en
Feedback
የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

Open in Telegram

ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡ አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን! ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን! ♻: https://api.whatsapp.com/send?phone=

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

Channel የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official) (@sultan_54) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 431 subscribers, ranking 6 432 in the Religion & Spirituality category and 2 526 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 431 subscribers.

According to the latest data from 31 August, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -47 over the last 30 days and by 4 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 20.42%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 2 742 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 51.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡ አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን! ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን! ♻: https://api.whatsapp.com/send?p...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 01 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

13 431
Subscribers
+424 hours
-147 days
-4730 days
Posts Archive
ፊትን መሸፈን(ኒቃብ) ጉዳይን በተመለከተ፡ ዑለሞች ከሴት ልጅ ፊትና ሁለት መዳፎች ውጭ ያሉትን የሰውነት ክፍሎች ሙሉ በሙሉ መሸፈን ግዴታ (ዋጅብ) መሆኑ ላይ በጋራ ተስማምተዋል (ኢጅማዕ አድርገዋል)። ማለትም፡ ሁለት እግሮቿን፣ እጅን እስከ ክርን ቢሆን ማሳየት ይፈቀዳል የሚል አንድም የለም። ​ሁለተኛ፡ ዑለሞች ፊትንና ሁለት እጆችን መሸፈን ትልቅ ደረጃ ያለው፣ (በላጭ ነው) የታዘዘበት እና የተወደደ (ሙስተሃብ) ተግባር መሆኑ ላይ ተስማምተዋል። ፊትን ማሳየት ይፈቀዳል የሚሉት እንኳ መሸፈኑ የተወደደ ነው ይላሉ፤ ምክንያቱም እጅግ ዝቅተኛው ጥቅም እንኳ ከልዩነት (ኺላፍ) ለመውጣት ይረዳልና። ​ሦስተኛ፡ በውበቷ ምክንያት ፈተና ይፈጠራል ተብሎ የሚሰጋባት ቆንጆ ሴት ፊቷንና ሁለት እጆቿን መሸፈን ግዴታ (ዋጅብ) ይሆንባታል በሚለው ላይ ተስማምተዋል። እንዲሁም ማሳየት ይፈቀዳል የተባለው ፊት ምንም ዓይነት ሜካፕ (የፊት መኳኳያ) የሌለበት መሆን አለበት በሚለው ላይም ተስማምተዋል።

ዲንን ማቃለል እና በ«ዑለሞች መካከል ልዩነት/ኺላፍ አለ» በሚል ሽፋን ስሜትን መከተል በዑለሞች መካከል ኺላፍ አለባቸው በሚል ምክንያት በርካታ ዲናዊ ጉዳዮችን ለማቃለል (ለማለስለስ) መሞከር፤ በልዩነቱም በመመካት ደካማ የአቋም ብያኔዎችን ለመከተል ሰበብ መፈለግ፤ እንዲሁም የተገለሉና አሻሚ አቅዋሎችን ማስተዋወቅ፣ ማሰራጨት እና በህዝቡ መካከል ማስፋፋት ሰዎች የተሳሳቱና አሻሚ አቋሞችን እንዲይዙ ማድረግ እጅግ አደገኛ መርዝ ነው። ይህ ድርጊት ያለ ምንም ጥርጥር ዲንን ከማበላሸት የሚቆጠር ሲሆን፣ መጥፎ አላማ ላላቸውና በሽታ ያለባቸው ደካማ ነፍስ ለአስከፊ ተግባራቸው እንዲሁም ሸይጣኖቻቸው በዓለም ላይ እንዲያሰራጩ የሚጎተጉቷቸውን መጥፎ ሃሳቦች ለመተግበር በሩን ይከፍትላቸዋል። ቃዲ አቡ በክር እብኑል አረቢ እንዲህ ብለዋል፡-
«የሚከሰቱትን ኺላፎች በሙሉ የምንከተልና የምንጠብቅ ቢሆን ኖሮ፣ ዲን በማንኛውም መሰረት ላይ ሊረጋገጥና ሊፀና ባልቻለ ነበር።»

