uz
Feedback
የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

ይህ ገፅ የቡራዩ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ትምህርት ቤት መልዕክቶችን ዘመኑ በሚፈቅደው መንገድ እንዲተላለፍበት በህዝብ ግንኙነት ክፍል የሚመራ ይፋዊ ገጽ ነው። 📞+251944247165 ሀሳብ አስተያየት ካሎት @finoteselam27PR በinbox አድራሻችን ያድረሱን።

Ko'proq ko'rsatish
1 679
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+67 kun
+430 kun
Postlar arxiv
የቡራዩ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል የፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ሲያስተምራቸው የቆዩ #ከ1ኛ - 7ኛ ክፍል #የጀማርያን ፣ #የ8ኛ እና #9ኛ ክፍል መርኃግብ
+2
የቡራዩ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል የፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ሲያስተምራቸው የቆዩ #ከ1ኛ - 7ኛ ክፍል #የጀማርያን ፣ #የ8ኛ እና #9ኛ ክፍል መርኃግብር ተማሪዎችን የካቴድራላችን ስብከተ ወንጌል ምክትል ኃላፊ  መር ቀሲስ ዳዊት፣ የሰ/ት/ቤቱ ጽህፈት ቤት አካላት ፣ ተመራቂ ተማሪዎች እና የተመራቂ ተማሪ ወላጆች በተገኙበት በዛሬው እለት በድምቀት አስመርቋል። በመርኃግብሩ ላይ ከየክፍላቱ በመንፈሳዊው ፣በዓለማዊ  ትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ፣ በየመርኃግብራቱ የተለያዩ የትምህርት ዓይነቶች ሲያስተምሩ ለቆዩ መምህራን የእውቅናና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።      |መስከረም 03/2019 ዓ.ም ፍኖተ ሰላም ሚዲያ

#ፍኖት_ከሰሞኑ_በረከት መስከረም 2 : ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://vt.tiktok.com/ZSq5RMqyA/
#ፍኖት_ከሰሞኑ_በረከት መስከረም 2 : ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://vt.tiktok.com/ZSq5RMqyA/

"በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ ምድረ በዳዉም ስብን ይጠግባል"። መዝ ፷፬፥፲፩ እንኳን ከዘመነ ማርቆስ ወደ ዘመነ ሉቃስ በሰላም አሸጋገረን። 🌼🌼 መልካም አዲስ ዓመት 🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼
"በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ ምድረ በዳዉም ስብን ይጠግባል"። መዝ ፷፬፥፲፩ እንኳን ከዘመነ ማርቆስ ወደ ዘመነ ሉቃስ በሰላም አሸጋገረን።       🌼🌼   መልካም አዲስ ዓመት    🌼🌼       🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼                   |🔵ፍ/ሰ/ሰ/ት/ቤት

