en
Feedback
የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

Open in Telegram

ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡ አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን! ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን! ♻: https://api.whatsapp.com/send?phone=

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

Channel የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official) (@sultan_54) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 480 subscribers, ranking 6 647 in the Religion & Spirituality category and 2 509 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 480 subscribers.

According to the latest data from 13 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -128 over the last 30 days and by 1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 12.92%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 5.94% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 1 741 views. Within the first day, a publication typically gains 800 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 12.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡ አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን! ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን! ♻: https://api.whatsapp.com/send?p...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 14 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

13 480
Subscribers
+124 hours
-107 days
-12830 days
Posts Archive
«ለኢብኑል ሙባረክ (አላህ ይዘንላቸውና)፦ “ከዕድሜህ አንድ ቀን ብቻ ነው የቀረው ቢባልህ ምን ታደርግ ነበር?” ተብሎ ተጠየቁ፤ እሳቸውም፦ “ሰዎችን አስተምር ነበር” ብለው መለሱ።»ምንጭ: በበይሀቂ (አል-መድኸል [2/45]) የተዘገበ።

ዐብላህ ኢብኑ መስዑድ እንዲህ ብለው ነበር "
ማንም ሰው በዲኑ ጉዳይ ላይ ሌላውን በጭፍን አይከተል።”
የታላቁ ሶሓቢይ አብዱላህ ኢብኑ መስዑድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ንግግር እጅግ ጥልቅና ሁሌም ሊታወስ የሚገባ መሠረታዊ መመሪያ ነው። በኢስላም መቼም ቢሆን እውነት በሰዎች ማንነት አይመዘንም፤ ይልቁንም ሰዎች በእውነትና በማስረጃ ይመዘናሉ እንጂ። ማንኛውንም ግለሰብ ከማስረጃ በላይ ማስቀደም ለጭፍን ወገንተኝነትና ለጥፋት በር ከፋች ነው።