በአንዳንድ ወጣቶች አእምሮ ውስጥ፣ አንዳንድ ጊዜ ከመጠን በላይ በሆነ እራስን የመተማመን ስሜት የታጀበ፣ ለስላሳ እና ሮማንቲክ የሆነ አስተሳሰብ ይሰረጻል፤ ይህም አንዳንዶቹ፡ «ዲኗን ያልጠበቀች ወይም የላቀ በጎ ምግባር የሌላትን ሴት አግብቼ በራሴ እጅ አርማታለሁ፤ ወይም እቀይራታለሁ ፣ ወደ ቅን መንገድም እመራታለሁ» ብለው እንዲያስቡ ያደርጋቸዋል። ይህንንም የሚያስቡት በጥበባቸው፣ በጠንካራ ስብዕናቸው እና በሰዎች ላይ ባላቸው የማነፅ አቅም በመተማመን ነው። ​ይህ አስተሳሰብ፣ ውጫዊ ገጽታው በመልካም እሴት የተሸፈነ ቢመስልም፣ በውስጡ ግን ትልቅ ስህተትን እና ፍጹም ተገቢ ያልሆነ ዓይነ-ሥውር የሆነ በራስ የመተማመን ጥግ ነው። نعوذ بالله من الحور بعد الكور!

​"ዋናው ቁምነገር ሰው ማግባቱ ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም ትልቁ ቁልፉ ነጥብ፤ ማንኛዋን ያገባል?? የሚለው ነው። ​የዲን ባለቤት የሆነችዋን አግኝተህ ፤ ፈጥነህ አግባ፣ ይህን ካደረግህ (ዲነኛዋን ካገ
​"ዋናው ቁምነገር ሰው ማግባቱ ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም ትልቁ ቁልፉ ነጥብ፤ ማንኛዋን ያገባል?? የሚለው ነው። ​የዲን ባለቤት የሆነችዋን አግኝተህ ፤  ፈጥነህ አግባ፣ ይህን ካደረግህ (ዲነኛዋን ካገባህ) ታላቅ ሀብትን/ከንዝን አግኝተህ አሸንፈሃል፤ በረካም ተጎናጽፈሃል። አሊያ  ግን እጆችህ አፈር ይፈርሱ (የያዘከው ሀብት አይባረክ!)"ከታላቁ ዓሊም ሸይኽ ሷሊሕ አል-ፈውዛን (አላህ ይጠብቋቸው)

«ስለ ፂም መላጨት ከተነሳ፤ በአላህ ይሁንብኝ! በራሴ ላይ መጥፎ ድርጊትንና መጥፎ ንግግርን አላጣምርም። እኔ በተግባር የጣስኩት ቢሆንም እንኳ እውነትን አልሸሽግም። በአላህም ሆነ በሰዎች ላይ አልዋሽ
«ስለ ፂም መላጨት ከተነሳ፤ በአላህ ይሁንብኝ! በራሴ ላይ መጥፎ ድርጊትንና መጥፎ ንግግርን አላጣምርም። እኔ በተግባር የጣስኩት ቢሆንም እንኳ እውነትን አልሸሽግም። በአላህም ሆነ በሰዎች ላይ አልዋሽም። በዚህ ድርጊቴ ላይ ተሳስቼ የተገኘሁ መሆኔንም በራሴ ላይ አመምናለሁ። ይህን ስህተት ለመተው ደጋግሜ ሞክሬ ነበር፤ ነገር ግን የነፍስ ፍላጎትና የልማድ ኃይል አሸነፈችኝ። ፂሜን እስክለቅ ድረስ አላህ በነፍሴ ላይ እንዲረዳኝ እጠይቀዋለሁ፤ እናንተም ይህንኑ አላህን እንዲለምንልኝ እጠይቃለሁ፤ የኢማን ወንድም ለወንድሙ በሩቅ የሚያደርገው ዱዓ በአላህ ፈቃድ ተቀባይነት አለው።» ✍ሸይኽ አሊ አጥ-ጠንጣዊ

በሁኔታዎችህ (በስራህ) ምክንያት ከቁርኣን እንዳትራራቅ ተጠንቀቅ! በአላህ እምላለሁ! እነዚያን ሁኔታዎችህን እንድትወጣ ከቁርኣን ቲላዋ በረካ ውጭ ምንም የሚያግዝህ የለምና ..» ​ቃሪእ ሸዕባን ፋይዝ

