uk
Feedback
የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

Відкрити в Telegram

ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡ አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን! ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን! ♻: https://api.whatsapp.com/send?phone=

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

Канал የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official) (@sultan_54) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 13 475 підписників, посідаючи 6 644 місце в категорії Релігія і духовність та 2 508 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 13 475 підписників.

За останніми даними від 11 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -136, а за останні 24 години на -3, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 12.69%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 5.58% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 1 710 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 752 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 12.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡ አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን! ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን! ♻: https://api.whatsapp.com/send?p...

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 12 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

13 475
Підписники
-324 години
-197 днів
-13630 день
Архів дописів
🖋️ አንዲት ኒቃብ የለበሰች ሙስሊም ሴት በጀርመን አገር በሚገኝ አንድ የገበያ ማዕከል ውስጥ እየሸመተች ነበር። የሚያስፈልጋትን ዕቃ ገዝታ ከጨረሰች በኋላ፣ የገዛችበትን ሂሳብ ለመክፈል ወደ መክፈያ
🖋️ አንዲት ኒቃብ የለበሰች ሙስሊም ሴት በጀርመን አገር በሚገኝ አንድ የገበያ ማዕከል ውስጥ እየሸመተች ነበር። የሚያስፈልጋትን ዕቃ ገዝታ ከጨረሰች በኋላ፣ የገዛችበትን ሂሳብ ለመክፈል ወደ መክፈያ ማሽኑ (ካሽየሩ) አመራች። ከመክፈያ ሳጥኑ በስተጀርባ የተቀመጠችው ሰራተኛ ሂጃብ ያላደረገችና የዓረብ ዝርያ ያላት ሴት ነበረች፤ ኒቃብ የለበሰችውን እህት በንቀት ዓይን ከተመለከተቻት በኋላ፣ የገዛቻቸውን ዕቃዎች በግልጽ በሚታይ ንዴት ጠረጴዛው ላይ እያጋጨች መቁጠር ጀመረች። ኒቃብ የለበሰችው እህት ግን ምንም ዓይነት ምላሽ ሳትሰጥ በጥንካሬና በዝምታ ተረጋግታ ቀጠለች፤ ይህ ሁኔታ የሰራተኛዋን ንዴት ይባስ አባባሰው። በመጨረሻም ትንኮሳ በሞላበት ድምፅ እንዲህ አለቻት፦ “እኛ እዚህ ጀርመን ውስጥ በቂ ችግርና ቀውስ አለብን፤ ያንቺ ኒቃብ ደግሞ ከችግሮቹ አንዱ ነው! እኛ እዚህ ያለነው ለንግድ እንጂ ሃይማኖትን ወይም ታሪክን ለማሳየት አይደለም። ሃይማኖትሽን መለማመድ ወይም ኒቃብ መልበስ ከፈለግሽ፣ ወደ ሀገርሽ ተመልሰሽ እዚያ የፈለግሽውን ማድረግ ትችያለሽ።” ኒቃብ የለበሰችው እህት የገዛቻቸውን ዕቃዎች ወደ ቦርሳዋ መክተቷን አቆመችና በዝምታ ተመለከተቻት… ከዚያም ፊቷ ላይ የነበረውን ኒቃብ ገለጥ አደረገችው፤  ሰማያዊ ዓይን ያላት፣ ፀጉረ ወርቅ (ብላንድ) ጀርመናዊት ነበረች። በመረጋጋትም እንዲህ አለቻት፦ “እኔ አባቴም አያቴም (ስር መሰረቴ) እውነተኛ ጀርመናዊት ነኝ… ይህ ደግሞ የኔ እስልምና ነው… ይህችም የኔ ሀገር ናት… እናንተ ግን ዲናችሁን ሸጣችሁት… እኛ ደግሞ ገዛነው።”

