገር ድንግል ስጋሽ በምድር ላይ የታል እንደፍጡር ድንግል አርጓል ወደ ሰማይ ከክርስቶስ መንበር ድንግል             /አዝ = = = = = ስጋሽን ሲያሳርጉ መላክት ከሰማይ ድንግል ቶማስ በደመና ሲመጣ መንገድ ላይ ድንግል መግነዝ ተረከበ ለሐዋርያት ሊያሳይ ድንግል             /አዝ = = = = = ትንሳኤሽን ሽተው ግራ ሲገባቸው ድንግል ሐዋርያት ጾመው ተገልጥሽላቸው ድንግል ተቀብራ አልቀረችም በምድር ከደጅዋ ድንግል ወደላይ አረገች እርሱዋም እንደልጅዋ ድንግል             /አዝ = = = = = ለማየት ሲጓጉ የድንግልን ትንሳኤ ድንግል እርገቱዋን አወቁ በልዩ ሱባኤ ድንግል እኛም እንጸልይ በራችንን እንዝጋ ድንግል ከወላዲተ አምላክ እንድናገኝ ዋጋ ድንግል 👉ሊቀ መዘምራ ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ። ╔✞════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ
724
7
ታቦር አበራ ታቦር አበራ ምድርን ከደናት ያደመና እንቅልፍ የለንም ታላቅ ነጎድጕድ ሆኗልና አነቃን ለምስጋና ሙሴም የቀደመው ሰዉ  ኤልያስ ኃይለኛው ተገኝተዋል በታቦር ምስክርህ ሆነው እኛም ከገናናው ክብር ያባቱን ቃል ሰምተናል በረዶ ሆኗል ልብሱ እፁብ እፁብ ብለናል        /አዝ = = = = = ቃል ገብተህልኝ ነበር ልታሳየኝ ክብርህን ንገስ ከሞት ገስግሰህ አይቸሃለሁ አሁን የሳት ፈረሶች አሉህ ታዋጊው የኔ ጌታ አርሙኒየም ደስ አለው ስሳራን ስለመታ        /አዝ = = = = = እጠብቅሃለሁኝ በምታልፍበት ቆሜ መብራቶቼን አብርቼ ነጩን ልብስ ተሸልሜ የዳዊት ልጆይ ግባ ኢየሱስ ወደቤቴ ብልኤል እልሀለሁ ድናለች ሰውነቴ        /አዝ = = = = = ሁሉንም ብታከብር ሁሉንም ብትምረው ማነው ቸርነትህን የሚከለክለው ጠዋትም የተጠራ አምሽቶ የገባው ሆነዋል ባለዋጋ ከበዛው ስጦታው        /አዝ = = = = = የረዳኸው ይናገራል ያሰበከው በሕይወቱ አቤነዘር እያለ ይዘምር ባንደበቱ በደስታየም ቀን አለህ አይሃለሁ ከጎኔ ከነጋር አልቅሰሃ አሳዝኖህ ሀዘኔ ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ
910
8
✞ ወፌ ሰንብታ ✞                         ወፌ ሰንብታ መጣች ለፍልሰታ አግርሽ የት ነው ኤፍራታ አሳድሪኝ ማታ ይናፍቀኛል ሌሊት የሰማዩ እልፍኝ መብራት ወፌ የኔ እመቤት/2×/ በክንፍሽ ጥላጋርደሽ/2×/ ከልጅሽ ሥፍራ ወስደሽ/2×/ እንዳልቆምበሽ በግራ እንዳያሰቃየኝ መከራ ወፌ ነፍሴን አደራ/2×/ አንቺን ስለምን ስለምን ደግሞም በልጅሽ ሳምን ሲኦል ይብላኝ ወይ እኔን?/2×/ እሳት አዝላ እሳት አዝላ ወዴት ባከነች ከገሊላ? ባረፍሽበት ከዚያ ሥፍራ ሽፍቶች ጠበቁሽ በዚያ ቆላ ዓይኖችሽ ፈርተው ስለነሱ እንባዎችንም አፈሰሱ የኔ ይጥፋልሽ ሁለት ዐይኔ ባንቺ ፋንታ ባንቺ ፋንታ እኔ በስደት ልንገላታ እኔን ይጭነቀኝ ይጥበበኝ እንደጠበበሽ ግራ ቀኝ ሽፍቶች ከበውሽ ሲማከሩ ዐይኖችሽ ፈርተው እንባን ዘሩ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።         ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖   ❖ @enamsgn @enamsgn ❖         ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
1 320
9
​​​​​​ፍልሰታ ምን ማለት ነው? ሊቀ ማእምራን ደጉ ዓለም ለዚህ ጥያቄ የሚከተለውን ምላሽ ሰጥተዋል፤ "ፍልሰታ ማለት ፈለሰ /ተሰደደ/ ከሚለው ግስ የወጣ ነው።" ‹ፍልሰት› ማለት ደግሞ የተለያየ ትርጕም ቢሰጠውም ‹ፍልሰታ  ለማርያም› ተብሎ ሲገለጽ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከሚያልፈው  ወደ ማያልፈው ዓለም ከመቃብር የወጣችበት (የተነሣችበት) ቀን ማለት ነው፡፡ ወይም ደግሞ ከሥጋዊው ዓለም ወደ መንፈሳዊው ዓለም የተሸጋገረችበት ማለት ነው፡፡›› ቀሲስ ስንታየሁ አባተም በተመሳሳይ መልኩ ስለ ፍልሰታ እንዲህ በማለት ማብራርያ ሰጥተዋል፡፡  ‹ፍልሰታ ለማርያም› የሚለው የግእዝ  ቃል ሲኾን ‹ፍልሰታ› ማለት ደግሞ ‹ፈለሰ› ከሚል ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ‹ፍልሰት› ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መሔድን (መፍለስን) ያመለክታል፡፡ እመቤታችን ካረፈች በኋላ የሥጋዋን መፍለስ አስመልክቶ ሐዋርያት የእመቤታችን ሥጋ የት እንደ ተቀበረ አላወቁም ነበርና እግዚአብሔር የእመቤታችንን ሥጋ እንዲገልጥላቸው የጾሙት ጾም ነው፡፡ ሐዋርያት ሁለት ሱባዔ ጾመው የእመቤታችንን ሥጋዋን ሰጥቷቸው  ትንሣኤዋንና ዕርገቷን በማየት በረከት ያገኙበት ጾም ነው፡፡ ስለኾነም ምእመናን ፍልሰታ ለማርያምን ከልጅ እስከ አዋቂው በጾም በጸሎትና በመቍረብ በጋራ በፍቅር፣ በሰላም ያሳልፉታል፡፡››  ሊቀ ማእምራን ደጉ ዓለም ካሣ እንዳብራሩት ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን እንዲጠብቃት ከተደረገ በኋላ ሐዋርያት ‹‹የእመቤታችን ነገር እንዴት ነው?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ‹‹እመቤታችንማ በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር ናት›› ብሎ ነገራቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ሐዋርያት እመቤታችን ከመቃብር መነሣቷንና ማረጓን ማየት አለብን፤ እንዴት ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ እንቀራለን ብለው በመንፈሳዊ ቅናት በመነሣሣት ነሐሴ አንድ ቀን በዕለተ ሰኞ ሁለት ሰባት ሱባዔ ያዙ፡፡ በዐሥራ አራተኛው ቀን ጌታችን የእመቤታችንን ሥጋ አንሥቶ ሰጣቸውና በጌቴሴማኒ ቀበሯት፡፡ እመቤታችን በ፷፬ ዓመቷ ጥር ፳፩ ቀን ዐርፋ ነሐሴ ፲፬ ቀን ተቀብራለች፡፡ ይኹንና ሐዋርያት ቢቀብሯትም ትንሣኤዋንና ዕርገቷን አላዩም ነበር፡፡ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ያየው ሲቀብሯት ያላየው ሐዋርያው ቶማስ ነው፡፡ ቶማስ እንዲያስተምር ሕንድ አገር ዕጣ ደርሶት አስተምሮ በደመና ሲመለስ ነሐሴ ፲፮ ቀን እመቤታችን ስታርግ ሕዋ ላይ ተገናኙ በማለት ሊቀ ማእምራን ደጉ ያስረዳሉ፡፡ እንደ እርሳቸው አገላለጽ ምእመናን ጾመ ፍልሰታ የእመቤታችን ዕረፍት፣ ትንሣኤና ዕርገቷ የሚዘከርበት ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ የኾነ ጾም ነው፡፡ በየዓመቱ ሕፃን አዋቂው ሳይቀር የእመቤታችን ፍቅር አድሮባቸው ጾሙን ይጾማሉ፣ ያስቀድሳሉ፤ ይቈርባሉ፡፡ የፍልሰታን ጾም ከሌሎቹ አጽዋማት ልዩ የሚያደርገው ምንድን ነው? የፍልሰታን ጾም ከሌሎቹ አጽዋማት ልዩ የሚያደርገው ምንድን ነው? ለሚለው ጥያቄ ሊቀ ማእምራን ደጉ ምላሽ ሲሰጡም "ኢትዮጵያ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዐስራት ሀገር በመሆኗ እና ሕዝበ ክርስትያኑ ለእመቤታችን ልዩ ፍቅር ስላላቸው መሬት ላይ እየተኙ፣ ጥሬ እየበሉ በሰላም በፍቅር ይጾሙታል፡፡  ምእመናን ፍልሰታን ከሌሎች አጽዋማት በተለየ መልኩ መሬት ላይ እየተኙ ይጾሙታል፡፡ ይህ ደግሞ የእመቤታችን ፍቅር ስለሳባቸው ነው ፍቅር›› በማለት ያብራራሉ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
1 564
10
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!              🕯 #ዮሴፍ_አረጋዊ    አረጋዊው ዮሴፍ ትውልዱ ከነገደ ይሁዳ ከቤተ ዳዊት ሲሆን እግዚአብሔርን የሚፈራ፣ ለሰው የሚራራ ደግ ሰው ነበር፤ (ማቴ 1፥16-25 ፣ ሉቃ 1፥27)፡፡ ድግር ጠርቦ፣ ጥርብ አለዝቦ በመሸጥ ይተዳደር ነበር፤ ለዚህም ነው ኢየሱስ ክርስቶስን ‹‹የጠራቢው ልጅ አይደለምን?›› እያሉ የሚጠሩት፤ (ማቴ 13፥55-56)፡፡ ቅዱስ ዮሴፍ ማርያምን (የቅድስት ኤልሳቤጥና ቅድስት ሐና እመ ማርያም እኅት) አግብቶ ያዕቆብ፣ ዮሳ፣ ስምዖን፣ ይሁዳና ሰሎሜ የሚባሉ ልጆችን ወልዷል፡፡ ሚስቱ ከሞተችበት በኋላ አይሁዳውያን በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ላይ በጠላትነት ተነሥተው ከቤተ መቅደስ ትውጣልን ባሉ ጊዜ ወስዶ ከቤቱ አስቀምጧታል፡፡ ከዚህ በኋላ እስከ ዕለተ ሞቱ ድረስ በደስታዋም በኀዘኗም ጊዜ አልተለያትም፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በወለደች