አንድ ወጣት እንዲህ ይላል፦ "አንድ ቀን እኔና ጓደኛዬ የገንዘብ ቦርሳችንን (ዋሌታችንን) ተለዋወጥን። እኔ የእሱን ቦርሳ ስፈትሽ፣ እሱ ደግሞ የእኔን ቦርሳ ይፈትሽ ነበር። ቦርሳው ውስጥ የነበሩትን በርካታ የወረቀት ቁርጥራጮች እያነበብኩ ነበር። በአንዱ ወረቀት ላይ የተጻፈውን አነበብኩ ፊቴ በደስታና በግርምት ተሞላ። 'ይህ ምንድን ነው?' ብዬ ጠየቅኩት፤ – በስሜ የተቆረጠ የበጎ አድራጎት ድርጅት ደረሰኝ ነበር – እሱም፡ 'የአንድ አባት የሌለው ልጅ (የየቲም) እርዳታ/ድጋፍ ነው' አለኝ። እኔም፡ 'ግን ለምን በኔ ስም ሆነ!?' አልኩት። እሱም፡ 'በአንተ ስም ነው የቲሙን የደገፍኩት' አለኝ። እኔም፡ 'ከመቼ ጀምሮ ነው?' አልኩት። እሱም፡ 'ከሁለት ዓመት በፊት ጀምሮ' አለኝ። እኔም፡ 'ለምን ይህንን አደረግክ!' ብዬ ጠየቅኩት። እሱም፡ 'እሳት (ጀሃነም) እንዳይነካህ ስለፈራሁልህ ነው' ሲል መለሰልኝ።” አላህ ሆይ! መልካም እና ደግ ጓደኛን ወፍቀን! 🥺

اللهم مع شروق هذا اليوم، نسألك خيراً في كل أمر، ونوراً في كل درب، وراحة في البال، وتوفيقاً يرافق خطواتنا.

ነገሮች ሲዘበራረቁ ቦታቸውን እያየዙ ሊሆን ይችላል፤ ተስፋ አትቁረጥ! በአንድ ጉዳይ ላይ ወደ አላህ አብዝተህና አጥብቀህ ዱዓ አድርገህ ... ከዚያ በኋላ ግን ሁሉም ነገር ወደ ተቃራኒው ሲቀየር ብታይ፣ ዱአዬ አልተቀበለኝም ብለህ እንዳታስብ! አላህ መልካሙን ነገር አንተ ልትረዳው በማትችለው መንገድ እየመራው ይሆናል፤ በክስተቶችም የምስክርነትህንና የእምነትህን ጥንካሬ ይፈትናል። የእምነትህ ፅናት ሳይናወጥ የጸና ሆኖ ካገኘው ደግሞ ባልጠበቅኸው ስጦታ ያስገርምሃል.. አላህ በእርሱ በሚተማመኑት ባሮቹ ጥርጣሬና ግምት ልክ ነው!♥️

በአቅራቢያዋ ሰላምና ስክነት አለ…🕊️ በአላህ መልእክተኛ ﷺ መስጂድ ቅጽር ግቢ ውስጥ ደግሞ ከምንም ነገር ጋር የማይመሳሰል የልብ እርጋታና እረፍት ይገኛል። 💚
በአቅራቢያዋ ሰላምና ስክነት አለ…🕊️ በአላህ መልእክተኛ ﷺ መስጂድ ቅጽር ግቢ ውስጥ ደግሞ ከምንም ነገር ጋር የማይመሳሰል የልብ እርጋታና እረፍት ይገኛል። 💚

