ABRET PRO
Open in Telegram
የአብሬት እንዲሁም የቃዲሪይ ሲልሲላ መንዙማዎችን ፣ ከአካቢሮች የሰማናቸውን ቀሰሶች ፣ እንዲሁም ከመሻኢኾቻችን ኪታቦች አንዳንድ ጠቃሚ ነገሮችን የምንማማርበት አጠቃላይ የሀድራ ስራዎችን የምንዘክርበት ቻናል ነው @Abretpro
Show more4 604
Subscribers
No data24 hours
+27 days
+8730 days
Posts Archive
4 606
የጉራጌ ማህበረሰብ በስፋት ይከተለው የነበራው ዋቅ እንዲሁም ቦዠ የሚባለው ባእድ እምነት ምን ያህል ጥልቅ እና ከማህበረሰቡ ጋር የተሳሰረ እንደነበር ብዙዎቻችን ላንገነዘበው እንችል ይሆናል:: ይህ ጭለማ በሸኾቹ ጥረት እጅግ ከፍተኛ በሆነ ጁህድ ተገርስሶ ነው በኑረል ኢማን የበራው::
ሠይድ ኢብራሂም የመጀመሪያው አብሬት ሸይኽ(ሠይድ ባኡ ሳኒ(ቀ.ሢ) አባት ከዚህ ባእድ አምልኮ መሪዎች ቤት ወጥተው ፣ ስርአቱን አዛብተው ፣ እጅግ ጉሩም በሆነ መልኩ በልጅነት እስልምናን ተቀብለው ፣ ጉራጌ ላይ የኢማን ችቦ ለኮሱ::
ይህን ግሩም ታሪክ fuad ዘርዘር አድርጎ በጥሩ ሁኔታ አቀናጅቶታል ተጋበዙልን
https://youtu.be/pY2SrWRRFL8?si=IAFDQX7PzkuGLgVc
4 606
💚🔥 zahid
ማማሪያዬ ነቢ | አብዱሰላም አበራ| እንዴት ነሁ | አዲስ ነሺዳ
https://youtu.be/kGnOQcQgkWI?si=4ubrKNvlqBMVN8nC
4 606
ኸሚስ💚🔥
ሠላም ዐለይኩም ያኑሩ ያጣሀ በድረል ሙኒሩ
ሶላቱላሂ ዐለይከ ማ ሐነ ሩሑ የዝኩሩ
سلامْ عَلَيْكُمْ يَا نُورُ يَا طَهَ الْبَدْرُ الْمُنِيرُ
صلاةُ اللهِ عَلَيْكَ مَا حَنَّ الرُّوحُ يَذْكُرُ
የአብሬትዩ ሳኒ ሠይዲ አባ ራሙዝ(ቀ.ሢ) የመውሊድ መድህ በሸይኽ ኤሊያስ እና ሸይኽ ኸይሬ እስከነ ፅሁፉ
https://youtu.be/nqHWxhbBEHo?si=rxlzhWwEAJUFo787
4 606
በልጅነቴ ነው በካሴት የተቀዳውን የአብሬትዩ ሳኒ ወአዝ አባቴ ከሆነ ቦታ አግኝተው በክብር ይዘዉት መጡ... ወቅቱ ባእደል መግሪብ ነው:: ፀጥ ረጭ ብለን ሁላችንም ተሰባስበንና ቴፑን ከበን በተዋዱእ በጥሞና የአባባን ድምፅና ወአዙን የሚያስተጋባውን ሰው አደመጥን:: የአነጋገር ዘይቤያቸው እጅግ ልዩ ነው:: ጉራጊኛ ቋንቋ በሳቸው አንደበት ሲሰማ ውበቱ ለጉድ ነው:: የዛን ቀን የሰማሁት ወአዝ ጥፍጥናው አሁን ድረስ ውስጤ አለ:: ለህይወቴ ሙሉ ቀለብ ሆኖኛል:: የዛን ቀን ከሰማሁትና ህይወቴን ያሰመረልኝ ወአዝ
