Setaweet (ሴታዊት)
Open in Telegram
Setaweet Movement aims to articulate Ethiopian feminism. The movement creates a space for dialogue, research and activism by Ethiopian women and men!🇪🇹 More info call +251118225451
Show more2 232
Subscribers
No data24 hours
+27 days
+330 days
Posts Archive
2 232
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
“ ከ4,000 በላይ ሴቶች ተደፍረዋል ” - የአማራ ክልል ሴቶች ማኀበር
የኢትዮጵያ ሴቶች ማኀበር ሴቶች ላይ እየደረሱ ናቸው የተባሉ ፈርጀ ብዙ ችግሮችን በተመለከተ በየክልሉ በዘርፉ የተሰማሩ ተቋማትን በመጋበዝ ትላንት ረቡዕ በአዲስ አበባ ኢሊሊ ሆቴል የውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር።
በዚህም ላይ ከተገኙት ባለድርሻ አካላት መካከል የአማራ ክልል ሴቶች ማኀበር አንዱ ነው።
በአማራ ክልል በ “ፋኖ” ታጣቂዎችና በመከላከያ ሠራዊት መካከል በየወቅቱ እያገረሸ የሚስተዋለውን የተኩስ ልውውጥ ተከትሎ በሴቶችና ሕጻናት ላይ የሚስተዋለው ሞት እየጨመረ መሆኑን፣ ሴቶችም ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀሎች እየተበራከቱ መሆኑን የክልሉ ሴቶች ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የክልሉን ሴቶች ማኀበር ወክለው የመጡ ወ/ሮ በላይነሽ ሽባባው ምን አሉ ?
➡ ከጤና ጋር ተያይዞ የእናቶች ሞት፣ የሕጻናት ሞት ከበፊቱ በጣም እየጨመረ መጥቷል።
➡ በጣም በርካታ ሴቶች ከጦርነቱ ጋር ተያይዞ ጥቃት እየደረሰባቸው ነው። አንደኛ ፍትህ የሚያገኙበት አጋጣሚም የለም። ሁለተኛ ደግሞ ከጦርነቱ ዘለው ወደ IDP center እንኳን ሲገቡ እዚያው ውስጥም መልሶ ጥቃት የሚያጋጥምበት ሁኔታ አለ።
➡ ሰላም አስካልተጠበቀ ድረስ ሴቶች ነገም፣ ከነገ በኋላም የጥቃቱ ሰለባ ናቸው። በአጠቃላይ እንደ አገራችን፣ እንደ አማራ ክልልም ሴቶች ጥቃት እየደረሰባቸው ያለው ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ ነውና የሴቶች አደረጃጀቶች ሰላምን ከማስጠበቅ አንጻር ጎልተው መውጣት አለባቸው።
➡ አማራ ክልል ራሱ የበፊቱን እንኳን ትተነው አሁን በሚስተዋለው ግጭት ብቻ ከ4,000 በላይ ሴቶች ተደፍረዋል። ስለዚህ በዋናነት ይህን ጥቃት ለማስቆም መስራት ያለብን ሰላሙ ላይ ነውና በተለይ የሴቶች አደረጃጀት ደግሞ በጋራ ሆነው መንግሥትን፣ ሌላውንም አካል በማወያየት ሰላሙ ላይ ብንሰራ የሴቶችን ጥቃት መቀነስ ይቻላል.
በትላንቱ መርሀ ግብር የተለያዩ ተቋማትን ወክለው የተገኙ ኃላፊዎች በበኩላቸው ማኀበራቱ ሁሉ በጸጥታ ወቅት የሚፈጸሙ ፆታዊ ጥቃቶችን በተመለከተ ቅንጅት በሠፍጠር ልዩ ትኩረት እንዲሰጥበት በውይይታቸው አንስተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተከታታይ የመረጃ ልውውጥ ያደርጋል።
መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የአዲስ አበባ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ኢዮብ ትኩዬ ነው።
@tikvahethiopia
2 232
Repost from AHRE( Association for Human Rights in Ethiopia)
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በትግራይ ክልል ያለውን የሰብዓዊ መብት ሁኔታ ተከታትሎ ይፋ ባደረገው ሪፖርት መሠረት አብዛኞቹ ወሲባዊ እና ፆታን መሠረት ያደረገ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች ጥቃቱ የተፈፀመባቸው በፕሪቶሪያ ከተፈረመው ስምምነት በፊት ቢሆንም፣ አሁንም የኤርትራ ወታደሮች እና የአማራ ኃይሎች ከሚቆጣጠሯቸው ቦታዎች የሚመጡ ሴቶች ወሲባዊ እና ፆታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች እንደተፈፀመባቸው ገልፀዋል። ጥቃቱ የተፈፀመባቸው ሴቶች የሕክምና፣ የሥነ ልቦና፣ የሕግ እና መልሶ የማገገሚያ አገልግሎት እጥረት እንደሚያጋጥማቸውም በሪፖርቱ ውስጥ ተጠቅሷል። በተጨማሪም፣ የጥቃቱ ሰለባ የሆኑ ሴቶች ከማኅበረሰቡ የሚደርስባቸውን መገለል ፍራቻ ጥቃቱን ሪፖርት እንደማያደርጉ እና ወደጤና ተቋማትም እንደማይሄዱ ሪፖርቱ ያብራራል።
ወሲባዊ እና ፆታን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶችን የፈፀሙ አካላትን ለሕግ የማቅረብ እና ተጠያቂ የማድረግ ሥራ የሚገባው ትኩረት ተሰጥቶት ወሲባዊ እና ፆታን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶችን እንደጦር መሣሪያ መጠቀምም ሊያስቆም የሚያስችል የእርምት እርምጃ ሊወሰድ ይገባል። ግብረሰናይ ድርጅቶችም በሁሉም ግጭት በተካሄደባቸው እና በሚካሄድባቸው አካባቢዎች አንገብጋቢ የሆነውን እገዛ በማቅረብ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል።
2 232
Full video out NOW!
Ambassador Genet Zewde is an academician, politician, a former Member of Parliament and the first woman to hold a minister position at the Ministry of Education in Ethiopia. She was active in the student’s struggle in 1960s and 70s. As a high school student, she made a name for herself by challenging the school administration to let girls take the national exam that allows students join a university.
In this exclusive interview, she tells us her story and encourages the younger generation to persevere and fight for democracy and women's rights, and not to give up standing up for their beliefs.
We are only getting started!
2 232
Community Empowerment for Local Development (CELD), Adoye Center for Ethiopian Women Empowerment, Fratello Humanitarian Association, and Birmaji Youth Association, as well as other organizations, called for swift resumption of talks between the government and OLA and urged the government and urged the inclusion of women in negotiations.
https://addisstandard.com/news-women-led-civil-societies-in-ethiopia-call-for-sustained-dialogue-with-armed-groups-inclusion-of-women-in-peace-talks/
2 232
Watch Saba Gebremedhin, director of NEWA, talking to EBS about workplace harassment https://www.youtube.com/watch?v=eLwVyowzAI0
2 232
The UN Secretary-General has released the Zero Draft of the CSW68 "Accelerating the achievement of gender equality and the empowerment of all women and girls by addressing poverty and strengthening institutions and financing with a gender perspective". In advance of CSW68 in March, NGOs and civil society are encouraged to submit input on language for incorporation into the final Outcome Document.