«ደካማ የሆነ ምላሽ(ረድ) ከሚሰጠው ጥቅም ይልቅ የሚያደርሰው ጉዳት ያመዝናል! ጠንካራ ያልሆነ ምላሽ ሊመልሱ ወይም ማስረጃ የማይሆንን ነገር እንደ ማስረጃ ሊያቀርቡ ይችላሉ፤ ከዚያም በህዝቡ መካከል ሲበተኑት፣ በዚህ ጥርጣሬ (ሹብሃ) የተበከለው ሰው ምላሽህ ደካማ መሆኑን ሲያውቅ ያኔ ጥርጣሬው በልቡ ውስጥ የበለጠ ይስፋፋል። አንተ የአህሉሱና ተወካይ ነህ፤ በዚህ ጃህል እይታ ውስጥ የአንተ ድክመት ማለት የሱና መንገድ (መዝሀብ) ድክመት ተደርጎ ይወሰዳል—ይህ ደግሞ ትልቅ ችግር ነው። አንዳንዶች ምላሽ ለመስጠት በቅድመ-ግንባር ይሰለፋሉ፤ ነገር ግን ምላሾቻቸው ደካማና ተሰባሪ ናቸው፤ አስፈላጊው ዕውቀት፣ ጥንካሬና ጥልቀት የላቸውም። በራስህ ውስጥ የዚህ መስክ ባለቤት አለመሆንህን ካወቅህ፣ አላህ ከአቅምህ በላይ አልጫነብህምና ጉዳዩን ለሌሎች ተወው። በህዝቡ መካከል 'ይህ የአህሉሱና መንገድ ነው' ብለህ እያሰራጨህ ምላሽህ ግን ያን ያህል ጠንካራ ካልሆነ፣በጣም አደገኛ ጉዳይ ነው። ይህም ወደ ሌላ ነባራዊ ሁኔታ ትኩረት እንድስብ ያደርገኛል፤ እርሱም፦ ዛሬ ያሉ ወጣቶች በልቦቻቸው ውስጥ ጥርጣሬዎች ሊፈጠሩ ይችላሉ። ጥርጣሬዎቹ ከቀደር ጋር የተያያዙ፣ ከአንዳንድ ሕግጋት ጋር የተያያዙ፣ ወይም ደግሞ ከፈጣሪ (ሱብሃነሁ ወተዓላ) ማንነት ጋር የተያያዙ ሊሆኑ ይችላሉ። እንዲሁም የማህበራዊ ሚዲያና የኢንተርኔት መረቦች በዚህ ግልጽ በሆነ የጥመቶች ስብስብ የተሞሉ ናቸው፤ ስለዚህ ከእነዚህ ጥርጣሬዎች መካከል የሆነ ነገር በዚያ ወጣት ልብ ውስጥ ሊያድር ይችላል። እናም አንተ በትምህርት ቤት ውስጥ ያለህ አስተማሪ፣ በ መስጂድ ውስጥ ያለህ ኢማም፣ ወይም ደግሞ እርሱ እንደ ሸይኽና እንደ ዓሊም (ዕውቀት ያለው ሰው) አድርጎ የሚያይህ ሰው ወደ አንተ መጥቶ ጥያቄውን ሲያቀርብልህ፤ እንዴት ምላሽ መስጠት አለብህ? በአላህ መልካም ፈቃድ ጥርጣሬውን ከልቡ የሚያስወግድ፣ አጥጋቢና ትክክለኛ የሆነ ምላሽ ካልሰጠኸው፣ ማድረግ የሚገባህን አልሰራህም። በዚያ ደካማ ምላሽ ምክንያት እርሱ ዝም ሊል ወይም በፊቱ አንገቱን ሊነቀንቅ ይችላል፤ ነገር ግን በእውነቱ በልቡ ውስጥ 'ጉዳዩ በእርግጥም አጠራጣሪ ነው፣ እረ እናንተ ሸይኾች ዘንድ ምንም ምላሽ የላችሁም' ብሎ ያምናል። ይህንንም ከአንዳንዶቹ ሰምቼዋለሁ፤ ከእነዚህ ወጣቶች አንዱ ስላጋጠመው ጥርጣሬ ሲጠይቅ የተሰጠው ምላሽ፦ 'ይህን ንግግር ተወው!' የሚል ነበር። 'ይህን ንግግር ተወው' የሚለው ምላሽ በልቡ ውስጥ ያለውን ጥርጣሬ ያስወግደዋልን? አያስወግደውም! በተለይም የዛሬ ወጣቶች አሳማኝ ማስረጃ ያስፈልጋቸዋል፤ ልስላሴ ልታሳያቸው፣ በሚረዱትና በሚገባቸው ቋንቋ ልታበራራላቸው ይገባል። ስለዚህ አንተ በቁጣ፣ ወይም 'ዝም በል' በማለት፣ ወይም ደግሞ በደካማ ምላሽ ካሰናበትከው፣ ጥርጣሬውን በልቡ ውስጥ የበለጠ ታጠናክራለህ። ስለሆነም፦ ወይም አጥጋቢ ምላሽ ስጠው፣ ወይም ደግሞ መልካም ምላሽ መስጠት ወደሚችልና ወደሚያውቅ ሰው እጁን ይዘህ ውሰደው።" ፕሮፌሰር ሸይኽ ሷሊሕ አስ–ሲንዲ