# ስለ “ዐቂቃህ” ሕግጋትና አሕካሞች የተዘጋጀ አጭር ማጠቃለያ ## 1. መግቢያ እና ትርጓሜ * ዐቂቃህ ማለት ምን ማለት ነው? ለወንድ ወይም ለሴት ልጅ መወለድ ምስጋናን ለመግለጽ ሲባል የሚታረድ ልዩ የ”እርድ” ዓይነት ነው። * የስያሜው ምስጢር፦ * “ዐቂቃህ” የሚለው ስያሜ የተሰጠበት ምክንያት፤ የሚታረደው እንሰሳ የምግብ፣ የመጠጥና የአየር ማስገቢያና ማስተላለፊያው (ጉሮሮው) ስለሚቆረጥ ነው። * በተጨማሪም “ተሚማህ” የሚል ስያሜ አለው፤ ይህም ዐቂቃህ የተደረገለት ልጅ ሥነ-ምግባሩ የተሟላ ይሆናል ከሚል እምነት የተነሳ ነው። ## 2. የ“ዐቂቃህ” ሸሪዓዊ ብይን (ሑክም) * ዐቂቃህ በሸሪዓዊ ፍርድ “ሱናህ” (የተወደደ) የሚለውን ቦታ ይይዛል። * ነገር ግን አቅም ያለው ሰው ሳይፈጽመው ቢቀር ይጠላል፤ እንዲያውም “ዋጂብ” (ግዴታ) ነው ያሉ ዑለማዎችም አሉ። * ዐቂቃን አስመልክቶ ከሰላሳ በላይ ሐዲሶች ተዘግበዋል። ነቢዩ (ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦ > “ልጅ የተወለደለትና ለእርሱ ማረድ (መስዋዕት ማድረግ) የፈለገ ሰው ይፈጽም።” *(አቡ ዳውድ)* > * የሐዲሱ ጽንሰ-ሐሳብና ጥቅሞች፦ * ዐቂቃ የተደረገለት ልጅ ደስተኛና ነፃ ይሆናል። * ወላጅና ኃላፊ የሆኑ ሰዎች ለልጁ ዐቂቃ ካላደረጉ፣ ልጁ በዕለተ-ቂያማህ ለቤተሰቡ አማላጅ (ሸፋዓ) አይሆንም። * ዐቂቃህ ከልጁ ጋር የማይፋታ እዳ መሆኑን ለመጠቆም በሐዲሱ ላይ *“እያንዳንዱ ህጻን በዐቂቃው የታገተ ነው”* የሚል የአፅንኦት ቃል ተጠቅሷል። ## 3. የእንስሳቱ ዓይነት፣ ዕድሜና የዕርድ ብዛት ### ሀ. ለወንድ እና ለሴት ልጅ የሚታረደው መጠን፡ * ለወንድ ልጅ፦ ሁለት በግ። (ሁለቱ በጎች በአካል መጠናቸውና በዕድሜያቸው ተቀራራቢ ቢሆኑ ተመራጭ ነው) ። * ለሴት ልጅ፦ አንድ በግ። > ነቢዩ (ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም)) እንዲህ ብለዋል፦ *“ስለ ወንድ ልጅ እኩል የሆኑ ሁለት በጎች፣ ስለ ሴት ልጅ ደግሞ አንድ በግ ይታረዳል::”* *(አቡ ዳውድ/አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል)* > ### ለ. ለዐቂቃ የሚሆኑ እንስሳትና የዕድሜ መስፈርት፡ ለዐቂቃ የሚሆኑት የቀንድ ከብቶች (የቤት እንስሳት) ሲሆኑ የእድሜ ገደባቸው እንደሚከተለው ነው፦ | የእንስሳው ዓይነት | ሊኖረው የሚገባው አነስተኛ ዕድሜ | |---|---| | ግመል | 5 ዓመት የሞላው | | በሬ / ላም | 2 ዓመት የሞላው | | ፍየል | 1 ዓመት የሞላው | | በግ | 6 ወር የሞላው | ## 4. የዐቂቃ ጊዜና ሥነ-ሥርዓት * የመታረጃው ጊዜ፦ ዋናው ሱናው ህጻኑ በተወለደ በሰባተኛው ቀን ማረድ ነው። * *ምሳሌ፦* ልጁ እሑድ ከተወለደ ዐቂቃው ቅዳሜ ቀን ይሆናል። * አስፈላጊ ማሳሰቢያ፦ ዐቂቃ ማለት እርድ የተፈፀመበት ዕለት እንጂ ሥጋው የተበላበት ቀን ማለት አይደለም። (ስለዚህ በሰባተኛው ቀን አርዶ ሥጋውን በሌላ ቀን ማዘጋጀትና መጋበዝ ይቻላል)። * አስፈላጊ ዚክር፦ በሚታረድበት ጊዜ በልዩ ሁኔታ በአፍ የሚባል የተለየ ዚክር የለም፤ ባለቤቱ “በልቡ ዐቂቃ መሆኑን ነይቶ” “ቢስሚላህ አላሁ አክበር” በማለት ያርዳል። ## 5. የሥጋ ክፍፍልና ማኅበራዊ ጉዳዮች * የሥጋው አጠቃቀም፦ ለራስ (ለቤተሰብ ብቻ) መመገብ፣ ወይም ጓደኞችንና ዘመዶችን ጠርቶ መጋበዝ፣ አሊያም ለድሆች በሰደቃ መልክ ማከፋፈል ይቻላል። * ዋና ማሳሰቢያ፦ የበጉን ዋጋ (ክፍያ) ለሌላ ሰው በሰደቃ መልኩ ሰጥቶ “አርድልኝ” ማለት አይፈቀድም። ምክንያቱም ባለቤቱ ራሱ (ወይም ወኪሉ) በእጁ ደም በማፍሰስ ወደ አላህ ሊቃረብ ስለሚገባ ነው። * ለተጋባዦች ዐቂቃ መሆኑን በግልጽ መናገር ግዴታ ባይሆንም፣ ቢነገራቸው ግን ለልጁ ዱዓእ ሊያደርጉለት ስለሚችሉ የተሻለ ነው። (ነገር ግን ካበላ በኋላ “ዱዓእ አድርጉ” ብሎ መጠየቅ የለበትም) ። ## 6. የተለያዩ ወሳኝ አሕካሞች (ሕግጋት) * በተለያዩ ቀናት ማረድ፦ ሁለት በግ በአንዴ ማግኘት ያልቻለ ሰው፣ አንዱን ካገኘ ማረድ ይበቃለታል፤ ሁለቱን በጎች በተለያዩ ቀናት ማረድ ይፈቀዳል። * የእናት ሚና፦ ወላጅ አባት በሕይወት ከሌለ፣ እናት አባትን ወክላ ማረድ ወይም ማሳረድ ትችላለች። * ካደገ በኋላ ማረድ፦ ልጅ ዐቂቃ ሳይደረግለት ካደገ፣ የአባት ግዴታ/ሱና ቢሆንም እንኳ ልጁ ለራሱ ማረድ ይፈቀድለታል። * ስለ ቅርጫ፦ ለዐቂቃ በሚታረደው እርድ ላይ ከአንድ በላይ ሰው ሆኖ በቅርጫ መካፈል አይቻልም። * ስለ አጥንት ስባሪ፦ አጥንት ሳይሰባበር መታረድና መበለት አለበት የሚሉ ከፊል ዓሊሞች አሉ። ይህንንም የሚያደርጉት “የልጁ ዕድል (ዕጣ ፈንታ) እንዳይሰባበር” በሚል መልካም ተስፋና ምኞት ነው። ሆኖም ለዚህ አመለካከት ሰሒሕ (ትክክለኛ) የሆነ መረጃ ማቅረብ አይቻልም። ## ፯. በ“ኡድሒያ” እና በ“ዐቂቃህ” መካከል ያለው ልዩነት ሁለቱን አጣምሮ በአንድ እርድ መነየት አይቻልም (በአልባኒ ፈትዋ መሠረት)። ዋና ዋና ልዩነቶቻቸውም የሚከተሉት ናቸው፦ 1. የሥጋው አዘገጃጀት፦ የዐቂቃ ሥጋ ተቀቅሎ (ተሰርቶ) ማከፋፈል ወይም መጋበዝ ተመራጭ ነው። 2. ስለ አጥንት፦ በዐቂቃ ላይ (በከፊል ዓሊሞች ዘንድ) አጥንት አለመስበር ይወደዳል። 3. ስለ ቅርጫ፦ በኡድሒያ ላይ በግመልና በበሬ ቅርጫ የሚፈቀድ ሲሆን፣ በዐቂቃ ላይ ግን በጋራ መታረድ (ቅርጫ) በፍጹም አይቻልም። > ማጠቃለያ፦ ይህ ጥናት በተቻለ መጠን ዋና ዋና ነጥቦችን ለማሰባሰብ የተሞከረበት ሲሆን፣ በርዕሰ ጉዳዩ ላይ ይበልጥ ሰፊ ዕውቀት ለማግኘት ሌሎች ተዛማጅ የፊቅህ መጽሐፍትን ማንበብ ይመረጣል። > ወላሁ አዕለም (አላህ ይበልጥ አዋቂ ነው) > * ዝግጅት፦ አቡ ሑዘይፋ ሱልጣን ኸዲር >