በጉራጊኛ + በአማርኛ እንካቹ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬👇
የኒዕማ ጉነረታ ኢማኑ ኢስላሙ... በሃንቄ የኸረ በኸረ አፊያው:: ዄተኽኖ ያነን ሰብ አነሴም ይብሬ ሀቅ ኤትገቧን:: አላህ ባበ ቃር ቲትብቋቄ ግዝየ ወሄ ቃሩ:: ያበ ሁታ ይጣኒሸ ቲቡሪ ወሄ ቃሩ:: ባነከዊ ሁታ ሰብር አንብኸሮቱ... ነከዊምታ ቦረ ኹታ ሰብር አንብኸሮቱ... ይጣኒሸ በሮቱ :: ይጣኒሸ የባር ሰብ ይወጣረ:: ይጣኒሸ የባረ ሰብ ቀልብመታ ያᎈ ጅስማመታ ያᎈ:: ይጣኒሸ ያንባረ ሰብ ፎያት ኤረኽብ ቀልብመታ ጅስማመታ ፎያት ኤረኽብ::
━━━━━━⊱⊰━━━━━━አማሪኛ👇
የኒዕማ(ስጦታ) ራሱ(ቁንጮው) ኢማን ነው... እስልምና ነው:: ከዛ ቀጥሎ እንደሆነ አፊያ ነው:: ሁለቱ ያለው ሰው አንሶኛል ለማለት ሀቅ አይገባውም:: አላህ በሰጠ ነገር ሲብቃቁ ጥሩ ነው:: የሰጠው ነገር ይበቃኛል ሲባል ጥሩ ነው:: ባልተገኘው ነገር ሰብር አለማጣት ነው:: ተገኝቶ በታጣው(በሄደው) ሰብር አለማጣት ነው:: ይበቃኛል ማለት ነው:: ይበቃኛል ያለ ሰው ይበቃዋል:: ይበቃኛል ያለ ሰው ቀልቡም ያርፋል... ሰውነቱም ያርፋል:: ይበቃኛል ያላለ ሰው እረፍት አያገኝም:: ቀልቡም ጀሰዱም እረፍት አያገኝም::
4 606
ጉድ! ብሎ ዝም ነው የሙሐመድﷺ ነገር:: ክቡር የሆኑት አንቢያኦች ሁሉም በነብያችንﷺ የኑር ጠብታ ተኸለቁ::
وَجَمِيعُهُمْ خُلِقُوا مِنْ قَطَرَاتِ نُورِهِ
وَالأنْبِيَاءُ الْكُرَمَا وَعِنْدَ الْكُلِّ يُشْكَرُ
4 606
ኸሚስ💚🔥
☆☆ ☆ ☆☆
ሶላ ዐለይከ ነብዩ ያሢራጅ ያሙኒሩ
ወሠለመከ ኢላሁ ያሐቢቡ ያበሺሩ
የአብሬትዩ ሳኒ ሠይዲ አባ ራሙዝ(ق) የመውሊድ መድሕ
በሸይኽ ኤሊያስ እና ሸይኽ ኸይሬ እስከነ ፅሁፉ
صَلَّى عَلَيْكَ نَبِيُّ يَا سِرَاجُ يَا مُنِيرُ
وَسَلَّمَكَ الإلَهُ يَا حَبِيْبُ يَا بَشِيْرُ
https://youtu.be/tQWyVfRMC1Q?si=8hbfu_ku1FKZpi90
4 606
ከመቶ አመታት በፊት ኢብን ስዑዲ በመባል የሚታወቀው ንጉስ አብዱልአዚዝ ሒጃዝን በጦ$ርነት አሸንፎ ከተቆጣጠረ በሁሗላ ሒጃዝ ላይ ብዙ የቀ$ብር ቁባዎችን እንዳፈረሱ ፣ ብዙ የተሰዉፍ ኪታቦችን እንዳ$ቃጠሉ ፣ ብዙ አህለ በይቶችን እንደገ#ደሉና የተቀሩት አህለ በይቶች በብዛት ወደ የመን ሸሽተው እንደተሰደዱ አንድ እጅግ የማከብራችው የጥልቅ ዒልም ባልተቤት የሆኑ አጎቴ ሐፊዘሁላህ ሲያወሩ ሰምቼ ነበር::