🔴 የጁምዓ ኹጥባ 🎙 خطبة الجمعة أحوال يوم القيامة (الشفاعة) ✨ የቂያማ ቀን ክስተቶች 2 ሸፋዐ (ምልጃ) ⚠️ሊደመጥ የሚገባ ኹጥባ❗️ 🎙በኡስታዝ ሱልጧን ኸድር 💫የአጅሩ ተካፋይ እንድንሆን ሼር! 🕌 ቃሊቲ ሀምዛ መስጂድ 🗓 ሶፈር 25/1448 አ/ሂ http://t.me/kalityhamzamesjid

«በጀመዓ (በአንድነት) ውስጥ ያለ ችግር፣ በመለያየት ከሚገኝ ምቾት ይበልጣል።» ሸይኽ ሷሊሕ ኢቢኑ አብደልዐዚዝ ኢቢን ዑሥማን አስ-ሲንዲ (በመዲና ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ የዐቂዳ ፕሮፌሰር)
«በጀመዓ (በአንድነት) ውስጥ ያለ ችግር፣ በመለያየት ከሚገኝ ምቾት ይበልጣል።» ሸይኽ ሷሊሕ ኢቢኑ አብደልዐዚዝ ኢቢን ዑሥማን አስ-ሲንዲ (በመዲና ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ የዐቂዳ ፕሮፌሰር)

በሰላቱ ላይ የዘወተረ ሰው፣ በሁለት ሰላቶች መካከል ይሞታል፡ በሰገዳት እና በሚጠብቃት ሰላት መካከል፤» 🥹🌻🌸 አላህ ሆይ! ያማረ መጨረሻንና ከፍተኛዋን ጀነት (ፊርደውስን) እንለምንሃለን።

በሁሉም ነገር ውስጥ የአላህን ቸርነት እና ደግነት መፈለግን ለራሳችሁ ልማድ አድርጉ፤ ግራ በሚያጋቡ አጋጣሚዎች እና በጭንቀት/በመከራ ወቅትም እንኳ ቢሆን። ሁልጊዜም፦ «ምናልባት መልካም ይሆናል፤ ምናልባት አላህ የማላውቀውን ክፉ ነገር ከእኔ አርቆልኝ ይሆናል፤ ምናልባት ከዚህ በኋላ መላቀቅ፣ እረፍት እና ማቃለል ይመጣል» ማለትን ልማድ አድርጉ። ሁልጊዜም በአላህ ውሳኔ የመርካት (ቀደርን የመቀበል) መንፈስ ይኑራችሁ... ከዚያም በኋላ አላህ እንዴት እንደሚያስደስታችሁ እና እንዴት እንደሚበቃችሁ ታያላችሁ።

እውነተኛ ጓደኝነት ለአላህ ብሎ ሲሆን… ✨ በዚህች ምድር ላይ ለአንድ አማኝ ከተሰጡት ትላልቅ ጸጋዎች አንዱ "መልካም ጓደኛ" ነው። ይህ ጓደኛ በገንዘብ፣ በዝና ወይም በጊዜያዊ ጥቅም ሳይሆን፣ ንጹህ በሆነው የአላህ ፍቅር ብቻ የተሳሰራችሁት ነው። አብዛኛው የሰው ልጅ ግንኙነት በግላዊ ጥቅም ላይ በተመሰረተበት በዚህ ጊዜ፣ ለአላህ ተብሎ የሚመሰረት ውዴታ እጅግ ውድ ነው። ነቢዩ ሰለሏሁ አይሂ ወሰለም አላህ ዘንድ በልዩ ሁኔታ ስለሚጠለሉት ሰዎች ሲናገሩ፦ "ስለ አላህ ብለው የተዋደዱ፣ በእርሱ ላይ የተሰበሰቡና በእርሱ ላይ የተለያዩ..." ብለዋል። ይህ ማለት ለአላህ ተብሎ የተገነባ የወንድማማችነት ፍቅር በሞት አያበቃም፤ ጠቀሜታውም ሆነ አማላጅነቱ ጀነት ድረስ የሚዘልቅ ዘላለማዊ ትስስር ነው! 🤲 ኢላሂ! ወደ አንተ የሚመሩንን፣ ስንዘናጋ የሚያስታውሱንን እና ትዕዛዝህን በመፈጸም ላይ የሚያግዙንን መልካም ጓደኞች ወፍቀን። ውዴታችንን ላንተ ብሎ ብቻ አድርግልን፤ በቂያማ ቀንም ምንም ጥላ በሌለበት ጊዜ በአርሽህ ጥላ ስር ከሚሰበሰቡት ባሮችህ አድርገን። አሚን! 🤍

