ABRET PRO
رفتن به کانال در Telegram
የአብሬት እንዲሁም የቃዲሪይ ሲልሲላ መንዙማዎችን ፣ ከአካቢሮች የሰማናቸውን ቀሰሶች ፣ እንዲሁም ከመሻኢኾቻችን ኪታቦች አንዳንድ ጠቃሚ ነገሮችን የምንማማርበት አጠቃላይ የሀድራ ስራዎችን የምንዘክርበት ቻናል ነው @Abretpro
نمایش بیشتر4 622
مشترکین
-324 ساعت
+137 روز
+8030 روز
آرشیو پست ها
4 622
🎉 30,000 subscribers! 🎉
ለምታደርጉልን ድጋፍ ለእያንዳንዳችሁ ከልብ የመነጨ ምስጋና እናቀርባለን! ❤️ የምትሰጡን like ፣ comment ፣ share እና ማበረታቻ ለእኛ እጅግ ትልቅ ትርጉም አላቸው።
30 ሺህ ደርሰናል፤ ኢንሻአላህ አሁንም እያደግን ወደ ቀጣዩ የስኬት ጉዞ እንቀጥላለን! 🚀🙌
4 622
መገርገብያ
ዒባዳ የሆነ እንደሆነ ኒّያ አለው:: ከኒያው በፊት ዓደቡ ጋር መድረስ ነው:: ከኒያ በሑዋላ በዐደቡ መግባት ነው:: ኒያ የሚጠናው በሐድረቱላህ ሙዐለቃ ከሆነ ነው:: ሙዐለቅ የሆነ ሰው ሁሌም በውስጡ (በኢባዳ) አለ:: መላኢካዎች ስራቸውም ነው... ኒያ አያስፈልጋቸውም:: አህሉላሆች የሆኑ እንደሆነ በውስጡ አሉ... ኒያ አያስፈልጋቸውም:: መቼም አንድ ግዜ ነይተው ገብተዋል... ከገቡ በሁዋላ ድጋሚ አይወጡም... ያው ስራቸውም ነው::
ሠይዲ አባራሙዝ ቀ.ሢ
4 622
የሸይኽ ሚስባህ መውሊደ ነቢይﷺ
ጠሮ መስጂድ አካባቢ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው እሁድ መስከረም 03-01-2019 ከጠዋት ጀምሮ የሚከበር ይሆናል::
በጠዋቱ የአብሬትይ የመውሊድ ሲራ ኪታብ ዱረሩል መዓኒ ይቀራል:: የነቢይﷺ መድህ እንደጉድ ይዘከራል:: መውሊዱ ለሁሉም ክፍት ነው:: የቻለ ሰው ቢገኝ ያለምንም ጥርጥር ይጠቀማል::4 622
ሡፍያን አልثውሪይን ዋቢ አድርገው አብሬትዩ ሳኒ(ቀ.ሢ) ኪታባቸው ላይ እንደዘገቡት ሡፍያኑ ثውሪይ(ረ.ዐ) አለ:- በረሀ ላይ አንድን ሰው አየሁ እግሩን አያነሳም እንዲሁም አይሳርፍም በነብዩﷺ ላይ ሰለዋት አውርዶ ቢሆን እንጂ:: ምንድነው ይሄ? ተሥቢህን እንዲሁም ተሕሊል ትተህ ሁሉንም በሰለዋት ቀየርክን? ብዬ ስለው ለመሆኑ አንተ ማን ነህ ብሎ ጠየቀኝ እኔ ሱፍያኑ ثውሪይ ነኝ አልኩት... ሶሀባ ባትሆን ኖሮ ሁኔታዬን ባልገለጽኩልሁ ሚስጥሬን ባልነገርኩህ ነበር። ከአባቴ ጋር ሆነን ወደ በይቱላህ ለሀጅ ጉዞ ወጣን ርቀን ከተጓዝን በሗላ መንግድ ላይ አባቴ ታሞ አረፍን በዛው አባቴ ሞ ተ ፊቱ ጠቆረ... ፊቱን በልብሶቹ ሸፈንኩት ድካም አይኖቼን አሸንፎ እንቅልፍ አሸለበኝ...