ጊዜም ዳስ ሠርቶ አገልግሏታል፡፡    ሄሮድስ ሕፃናትን በሰይፍ በአስፈጀ ጊዜ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልጇን ለማዳን ወደ ግብፅና ኢትዮጵያ በተሰደደች ጊዜ ሦስት ዓመት ከመንፈቅ ረሃቡን፣ ጥሙን፣ የቀን ሐሩሩን፣ የሌሊት ቁሩን ታግሣ በረሀ ለበረሀ በተንከራተተችበት ወቅት አልተለያትም፤ (ማቴ ምዕራፍ 2)፡፡    ከስደት ከተመለሱ በኋላም ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ አባት ሆኖ አሳድጎታል፤ አይሁዳውያን ጌታን የዮሴፍ ልጅ የሚሉትም በዚህ ምክንያት ነው፡፡ ቅዱስ ዮሴፍ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ከኒቆዲሞስ ጋር ገንዞ በአዲስ መቃብር አኑረውታል፤ (ዮሐ 19፥38)፡፡ አረጋዊው ዮሴፍ በ104 ዓመቱ ሐምሌ 26 ቀን ዐርፏል፡፡ የአረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ ጸጋና በረከት ይደርብን አሜን!           ወስብሐት ለእግዚአብሔር! ምንጭ፦ መጽሐፍ ቅዱስ
1 325
11
​​​​👆የቀጠለ እኒኽም ቅዱሳን ይኽንን በሚነጋገሩበት ጊዜ በውስጡ አንገትን የሚቆለምም ልብንም የሚያቀልጥ ሆድን የሚሰነጥቅ ሥርን የሚበጣጥስ መሳሪያ ካለበት የብረት ጋን ውስጥ ጨመራቸው፡፡ ከዚህ በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደና የብረቱን ጋን እሳት አጠፋው፡፡ ከቅዱሳኑም አንዳቸውንም ሳያቃጥላቸው የብረቱ ጋር ማቃጠሉና መፍላቱ ጸጥ አለ፡፡ ወንድሞቻችን ሆይ እንግዲህ በጭንቃቸው ጊዜ ገድላቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ይህ መልአክ ከሰማእታትና ከጻድቃን ጐን እንደማይለይ እወቁ ለኃጥአንም ኃጢአታቸውን ይቅር ይላቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ይጸልይላቸዋል፡፡ እኛም የዚህ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓሉን እያከበርን አማላጅና ወዳጅ እናድርገው። በዚህም በሚመጣውም ዓለም ሊረዳን ይችላልና፡፡ ዳግመኛም መስፍኑ ሐሳቡ ሳይሳካለት ስለቀረ 14 የሾሉና የጋሉ የብረት ችንካሮች አምጥተው ሰባቱን በእናቱ በኢየሉጣ አካል ሰባቱን በራሱ በቂርቆስ አካል ማለት ሁለቱን በጆሮዎቹ ሁለቱን በዐይኖቹ ሁለቱን በአፍንጫዎቹ አንዱን በልቡ ይቸነክራቸው ዘንድ ጭፍሮቹን አዘዘ፡፡ ዳግመኛም የህፃኑን የእራስ ቆዳ ገፈው እሳት ውስጥ ይጨምሩ ዘንድ አዘዘ፡፡ አሁንም መልአኩ መጥቶ ይህንን መከራ ከእርሱ አራቀለት፡፡ ቀጥሎም በመቃን ውስጥ ጨምረው በገመድ እንዲጎትቱት አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ መልአኩ አዳነው፡፡ ሕዝቡም ይህንን ሁሉ ተአምር ባዩ ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገኑት ቅዱስ ገብርኤልንም አከበሩት፡፡ ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት እየሉጣ ብዙ መከራ ከተቀበሉ በኋላ ጥር 15 በሰይፍ ተመትተው ስማትነትን ተቀብለዋል። የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል ፣ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት እየሉጣ ተራዳኢነት ጸሎት አይለየን። ከዚህ በኋላ ሕፃኑን አስፈልገው ቢጠይቁት ነቢዩ ዳዊት የተናገረው ኃይለ ቃል መንፈስ ቅዱስ ተገልጾለት፤ ‹‹የአሕዛብ ጣዖታት የወርቅና የብር የሰው እጅ ሥራዎች ናቸው፡፡ የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ›› መዝ. ፻፴ በማለት ሲዘልፏቸው አገር ገዥው ሰምቶ ተቆጣና የብረት ጋን አስመጥቶ ውኃ ሞልቶ ከዕቶን እሳት ላይ ጥዶ ልዩ ልዩ ማገዶዎች በመጨመር ነበልባሉ ከመጠን በላይ ሆነ፡፡ የብረት ጋኑም ድምፅ እንደ ክረምት መብረቅና ነጎድጓድ እስኪያስፈራ ድረስ አስነድዶ ሕፃኑን ከነእናቱ ወስዳችሁ ጨምሩአቸው ብሎ አዘዘ፡፡ በዚህ ጊዜ ቅድስት ኢየሉጣ በጣም ፈራች፡፡ የእግዚአብሔር ሥራ እፁብ ድንቅ ግሩም ረቂቅ ነው፡፡ ገና አፉን ያልፈታ የሦስት ዓመት ሕፃን ‹‹እናቴ ሆይ! ገድላችን እንፈጽም ዘንድ ጨክኝ በርቺ›› አላት፡፡ ቅድስት ኢየሉጣም ‹‹ልጄ የነፍስ አባት ሁነኝ›› አለችው፡፡ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ከዘመናቸው ሳይደርስ፣ ታሪካቸውን ሳይማር የሠለስቱ ደቂቅን ታሪክ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ‹‹አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል›› ቢላት ፍርሃቱ ሊለቃት ባለመቻሉ፣ ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ጸለየ፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ! የወይኑን ፍሬ ስትሻ ግንዱን ታጠፋለህን? እንደዚህስ ሁሉ እኔን አድነህ እናቴን ታጠፋታለህን?›› ብሎ በጸለየጊዜ መንፈስ ቅዱስ አደረባትና መንግሥተ ሰማያትን በዓይነ ሥጋ እንድታይ አደረጋት፡፡ ከዚህ በኋላ ፍርሃቱ ለቀቃትና ‹‹ልጄ ሆይ! ከዛሬ ጀምሮ መምህሬ፣ አባቴ፣ መካሪዬ እልሃለሁ እንጂ ልጄ አልልህም›› ብላ በጭካኔ ከልጅዋ ጋር ወደ ፈላው የብረት ጋን ገባችበት፡፡ በዚህ ጊዜ ሕፃኑ ቂርቆስ አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል ያለውን ቃል ለመፈጻም እግዚአብሔር አምላክ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው፡፡ መልአኩም በትእምርተ መስቀል እሳቱን ቢባርከው እንደ በረዶ ቀዝቅዞላቸዋል፡፡ በመልካቸውም እንደ ፀሐይ አበራ፡፡ ከእግር ጥፍራቸው እስከ ራስ ጠሩራቸው አንድም ሳይጎዳቸው በደህና ወጡ፡፡ በመጨረሻም ሕፃኑ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ እንዲህ አለ፡፡ ይህን ያህል ገድል ተጋድዬ ምን ዋጋ ትሰጠኛለህ ቢለው፣ ጌታ በልብህ ያለውን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው፡፡ ዳግመኛም ሥጋህ በምድር ላይ እንዳይፈርስ እንዳይበሰብስ በኤልያስ ሠረገላ ላይ አኖርሃለሁ አለው፡፡ ስለሆነም በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያናችን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለእናታችን ለቅድስት ኢየሉጣ እና ለሕፃኑ ለቅዱስ ቂርቆስ ያደረገውን ይህን ታላቅ ተአምር ድንቅ ሥራ በማሰብ ከዋዜማው ጀምራ እግዚአብሔርን ስታመሰግን ትውላለች ታድራለች፡፡ የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል በረከት ተራዳኢነት ከሁላችን ጋር ይኑር አሜን፡፡
1 366
12
​​ሐምሌ 19 ቅዱስ ገብርኤል እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!! በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በዓል ነው፡፡ ይህ ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ቅዱስ ቂርቆስን ከሞት አደጋ እንደታደገበት የሚታሰብበት ዕለት ነው። የሐምሌ 19 ስንክሳርና የሐምሌ ወር ድርሳነ ገብርኤል እንዲህ ተርከውታል፡፡ በዘመነ ሰማእታት ከሐድያን ነገሥታትና መኳንንት በክርስቲያኖች ላይ መከራ አጽንተውባቸው ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ብዙዎች ሰማእትነትን ሲቀበሉ የተቀሩት አገር ጥለው ተሰደዱ። እየሉጣም የሦስት ዓመት ህፃን የነበረውን ቅዱስ ቂርቆስን ይዛ ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኮንን አገኘችው ሰዎችም ነገር አሰሩባት ወደእርሱ አስቀረባት እና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኮንን ሆይ ዕድሜው ሦስት አመት የሆነው ህፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እሱን ጠይቅ አለችው፡፡ ህፃኑም ወዳለበት ጭፍራውን ልኮ ወደእርሱ አስመጣው ህፃኑም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ህፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው፡፡ ህፃኑም መልሶ አዎ ለኔ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ሐዘንና ለቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው፡፡ መጻሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏል እና አለው፡፡ እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስካስደነገጣቸው ድረስ ንጉሱን መኳንንቱንና ጣኦታቱን ረገማቸው፡፡ከብርታቱም የተነሳ አደነቁ፡፡ መኮንኑም በአፈረ ጊዜ በያይነቱ በሆነ ስቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ስቃይን አሰቃየው እናቱንም ከእርሱ ጋር አሰቃያት፡፡ እግዚአብሔርም ያለ ምንም ጉዳት ያነሳቸው ነበር፡፡ ብዙዎች አህዛብም ይኸንን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማእትነት አረፉ፡፡ የሰማእትነትንም አክሊል ተቀበሉ፡፡ በህፃኑም ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት፡፡ ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው፡፡ መስፍኑም በውስጡ ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ የዶሮ ማር፣ እርሳስ፣ ብረት፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል ጨምራችሁ ታላቅ የብረት ጋን አንጡልኝ ብሎ ጭፍሮቹን አዘዛቸው፡፡ ጭፍሮቹም እንዳዘዛቸው ካአደረጉ በኋላ ያዘዝከንን ሁሉ ፈጽመን እሳቱ ነዶ ፈልቷል፡፡ ድምፁ እንደነጐድጓድ ይጮኸል ወላፈኑም እንደጸሐይ ነጸብራቅ በሩቁ ይጋረፋል፡፡ የፍላቱም ኃይል በ14 ክንድ ያኽል ከፍታ ወደ ላይ ይዘላል፡፡ እንግዲህ በውስጡ የሚጣሉትን እዘዝ አሉት በዚህ ጊዜ ህፃን ቂርቆስና እናቱ እየሉጣ በክርስቶስ ስም ስለሚያምኑ አስረዋቸው ነበርና ከፍላቱ ሊጨምሯቸው ከእስር ቤት አወጧቸው፡፡ በዚያም ፍላቱ ወደላይ በሚዘል ብረት ጋን ውስጥ ለመጨመር ሲወስዷቸው የነዚህን ቅዱሳን አሟሟት ያዩ ዘንድ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲሰበሰቡ አዘዛቸው፡፡ በዚህን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ የፍላቱን ጩኸት በሰማችና ባየች ጊዜ ተሸበረች፡፡ ተዘጋጅቶላት ከነበረው ክብር ልታፈገፍግ ሞከረች፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ግን እናት ሆይ ከዚህ የብረት ጋን ግርማ የተነሳ አትፍሪ ድንጋጼም አይደርብሽ አናንያንና አዛርያን ሚሳኤልንም እግዚአብሔር ከእቶነ እሳት እንዳወጣቸው ሁሉ እኛንም ከዚህ ከብረት ጋን ሊያወጣን ችሎታ ያለው መሆኑን አትጠራጠሪ፡፡ እናት ሆ ከዚህ ከሚያልፈው ዓለም ጭንቅና መከራ ለመዳን ስትይ በማያልፈው ዘላለማዊ እሳት ለመቀጣት ትመርጫለሽን ይኽስ አይሆንም ይቅርብሽ፡፡ በአሁኑ ጊዜ እግዚአብሔር በመካከላችን አለና ይረዳናል፡፡ እናት ሆይ ሶስናን ከእደ ረበናት /መምህራነ አይሁድ/ ዳንኤልን ከአፈ አናብስት ያዳነ እርሱ እኛንም ከጋን ፍላት ያወጣናል፡፡ ይልቁንም እግዚአብሔር በዚህ የብረት ጋን ውስጥ ግዳጃችንን ልንፈጽም ፈቅዶ ከሆነ ኢዮብ ንብረቱንና ገንዘቡን ልጆቹንና ሚስቱን በመጨረሻም የተፈጥሮ አካሉን ባሳጣው ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ እግዚአብሐር ሰጠ እግዚአብሔር ነሳ እግዚአብሔርም እንደወደደ አደረገ ከማለት በስተቀር ምንም የተናገረው ነገር እንደሌለ ሁሉ እኛም የሱን ዓላማ በመከተል ይኽንን መከራ ልንታገስ ይገባናል፡፡ ነገር ግን እናቱ በዚህ ምክር ልትጽናና ባለመቻሏ ቅዱስ ቂርቆስ ዐይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ አቤቱ አምላክ ሆይ ይችን ባሪያህን ከርስትህ የምትለያት ከሆነ ከባለሟልነትህ መጽሐፍ ፋቀኝ፤ አቤቱ አዝመራውን አቃጥለ ፍሬውን ልትባርክ ትወዳለህን ይኽን እንዳታደር ግን ቸርነትህ ትከለክልኸለች አቤቱ እንጨቱን ቆርጣችሁ አንድዱት ቅጠሉን ግን ጠብቁት ብለኽ ልታዝ መለኮታዊ ባሕሪህ አይደለም፡፡ ነገር ግን እንጨቱንም ቅጠሉንም በአንድ ጠብቁት ብለኽ ታዝዛለኽ እንጂ፡፡ እንግዲህ በዚህ ምክንያት ይኽንን ያየ ሁሉ ማዳን የሚችል አምላክ ቢኖራቸውስ ኖሮ ከእሳት ባልሸሹም ነበር ብሎ አይጠራጠር፡፡ አቤቱ ዲያብሎስም ከባለስልጣኑ ይልቅ እኔ በረታሁ ቅዱሳኖቹንም ድል