ስለ ዐቂቃ ምን.pptx7.10 KB

​“ቁርኣንን አንቡ፤ እርሱ በቂያማ እለት ለባልደረቦቹ (ለሚያነቡትና ለሚተገብሩት) አማላጅ ሆኖ ይመጣልና።” ​(ሐዲሱን ኢማም ሙስሊም ዘግበውታል)
“ቁርኣንን አንቡ፤ እርሱ በቂያማ እለት ለባልደረቦቹ (ለሚያነቡትና ለሚተገብሩት) አማላጅ ሆኖ ይመጣልና።”
(ሐዲሱን ኢማም ሙስሊም ዘግበውታል)

ኢላሂ! እኛ እየሞከርን ነውና ወደፈለግንበት አድርሰን፤ ኃጢአት እንሰራለን እና እባክህ ማረን፤ እንፈራለንና አማንን ስጠን፤ እንሰናከላለንና ቀና አድርገን።

اللهم إننا نحاول فأوصلنا وإننا نذنب فآغفرلنا وإننا نخاف فآمنا، وإننا نتعثر فأقمنا.

🖋️ አንዲት ኒቃብ የለበሰች ሙስሊም ሴት በጀርመን አገር በሚገኝ አንድ የገበያ ማዕከል ውስጥ እየሸመተች ነበር። የሚያስፈልጋትን ዕቃ ገዝታ ከጨረሰች በኋላ፣ የገዛችበትን ሂሳብ ለመክፈል ወደ መክፈያ
🖋️ አንዲት ኒቃብ የለበሰች ሙስሊም ሴት በጀርመን አገር በሚገኝ አንድ የገበያ ማዕከል ውስጥ እየሸመተች ነበር። የሚያስፈልጋትን ዕቃ ገዝታ ከጨረሰች በኋላ፣ የገዛችበትን ሂሳብ ለመክፈል ወደ መክፈያ ማሽኑ (ካሽየሩ) አመራች። ከመክፈያ ሳጥኑ በስተጀርባ የተቀመጠችው ሰራተኛ ሂጃብ ያላደረገችና የዓረብ ዝርያ ያላት ሴት ነበረች፤ ኒቃብ የለበሰችውን እህት በንቀት ዓይን ከተመለከተቻት በኋላ፣ የገዛቻቸውን ዕቃዎች በግልጽ በሚታይ ንዴት ጠረጴዛው ላይ እያጋጨች መቁጠር ጀመረች። ኒቃብ የለበሰችው እህት ግን ምንም ዓይነት ምላሽ ሳትሰጥ በጥንካሬና በዝምታ ተረጋግታ ቀጠለች፤ ይህ ሁኔታ የሰራተኛዋን ንዴት ይባስ አባባሰው። በመጨረሻም ትንኮሳ በሞላበት ድምፅ እንዲህ አለቻት፦ “እኛ እዚህ ጀርመን ውስጥ በቂ ችግርና ቀውስ አለብን፤ ያንቺ ኒቃብ ደግሞ ከችግሮቹ አንዱ ነው! እኛ እዚህ ያለነው ለንግድ እንጂ ሃይማኖትን ወይም ታሪክን ለማሳየት አይደለም። ሃይማኖትሽን መለማመድ ወይም ኒቃብ መልበስ ከፈለግሽ፣ ወደ ሀገርሽ ተመልሰሽ እዚያ የፈለግሽውን ማድረግ ትችያለሽ።” ኒቃብ የለበሰችው እህት የገዛቻቸውን ዕቃዎች ወደ ቦርሳዋ መክተቷን አቆመችና በዝምታ ተመለከተቻት… ከዚያም ፊቷ ላይ የነበረውን ኒቃብ ገለጥ አደረገችው፤  ሰማያዊ ዓይን ያላት፣ ፀጉረ ወርቅ (ብላንድ) ጀርመናዊት ነበረች። በመረጋጋትም እንዲህ አለቻት፦ “እኔ አባቴም አያቴም (ስር መሰረቴ) እውነተኛ ጀርመናዊት ነኝ… ይህ ደግሞ የኔ እስልምና ነው… ይህችም የኔ ሀገር ናት… እናንተ ግን ዲናችሁን ሸጣችሁት… እኛ ደግሞ ገዛነው።”