በመናሜ አንድ ሰው አየሁ... እንደሱ ውብ የሆነ ፊት ፥ ፅዱ የሆነ ልብስ ፥ ልዩ የሆነ ማራኪ ሽታ አላየሁም:: አንድ እግሩን አንስቶ ሌላኛውን እግሩ ሲያሳርፍ አባቴ አጠገብ መጥቶ ደረሰ... የአባቴ ፊት ላይ የተሸፈነውን ልብስ ከፍቶ ፊቱን በእጁ አበሰው ጠቁሮ የነበረው የአባቴ ፊት በራ... ተመልሶ ወደ መጣበት ሊሄድ ሲል ልብሱን ይዤ ማን ነህ አንተ አባቴ ላይ ረሕመት አድርጎ አላህ የላከህ? አልኩት... አታውቀኝምን? እኔ ሳሂቡል ቁርአን ሙሐመድﷺ ቢን ዐብደላህ ነኝ... አባትህ ነፍሱ ላይ ኢስራፍ የሚሰራ ሰው ነበር... ነገር ግን አብዝቶ እኔ ላይ ሰለዋት ያወርድ ነበር... በጭንቁ ግዜ የኔን እገዛ(ጊያሳ) ጠየቀ በኔ ላይ አብዝቶ ሰለዋት ለሚያወርድ ሰው እኔ ረዳቱ ነኝ:: (reposted)
ሰለዋቱ ረቢ ወሠላሙሁ💚
4 622
እዚህ ቦታ ሲደርሱ ልክ እንደ መዲና ቀልብ ይረጋጋል ፣ ሩሕ ሰላም ያገኛል ፣ ቀልብ በኢማን ይሞላል ፣ ጥርጣሬ ብዥታ ምናምን ብን ብሎ ይጠፋል::
4 622
የሸኾቹ ወዳጅ የውድ ወንድማችን ዑስታዝ አብዱልሐሚድ እናት ወደ ማይቀረው ሀገር ተሻግረዋል… አላህ ከፍ ባለው ደረጃ በጀነቱ ያኑርልን ፣ ለዑስታዝ አብዱልሐሚድ ለወዳጅ ዘመዱ ሁሉ ብርታቱን አላህ ይስጥልን 🤲
አልፋቲሓ
4 622
የጉራጌ ማህበረሰብ በስፋት ይከተለው የነበራው ዋቅ እንዲሁም ቦዠ የሚባለው ባእድ እምነት ምን ያህል ጥልቅ እና ከማህበረሰቡ ጋር የተሳሰረ እንደነበር ብዙዎቻችን ላንገነዘበው እንችል ይሆናል:: ይህ ጭለማ በሸኾቹ ጥረት እጅግ ከፍተኛ በሆነ ጁህድ ተገርስሶ ነው በኑረል ኢማን የበራው::
ሠይድ ኢብራሂም የመጀመሪያው አብሬት ሸይኽ(ሠይድ ባኡ ሳኒ(ቀ.ሢ) አባት ከዚህ ባእድ አምልኮ መሪዎች ቤት ወጥተው ፣ ስርአቱን አዛብተው ፣ እጅግ ጉሩም በሆነ መልኩ በልጅነት እስልምናን ተቀብለው ፣ ጉራጌ ላይ የኢማን ችቦ ለኮሱ::
ይህን ግሩም ታሪክ fuad ዘርዘር አድርጎ በጥሩ ሁኔታ አቀናጅቶታል ተጋበዙልን
https://youtu.be/pY2SrWRRFL8?si=IAFDQX7PzkuGLgVc
4 622
💚🔥 zahid
ማማሪያዬ ነቢ | አብዱሰላም አበራ| እንዴት ነሁ | አዲስ ነሺዳ
https://youtu.be/kGnOQcQgkWI?si=4ubrKNvlqBMVN8nC
4 622
ኸሚስ💚🔥
ሠላም ዐለይኩም ያኑሩ ያጣሀ በድረል ሙኒሩ
ሶላቱላሂ ዐለይከ ማ ሐነ ሩሑ የዝኩሩ
سلامْ عَلَيْكُمْ يَا نُورُ يَا طَهَ الْبَدْرُ الْمُنِيرُ
صلاةُ اللهِ عَلَيْكَ مَا حَنَّ الرُّوحُ يَذْكُرُ
የአብሬትዩ ሳኒ ሠይዲ አባ ራሙዝ(ቀ.ሢ) የመውሊድ መድህ በሸይኽ ኤሊያስ እና ሸይኽ ኸይሬ እስከነ ፅሁፉ
