ይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት Yihunie woldu metasebiya Dessie Special Boarding School
Open in Telegram
በአማራ ክልል የመጀመሪያው ስለሆነው ደሴ ልዩ አዳሪ ትምሀርት ቤት ወቅታዊ መረጃ እንዲሁም አዳዲስ ፈጠራዎች ፣ ለተማሪዎችና ለመምህራን አጋዥ መፅሀፎች፣ ጥያቄዎች፣ ማስታወቂያዎች እዚህ ቻናል ላይ ያገኛሉ።
Show more3 739
Subscribers
+424 hours
+147 days
-2430 days
Posts Archive
Hello, dear colleagues. Hope u r doing great. Harvard Language Center is gonna have a graduation ceremony in our school tomorrow, on Sunday starting from 8:00 local time. And l want everyone of you to attend this very special and tremendous celebration.
Thank you in advance.
Getachew Tadesse
🦚🌻💐💐🍁💐🌻🦚🦚💐💐🍁💐
ለት/ቤታችን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ⛹
1. የጥናት ፕሮግራማችሁ ላይ ምንም አይነት መዘናጋት እንዳይኖር
2.የOnline ፈተና ልምምድ ከሰኞ ጀምሮ ተጠናክሮ ይቀጥላል የሰዓት ፊርማም የተዘጋጀ በመሆኑ በጥብቅ ክትትል ስለሚደረግ ያለምንም ምክንያት እንድትገኙ በማለት እናሳስባለን።
3.ከት/ቤት ውጭ የምትወጡና የምታድሩ ተማሪዎች ከዛሬ ጀምሮ ጥብቅ ክትትል በዶርም ስለሚደረግ ያልተገኘ ተማሪ ላይ ተገቢውን እርምጃ ት/ቤቱ ይወስዳል።
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏መልካም የዝግጅትና የጥናት ግዜን እንመኛለን!!
💐🦚🌻🦚🌻💐🍁💐🌻🌻🦚💐🍁
Repost from Ethiopian Artificial Intelligence Institute
ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ለሆናችሁ ተማሪዎች በሙሉ!
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በተከታዮቹ መስኮች ራሳችሁን የምታንጹበት ታላቅ የክረምት ስልጠና አዘጋጅቶላችኋል።
🤖በፈንዳሜንታል ኦፍ ኤ.አይ፣
💻 ፕሮግራሚንግ፣
🧠 ማሽን ለርኒንግ፣
⚙️ በሮቦቲክስ እና IOT፣
📊 ዳታ ሳይንስ እና በሌሎችም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ዘርፎች ራሳችሁን የምታንጹበት ታላቅ የክረምት ስልጠና ተዘጋጅቶላችኋል።
እስከ ሰኔ 30፤ 2018 ዓ.ም ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ በተከታዩ የጉግል ፎርም https://forms.gle/uDGPmQsiZcWWeNuRA በመጠቀም ይመዝገቡ።
PREPARED BY HAJI MAMO
review biology from 9-12.docx2.33 KB
ቀን፡-28/09/2018
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች
12ኛ ክፍል ኦላይን ተፈታኝ ተማሪዎች መለማመጃ ሊንክ exam2.ethernet.edu.et የነበረ እና አንዳንድ ጊዜ የሚያሰቸግር መሆኑ ይታወቃል፡፡በመሆኑም አዲስ መለማመጃ ሊንክ mock2.ethernet.edu.et በመሆኑ ተማሪዎች ልምምዳችሁን አጠናክራቸሁ እንዲትቀጥሉ በማለት እናሳዉቃለን፡፡
ት/ቤቱ
Grade-12 Model Exam Program(Revised 2018).docx0.16 KB
የፈተና ስልቶች (Exam Strategies)
ፈተናን በተሳካ ሁኔታ እንዴት መውሰድ ይቻላል?
1. ፈተናው አንድ ሳምንት ሲቀረው
* ያለፉ የፈተና ሽቶችን መስራት
* የማጠቃለያ ማስታወሻዎችን መከለስ
2. ፈተናው እንደ ነገ ሆኖ ዛሬ ማታ
* የፈተና ቁሳቁሶችን (እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ) ያዘጋጁ
* የፋይዳ መታወቂያና አድሚሽን ካርድ ያደራጁ
* ሰዓት ያደራጁ
* ያለምንም ጭንቀት ዘና ብለው ይተኙ
3. በፈተና ክፍል ውስጥ (በፈተና ጊዜ)
I. ወደ ፈተና ክፍል ከገቡ በኋላ፡-
* መረጋጋትና በእርጋታ መፈተኛ ወንበር ላይ መቀመጥ
* ጭንቀትን ያስወግዱ
* የፈተና ወረቀቶች ሲሰራጩ ዘና ብለው ይተንፍሱ
II. ፈተናውን መስራት ሲጀምሩ፡-
* መመሪያዎችን (Instructions) ያንብቡ
* ጊዜን መቆጣጠር – ሰዓት እያዩ ፈተናውን መስራት
* በመጀመሪያ ቀላል የሆኑትን ጥያቄዎች ይስሩ።
* ከባድ ጥያቄ ካጋጠሞት፣ በስልታዊ ግምት አጥቁረው ሰርተው ወደሚቀጥለው ጥያቄ ይሂዱ። በፍፁም ሳያጠቁሩ ባዶ ቦታ ትተው እንዳያልፉ፡፡
* በአንድ ጥያቄ ላይ ረጅም ጊዜ አያጠፉ ምክንያቱም አጭር ጊዜ የሚወስዱ ብዙ ቀላል ጥያቄዎች አሉ።
* መጨረሻ ላይ ጊዜ ካለዎት፣ በግምት ቀብተው ያለፏቸውን ጥያቄዎች ተመልሰው ይስሩዋቸው።
* ስልታዊ ግምት 1/4ኛ መልሱን የማግኘት ዕድል አለው፡፡ ዝም ብሎ በደመነፍስ መገመት ሳይሆን ስልታዊ ግምት ይጠቀሙ፡፡
ለሁሉም የትም/ቤታችን ሙስሊም ተማሪዎችና የስራ ባልደረቦች እንዲሁም የሀገራችን ሙስሊሞች እንኳን ለ1447ኛዉ የኢድ አልአደሃ(አረፋ) በአል በሰላም አደረሳችሁ፡፡ መልካም በአል ይሁንላችሁ ሀገራችንንም አምላክ ሰላም ያድርግልን
ለሁሉም የትም/ቤታችን ሙስሊም ተማሪዎችና የስራ ባልደረቦች እንዲሁም የሀገራችን ሙስሊሞች እንኳን ለ1447ኛዉ የኢድ አልአደሃ(አረፋ) በአል በሰላም አደረሳችሁ፡፡ መልካም በአል ይሁንላችሁ ሀገራችንንም አምላክ ሰላም ያድርግልን
🌺🌺🦚🦚🌻🌻🍁🍁💐💐❤❤🌻🌻
ለት/ቤታችን ሙስሊም ማህበረሰብ በሙሉ
እንኳን 1447ኛው ለኢድ አል አድሃ አረፍ በአል በሰላም አደረሳችሁ።
ኢድ ሙባረክ!!
🌻🌻💐💐💐🍁🍁🌻🌻🍁🍁🦚🦚🌺
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የፈተና ሂደትና ዝግጅትን በተመለከተ የተደረገ የግንዛቤ ፈጠራ
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