የእለቱ መልክት የአላህ መልክተኛ ﷺ ካሉት በላይ አትጨምር! የኢማም አሕመድ ኢብኑ ሐንበል ልጅ ዐብዱላህ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦ «እኔና አባቴ በመስጂድ ውስጥ እያለፍን ነበር፤ በዚህ መሀል አንድ ተራኪ (ቀሳስ) “ሐዲሠ ኑዙልን” (አላህ ወደ ቅርቢቱ ሰማይ ስለመውረዱ የሚገልጸውን ሐዲሥ) ሲያወራ ሰማነው። እንዲህም አለ፦ “የሸዕባን ወር ግማሽ ሌሊት (ኒስፉ ሸዕባን) በሚሆንበት ጊዜ አላህ (ዓዘ ወጀል) ያላንዳች መወገድ (ከቦታው ሳይለቅ)፣ ያላንዳች መዘዋወር፣ ያላንዳች መለዋወጥና ሁኔታው ሳይቀየር ወደ ቅርቢቱ ሰማይ ይወርዳል”። ​በዚህ ጊዜ አባቴ (ኢማም አሕመድ) ከንዴት የተነሳ ተንቀጠቀጡ፣ ቀለማቸውም ቢጫ ሆነ (ፊታቸው ተለወጠ)፣ እጄንም ያዙኝ፤ እኔም እስኪረጋጉ ድረስ ያዝኳቸው። ከዚያም፦ “ወደዚህ አስመሳይ (ያለ እውቀት ወደሚዘባርቀው ሰው) ውሰደኝ” አሉ። ልክ እሱ ጋ ሲደርሱ እንዲህ አሉት፦ “አንተ ሰውዬ! የአላህ መልክተኛ ﷺ ከአንተ ይበልጥ ለጌታቸው (ለአላህ) ክብር ተቆርቋሪ ነበሩ፤ የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዳሉት ብቻ በል (ከራስህ ፍልስፍና አትጨምር)፤፤” ከዚያም ዘወር ብለው ሄዱ።» ​📔 [አል-ኢቅቲሷድ ፊ አል ኢዕቲቃድ — ሊዐብዱል ገኒይ አል-መቅዲሲ (21)]

📚 قال الإمام ابن القيم (رحمه الله) : ((فإن للإيمان فرحة وحلاوة ولذاذة في القلب ، فمن لم يجدها فهو فاقد للإيمان أو ناقصه)). 📔 الرسالة التبوكية (7) ••❥❥✺•✿•✺❥❥•• 📚 ኢማም ኢብኑል ቀዪም (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦ > ኢማን በልብ ውስጥ ደስታ፣ ጣፋጭ ቃና እና እርካታ አለው፤ ይህንን ያላገኘ ሰው ወይ ኢማን የሌለው ወይ ኢማን የጎደለው ነው፤፤)) > 📔 አር-ሪሳላህ አት-ተቡኪያህ (7) ••❥❥✺•✿•✺❥❥••

ዓብደላህ ኢብኑል ሙባረክ እንዲህ ተጠየቁ፦ 'ዑመር ኢብኑ ዐብደልዓዚዝ ይበልጣል ወይስ ሙዓዊያ?' እርሳቸውም እንዲህ ሲሉ መለሱ፦ 'ሙዓዊያ ከአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ጋር በተሳተፈባቸው በአንዳንዶቹ የውጊያ አውደ ግንባሮች ላይ ሳለ ወደ አፍንጫው የገባው አቧራ እንኳ ከዑመር ኢብኑ ዐብደልዐዚዝ ይበልጣል።'"(ምንጭ፦ አል-ሁጃ ፊ በያኒል ሙሐጃ [2/377] በአቡ ቃሲም አል-አስበሃኒ የተዘጋጀ)