የየመኖች የመውሊድ አከባበርና ጥልቅ የነቢዩﷺ ሙሓባ ሲታይ እውነት አህለ በይቶች በብዛት የመን ውስጥ መኖራቸውን መረዳት ይቻላል::
4 606
+9
👆 የነብያችንንﷺ መውሊድ አታክብሩ አይበቃም የሚሉ ሰዎች ከመጡ ወዲህ ሙሒቡ ካልበቃማ እንጨምራለን ያለ ይመስላል:: የመውሊድ አከባበር ድምቀት በመላው አለም እጅግ እየተባባሰ እየደመቀ ነው የመጣው:: አልሐምዱሊላህ
በአለማችን የተለያዩ ክፍሎች በጥቂቱ የመውሊድ አከባበር በምስል ይህን ህመስል ነበር
4 606
አንገታችንን ቀና አድርገውልናል:: የእስልምናን ውበት ሰው የመሆንን ትርጉም ለሁሉም አጉልተው አሳይተዋል:: የሙፍቲ ትውልድ በመሆናችን አልሐምዱሊላህ ኩራት ይሰማናል:: ዒዱም መውሊዱም በመጣ ቁጥር ሁሌም ልናስባቸው ግድ ይለናል::
4 606
በዛሬው እለት ማክሰኞ ረቢዕ 12 1448 ዓመተ ሒጅራ የነብዩﷺ መውሊድ በታላቁ አንዋር መስጂድ በተከበረበት መድረክ
አብሬትዩ ሳሊስ መውላና ሠይድ ሸይኽ ሚቅባሰል ኑር(ق) ሸይኽ ሠይድ ሙሐመድ ቡደላ(ق)
ሼይኽ ሙሀመድ ሁሴን (ኮንቦልቻ)
ዑስታዝ ፈድሉዲን ሀሰን(ዑስታዝ ፈድሉ)
የመንዙማ ዘርፉን በማሳደጋቸው፣ በዘርፉ አያሌ ድርሳናትን በመሰነዳቸው እና በርካታ ተተኪ ትውልድ በማነፃቸው የመጀመሪያዎቹ ሦስት ተሸላሚ ተደርገው ተመርጠዋል።
ፀሀፊ ኸድር ታጁ በሰራው በርካታ የታሪክ ድርሳናት የአዋርዱ ተሸላሚ ሆኖ ተመርጧል::
4 606
ረቢዐል አወል 12ኛው ለይል ከአስር ሰአት በሁዋላ ፈጅር መቃረቢያው ላይ ትልቁ ሰውﷺ ተወለዱ።
እንኳን ለነብዩ ﷺ መውሊድ አደረሳችሁ::
💚🎉
4 606
🌟 አልሀምዱሊላህ! ፍትህ አሸነፈች - የዘንድሮው መውሊድ በወሊሶ የአብሬት ኑር መስጂድ - በደማቅ ሁኔታ ይከበራል! 🌟
===== ⨳ ===== ⨳ ===== ⨳ =====
ትናንትና እና ዛሬ በተደረገዉ ተከታታይ፣ ሰላማዊ እና ህጋዊ ጥያቄ መሰረት፤ በወሊሶ አብሬት ኑር መስጂድ የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መውሊድ በነፃነት እንዲከበር በይፋ ተፈቅዷል!
በዚህም መሰረት የመውሊዱ ፕሮግራም ከዛሬ ማታ ጀምሮ የሚጀመር ሲሆን፣ ዋናው እና ታላቁ የመውሊድ በዓል ነገ ረቢዕ አል-አወል 12፣ 1448 ዓ.ሂ ሙሉ ቀን በታላቅ ድምቀት በአብሬት ኑር መስጂድ ይከበራል!