https://mcusercontent.com/eb520eecfe82a5bf0d814ea1f/files/4d3d9e08-edbc-6b5f-7a6c-b2405e117758/CSW68_Zero_Draft_2.5.24_.pdf?mc_cid=220f74c626&mc_eid=56752fba5e
2 232
According to UNICEF's research, 25 million women and girls have undergone FGM in Ethiopia and 5 in 10 adolescent girls aged 15 to 19 years experience female genital mutilation/cutting (2020). February 6th marks our continued commitment to ending FGM/C in Ethiopia. #zerotolerance #endfgm
Image credit: UNICEF
2 232
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Hawassa
" ተማሪው ላይ ጾታዊ ትንኮሳ ፈጽሟል " በሚል #የተጠረጠረው ርእሰ መምህር በቁጥጥር ስር እንዳሚገኝ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።
በሀዋሳ ከተማ ታቦር አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወስጥ አንዲት ተማሪ ርእሰ መምህሯን " ጾታዊ ትንኮሳ ፈጽሞብኛል " በሚል ክስ መመስረቷን ተከትሎ ፖሊስ ተጠርጣሪዉን ግለሰብ ከስራ ገበታዉ ድረስ በመሄድ በቀን 20/05/2016 ዓ/ም በቁጥጥር ስር ማዋሉን ለማወቅ ተችሏል።
የሀዋሳ ከተማ ሴቶችና ህጻናት ቢሮ ሀላፊዋ ወይዘሮ ፍሬህይወት ወልደጻዲቅ ጉዳዩን በተመለከተ ከቲክቫህ ኢትዮጽያ የሀዋሳው አባል ጋር በነበራቸዉ ቆይታ ፤ " የተጠቂዋ ቤተሰቦች ጉዳዩን ይዘዉ ቅድሚያ ለማመልከት የመጡት ወደእኛ ቢሮ ነበር " ያሉ ሲሆን ጉዳዩን ወደ ህግ እንዲወስዱት በማድረግ ማንኛዉንም የህግ ከለላና አስፈላጊ ድጋፎችን ሊሰጡ እንደሚችሉ ቃል ገብተው አንዳበረታቷቸው ገልጸዋል።
ከዚህ በኋላ ክሱ ተመስርቶ ተጠርጣሪዉ በህግ ጥላ እንደዋለና ምርመራ እየተደረገ መሆኑን የገለፁት ኃላፊዋ " አሁን ላይ የሀዋሳ ከተማ ትምህርት መምሪያ መረጃዎችን አጠናክሮ የክስ ሂደቱን ከኛ ጋር ለመደገፍ እንቅስቃሴ ላይ ነው " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዉ በትምህርት ቤት ውስጥ ሲያዝ የነበረዉን ሁኔታ እና ድርጊቱን በተመለከተ የትምህርት ቤቱ አስተዳደር የሚያውቀዉ ነገር እንዳለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የትምህርት ቤቱ ምክትል ርእሰ መምህር አቶ ሀንዳሞ ፈይሳ ፤ በወቅቱ ተጠርጣሪው ለጥያቄ ትፈለጋለህ ተብለዉ መሄዳቸውን ፤ አሁን ላይ በህግ ቁጥጥር ስር ከዋሉ ሳምንት እንዳለፋቸው ገልጸዋል።
ክስ አቅራቢዋ ተማሪ ከትምህርት ገበታዋ ደጋግማ በመቅረቷ ምክንያት " ወላጅ አምጭ አታምጭ " በሚል ከሚመለከታቸዉ መምህራኖቿ እና ከተጠርጣሪው ርእሰ መምህር ጋር ስትጨቃጨቅ እንደነበር የሚያስታዉሱት አቶ ሀንዳሞ ፤ ይህ ጉዳይ ለእርሳቸውም ሆነ ለትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ #አስደንጋጭ እና ግራ ያጋባ መሆኑን አስረድተዋል።
ፖሊስ አስፈላጊዉን ማጣራት አድርጎ እዉነቱ ላይ እስኪደርስ እየጠበቁ መሆኑንም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የሐዋሳዉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነዉ።
@tikvahethiopia
2 232
Kenya femicide: why men fail to condemn deadly misogyny https://www.bbc.com/news/world-africa-68178445
2 232
ለሞት የሚዳርግ ጾታዊ ጥቃት አንዳንድ እውነታዎች #femicide #stopgbvethiopia
https://www.unwomen.org/en/news-stories/feature-story/2022/11/five-essential-facts-to-know-about-femicide
2 232
ለሞት የሚዳርግ ጾታዊ ጥቃት አንዳንድ እውነታዎች #femicide #stopgbvethiopia
https://www.unwomen.org/en/news-stories/feature-story/2022/11/five-essential-facts-to-know-about-femicide
2 232
The Institute of Ethiopian Studies is hosting a book talk with Prof. Siphokazi Magadla on her book 'Guerrillas and Combative Mothers: Women and Armed Struggle in South Africa'. Join this Friday at 10 am at AAU.