> አካልህ ቢቆራረጥ እንኳ የጠዋትና የማታ አዝካሮችን አትተው! በፍጹም እንዳትተው። > ከምሽት ዚክሮች መካከል አንዱን እንኳ ብትል እንኳ አድርገው። ለምሳሌ፦ 'በስሚላሂለዚ ላ የዱሩ መዓ ኢስሚሂ ሸይኡን ፊል አርዲ ወላ ፊ አስ–ሰማኢ ወሁወስሰሚኡል ዓሊም' (በስሙ በምድርም ሆነ በሰማይ ምንም ነገር የማይጎዳውን በአላህ ስም እጀምራለሁ፤ እርሱም ሰሚውና አዋቂው ነው) የሚለውን ዱአ ብቻ ብትል እንኳ የጠዋትና የማታ ዚክርን እንዳደረግክ ይቆጠርልሃል። በምሽትም እንዲሁ። > የመጨረሻው ደግሞ ከመተኛት በፊት የሚደረጉ ዚክሮች ናቸው። ከመተኛትህ በፊት እነዚህን ማውሻዎች ሳታደርግ በፍጹም እንዳትተኛ። > አንዲት ዚክር ብቻ እንኳ ብትሆን፤ ለምሳሌ፦ 'አስተግፊሩላሀለዚ ላ ኢላሀ ኢላ ሁወል ሀዩል ቀዩሙ ወአቱቡ ኢለይህ' (ያ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለውን፣ ህያውና ሁሉን ቻይ የሆነውን አላህ ምህረት እለምነዋለሁ፤ ወደ እርሱም እመለሳለሁ) ብትል ምን እንደሚሆን ታውቃለህ? > ከጦርነት ሜዳ የሸሸህ እንኳ ብትሆን፣ ወይም የወነጀልከው ወንጀል የዚህችን ዓለም አሸዋ ያህል የበዛ ቢሆን እንኳ አላህ ወንጀሎችህን በሙሉ ይምርሃል። > እና ይሄ ከባድ ነው? እንግዲያውስ ከአላህ ጋር ኑር!" >

"ከከሀዲያን እና ከቢድዓ ባለቤቶች ጋር በአደባባይ ወይም በየቲቪ ቻናሎቹ የሚደረጉ ይፋዊ ክርክሮች፤ ይህ ከሰለፎች  የዳዕዋ መንገድ ነውን? ውጤቱስ ምንድን ነው?! ይህንን በተመለከተ፤ ከሰለፎች (አላህ ይዘንላቸውና) በሰፊው የተነገረውና የታወቀው መንገድ፡ ከቢድዓ ባለቤቶች ጋር ከመቀማመጥ፣ እነሱን ከመስማት፣ ከእነሱ ጋር ከመከራከርና ክርክር ከመግጠም መራቅ ነው። ለዚህም ምክንያቱ፦ * አንደኛ፦ ክርክር ልብን ያደክማል፣ ቂምና በቀልንም ያወርሳል። * ሁለተኛ፦ ሰሚው  (ሰፊው)ማህበረሰብ እውነቱ የትኛው እንደሆነ መለየት ላይችል ይችላል። በተለይም የቢድዓው ባለቤት አቀራረቡ የተዋጣለትና አንደበተ ርቱዕ ከሆነ፣ እንዲሁም የሱናው ባለቤት ደግሞ የማስረዳት አቅሙ ደካማ ከሆነ፤ ይፋዊው ክርክር ለሰፊው ህዝብ ፈተና (ፊተና) መሆን ይጀምራል። ህዝቡም ጥመትን እውነት ነው ብሎ ሊከተል ይችላል። ስለዚህ ሰለፎች ይከለክሉ የነበሩት ለዚህ ነው።" "አላህ ይጠብቃችሁና፤ በዚህ ዘመን በሳተላይት የቲቪ ቻናሎች ላይ የሚደረጉ የክርክር መድረኮችን በተመለከተ፦ እነዚህ መድረኮች አብዛኛውን ጊዜ ከጥቅማቸው ይልቅ ጉዳታቸው ያመዝናል። ለምን ቢባል? * አንደኛ፦ ጥያቄዎችንና ጥርጣሬዎችን (ሹብሃቶችን) ወደማያውቁትና ንፁህ ወደሆኑት የሰፊው ህዝብ ልቦች ውስጥ ያስርጻሉ። አንድ ተራ ሙስሊም በቤቱ ተቀምጦ ሳለ፣ ከዚህ በፊት ሰምቶት የማያውቀውንና በጭንቅላቱ ውስጥ ጨርሶ ያልነበረን ጥርጣሬ (ሹብሃ) በነዚህ መድረኮች አማካኝነት እንዲሰማ ይደረጋል። ከዚያም ያ ጥርጣሬ ልቡ ውስጥ ይፈጠራል። በክርክሩ ላይ ለቀረበው ጥርጣሬ የተሰጠው ምላሽ በቂ ባይሆን ወይም ግልጽ ባይሆንለትስ?! ያ ሰው ጥርጣሬው ልቡ ውስጥ እንደታተመ ይቀራል ማለት ነው። ይህ ደግሞ ትልቅ አደጋ ነው። * ሁለተኛ፦ እነዚህ መድረኮች ለቢድዓ ባለቤቶችና ለጠማሞች የራሳቸውን መርዝና ጥመት የሚረጩበት ሰፊ መድረክና ነፃ ማስታወቂያ ይሆኑላቸዋል። መቼም ቢሆን ሊያገኙት የማይችሉትን ሰፊ ህዝብ በእነዚህ ቻናሎች አማካኝነት ያገኛሉ። ስለዚህ ትክክለኛውና ጥንቃቄ የተሞላበት መንገድ፡ እውነትንና ሱናን በራሱ ጥራቱና ውበቱ ለህዝቡ ማስተማር ነው። የጠማሞችን ጥርጣሬ ግን ስማቸውን ሳያነሱና መድረክ ሳይሰጧቸው፣ እውነቱን ጠንካራ በሆነ መረጃ በማብራራት ማፍረስ ይገባል።" ሸይኽ ዶ/ር ሳሊህ አስ-ሰንዲ