ይህ የፍትህ ድምፅ ሰምሮ የደስታው ተካፋይ እንድንሆን ላደረጉ አካላት በሙሉ ታላቅ ምስጋና ማቅረብ እንወዳለን፦
1:- ለፍትህ ዘብ ለቆሙ የመንግስት አካላት፡ ሀላፊነታቸውን በአግባቡ በመወጣት፣ ከፍትህ ጎን በመቆም ለማህበረሰቡ ድምፅ ለሆኑት ለወሊሶ ብልፅግና ፅ/ቤት ምክትል ሀላፊ ለጁዋሪያ አህመዲን (Juwariya Ahmedin) እንዲሁም ለወሊሶ ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ ለኢፋ አንጋሳ (Ifa Angasa) ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
2:- ለሰላማዊ ታጋዮች፡ በርቀትም ሆነ በአካል በመገኘት፣ ህገ-መንግስታዊ መብታችሁን ለማስከበር ከሚመለከተው አካል ጋር ሰላማዊ እና ስልጡን በሆነ መንገድ ጥያቄያችሁን ላቀረባችሁ አካላት ሁሉ ክብር ይገባችኋል።
3: ለነባሩ የመስጂድ ኮሚቴ፡ መስጂዱ ከእጃችሁ ከመነጠቁ በፊት፣ በመስራቹ በአብሬት ሸህ ብሂል እና እሴት መሰረት መስጂዱን እያሰራችሁ በሰላምና በፍትህ ስታስተዳድሩ ለነበራችሁት ነባር ኮሚቴዎች አላህ ምንዳችሁን ይክፈላችሁ። ከአላህ ጋር ፍትሀቹ ሙሉ ይሆናል።
4:- ለማህበራዊ ሚዲያ ቤተሰቦች፡ የጉዳዩን አሳሳቢነት እና ኢ-ፍትሀዊነት በመገንዘብ፣ ትናንት የደረሰብንን በደል ሼር በማድረግ፣ በየደረጃው የሚገኘው የሚመለከተው የመንግስት አካል ጉዳዩን እንዲያውቀው ድምፅ ለሆናችሁን ሁሉ ታላቅ ምስጋና እናቀርባለን።
የእውነተኛ ሙሂብነት መለኪያው ይሄው ነው! የአባባ እውነተኛ ተወላጅም ሆነ ወዳጅ፤ በገዛ መስጂዳቸው ከተርቲባት እስከ መውሊድ የሳቸዉ መንገድ እንዳይሰፍን ተከለከለ ፣ ህገመንግስታዊ የሙሪዶቻቸዉ መብት ተነጠቀ፣ ሲባል ቆሞ የሚያይ በፍፁም ሊሆን አይችልም። ቢያንስ አስቀድሞ በሚችለው አቅም ሙከራ ያደርጋል፣ አብሮ ይገፋል፣ ሰላማዊ በሆነ መልኩ ፍትህን ይሻል፣ ሁሌም ከሚበደሉት ጎን ይቆማል እንጂ!
እንኳን ደስ አለን! ኑ! የነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) መውሊድ በደስታ፣ በሰላምና በፍቅር እናክብር!
4 606
+3
መውሊደ ነቢይﷺ በአብሬቱ ኑር በሠይዲ(ق) ቤት በቀኑ ድምቅ ብሎ ይከበራል:: በሸኾች መድሕ ነቢይንﷺ ለጉድ እንመድሀለን ፣ በነቢይﷺ ዊላዳ እንደሳለን ፣ ለነቢይﷺ እናሽቃለን ፣ በሙሓባ እንወዘወዛለን:: የነቢ ወዳጆች በሙሉ አርሒቡ የተንቢ በሩ ክፍት ነው::
4 606
ከፍጥረት ሁሉ የላቁት ነብያችንﷺ በመወለዳቸው በይቱላህ በደስታ ዘለለ (ደነሰ) ፣ መዋቅሩም ተወዛወዘ::
رَقَصَتْ بَيْتُ اللهِ وَمالَ بِنَاؤُها
فَرَحًا بِمَوْلِدِ أجلِّ الْبَريَّةِ
4 606
የገዛ ቤታችን ባይተዋር ሲያደርገን፡ በወሊሶ አብሬት ኑር መስጂድ የተፈፀመው የረቢዕ ዙልም!