2 232
#NEWA #EWLA #SETAWEET #ehrdc #EWRA #AwSad #TERKANFI #AAWA #lhr #fsa #AHRE #Sara #ewdna #ACDD #Elida #WCDI #CARD #EID #EMWA #SWDA #GPRDO #FAWE #wise #CFID #AWA #GRWA #SEPWA #SWA #SoWA #AfWf #TWA #BGWA #SWERA #Mujejewa #CoC #SCD #DDTA #DDWF #HPWDA #Talita #Medhin #Mums for Mums
2 232
#NEWA #EWLA #SETAWEET #ehrdc #EWRA #AwSad #TERKANFI #AAWA #OWA #lhr #fsa #AHRE #Sara #ewdna #ACDD #Elida #WCDI #CARD #EID #EWMA #SWDA #GPRDO #FAWE #elrw #wise #CFID #nywse #NWWEO #AWA #GRWA #SEPWA #SWA #SoWA #AfWA #TWA #BGWA #SWERA #Mujejewa #SWDS #SoNSAC #MCDO #QWDA #CoC #SCD #DDTA #DDWF #RWPWDA #HPWDA #Talita #Medhin Harari #Mums for Mums
2 232
Repost from ATC NEWS
በኦሮሚያ ክልል፣ ቄለም ወለጋ ዞን፣ ደምቢ ዶሎ ከተማ በመማርያ ክፍል ውስጥ የክፍል ጓደኛቸውን በቡድን የደፈሩት ሁለት ተማሪዎች በእስራት ተቀጡ።
በደምቢ ዶሎ ከተማ የፋሲሎ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች የሆኑት ሰቦና ዲሪብሳ እና ኤቢሳ አድማሱ የክፍል ጓደኛቸውን በቡድን በመድፈራቸው አምስት ዓመት ከስድስት ወር ጽኑ እስራት ተፈርዶባቸዋል።
የፍርድ ሂደቱን የመሩት ዳኛ ምትኩ ወዳጆ “ተበዳይዋ ተማሪ ስትሆን የወንጀል ድርጊቱን የፈጸሙትም የክፍል ጓደኞቿ ናቸው” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ይህ ወንጀል የተፈጸመው ተበዳይዋ የውጤት ስህተት ለማስተካከል ሰኔ 9/2015 ዓ. ም. ትምህርት ቤት በሄደችበት ወቅት ነው።
“ውጤት ለማስተካከል ትምህርት ቤት በሄደችበት ወቅት ብዙ ተማሪ አለመኖሩን እንደ አጋጣሚ ተጠቅመው እያጫወቱ ወደ ክፍል ውስጥ ካስገቧት በኋላ በር ዘግተው የመድፈር ወንጀል ፈጽመውባታል” ብለዋል ዳኛ ምትኩ ወዳጆ።
ሁለተኛ ተከሳሽ የክፍሉን በር ሲዘጋ የመጀመሪያ ተከሳሽ የመድፈር ወንጀል ፈጽሟል። ከአንደኛ ተከሳሽ በመቀጠልም ሁለተኛው ተከሳሽ በድጋሚ የወንጀል ድርጊቱን በ10ኛ ክፍል ተማሪዋ ላይ መፈጽሙን የሰዮ ወረዳ ፍርድ ቤት መዝገብ ያሳያል።
“ወንጀሉ ሲፈጸም ልጅቷ የድረሱልኝ ጩኸት ስታሰማ ነበር። ነገር ግን በወቅቱ ከባድ ዝናብ እየዘነበ ስለነበረ ድምጿን ማንም አልሰማም” በማለት ዳኛው ጨምረው ተናግረዋል።
ተበዳይዋ የወንጀል ድርጊቱ ከተፈጸመባት በኋላ ወደ መኖሪያ ቤቷ ሄዳ መቆየቷን ዳኛው ይናገራሉ። “ከዛ በኋላ ግን ሕመም ሲሰማት የደረሰባትን ለርዕሰ መምህሩ ተናገረች” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ከዚያም የደምቢዶሎ ከተማ ፖሊስ ምርመራ አካሂዶ ዐቃቤ ሕግ በሰዮ ወረዳ ፍርድ ቤት ክስ መመሥረቱን ዳኛ ምትኩ ይናገራሉ።