«አላህ (ሱብሓነሁ ወተዓላ) እንዲህ ይላል፦ "ከሥራም ወደሠሩት እንመጣለን፤ የተበተነም ትቢያ እናደርገዋለን።" *(ሱረቱ አል-ፉርቃን፡ 23)* ፉደይል የተባሉት ታላቅ ዓሊም ይህንን የቁርዓን አንቀጽ አስመልክተው ሲናገሩ፦ "ከማያስቡትም ከአላህ ዘንድ ለእነሱ ግልጽ ሆነላቸው።" *(ሱረቱ አዝ-ዙመር፡ 47)* እንዲህ አሉ፦ "መልካም ሥራዎችን የሠሩ መስሏቸው ነበር፤ ነገር ግን (በትንሣኤ ቀን) ሲያዩት ወንጀል ሆኖ አገኙት።" እነዚህ ሥራዎች (በውስጣቸው ለአአሏህ ብቻ ያልጠሩ) ጉድለት ያለባቸው ሥራዎች ናቸው። ለአላህ ብሎ የሚሠራ ይመስላል፤ ነገር ግን በእውነታው ለራሱ ስምና ዝና (ወይም ለሌላ ምድራዊ ጥቅም) ነው የሠራው። ለአላህ ብሎ በተገቢው መንገድ አላጠራውም። ይህ ሰው (በቂያማ ቀን) ወንጀል እንጂ መልካም ምንዳ አይኖረውም። እሱ ግን መልካም ሥራ የሠራ መስሎት ነበር። ለምን? ምክንያቱም ቀደም ሲል እንደጠቀስኩት ራሱን በትክክል አያውቅም ነበር። ራሱን በአግባቡ የሚያውቅና አላህ ከራሱ (ከነፍሱ) ክፋት እንዲጠብቀው የሚለምን ሰው፣ ነፍሱ አታታለውም። ይህ (የተሸወደው) ሰው ግን መልካም ሥራ የሠራ መስሎት ይመጣል፤ ነገር ግን በእውነቱ ለአላህ ብሎ አልሠራም፣ ለራሱ ስሜት ሲል ነው የሠራው። በዚህም ምክንያት የሠራው ሥራ ሁሉ "የተበተነ ትቢያ" (ዋጋ ቢስ) ሆኖ ይቀራል።»