#የመረጃ_ሰዓት ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዓውደ ዓመት ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወተስዓቱ ዓመተ ምሕረት፤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!! በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣ በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፣ በየዓመቱ የይቅርታ እጁን እየዘረጋ የሚመግበን እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ከዘመነ ማርቆስ ሁለት ሺሕ ዓሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት ወደ ዘመነ ሉቃስ ሁለት ሺሕ ዓሥራ ዘጠኝ ዓመተ ምሕረት በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ! “ወይእዜኒ ነስሑ ወተጠመቁ፤ ወይደመሰስ ለክሙ ኃጢኣትክሙ፤ ወይመጽእ ለክሙ መዋዕለ ሣህል እምቅድመ ገጹ ለእግዚአብሔር፤ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንዲመጣላችሁ፣ ኃጢአታችሁም እንዲደመሰስ አሁንም ንስሐ ግቡ ተመለሱም” (የሐ.ሥራ ፫፡፲፱) የሰው ልጅ በስሑት ስራውና አእምሮው ምክንያት የኃጢአት ማዕበል በሚያናውጠው ባሕረ ዓለም እንደሚኖር ይታወቃል፤ የዓለሙ ባሕር በማዕበሉ በተናጠ ቁጥር በመርከቡ ተሳፍረው የሚጓዙ ሁሉ ጭንቀት ላይ መውደቃቸው የማይቀር ነው፤ በዚህ ጊዜ የሚያጽናና የቊርጥ ቀን ረዳትና ኃይል ያስፈልጋቸዋል፤ ሆኖም ረዳት በፍጥነት እንዲደርስላቸው መጮኽና መጣራት ከነሱ ያስፈልጋል፤ የምንኖርባት ዓለም ወይም ፕላኔት የክፋትና የጭካኔ ማዕበል በእጅጉ እየበረታባት መጥቶአል፤ ዓለማችን በስጋትና በፍርሓት፣ በራስ ወዳድነትና ባለመተማመን ተከባለች፣ በመሆኑም ዓለማችን ከምን ጊዜውም  በላይ የመጽናናት ዘመን እንዲመጣላት ትሻለች፤ እግዚአብሔር ለፍጥረቱ የሚያስፈልገውን ሁሉ አሟልቶ የሰጠ አምላክ እንደሆነ በግልጽ የሚታይ ነው፤ ይሁንና እግዚአብሔር ከኛ የሚፈልጋቸው ብዙ ነገሮች እንዳሉ በማያሻማ ሁኔታ አሳውቆአል፤ ከእነሱም መካከል በእውነተኛው መንፈስ ንስሐ መግባት፤ መጸጸትና መመለስ ናቸው፤ የዓለምን ሕዝብ በወሳኝነት ማጽናናት የሚችል እግዚአብሔር ብቻ ነው፤ እኛ ራሳችንን በራሳችን ለማጽናናት እንኳ በቂና ዘላቂ ዓቅም የሌለን ውሱኖች ነን፤ ይህንን እውነት ዓውቀን የእርሱን ርዳታ እንድንሻ እግዚአብሔር ይፈልጋል፤ ይህንንም ከልብ በመጸጸትና ከቀደመው ስሑት ተግባራችን በመመለስ በፊቱ ተንበርክከን መታዘዛችንን በተጨባጭ እንድናሳይ ይፈልጋል፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት! እግዚአብሔር ከታላቅ ቸርነቱ የተነሣ የመታደስ ዘመንን በየዓመቱ ከመስጠት አልተቈጠበም፤ እንደ ሁሉጊዜ አሁንም አዲሱን ዘመን ባርኮ ሰጥቶናል፤ ሆኖም አዲሱ ዘመን የመጽናናት ዓመት እንዲሆንልን የእኛ ተሳትፎ ወሳኝ ሚና እንዳለው መዘንጋት የለብንም፤ ከሁሉ በፊት ያለፈውን ዓመት እንደ ግልም፣ እንደ ማኅበረ ሰብም፣ እንደ ሃገርም፤ እንደ ሃይማኖትም በኅሊናችን ልናስበውና ልንገመግመው ይገባል፤ ያለፈውን ዓመት በንጹህ ኅሊናችን በጥልቀት ስንገመግመው፤ የመጣንበትና ያለፍንበት ስለሆነ ኮለል ብሎ በፊታችን ይታያል፤ ጥቅሙም ሆነ ጉዳቱ በሙሉ ከኛ የራቀ ስለማይሆን ዳኝነት ለመስጠትና ውሳኔ ለመወሰን አንቸገርም፤ በመሆኑም ለፈጸምነው ስሕተት ይቅርታን ከመጠየቅ ባሻገር ድጋሚ ላንደግመው መወሰንና ለተግባራዊነቱ በጽናት መቆም አለብን፤ እኛ በዚህ ደረጃ ከቀደመው ስሕተታችን ተጸጽተን ንስሐ ከገባን እግዚአብሔር ከኛ የሚፈልገውን አግኝቶአል ማለት ነው፤ በመካከላችንም ትክክለኛ መግባባት ተፈጥሮአል ማለት ነው፤ በዚህ ጊዜ እሱም ዘላቂ የሆነ የመጽናናት ዘመን ለኛ ይሰጣል፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት! በዓለሙ እንዳለው ሁሉ እኛም ወዲያና ወዲህ ከሚያወዛውዝ ፈተና አላመለጥንም ያለፈውን ዓመት በንጹሁ አእምሮአችን ስንመዝነው፤ ጥሩ የሚባል አልነበረም፤ በየአካባቢው ግጭቶች የቀጠሉበት፣ የሰው ደም የፈሰሰበት፣ ዕገታዎች የተፈጸሙበት፣ ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት የተቃጠሉበት፣ ምእመናን የተገደሉበትና የተፈናቀሉበት፣ ስጋት ያየለበት፣ ኑሮም የተወደደበት፣ ሌላም ሌላም ለሰው ልጅ የማይበጁ ነገሮች የተከሠቱበት ዓመት አሳልፈናል፤ ታዲያ አዲሱን ዘመን ስንቀበል እነዚህን ሁሉ እንዳሉ ይዘናቸው እንቀጥል ይሆን? ይህስ ከሆነ ‹‹እንኳን ለአዲሱ ዘመን አደረሳችሁ›› መባባሉ ትርጉም ይኖረው ይሆን? እንዲህስ ልንሆን ፈጽሞ አይገባም፤ ይልቁንም ባለፈው ዓመት የሆኑትን ሁሉ ላንደግማቸው ሁላችንም እንወስን፤ እነሱንም ማስቀረት እንችላለን፤ ምክንያቱም ችግሮቻችን በሙሉ ሰው ሰራሽ እንጂ የተፈጥሮ አይደሉም፤ ሰው ሰራሽ ችግሮች ደግሞ በሰው እንደመጡ ሁሉ በሰው ሊቀሩ የሚችሉ ናቸውና እናስቀራቸው፤ ጦርነቱን፣ ዕገታውን፣ ጥላቻውን፣ ፉክክሩን፣ እልከኝነቱን፣ ጭካኔውን ራስ ወዳድነቱን ግድያውን፣ አብያተ ሃይማኖት ማቃጠሉንና ማፍረሱን እኛው እንዳመጣነው እኛው ማስቀረት እንችላለን፤ ስንተወው እኮ ይቀራል፡፡ ስለሆነም ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ያላችሁ ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን ሁሉ ኢትዮጵያን እንዳለች የጋራ ዕድልና ሃብት አድርጋችሁ ተቀበሉ፤ ሌላውን ረጅም ጊዜ ሰጥታችሁም ቢሆን በውይይትና በመግባባት እየፈታችሁ በአንድነት ቀጥሉ፤ በይቅርታመንፈስ በአንድነት ተቃቅፎ ከመቀጠል ውጭ ሌላ የተሻለ ዕድል እንደሌለ በውል ተገንዘቡ፤ ለዚህ ሁላችሁም የበኩላችሁን ልባዊ ጥረት ከማድረግ አትቈጠቡ ብለን ከልብ እንመክራለን፡፡ በመጨረሻም፤ ለሁሉም መድኃኒቱ ቀና አእምሮ ነውና በአዲሱ ዓመት እግዚአብሔር ቅንና በጎ አሳቢ አእምሮ እንዲሰጠን በሱም ያሉብንን ጉድለቶች አርመንና አስተካክለን ሰላም የሰፈነበትን የመጽናናት ዘመን ማየት እንችል ዘንድ እግዚአብሔር አምላካችንን እንለምን፤ እኛም በንስሐ እንመለስ እያልን በድጋሚ እንኳን ለአዲሱ ዘመን በሰላም አደረሳችሁ በማለት አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን ፡፡ እግዚአብሔር መልካም አዲስ ዘመን ያድርግልን፡፡ እግዚአብሔር ኣምላካችን ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር ኣሜን!! አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ መስከረም ፩ ቀን ፳፻፲፱ ዓ.ም አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ |ፍኖተ ሰላም ሚዲያ