የመልካም ጓደኝነት ውብ ከሆኑ ነገሮች አንዱ፡ በዚህች ዱንያ መጠናቀቅ የማይበቃ መሆኑ ነው፤ ይልቁንም እስከ ቂያማ የሚዘልቅ ሲሆን፣ ከአላህ ጥላ ውጭ ምንም ጥላ በሌለበት ቀን በአላህ ጥላ ስር አብረው ይጠለላሉ።

ሰላም! ለዚያች በፍቅሯ ልባችንን ላሸነፈችው ከተማ ..🤍💔 ሰላም! እሷን ላበሯት ነቢያችን ﷺ፣ ሰላም! በየቀኑ እሷን ለሚናፍቅ ልብ ። 💔🕊...
ሰላም! ለዚያች በፍቅሯ ልባችንን ላሸነፈችው ከተማ ..🤍💔 ሰላም! እሷን ላበሯት ነቢያችን ﷺ፣ ሰላም! በየቀኑ እሷን ለሚናፍቅ ልብ ። 💔🕊...

ወርቃማ ምክር ከሸይኽ ሙሐመድ ረምዛን ሃጅሪይ ሀፊዘሁላህ ​«ከአላህ ጋር ያለህን ምስጢር አድስ» «ሰዎች ቢያወድሱህም፣ ቢያስታውሱህም፣ ላደረግከው መልካም ነገር ቢያመሰግኑህም... አንተ ከማንም በላይ የራስህን ሰወር ጥፋቶች ታውቃለህ። የራስህን ምስጢር ታውቃለህ፣ ሌሊትህን ታውቃለህ፣ ቀንህን ታውቃለህ... ስልክህንና በእርሱ ውስጥ ያሉትን መልእክቶች፣ ያየሃቸውንና የሰማሃቸውን ነገሮች ሁሉ ታውቃለህ። የሰዎችን ሙገሳና አድናቆት ተወው፤ አንተ ከአላህ ጋር ያለህን ምስጢር ከማንም በላይ አዋቂ ነህ። ራስህን አስተካክል... ራስህን አክም! በውስጥህ ግድፈትና ጉድለት ካየህ፣ ያንነ አውቀህ አስተካክለው። የሰዎች ወሬና የአሞጋሾች ማወደስ አይሸንግልህ፤ አንተ ራስህን ከማንም በላይ ታውቃለህና ራስህን አርም! ጥፋትህን ➔ አስተካክለው! የልሳን ስህተት ➔ በዚክር (አላህን በማስታወስ) ለውጠው! ሐሜት ➔ በመልካም ወሬ ለውጠው! እግርህ ወደ ወንጀል አመራች? ➔ ወደ መስጂድ አቅናት! ምላስህ ተንሸራተተች? ➔ ቁርዓን ወደ ማንበብ ቀይረው! ዓይንህ? ➔ የአላህን መጽሐፍ ክፈት! ጆሮህ? ➔ ቁርኣንን፣ ዚክርንና መልካም ነገርን ስማ! ዝምድና መቁረጥ? ➔ ሂድና ያቋረጥከውን ሰው ቀጥል... አባትህ፣ እናትህ፣ አክስትህ፣ አጎትህ... እከሌ ቢሆን እንኳን ሂድና ይቅርታ ጠይቅ! ወለድ? ➔ ተወው! ወንጀል? የሙዚቃ/እያዩ የመስማት ነገሮች? ➔ ተጠንቀቅ፣ አስተካክለው! «በእርግጥ መልካም ሥራዎች መጥፎ ሥራዎችን ያስወግዳሉ!»»