https://youtu.be/nqHWxhbBEHo?si=rxlzhWwEAJUFo787
4 622
በልጅነቴ ነው በካሴት የተቀዳውን የአብሬትዩ ሳኒ ወአዝ አባቴ ከሆነ ቦታ አግኝተው በክብር ይዘዉት መጡ... ወቅቱ ባእደል መግሪብ ነው:: ፀጥ ረጭ ብለን ሁላችንም ተሰባስበንና ቴፑን ከበን በተዋዱእ በጥሞና የአባባን ድምፅና ወአዙን የሚያስተጋባውን ሰው አደመጥን:: የአነጋገር ዘይቤያቸው እጅግ ልዩ ነው:: ጉራጊኛ ቋንቋ በሳቸው አንደበት ሲሰማ ውበቱ ለጉድ ነው:: የዛን ቀን የሰማሁት ወአዝ ጥፍጥናው አሁን ድረስ ውስጤ አለ:: ለህይወቴ ሙሉ ቀለብ ሆኖኛል:: የዛን ቀን ከሰማሁትና ህይወቴን ያሰመረልኝ ወአዝ
በጉራጊኛ + በአማርኛ እንካቹ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬👇
የኒዕማ ጉነረታ ኢማኑ ኢስላሙ... በሃንቄ የኸረ በኸረ አፊያው:: ዄተኽኖ ያነን ሰብ አነሴም ይብሬ ሀቅ ኤትገቧን:: አላህ ባበ ቃር ቲትብቋቄ ግዝየ ወሄ ቃሩ:: ያበ ሁታ ይጣኒሸ ቲቡሪ ወሄ ቃሩ:: ባነከዊ ሁታ ሰብር አንብኸሮቱ... ነከዊምታ ቦረ ኹታ ሰብር አንብኸሮቱ... ይጣኒሸ በሮቱ :: ይጣኒሸ የባር ሰብ ይወጣረ:: ይጣኒሸ የባረ ሰብ ቀልብመታ ያᎈ ጅስማመታ ያᎈ:: ይጣኒሸ ያንባረ ሰብ ፎያት ኤረኽብ ቀልብመታ ጅስማመታ ፎያት ኤረኽብ::
━━━━━━⊱⊰━━━━━━አማሪኛ👇
የኒዕማ(ስጦታ) ራሱ(ቁንጮው) ኢማን ነው... እስልምና ነው:: ከዛ ቀጥሎ እንደሆነ አፊያ ነው:: ሁለቱ ያለው ሰው አንሶኛል ለማለት ሀቅ አይገባውም:: አላህ በሰጠ ነገር ሲብቃቁ ጥሩ ነው:: የሰጠው ነገር ይበቃኛል ሲባል ጥሩ ነው:: ባልተገኘው ነገር ሰብር አለማጣት ነው:: ተገኝቶ በታጣው(በሄደው) ሰብር አለማጣት ነው:: ይበቃኛል ማለት ነው:: ይበቃኛል ያለ ሰው ይበቃዋል:: ይበቃኛል ያለ ሰው ቀልቡም ያርፋል... ሰውነቱም ያርፋል:: ይበቃኛል ያላለ ሰው እረፍት አያገኝም:: ቀልቡም ጀሰዱም እረፍት አያገኝም::
4 622
ጉድ! ብሎ ዝም ነው የሙሐመድﷺ ነገር:: ክቡር የሆኑት አንቢያኦች ሁሉም በነብያችንﷺ የኑር ጠብታ ተኸለቁ::
وَجَمِيعُهُمْ خُلِقُوا مِنْ قَطَرَاتِ نُورِهِ
وَالأنْبِيَاءُ الْكُرَمَا وَعِنْدَ الْكُلِّ يُشْكَرُ
4 622
ኸሚስ💚🔥
☆☆ ☆ ☆☆
ሶላ ዐለይከ ነብዩ ያሢራጅ ያሙኒሩ
ወሠለመከ ኢላሁ ያሐቢቡ ያበሺሩ
የአብሬትዩ ሳኒ ሠይዲ አባ ራሙዝ(ق) የመውሊድ መድሕ
በሸይኽ ኤሊያስ እና ሸይኽ ኸይሬ እስከነ ፅሁፉ
صَلَّى عَلَيْكَ نَبِيُّ يَا سِرَاجُ يَا مُنِيرُ