===== ⨳ ===== ⨳ ===== ⨳ =====
"እንግዳ ተጠጋ ቢሉት፣ የቤቱን እቃ የት ላውጣው አለ" ይባላል በእኛ ሀገር። ልክ እስራኤላውያን የፍልስጤምን መሬት ተቆጣጥረው፣ ትክክለኛ ባለቤቶቹን በገዛ ቀያቸው ላይ በነፃነት መኖር እንደከለከሉና እንደሚያፈናቅሉት ሁሉ፤ ዛሬ በወሊሶ ከተማም ይህንኑ አስገራሚና አሳዛኝ ታሪክ የሚያስታውስ ግፍ በሙሒቦች ላይ እየተፈፀመ ይገኛል። የአብሬት ሸይህ ሰይድ አበልራሙዝ ከኪሳቸው ገንዘብ አውጥተው በገዙት መሬት ላይ፣ ሙሪዶቻቸው ጊዜ፣ ጉልበትና ገንዘባቸውን አፍስሰው ያነፁትና አሳምረው የገነቡት "የአብሬት ሸህ ኑር መስጂድ" ዛሬ ለትክክለኛ ባለቤቶቹ ባዕድ ሆኗል።
የመፈናቀሉ ጅማሮ...
መጀመሪያ ነገሩ የተጀመረው "የኮሚቴ እና የተርቲብ ለውጥ" በሚል ስውር ሽፋን ነበር። ልክ እንደ ወራሪ ኃይል ቀስ በቀስ መስፋፋትን የመረጡት አዲሶቹ አካላት፣ "የተራዊህ ዚክር አቁሙ" በሚል ሰበብ የሱፊያውን ማህበረሰብ በማንገላታትና እስከ መደብደብ በሚደርስ በደል ብቸኛውን የመውሊድ ማክበሪያ መስጂዳቸውን ነጠቋቸው። ባለቤቶቹም ግጭትን በማስወገድ፣ ዋናውን ሰፊ መስጂድ ትተው በግቢው ውስጥ በምትገኝ አንዲት ጠባብ የመድረሳ ክፍል ውስጥ (ልክ እንደ ጋዛ ሰርጥ) ተጠቅጠው መውሊድን በከፍተኛ መከራና እንግልት ከአመት አመት ሲያከብሩ ቆዩ። ይህ በራሱ በገዛ ቤት ስደተኛ መሆን ነበር።
የዘንድሮው ክህደት እና ታላቁ መርዶ...
ዘንድሮ ግን ግፉ ጣሪያ ነካ! በመጅሊስ አስገዳጅነት አዲስ የኮሚቴ ለውጥ ሲደረግ፣ የመንግስት አካላት ባሉበት "መውሊድ በመስጂዱ ላይ መከበሩ አይቋረጥም፤ ሁሉንም እኩል እንመለከታለን" በማለት ቁርኣን ይዘው የማሉ አካላት፣ የገቡትን አማና በሉ። ያቺው ጠባብ የመድረሳ ክፍል እንኳ ተነፍጋ፣ አምና ያከበሩበት ቦታ ላይ ቆመው "በፍፁም በዚህ ግቢ ውስጥ አታከብሩም!" የሚል ጥብቅና አሳዛኝ ክልከላ ተጣለባቸው።
አባቶች መስርተው፣ አባባ ሙሪዶች አሳምረው በገነቡት ቤት የነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) መውሊድ ማክበር መከልከል የዘንድሮው ረቢዕ ታላቅ መርዶ ነው።
የራስን መሬትና ንብረት ቀምቶ፣ ባለቤቱን "ውጣ" ከማለት በላይ ምን ዙልም አለ?
