የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት
Open in Telegram
ይህ ገፅ የቡራዩ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ትምህርት ቤት መልዕክቶችን ዘመኑ በሚፈቅደው መንገድ እንዲተላለፍበት በህዝብ ግንኙነት ክፍል የሚመራ ይፋዊ ገጽ ነው። 📞+251944247165 ሀሳብ አስተያየት ካሎት @finoteselam27PR በinbox አድራሻችን ያድረሱን።
Show more1 673
Subscribers
-124 hours
-87 days
+130 days
Posts Archive
#ፍኖት_ከሰሞኑ_በረከት
የሻደይ በዓልና ፍልሰታ
የሻደይ በዓል አጀማመርን በተመለክተ ከላይ
ከተቀመጡት ታሪኮች በተጨማሪ በአካባቢው
ሕዝብና በቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ዘንድ ተደጋግሞ የሚነሣው ታሪክ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤ በዓል ነው፡እግዚአብሔር ለአዳምና ሔዋን ከአምስት ሺሕ አምስት መቶ ዓመት በኋላ ወደዚህ ዓለም አንድያ ልጁን ልኮ ከኀጢአት እሥራት ነጻ እንደሚያወጣቸው በገባላው ቃል ኪዳን መሠረት አምላክ የተወለደባት እና ትንቢቱ የተፈጸመባት፣ ከገነት የተባረረው የሰው ልጅ ወደ ገነት እንዲመለስ ምክንያት የኾነችው፣ የሰው ልጆች መመኪያ የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከዚህ ዓለም ድካም ካረፈች በኋላ ሞትን ድል አድርጋ ከመቃብር ተነሥታ ወደ ሰማይ ዐርጋለች፡፡
በፍልሰታ ወቅት በዓሉ መከበሩ ለምንድን ነው ቢሉ
ለሻደይ ተጨዋቾች ተምሳሌትና የድንግልናቸው አርአያ የሚያደርጓት ድንግል ማርያም አካላዊ ሥጋዋ ከጌቴሰማኒ ወደ ገነት መፍለሱን፤ እንደዚሁም በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር ከነበረበት መነሣቱን ምክንያት በማድረግ እንደኾነ የሚገልጹት የዋግ ኽምራ ሀገረ ስብከት ስብከተ ወንጌል መምሪያ ሓላፊ መጋቤ ምሥጢር ገብረ ሕይወት ኪዳነ ማርያም ‹‹የሻደይ በዓል በልጃገረዶች ዘንድ ተወዳጅ የኾነው በሔዋን ምክንያት የተዘጋው ገነት በእመቤታችን አማካኝነት በመከፈቱ ነው። እመቤታችን መመኪያቸው ስለ ኾነች ልጃገረዶች በዓሉን በደስታ ያከብሩታል፤ ድንግልናቸውንም አደራ የሚሉት ለእርሷ ነው›› ሲሉ ይናገራሉ።
እመቤታችን በነሐሴ ፲፮ ቀን በቅዱሳን መላእክት ሽብሸባ፣ ዕልልታና ዝማሬ ታጅባ ከምድር ወደ ሰማይ ስታርግ ሐዋርያት በታላቅ ደስታ ይመለከቱ፣ ይደነቁም ነበር፡፡ ደናግልም ከቅዱሳን መላእክት ከተመለከቱት ሥርዓት በመነሣት ነጫጭ ልብሶችን ለብሰው፣ አምረውና አጊጠው፣ ረጃጅምና ለምለም ቅጠል በወገባቸው አሥረው እንደ መላእክቱ አክናፍ ወገባቸውን ከግራ ወደ ቀኝ እያመላለሱ፣እያዘዋወሩና እያሸበሸቡ፣ በአንደበታቸው እየዘመሩና በእጆቻቸው እያጨበጨቡ በአንድነት ተሰባሰባስበው በፍቅርና በሐሴት የወቅቱ መታሰቢያ የኾነውን የሻደይን በዓል ያከብራሉ ፡፡