ነሳኋቸው ብሎ እንዳይመካ ከመንጋውም አንድ በግ ቀማው በማለት እንዳይደነፋ ለእናቴ ጽኑ የሆነ ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ስጣት ብሎ በጸለየ ጊዜ ዲያብሎስ ከእየሉጣ አጠገብ ብን ብሎ ጠፋ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ በሰማያዊ መንግሥት አባት የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታኽ ኃይልን ሰጥቶኛልና የሚጠብቀንን ገድላችንን ፈጽመን ድል እናድርግ እነሆ በብረት ጋን ውስጥ የሚነደውን እሳት በማይበት ጊዜ በለምለም /በምንጭ/ ላይ እንደሚወርድ ጠል ሆኖ አይቸዋለሁና አለችው፡፡
1 007
13
✞ ገብርኤል ስሙ ✞ ገብርኤል ስሙ ዘአምኃ ለማርያም ዘበትርጓሜሁ አምላክ ውእቱ(፪×) ይበል ይበል አቅዲሙ ዜነዋ ለደብረ ልዑል ኢየሩሳሌም አምኃሁ ለዘይመጽዕ ዓቢይ ኖላዊ ኖላዊ(፪×) ይበል ይበል የፈላው ጋኑን--ገብርኤል ስሙ አቀዝቅዞት----ገብርኤል ስሙ ቂርቆስንና----ገብርኤል ስሙ እናቱን አዳነ---ገብርኤል ስሙ ዘአምኃ ለማርያም ዘበትርጓሜሁ አምላክ ውእቱ ይበል ይበል ሠለስቱን ሕፃናት--ገብርኤል ስሙ ያዳናቸው እርሱ---ገብርኤል ስሙ እኛንም ያድነን----ገብርኤል ስሙ ከሚነደው እሳት---ገብርኤል ስሙ ዘአምኃ ለማርያም ዘበትርጓሜሁ አምላክ ውእቱ ይበል ይበል መልአከ ራማ-----ገብርኤል ስሙ እኛን ይወደናል----ገብርኤል ስሙ ሃያሉ አባት--------ገብርኤል ስሙ ሊቀ መልአኩ------ገብርኤል ስሙ ዘአምኃ ለማርያም ዘበትርጓሜሁ አምላክ ውእቱ ይበል ይበል 👉ዘማሪት ቤርሲ ሰላም #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ
1 121
14
✞ ለገብርኤል የነገርኩት ✞ በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ለገብርኤል የነገርኩት ያስጨነቀኝ ታላቅ ድንጋይ ተንከባሎ በዓይኔ አየሁት ከአይን ጥቅሻ ቀድመህ ፈጥነህ ትደርሳለህ በምልጃህ ፀሎትህ ከእኔ ጋር አለህ ገብርኤል ገብርኤል ገብርኤል የምለው እጄን ስዘረጋ ብዙ ሰጥተኸኝ ነው        /አዝ = = = = = የደስታን ዜና ይዘዋል እጆችህ የአምላክ ውዳሴ ተሞልቷል ከንፈርህ ችግሬን አትሻም አትፈቅድም ጥፋቴን እንዳይሰናከል አቁመሀል እግሬን        /አዝ = = = = = በእሳቱ መሀል ምስጋና አስተምረኝ በእቶንም መካከል ውዳሴን አሳየኝ እንዳላጉረመርም በሆነው በአልሆነው ገብርኤል አሳየኝ አመስግኜ እንዳልፈው        /አዝ = = = = = ሲራቅና ሚሳቅ አብድናጎን ሆነው በሚነደው እሳት ከእቶን ተጥለው ገብርኤል ደረሰ ሊነግራቸው ዜና ችግር እንደሚርቅ በብዙ ምስጋና 👉 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ እና ዘማሪት መቅደስ ማርዬ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ
1 101
15
ሰኔ ፴ /30/ አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሠላሳ በዚች ዕለት ነቢይ ሰማዕትና ሐዋርያ የሆነ መጥምቁ ዮሐንስ ተወለደ። ይህም በእናቱ ማኅፀን ውስጥ ሳለ ለእግዚአብሔር ልጅ የሰገደው ነው። ይህም በመድኅን ክርስቶስ ራስ ላይ እጁን ጭኖ በውኃ ያጠምቀው ዘንድ የተገባው ነው። በቅዱስ ወንጌል እንደ ተነገረ ወንድ ልጅን ትወልድ ዘንድ የኤልሳቤጥ የፅንሷ ወራት በተፈጸመ ጊዜ ወንድ ልጅን ወለደች። ዘመዶቿና ጐረቤቶቿ እግዚአብሔር ቸርነቱን እንዳበዛላት በሰሙ ጊዜ ስለርስዋ ደስ አላቸው። በስምንተኛውም ቀን ሊገዝሩት መጡ በአባቱ ስም ዘካርያስ ብለው ጠሩት። እናቱ ግን አይሆንም ዮሐንስ ይባል አለች። ከዘመዶችሽ ስሙ እንዲህ የሚባል የለም አሏት ። አባቱንም ጠቅሰው ማን ሊባል ትወዳለህ አሉት። እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ ዮሐንስ ይባል ብሎ ጻፈ ። ሁሉም አደነቁ። ያን ጊዜም አንደበቱ ከድዳነት ተፈትቶለት ተናገረ እግዚአብሔርንም ፈጽሞ አመሰገነው። ስለ ልጁና ስለ መድኃኒታችን መምጣት ልጁ ዮሐንስም የልዑል ነቢይ እንደሚባልና በእግዚአብሔርም ፊት እንደሚሔድ ትንቢት ተናገረ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑርለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