ፍትህ የጠማው ይህ ማህበረሰብ ድምፅ ይፈልጋል። የሚመለከታቸው የመንግስትም ሆነ የመጅሊስ አካላት ይህንን ግልፅ በደል በትኩረት ተመልክተው አስቸኳይ እልባት እንዲሰጡ፣ ሁላችንም ይህን ግፍ ሼር በማድረግ የሙሪዶቹ ልሳን እንሁን!
#JusticeForAbretMurids #Woliso #Mawlid #StopTheInjustice
✍️በ yamin Amin
4 606
+2
የረቢዕ ዙልም በነቢ ሙሒብና በአባባ ሙሪዶች ላይ
===== ⨳ ===== ⨳ ===== ⨳ =====
በወሊሶ ከተማ የሚገኘውና የአብሬት ሸይህ ሰይድ አበልራሙዝ በገንዘባቸው የገዙት መሬት ላይ የተገነባው የአብሬት ሸህ ኑር መስጅድ ብቸኛ መውሊድ ይከበርበት የነበረ መስጂድ ቢሆንም የኮሜቴ ለውጥ በሚል ሽፋን በተደረገው የመንሃጅ እና የተርቲብ ለውጥ ምክንያት የተራዊህ ዚክር አቁሙ በሚል መነሾ ሱፍያው እስከ መደብደብደብ የደረሰ በደል ከተፈፀመበት በኋላ የዋናው መስጂድ ላይ ለማክበር ተከልክለው ቆይተዋል ።
በወቅቱ በተፈጠረው አለመግባባትም መውሊዱን ከዋናው መስጂድ አውጥቶ በአንድ ትንሽዬ የመድረሳ ክፍል ውስጥ እንዲከበር ተፈቅዶላቸው ከአመት አመት በከፍተኛ እንግልት እና መከራ መውሊዱን ሲያከብሩ ቆይተዋል ። ዘንድሮ ግን በመጅሊሱ አስገዳጅነት የኮሚቴ ለውጥ ሲደረግ የመንግስት አካላት ባሉበት "መውሊድ በመስጂዱ ላይ መከበሩ አይቋረጥም ፤ ሁሉንም እኩል እንመለከታለን" በማለት ቁርዓን መተው ምለው የገቡትን አማና በልተው አምና ያከበሩበት ቦታ ላይ እንኳን ተከልክለው በፍፁም እዚህ ግቢ ውስጥ አታከብሩም ተብለዋል።
የአብሬት ሸሆች በመሰረቱት ሙሪዶቻቸው ጊዜ ፣ ገንዘብ እና ጉልበታቸውን አውጥተው አሳምረው በገነቡት መስጂድ ላይ የነብዩ መውሊድ አታከብሩም የሚል ክልከላ የረቢዑ ታላቅ መርዶ ነው ። የሚመለከታቸው አካላት ጉዳዩን በትኩረት አይተው እልባት እንዲሰጣቸው በደላቸውን ሼር በማድረግ እናሳውቅላቸው።
Fuad Yasin
4 606
+2
አንድ ፀሀፊ የሆነ ጎረቤት ነበረኝ ይላሉ... አብሬትዬق "ከደጋጎች አንዱ" ብለው ኪታባቸው ላይ ያሰፈሯቸው አንድ ሰው::
ጎረቤቴ ሞ^ቶ በመናሜ አየሁት እናም አላህ ምን አደረገልህ ስል ጠየቅኩት... አላህ እኮ ማረኝ ብሎ አለኝ... በምን ማረህ ስል ጠየቅኩት:: ኪታቤ ላይ የነቢዩን ﷺ محمد ስም ከትቤ በሳቸው ላይ ሰለዋት አወረድኩ:: በዚህ ሰበብ አይኖች አይተውት የማያውቁት... ጆሮዎችም ሰምተውት የማያውቁት በሰው ልጆች ቀልብ እንዲህ አይነት ነገር ይሆናል ተብሎ ሊታሰብ የማይችል የሆነውን ጀነትን ሰጠኝ🥰