"የተባሉትን ቃል ለወጡ" — የሲፋት ማዛባት አደገኝነት
አሰላም ዓለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ የአላህን ሱብሃነሁ ወተዓላ ባህሪያት (ሲፋት) የሚቀይሩና ትክክለኛ ትርጉማቸውን የሚያዛቡ የብድዓ (የፈጠራ) ሰዎች፤ የአላህ عز وجل የሚከተለው ቃል በእነሱ ላይ ይፈጸማል፦ > "እነዚያ የበደሉት ሰዎች የተባሉትን ቃል ካልሆነ ሌላ ቃል ለወጡ።" *(አል-በቀራህ፡ 59)* > * "አር-ራህማን ከዐርሹ በላይ ከፍ አለ (ኢስተዋ)" ሲባሉ፤ እነሱ ግን፦ "አይደለም፣ ተቆጣጠረ (ኢስተውላ)" አሉ። የተባሉትን ቃል ወደ ሌላ ቃል ለወጡ። * "ይልቁንም ሁለት እጆቹ የተዘረጉ ናቸው" ሲባሉ፤ እነሱ ግን፦ "አይደለም፣ (እጅ ማለት) ጸጋውና ችሮታው ነው" አሉ። የተባሉትን ቃል ወደ ሌላ ቃል ለወጡ። * "የጌታህም ፊት (ዛት) ቀሪ ነው" ሲባሉ፤ እነሱ ግን፦ "አይደለም፣ (ፊት ማለት) የጌታህ ማንነት (ዛት) ብቻ ነው" አሉ። የተባሉትን ቃል ወደ ሌላ ቃል ለወጡ። * "ጌታችን ወደ ቅርቢቱ ሰማይ ይወርዳል፤ ለክብሩና ለግርማ ሞገሱ በሚገባ ሁኔታ" ሲባሉ፤ እነሱ ግን፦ "አይደለም፣ ትዕዛዙ ወይም እዝነቱ ወይም ከመላእክቱ አንዱ መልአክ ነው የሚወርደው" አሉ። እነዚያ የበደሉት ሰዎች የተባሉትን ቃል ባልሆነ ሌላ ቃል ለወጡ። * "ጌታህም (ለመፍረድ) በመጣ ጊዜ" ሲባሉ፤ እነሱ ግን፦ "አይደለም፣ የጌታህ ትዕዛዝ መጣ" አሉ። በሌሎችም ማዛባቶቻቸው ሁሉ ላይ የአላህ عز وجل ቃል ይገጥማቸዋል፦ > "እነዚያ የበደሉት ሰዎች የተባሉትን ቃል ካልሆነ ሌላ ቃል ለወጡ።" > ወሰላሙ ዓለይኩም አሽይኽ ወሊድ አስ–ሱዐይዳን

የተከበሩ ዶክተር ሸይኽ አሕመድ ኢብኑ ጧሊብ በሸሪዓ እና ኢስላማዊ ጥናቶች ክፍል የዶክትሬት (PhD) ዲግሪያቸውን በከፍተኛ ማዕረግ ( Excellent) ከመጀመሪያ ደረጃ ክብር (First-Class H
የተከበሩ ዶክተር ሸይኽ አሕመድ ኢብኑ ጧሊብ በሸሪዓ እና ኢስላማዊ ጥናቶች ክፍል የዶክትሬት (PhD) ዲግሪያቸውን በከፍተኛ ማዕረግ ( Excellent) ከመጀመሪያ ደረጃ ክብር (First-Class Honors) ጋር በማግኘታቸው እንኳን ደስ አሎት እንላለን። ​አላህ ይጠብቃቸው፣ በእሳቸው (ዒልም) ሌሎችን ይጠቅም ዘንድ እመኛለሁ።

​"ቁርኣን ላይ ያሉ አሻሚ ነጥቦችን (ሙተሻቢሃትን) በመምዘዝ የሚከራከሯችሁ ሰዎች ወደፊት ይመጣሉ። እናንተ ግን በሱና ሞግቷቸው/ያዟቸው፤ ምክንያቱም የሱና ባለቤቶች የአላህን መጽሐፍ (ቁርኣንን) ይበ
"ቁርኣን ላይ ያሉ አሻሚ ነጥቦችን (ሙተሻቢሃትን) በመምዘዝ የሚከራከሯችሁ ሰዎች ወደፊት ይመጣሉ። እናንተ ግን በሱና ሞግቷቸው/ያዟቸው፤ ምክንያቱም የሱና ባለቤቶች  የአላህን መጽሐፍ (ቁርኣንን) ይበልጥ አዋቂዎች ናቸውና።" (ዑመር ኢብኑ አል ኸጧብ) — ዳሪሚይ የዘገቡት