ሁለቱ ተማሪዎች የተከሰሱበት አንቀጽ በ1996 በወጣው አገሪቱ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 620/1 መሠረት ከአምስት እስከ 15 ዓመት እንደሚያስቀጣ ገልጸዋል። ተከሳሾች የወንጀል ማቅለያ ከግምት ገብቶላቸው ፍርድ ቤቱ ታኅሣሥ 25/2016 ዓ. ም. በዋለው ችሎት ሁለቱ ተከሳሾች እያንዳንዳቸው በአምስት ዓመት ከስድስት ወር በእስራት እንዲቀጡ መወሰኑን ተናግረዋል።
“እነዚህ ወጣቶች ከዚህ ቀደም ወንጀል ፈጽመው ስለማያውቁ እንደ ቅጣት ማቅለያ ተወሰዶላቸዋል። በዐቃቤ ሕግ በኩልም ቅጣት ማጠናከሪያ ተብሎ የቀረበ አስተያየት ስለሌለ ሌሎችን ያስተምራል የተባለ ቅጣት” መተላለፉን ዳኛው ተናግረዋል።
#ቢቢሲ
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
2 232
Repost from EHRDC_Update
የማህበራዊ ሚዲያዎች የንግድ ተቋማት ፣ የተቋማቱ ባለቤቶችን፣ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሠራጩ መረጃዎች አዘጋጆችን፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን እና የመንግስት አካላትን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት አፋጣኝ በሆነ ሁኔታ በማህበራዊ ሚዲያ እየተስፋፋ የመጣውን የፆተኝነት እና የተሳሳቱ አሉታዊ መልዕክት ያላቸው ሴት ተኮር ይዘቶች እና ይዘቶቹን ተከትሎ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስዱ ለማሳሰብ የተደረገ ጥሪ።
ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ:https://ethdefenders.org/%E1%8B%A8%E1%8C%8B%E1%88%AB-%E1%8C%8B%E1%8B%9C%E1%8C%A3%E1%8B%8A-%E1%88%98%E1%8C%8D%E1%88%88%E1%8C%AB/
2 232
Repost from EHRDC_Update
የማህበራዊ ሚዲያዎች የንግድ ተቋማት ፣ የተቋማቱ ባለቤቶችን፣ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሠራጩ መረጃዎች አዘጋጆችን፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን እና የመንግስት አካላትን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት አፋጣኝ በሆነ ሁኔታ በማህበራዊ ሚዲያ እየተስፋፋ የመጣውን የፆተኝነት እና የተሳሳቱ አሉታዊ መልዕክት ያላቸው ሴት ተኮር ይዘቶች እና ይዘቶቹን ተከትሎ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስዱ ለማሳሰብ የተደረገ ጥሪ።
ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ:https://ethdefenders.org/%E1%8B%A8%E1%8C%8B%E1%88%AB-%E1%8C%8B%E1%8B%9C%E1%8C%A3%E1%8B%8A-%E1%88%98%E1%8C%8D%E1%88%88%E1%8C%AB/