1 141
16
ዝግጅት አለዎት? ጭንቀቱን ለእኛ ይተውት! "ቤተ ብርሃን ዲኮር" አዲስ ስራ፣ አዲስ ውበት! ከቀላል የቤት ውስጥ ዝግጅት.. እስከ ታላላቅ መድረኮች፣ ቦታዎን በብርሃን እና በውበት ለመሙላት ተዘጋጅተና
ዝግጅት አለዎት? ጭንቀቱን ለእኛ ይተውት! "ቤተ ብርሃን ዲኮር" አዲስ ስራ፣ አዲስ ውበት! ከቀላል የቤት ውስጥ ዝግጅት.. እስከ ታላላቅ መድረኮች፣ ቦታዎን በብርሃን እና በውበት ለመሙላት ተዘጋጅተናል። እይታን የሚቀይር... ጥራቱ የማይነካካ፣ ቤተ ብርሃን ከመጣ... የውበት ጥማትዎ ይረካ! አሁኑኑ ይደውሉልን፣ ዝግጅትዎን በብርሃን እንሙላው!
1 033
17
✞ የልቤ ዜማ ✞ የልቤ ዜማ ነሽና ሰላም ነው ያንቺ ምስጋና ሞገሴ ነው ስምሽ ለኔ ስላለሽ ማርያም ከጎኔ በመገፍት ብኖር እምነቴን አፀናለሁ በጣቶችሽ  ተይዤ አዲሱ ቀን አያለሁ❨፪×❩ ስማፀን ደጅሽ መጥቼ ተመለሰኩ ተረጋግቼ እንደምን አንቺን እረሳለሁ በምልጃሽ ተፈውሻለሁ        /አዝ = = = = = የጠላቶቼን አራስ የሚቀጠቅጠው የአብራክሽን ፍሬ ተስፍዬን አበራው❨፪×❩ የድኅነት ምክንያት አርጎሻል ለአዳም ዘር ትምክህት ሆነሻል የልቤ ብርሃን ፋና አዛኝት ባንቺ ልፅናና          /አዝ = = = = = የአፌን እንጉርጉሮ ምስጋናዬ ወርሶታል እግሬ ከእረግረግ ወጥቶ በሰገነት ተተክሏል ❨፪×❩ ሐዘኔን የምሻገረው ስምሽን እየጠራሁ ነው አገኘው ደስታ ሰላም ጠርቼ ብዬ ማርያም  👉ዘማሪ ዲያቆን እንዳለ ደረጀ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ
1 356
18
✞ ትምክህተ ዘመድነ ✞ ትምክተ ዘመድነ❨፪×❩ ማርያም ዕምነ ማርያም ትምክህተ ዘመድነ የድነታችን አርማ የነፃነታችን የህይወት መሰረት ነሽ ድንግል እናታችን አንቺን ለኛ ዘርን ባያስቀር እንደጥንቱ እንደ ሰዶም ምድር ሁላችን በጠፋን ነበር        /አዝ = = = = = የአብርሀም ድንኮን ነሽ አምላክ ያደረብሽ የጌድዮንም ፀምር ለይቶ ያከበረሽ የኛ ቤዛ በጉ የተያዘብሽ የዋህ ርግብ  ከ አበውስር የተገኘሽ እፀሳቤቅ የህይወት ሀረገ ነሽ        /አዝ = = = = = አምላክ ከሰማይ ሆኖ ይችን አለም ሲቃኝ ንፅህይት ቅድስት ሁነሽ ማርያም አንቺን ቢያገኝ ትህትናሽን ሂወትሽንም ወዶ ቃል ሰው ሆነ ከሰማያት ወርዶ አከበረሽ በፋፁም ተዋህዶ        /አዝ = = = = = የመዳናችን ምክንያት የሰው ልጆች ሰላም ከሀጢያት ከመርገም የዳነብሽ አለም አምስት ሺ አምስት መቶ ዘመን በሲኦል ውስጥ ተግዘን የኖርን ድንግል ባንቺ ነፃነት አገኘን #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ
946
19
✞ እመቤቴ የአምላክ እናት ✞ እመቤቴ የአምላክ እናት ላመስግንሽ ቀን ከሌሊት ለልጅሽም ክብር ውዳሴ ታቀርባለች ዘወትር ነፍሴ❨፪×❩ ልቤ ተነሳሳ ተቀኘ ለክብርሽ በፍጹም ትህትና ሊያመሰግንሽ ጽዮን መጠጊያ ነሽ የአብርሃም ድንኳን የታጠረች ተክል እመ ብርሃን        /አዝ = = = = = የለመለመች መስክ አምላክ የመረጣት የጽላቱ ኪዳን  ታቦቱ ድንግል ናት የሰማይ የምድር ንግሥት ናትና ክብር ይገባታል ዘወትር ጠዋት ማታ        /አዝ = = = = = አደራሽን ማርያም የሁሉ እናት በምልጃሽ አስቢኝ ኋላ ስራቆት ያንን የእሳት ባሕር አሻግርኝ ድንግል ሆይ እንዳልወድቅ እንዳልሞት ከቶ እንዳላይ ስቃይ 👉ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።   ╔✞═════●◉❖◉●════✞╗        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖ ❖ @enamsgn @enamsgn ❖        ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ╚✞═════●◉❖◉●════​✞╝ ✍ ወድሰኒ
835
20