አንዋሮች ሆይ የተወዳጁንﷴﷺ መውሊድ እንዳደመቃቹት አላህ ያድምቃቹ🤲
4 606
የሐቢቢንﷺ ዊላዳ ሐቂቃ ደረጃ ብንረዳ ኖሮ ጉልበታችንንም ገንዘባችንንም እድሜያችንንም ሁሉ በመውሊዳቸው እየተደሰትን በጨረስን ነበር::
ليتنى عرفت قدر مولد احمد
وحبه الأكرم الأطهر والمسعد
4 606
ምስጋና
✦✦✦
ትናንት ለይለትል ጁሙዓ በዩቱብ ገልፃችን የተለቀቀቅ ሙሉ የአንድ ሰአት ከሀያ ሰባት ደቂቃ የዱረሩል መዓኒ ቅጂ subtitlሉን ከድምፁ ጋር እየጠበቁ ማስገባት እጅግ አድካሚና ብዙ ቀናትን የፈጀ ነበር::
ሙሉ ኪታቡን ወደ ፅሁፍ መቀየሩ ደግሞ ሌላ በጣም አድካሚ ፣ ሰፊ ግዜ የሚወስድና በጣም ጥንቃቄን የሚሻ ፈታኝ ስራ ነው:: ይህን ኪታብ ሀረካቱን ሳይቀር በጥንቃቄ ፅፈው ልከው ድካማችንን በግማሽ ላቀለሉልን ውድ ወንድሞቻችን በፌስቡክ ስማቸው Thamer Nur እና የጠይባ አህመድ ልጅ እጅግ በጣም እናመሰግናለን:: በነገራችን ላይ ከዚህ ቀደም እነሱ ፅፈው ልከውልን የተጠቀምናቸው ብዙ መድሆች አሉ::ለሚሰሩት ስራ ምስጋናም ሆነ ምንም አይነት ክሬዲት የሚሹ ባይሆኑም ልናመሰግናቸው ወደድን:: ምንዳችሁን ከአላህ🙏
4 606
+1
በኸይረኛው ወር ሁለት የኸይር ማስታወቂያ ከሁለት የተከበሩ ምርጥ መስጂዶች
1. በአንዋር መስጂድ ጁሙዐ ለየት ያለ ፕሮግራም /ሰርፕራይዝ ይኖራል:: የ 1501ኛ መውሊድ በዓልን ለማክበር ከተለያዩ አቅጣጫዎች የምትመጡ እህት ወንድሞቻችን በነገው እለት ኢንሻአላህ ያማረ እና የደመቀ ፕሮግራም ይኖረናል:: ይበልጥ ፕሮግራሙ እንዲያምር በነገው እለት ሁላችንም ነጭና አረንጟዴ ባንዲራዎችን እንዲሁም ነጭ ቶብ እንድንለብስ ፣ በጀምዓ ወደ መስጂድ የምንጏዝ ካለንም ሰለዋት እያወረድን እንድንመጣ የ የታላቁ አንዋር መስጂድ ወጣት ጀመዓ አደራ ብለዋል🙏
2. የኑር መስጂድ ወጣት ጀመዐ የታላላቅ ዑለሞችን እና ዳዒዎችን የማህበራዊ ሚድያ ተደራሽነትን ለማስፋት በማሰብ ከ facebook እና tiktok በተጨማሪ የ youtube ቻናል ከፍተዋል:: በዚህ ትዩብ የተለያዩ ታላላቅ መሻይኽ እና ዑለሞች ፣ የኡስታዞች እና የዳዒዎች ደርስ ይቀርብበታል:: በተጨማሪም በቻናላችን ላይ የተለያዩ ታሪካዊ እና ዘመን አይሽሬ የሆኑ የተላላቅ መሻይኾች ደርስ እና ንግግሮች ይገኙበታል:: ማስፈንጠሪያው ከታች አለላቹ Subscribe አድርጉ አህባቦችንም ጋብዙ🙏
www.youtube.com/@NurMesjid
https://youtu.be/2hB85SwJxZ4