እናቶችና እኅቶች በዐደባባይ ወጥተው የድንግል ማርያምን ትንሣኤና ዕርገት እንደ ነጻነታቸው ቀን በመቍጠር ከበሮ አዘጋጅተው ‹‹አሸንድዬ›› የተባለውን ቄጠማ በወገባቸው ታጥቀው ምስጋና በማቅረብ በዓሉን ይዘክራሉ፡፡ በአጠቃላይ የሻደይ ጨዋታ የፍልሰታ በዓል መከበር ከጀመረበት ጊዜ አንሥቶ በምእመኑ ዘንድ ለበርካታ ዓመታት እየተከበረ የኖረ ሃይማኖታዊ በዓል ነው፡፡ ይህንን ሃይማኖታዊ መሠረትነት ያለውን ትውፊት የመጠበቅና የማስጠበቅ ሓላፊነት ከኹላችንም ይጠበቃል።
የእመቤታችን አማላጅነት አይለየን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖
#የቡራዩ_ደ/ሰ መድኃኔዓለም_ካቴድራል
ፍኖተ_ሰላም_ሰንበት_ትምህርት ቤት
_
ፍኖተ ሰላም ሚዲያ
ነሐሴ 16/12/2017 ዓ.ም
✝ በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ።
ዲያቆን፦ ሮሜ 8÷31-ፍ.ም
ንፍቅ ዲያቆን፦ ዮሐ 2÷1-7
ንፍቅ ካህን፦ ግብረ ሐዋርያት፦ 1÷12-15
ምስባክ ፦ መዝ 45፥4-6
ቀደሰ ማኅድሮ ልዑል
እግዚአብሔር ውስተ ማዕከላ ኢትትሀወክ
ወይረድኣ እግዚአብሔር ፍፅመ
ትርጉም ፦
ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ
እግዚያብሔር በመካከሏ ነው አትናወጥም
እግዚያብሔርም ፈጥኖ ይረዳታል
ወንጌል ፦ ማቴ 16÷13-20
ቅዳሴ ፦ ዘእግዝእትነ(የእመቤታችን ቅዳሴ)
_
ፍኖተ ሰላም ሚዲያ
#ልዩ_ጉባኤ
#ዝክረ_ቅዱስ_እስጢፋኖስ ወቅድስት_ኪዳነ_ምሕረት
#እሑድ ነሐሴ 17
#ጠዋት 3:30 ጀምሮ
#ሁላችሁም ተጠርታችኋል።
# የነሐሴ ፲፭ የቅዳሴ ንባባት እና ምስባክ በንባብ
✝ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ ወንጌልና ምስባክ።
ሠራኢ ዲያቆን:- ፩ኛ ቆሮ ፲፪፥፲፰-ፍ.ም
ንፍቅ ዲያቆን:- ይሁዳ ፩፥፲፯-ፍ.ም
ንፍቅ ካህን:- ግብ ሐዋ ፩፥፲፪-፲፭
# ምስባክ፦ መዝ ፲፰፥፬
ውስተ ኩሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ
ወእስከ አፅናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ
ወውስተ ፀሐይ ሤመ ጽላሎቶ
# ትርጉም
ድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ
ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ
በእነሱም ውስጥ የፀሐይን ድንኳን አደረገ
# Afaan Oromoo hiikkaa
Sagaleen isaanii lafa guutuuf
Dubbiin isaanii hanga dhuma biyya lafaatti ba'e
Isaan keessattis dunkaana aduu hojjete
# ወንጌል፦ ማቴ ፲÷፩-፲፭
#ነሐሴ ፲፬ የዕለቱ ምንባባት
፩ኛ ቆሮ ፩፡፲ አስተበቍዐክሙ አኀዊነ በስሙ ለእግዚእነ
ያዕ ፩፡፲፪ ወብፁዕ ብእሲ ዘይትዔገሣ ለእኪት
ሐዋ ፲፡፴ ወይቤሎ ቆርኔሌዎስ ረቡዐ ዮም
ምስባክ መዝ ፵፫፡፬
ዘአዘዝከ መድኃኒቶ ለያዕቆብ ብከ ንወግዖሙ ለኵሎሙ ፀርነ ወበስምከ ናኀሥሮሙ ለዕለ ቆሙ ላዕሌነ
ወንጌል፡ ዘማቴዎስ ፲፯፡፲፬
ቅዳሴ፡ ዘእግዝእትነ አው ዘዮሐንስ አፈወርቅ
_
ፍኖተ ሰላም ሚዲያ
