የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)
ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡ አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን! ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን! ♻: https://api.whatsapp.com/send?phone=
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)
Channel የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official) (@sultan_54) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 503 subscribers, ranking 6 549 in the Religion & Spirituality category and 2 504 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 503 subscribers.
According to the latest data from 25 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 1 over the last 30 days and by -2 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 18.42%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 5.84% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 2 487 views. Within the first day, a publication typically gains 789 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 30.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡
አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን!
ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን!
♻: https://api.whatsapp.com/send?p...”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 26 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
"ዐብዱረዛቅ አል-በድር አባቱ ሸይኼ ነው፣ እሱ ደግሞ ተማሪዬ ነው፤ ዛሬ ግን እሱ ከእኔ ይበልጣል" ብለዋል።የሕይወት ታሪካቸውንና ትምህርቶቻቸውን ያስተዋለ ሰው አላህ የሰጣቸውን የብስለት አእምሮ፣ ጥበብና ቀጥተኛ አካሄድ በግልጽ ይመለከታል። እውቀትን ከተግባር፣ ዐቂዳን ደግሞ ነፍስን ከማጥራት(ተዝኪየቱ አን ነፍስ) ጋር ለማገናኘት ያላቸው ልዩ ትኩረት ይታያል፤ በዚህም የተነሳ የትምህርት መጃሊሶቻቸው በትህትና እና በሰኪና (በመረጋጋት) የተሞሉ ናቸው። በዒልማቸው በሳዑዲ ዓረቢያ ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ በርካታ ሕዝብ ተጠቃሚ ሆኗል። ታዋቂ ማብራሪያዎቻቸውና ትምህርቶቻቸው (ሸርሆች) ሸርሕ አል-ቀዋዒድ አል-ሙሥላ (شرح القواعد المثلى) ሸርሕ አል-ከሊም አጥ-ጦይብ (شرح الكلم الطيب) ሸርሕ ቀዋዒድ አል-አስማእ አል-ሑስና (شرح قواعد الأسماء الحسنى) ሸርሕ ሐሺየት ኢብን አቢ ዳውድ (شرح حاشية ابن أبي داود) የዋሲጢያህ፣ የሉምዐቱል ኢዕቲቃድ፣ የመሳኢል አል-ጃሂሊያህ እና የሌሎች ሰለፎች የዐቂዳ ኪታቦች ማብራሪያ። የሪያዱ አስ-ሷሊሒን፣ የተጅሪድ አስ-ሶሪሕ፣ የሙኽተሰር ሶሒሕ ሙስሊም እና የአርበዒን አል-ነወዊያህ ማብራሪያ። በስነ-ምግባርና በባህሪ ዙሪያ ጠቃሚ ትምህርቶች አሏቸው፤ ከእነዚህም፦ የአድ– ዳእ ወድ-ደዋእ ፣ የአኽላቅ ሐመለቲል ቁርዓን እና የዋቢል አስ-ሰዪብ ማብራሪያዎች። ታዋቂ መጽሐፎቻቸው ፦ ፊቅህ አል-አድዒያህ ወል-አዝካር (فقه الأدعية والأذكار) አል-ሐጅ ወተህዚብ አን-ኑፉስ (الحج وتهذيب النفوس) ተዝኪረቱል ሙእተሲ ሸርሕ ዐቂዳህ ዐብደልገኒ አል-መቅዲሲ (تذكرة المؤتسي) ዲራሰቱ አሠር አል-ኢማም ማሊክ ፊ ባብ አል-ኢስቲዋእ (دراسة أثر الإمام مالك) ተዕዚም አስ-ሶላት (تعظيم الصلاة) በሐዲስ፣ በፊቅህ፣ በዐቂዳና በስነ-ምግባር ዙሪያ የተሰሩ ምርምሮችና ጥናቶች። ፊቅህ አል-አስማእ አል-ሑስና (فقه الأسماء الحسنى) እነዚህና ሌሎች ጠቃሚ መጽሐፎች ያሏቸው ሲሆን፣ በቅርቡ መጽሐፎቻቸውና መልዕክቶቻቸው በሙሉ በአንድ ጠቃሚ ጥራዝ ተሰብስበው ታትመዋል። ማጠቃለያ፦ እሳቸው አላህ እውቀትንና ተግባርን፣ ማስረጃንና ርህራሄን፣ ሱናንና መልካም ስነ-ምግባርን በአንድ ላይ የሰበሰበላቸው ሸይኽ ናቸው። በመሆኑም ለአስተማሪ ዳዒና መካሪ ዓሊም ምርጥ ምሳሌ ናቸው። የእውቀት ፈላጊዎች ወደ መጽሐፎቻቸው እንዲዞሩ፣ ትምህርቶቻቸውን እንዲያዳምጡ እና ዐቂዳን በማረጋገጥ፣ ነፍስን በማጥራትና በመልካም አስተዳደግ ረገድ ካላቸው ጠንካራ አካሄድ እንዲጠቀሙ እንመክራለን። አላህ ሸይኹን ይጠብቃቸው፣ በእድሜያቸውና በእውቀታቸው ላይ በረከትን ያድርግላቸው፣ እስልምናንና ሙስሊሞችንም በእሳቸው ይጠቅም ዘንድ እንለምነዋለን።
"አላህ መሸጥን ፈቀደ፤ ወለድን ግን እርም አደረገ።" (አል-በቀራህ፡ 275)እንዲሁም አላህ እንዲህ ብሏል፦
"እናንተ ያመናችሁ ሆይ! እስከ ታወቀ ጊዜ ድረስ ባለ እዳ በተዋዋላችሁ ጊዜ ጻፉት።" (አል-በቀራህ፡ 282)ይህ ገዥ ዕቃው በሁለት የተለያየ ዋጋ ቀረበለት ማለት ነው፤ በጥሬ ገንዘብ (በካሽ) የሚከፈል ዋጋ እና በጊዜ ገደብ (በክሬዲት) የሚከፈል ዋጋ። ለምሳሌ የጥሬ ገንዘቡ ዋጋ 100 ነው እንበል፤ የጭልፊቱ ዋጋ ደግሞ 150 ነው፤ እሱም በዚያው በተቀመጡበት መጅሊስ ከቦታው ሳይበተኑ የክሬዲቱነረ (የ150ውን) መረጠ። ከዚያም ዕቃውን ይዞ ሄደ። በዚህ ጊዜ በእሱ እዳ ላይ 150 ዲናር በትክክልና በግልጽ ተቀምጦ ጸና። ይህ ዓይነቱ ሽያጭ ምንም ችግር የሌለበት ትክክለኛ ሽያጭ ነው። ምክንያቱም ገዢው በዚህ ወይም በዚያኛው ዋጋ ለመግዛት ምርጫ ተሰጥቶታል። ይህ ደግሞ በምንም መልኩ ከወለድ (ሪባ) ጋር አይገናኝም። ምክንያቱም ወለድ ማለት "ብርን በብር" (ገንዘብን በገንዘብ) ላይ ጨምሮ መሸጥ ማለት ነው። እዚህ ጋር ግን እየተሸጠ ያለው ዕቃ ነው፤ ዕቃን ደግሞ በጥሬ ገንዘብ ሲሆን በዚህ ዋጋ፣ በጊዜ ገደብ ሲሆን ደግሞ በዚያ ዋጋ መሸጥ ሙሉ በሙሉ የተፈቀደ ነው። እንዲሁም ይህ ሽያጭ ነቢዩ (ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም) ከከለከሉት "በአንድ ሽያጭ ውስጥ ሁለት ሽያጭ ማድረግ" (بيعتين في بيعة) ከሚለው ክልከላ ውስጥ አይገባም። ምክንያቱም እዚህ ጋር የተፈጸመው አንድ ሽያጭ ብቻ ነው። ሰውየው በሁለት አማራጮች መካከል ምርጫ ተሰጥቶት አንደኛውን መርጦ በአንዱ ላይ ብቻ ተስማምቶ ወጥቷልና።
የአላህ መልእክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ «የጠራችሁን ሰው ጥሪ ተቀበሉ (እሺ በሉ)፣ ስጦታን አትመልሱ፣ ሙስሊሞችንም አትምቱ።» (አህመድ ዘግበውታል፣ አልባኒም ሰሂህ ነው ብለውታል)የሐዲሱ ማብራሪያ (የግርጌ ማስተዋሻ) «የጠራችሁን ሰው ጥሪ ተቀበሉ»፦ ይህ የሰርግ ድግስም ይሁን ሌላ ማንኛውም ዓይነት ምግብ ላይ እንዲገኝ የጠራውን ሰው ጥሪ ምላሽ እንዲሰጥ የታዘዘበት ነው። «ስጦታን አትመልሱ»፦ ይህ ደግሞ ሁለተኛው ትዕዛዝ ሲሆን፣ የቀረበን ስጦታ ባለመመለስ መካከል ላይ ፍቅርና መተሳሰር እንዲኖር ያደርጋል። «ሙስሊሞችንም አትምቱ»፦ ይህ ሦስተኛው ትዕዛዝ ሲሆን፣ ያለ ምንም (ሸሪዓዊ ቅጣት) ወይም ያለ አግባብ ሙስሊሞችን ከመምታትና ከመበደል መቆጠብን ያዛል። መሠረቱ ግን ከእነሱ ጋር በቃልም ሆነ በተግባር በደግነትና በለስላሳነት መኖር ነው።
"ሰዎች ከሸሪዓዊ አውራዶች (የጠዋትና የማታ ዚክሮች) በዘነጉ ጊዜ፤ በእነሱ ላይ ጅን በዛባቸው፣ ተጫወተባቸውም (አላገጠባቸውም)።"• ሊቃኡል ባቢል መፍቱህ (197)
የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፦ "ሁለት ጸጋዎች አሉ፤ ከሰዎች አብዛኛዎቹ በእነሱ (በአጠቃቀማቸው) ይሸወዳሉ ፦ እነሱም ጤና እና ትርፍ ጊዜ ናቸው።" (ቡኻሪ ዘግበውታል)