وَسَلَّمَكَ الإلَهُ يَا حَبِيْبُ يَا بَشِيْرُ
https://youtu.be/tQWyVfRMC1Q?si=8hbfu_ku1FKZpi90
4 622
ከመቶ አመታት በፊት ኢብን ስዑዲ በመባል የሚታወቀው ንጉስ አብዱልአዚዝ ሒጃዝን በጦ$ርነት አሸንፎ ከተቆጣጠረ በሁሗላ ሒጃዝ ላይ ብዙ የቀ$ብር ቁባዎችን እንዳፈረሱ ፣ ብዙ የተሰዉፍ ኪታቦችን እንዳ$ቃጠሉ ፣ ብዙ አህለ በይቶችን እንደገ#ደሉና የተቀሩት አህለ በይቶች በብዛት ወደ የመን ሸሽተው እንደተሰደዱ አንድ እጅግ የማከብራችው የጥልቅ ዒልም ባልተቤት የሆኑ አጎቴ ሐፊዘሁላህ ሲያወሩ ሰምቼ ነበር::
የየመኖች የመውሊድ አከባበርና ጥልቅ የነቢዩﷺ ሙሓባ ሲታይ እውነት አህለ በይቶች በብዛት የመን ውስጥ መኖራቸውን መረዳት ይቻላል::
4 622
+9
👆 የነብያችንንﷺ መውሊድ አታክብሩ አይበቃም የሚሉ ሰዎች ከመጡ ወዲህ ሙሒቡ ካልበቃማ እንጨምራለን ያለ ይመስላል:: የመውሊድ አከባበር ድምቀት በመላው አለም እጅግ እየተባባሰ እየደመቀ ነው የመጣው:: አልሐምዱሊላህ
በአለማችን የተለያዩ ክፍሎች በጥቂቱ የመውሊድ አከባበር በምስል ይህን ህመስል ነበር
4 622
አንገታችንን ቀና አድርገውልናል:: የእስልምናን ውበት ሰው የመሆንን ትርጉም ለሁሉም አጉልተው አሳይተዋል:: የሙፍቲ ትውልድ በመሆናችን አልሐምዱሊላህ ኩራት ይሰማናል:: ዒዱም መውሊዱም በመጣ ቁጥር ሁሌም ልናስባቸው ግድ ይለናል::
4 622
በዛሬው እለት ማክሰኞ ረቢዕ 12 1448 ዓመተ ሒጅራ የነብዩﷺ መውሊድ በታላቁ አንዋር መስጂድ በተከበረበት መድረክ
አብሬትዩ ሳሊስ መውላና ሠይድ ሸይኽ ሚቅባሰል ኑር(ق) ሸይኽ ሠይድ ሙሐመድ ቡደላ(ق)
ሼይኽ ሙሀመድ ሁሴን (ኮንቦልቻ)
ዑስታዝ ፈድሉዲን ሀሰን(ዑስታዝ ፈድሉ)
የመንዙማ ዘርፉን በማሳደጋቸው፣ በዘርፉ አያሌ ድርሳናትን በመሰነዳቸው እና በርካታ ተተኪ ትውልድ በማነፃቸው የመጀመሪያዎቹ ሦስት ተሸላሚ ተደርገው ተመርጠዋል።
ፀሀፊ ኸድር ታጁ በሰራው በርካታ የታሪክ ድርሳናት የአዋርዱ ተሸላሚ ሆኖ ተመርጧል::
4 622
ረቢዐል አወል 12ኛው ለይል ከአስር ሰአት በሁዋላ ፈጅር መቃረቢያው ላይ ትልቁ ሰውﷺ ተወለዱ።
እንኳን ለነብዩ ﷺ መውሊድ አደረሳችሁ::
💚🎉
4 622
🌟 አልሀምዱሊላህ! ፍትህ አሸነፈች - የዘንድሮው መውሊድ በወሊሶ የአብሬት ኑር መስጂድ - በደማቅ ሁኔታ ይከበራል! 🌟
===== ⨳ ===== ⨳ ===== ⨳ =====
ትናንትና እና ዛሬ በተደረገዉ ተከታታይ፣ ሰላማዊ እና ህጋዊ ጥያቄ መሰረት፤ በወሊሶ አብሬት ኑር መስጂድ የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መውሊድ በነፃነት እንዲከበር በይፋ ተፈቅዷል!