​​​​ሰኔ 12 #የቅዱስ_ሚካኤል ዓመታዊ በዓል! እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለእናታችን ቅድስት አፎሚያ አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ። ሰኔ 12 ቅዱስ ሚካኤል እናታችን ቅድስት አፎሚያን ከጠላት ዲያብሎስ እጅ ያዳነበት ፣ እናታችን ቅድስት አፎሚያ እረፍቷ ነው ።እግዚአብሔር ከቅዱሱ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ፣ ከእናታችን ቅድስት አፎሚያ በረከት ተካፋይ ያድርገን ። 👉 በወርኃ ሠኔ መታሰቢያ ከሚደረግላቸው ቅዱሳን መካከል እግዚአብሔርን የሚፈራ የአስተራኒቆስ ሚስት የሆነች የቅድስት አፎምያን ታሪክ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡ ቅድስት አፎምያ በትዳር በነበረችባቸው ዘመናት እግዚአብሔርን ከሚወድ ባለቤቷ ጋር እግዚአብሔርን ስታገለግለው የኖረች ሴት ነበረች፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ እንደነበር ታሪካቸው ይነግረናል፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጉል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡ ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፡፡ የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ ባያት ጊዜ ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ፣ ሌላ ባል አግብታ፣ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡ ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ፤ እነሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ፤ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡ በሠኔ ፲፪ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ሞከረ፡፡ ሰይጣን አስቀድሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንቶስ መጻሕፍትን እየጠቀሰ እንደተፈታተነው ሁሉ ቅድስት አፎምያንም ለማሳመንም አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዳዊትን የመሳሰሉ ደጋግ አባቶችን ታሪክ እየጠቀሰ ወደ ትዳር እንድትገባ ደጋግሞ ወተወታት፡፡ ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና “የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?” በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡ ለጊዜው “በኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም” ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ፡፡ ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን “ድረስልኝ” እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሠኔ ፲፪ ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡ ይህች የታመነች ቅድስት አፎምያ በሰላም እስክታርፍ ጊዜ ድረስ የተጓዘችበትን መንፈሳዊ ጎዳና አስተውለን ይሆን? አስቀድማ ከባሏ ጋር አንድ ሆና በታማኝነት ፈጣሪዋን አገለገለችው፡፡ በኋላም የባሏን ኑዛዜ አክብራ ምንም እንኳን ኃጢአት ባይሆንባትም በሁለተኛ ትዳር ራስዋን ማጠላለፍ አልፈለገችም፡፡ በጎ ሥራ አብልጣ በመሥራት እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ተፋጠነች እንጂ፡፡ ሰይጣን ልጅ አለመውለዷን ተጠቅሞ ያቀረበላትን የጋብቻ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ “መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ መናፍስት ከእግዚአብሔር እንደሆኑ መርምሩ” ተብሎ በቅዱሳት መጻሕፍት የታዘዘውን መመሪያ ተጠቅማ ሰይጣንን በተወክሎ እግዚአብሔር ተቃውማ አሸነፈችው፡፡ የቅዱስ ሚካኤልን ርዳታ ያገኘችውና በሰላም ዐርፋ ወዳገለገለችው እግዚአብሔር በክብር የሔደችው በጽናት ተጋድላ ነው፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በጸሎቷ ይማረን፤ የቅዱስ ሚካኤል የረድኤቱ ኃይል ሁላችንንም ይጠብቀን፣ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
1 117