#ተለቋል 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #የ2019_ዓ.ም_ባህረ_ሃሳብ 👇👇👇👇 https://vt.tiktok.com/ZSqyFw3NT/ 👆👆👆👆 ለሁሉ እንዲዳረስ:- #Repost #Li
#ተለቋል 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #የ2019_ዓ.ም_ባህረ_ሃሳብ 👇👇👇👇 https://vt.tiktok.com/ZSqyFw3NT/ 👆👆👆👆 ለሁሉ እንዲዳረስ:- #Repost #Like #Share የሚዲያ ገፃቻችንን #Follow ያድርጉ። 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ዛሬ ምሽት 2:00 ሰዓት ላይ በ#Tiktok እና #Instagram ገፃችን ይጠብቁን። 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ዛሬ ምሽት 2:00 ሰዓት ላይ በ#Tiktok እና #Instagram ገፃችን ይጠብቁን። 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

|ፍኖት_ምን_አዲስ |የትምህርት_ማስታወቂያ |ለመመዝገብ 👇👇👇 እዚህ_ይጫኑ 👆👆👆 |ትምህርት ክፍል
|ፍኖት_ምን_አዲስ |የትምህርት_ማስታወቂያ |ለመመዝገብ 👇👇👇 እዚህ_ይጫኑ 👆👆👆 |ትምህርት ክፍል

#የአንድነት ጉባኤ #ነገ ጠዋት 3:30 -5:30
#የአንድነት ጉባኤ #ነገ ጠዋት 3:30 -5:30

#የአንድነት (አርብ) ፀሎት መርኃግብር #ነገ 12:00 - 1:00
#የአንድነት (አርብ) ፀሎት መርኃግብር #ነገ 12:00 - 1:00

#ፍኖት_ምን_አዲስ #የትምህርት_ማስታወቂያ
#ፍኖት_ምን_አዲስ #የትምህርት_ማስታወቂያ

#ፍኖት_ምን_አዲስ #የህፃናትና_አዳጊዎች_የትምህርት_ማስታወቂያ
#ፍኖት_ምን_አዲስ #የህፃናትና_አዳጊዎች_የትምህርት_ማስታወቂያ

#የአንድነት ጉባኤ #ነገ ጠዋት 3:30 -5:30
#የአንድነት ጉባኤ #ነገ ጠዋት 3:30 -5:30