በዚህም መሰረት የመውሊዱ ፕሮግራም ከዛሬ ማታ ጀምሮ የሚጀመር ሲሆን፣ ዋናው እና ታላቁ የመውሊድ በዓል ነገ ረቢዕ አል-አወል 12፣ 1448 ዓ.ሂ ሙሉ ቀን በታላቅ ድምቀት በአብሬት ኑር መስጂድ ይከበራል!
ይህ የፍትህ ድምፅ ሰምሮ የደስታው ተካፋይ እንድንሆን ላደረጉ አካላት በሙሉ ታላቅ ምስጋና ማቅረብ እንወዳለን፦
1:- ለፍትህ ዘብ ለቆሙ የመንግስት አካላት፡ ሀላፊነታቸውን በአግባቡ በመወጣት፣ ከፍትህ ጎን በመቆም ለማህበረሰቡ ድምፅ ለሆኑት ለወሊሶ ብልፅግና ፅ/ቤት ምክትል ሀላፊ ለጁዋሪያ አህመዲን (Juwariya Ahmedin) እንዲሁም ለወሊሶ ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ ለኢፋ አንጋሳ (Ifa Angasa) ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
2:- ለሰላማዊ ታጋዮች፡ በርቀትም ሆነ በአካል በመገኘት፣ ህገ-መንግስታዊ መብታችሁን ለማስከበር ከሚመለከተው አካል ጋር ሰላማዊ እና ስልጡን በሆነ መንገድ ጥያቄያችሁን ላቀረባችሁ አካላት ሁሉ ክብር ይገባችኋል።
3: ለነባሩ የመስጂድ ኮሚቴ፡ መስጂዱ ከእጃችሁ ከመነጠቁ በፊት፣ በመስራቹ በአብሬት ሸህ ብሂል እና እሴት መሰረት መስጂዱን እያሰራችሁ በሰላምና በፍትህ ስታስተዳድሩ ለነበራችሁት ነባር ኮሚቴዎች አላህ ምንዳችሁን ይክፈላችሁ። ከአላህ ጋር ፍትሀቹ ሙሉ ይሆናል።
4:- ለማህበራዊ ሚዲያ ቤተሰቦች፡ የጉዳዩን አሳሳቢነት እና ኢ-ፍትሀዊነት በመገንዘብ፣ ትናንት የደረሰብንን በደል ሼር በማድረግ፣ በየደረጃው የሚገኘው የሚመለከተው የመንግስት አካል ጉዳዩን እንዲያውቀው ድምፅ ለሆናችሁን ሁሉ ታላቅ ምስጋና እናቀርባለን።
የእውነተኛ ሙሂብነት መለኪያው ይሄው ነው! የአባባ እውነተኛ ተወላጅም ሆነ ወዳጅ፤ በገዛ መስጂዳቸው ከተርቲባት እስከ መውሊድ የሳቸዉ መንገድ እንዳይሰፍን ተከለከለ ፣ ህገመንግስታዊ የሙሪዶቻቸዉ መብት ተነጠቀ፣ ሲባል ቆሞ የሚያይ በፍፁም ሊሆን አይችልም። ቢያንስ አስቀድሞ በሚችለው አቅም ሙከራ ያደርጋል፣ አብሮ ይገፋል፣ ሰላማዊ በሆነ መልኩ ፍትህን ይሻል፣ ሁሌም ከሚበደሉት ጎን ይቆማል እንጂ!
እንኳን ደስ አለን! ኑ! የነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) መውሊድ በደስታ፣ በሰላምና በፍቅር እናክብር!
4 622
+3
መውሊደ ነቢይﷺ በአብሬቱ ኑር በሠይዲ(ق) ቤት በቀኑ ድምቅ ብሎ ይከበራል:: በሸኾች መድሕ ነቢይንﷺ ለጉድ እንመድሀለን ፣ በነቢይﷺ ዊላዳ እንደሳለን ፣ ለነቢይﷺ እናሽቃለን ፣ በሙሓባ እንወዘወዛለን:: የነቢ ወዳጆች በሙሉ አርሒቡ የተንቢ በሩ ክፍት ነው::
4 622
ከፍጥረት ሁሉ የላቁት ነብያችንﷺ በመወለዳቸው በይቱላህ በደስታ ዘለለ (ደነሰ) ፣ መዋቅሩም ተወዛወዘ::
رَقَصَتْ بَيْتُ اللهِ وَمالَ بِنَاؤُها
فَرَحًا بِمَوْلِدِ أجلِّ الْبَريَّةِ