የእለቱ መልክት የአላህ መልክተኛ ﷺ ካሉት በላይ አትጨምር! የኢማም አሕመድ ኢብኑ ሐንበል ልጅ ዐብዱላህ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦ «እኔና አባቴ በመስጂድ ውስጥ እያለፍን ነበር፤ በዚህ መሀል አንድ ተራኪ (ቀሳስ) “ሐዲሠ ኑዙልን” (አላህ ወደ ቅርቢቱ ሰማይ ስለመውረዱ የሚገልጸውን ሐዲሥ) ሲያወራ ሰማነው። እንዲህም አለ፦ “የሸዕባን ወር ግማሽ ሌሊት (ኒስፉ ሸዕባን) በሚሆንበት ጊዜ አላህ (ዓዘ ወጀል) ያላንዳች መወገድ (ከቦታው ሳይለቅ)፣ ያላንዳች መዘዋወር፣ ያላንዳች መለዋወጥና ሁኔታው ሳይቀየር ወደ ቅርቢቱ ሰማይ ይወርዳል”። ​በዚህ ጊዜ አባቴ (ኢማም አሕመድ) ከንዴት የተነሳ ተንቀጠቀጡ፣ ቀለማቸውም ቢጫ ሆነ (ፊታቸው ተለወጠ)፣ እጄንም ያዙኝ፤ እኔም እስኪረጋጉ ድረስ ያዝኳቸው። ከዚያም፦ “ወደዚህ አስመሳይ (ያለ እውቀት ወደሚዘባርቀው ሰው) ውሰደኝ” አሉ። ልክ እሱ ጋ ሲደርሱ እንዲህ አሉት፦ “አንተ ሰውዬ! የአላህ መልክተኛ ﷺ ከአንተ ይበልጥ ለጌታቸው (ለአላህ) ክብር ተቆርቋሪ ነበሩ፤ የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዳሉት ብቻ በል (ከራስህ ፍልስፍና አትጨምር)፤፤” ከዚያም ዘወር ብለው ሄዱ።» ​📔 [አል-ኢቅቲሷድ ፊ አል ኢዕቲቃድ — ሊዐብዱል ገኒይ አል-መቅዲሲ (21)]

📚 قال الإمام ابن القيم (رحمه الله) : ((فإن للإيمان فرحة وحلاوة ولذاذة في القلب ، فمن لم يجدها فهو فاقد للإيمان أو ناقصه)). 📔 الرسالة التبوكية (7) ••❥❥✺•✿•✺❥❥•• 📚 ኢማም ኢብኑል ቀዪም (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦ > ኢማን በልብ ውስጥ ደስታ፣ ጣፋጭ ቃና እና እርካታ አለው፤ ይህንን ያላገኘ ሰው ወይ ኢማን የሌለው ወይ ኢማን የጎደለው ነው፤፤)) > 📔 አር-ሪሳላህ አት-ተቡኪያህ (7) ••❥❥✺•✿•✺❥❥••

ዓብደላህ ኢብኑል ሙባረክ እንዲህ ተጠየቁ፦ 'ዑመር ኢብኑ ዐብደልዓዚዝ ይበልጣል ወይስ ሙዓዊያ?' እርሳቸውም እንዲህ ሲሉ መለሱ፦ 'ሙዓዊያ ከአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ጋር በተሳተፈባቸው በአንዳንዶቹ የውጊያ አውደ ግንባሮች ላይ ሳለ ወደ አፍንጫው የገባው አቧራ እንኳ ከዑመር ኢብኑ ዐብደልዐዚዝ ይበልጣል።'"(ምንጭ፦ አል-ሁጃ ፊ በያኒል ሙሐጃ [2/377] በአቡ ቃሲም አል-አስበሃኒ የተዘጋጀ)

> አካልህ ቢቆራረጥ እንኳ የጠዋትና የማታ አዝካሮችን አትተው! በፍጹም እንዳትተው። > ከምሽት ዚክሮች መካከል አንዱን እንኳ ብትል እንኳ አድርገው። ለምሳሌ፦ 'በስሚላሂለዚ ላ የዱሩ መዓ ኢስሚሂ ሸይኡን ፊል አርዲ ወላ ፊ አስ–ሰማኢ ወሁወስሰሚኡል ዓሊም' (በስሙ በምድርም ሆነ በሰማይ ምንም ነገር የማይጎዳውን በአላህ ስም እጀምራለሁ፤ እርሱም ሰሚውና አዋቂው ነው) የሚለውን ዱአ ብቻ ብትል እንኳ የጠዋትና የማታ ዚክርን እንዳደረግክ ይቆጠርልሃል። በምሽትም እንዲሁ። > የመጨረሻው ደግሞ ከመተኛት በፊት የሚደረጉ ዚክሮች ናቸው። ከመተኛትህ በፊት እነዚህን ማውሻዎች ሳታደርግ በፍጹም እንዳትተኛ። > አንዲት ዚክር ብቻ እንኳ ብትሆን፤ ለምሳሌ፦ 'አስተግፊሩላሀለዚ ላ ኢላሀ ኢላ ሁወል ሀዩል ቀዩሙ ወአቱቡ ኢለይህ' (ያ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለውን፣ ህያውና ሁሉን ቻይ የሆነውን አላህ ምህረት እለምነዋለሁ፤ ወደ እርሱም እመለሳለሁ) ብትል ምን እንደሚሆን ታውቃለህ? > ከጦርነት ሜዳ የሸሸህ እንኳ ብትሆን፣ ወይም የወነጀልከው ወንጀል የዚህችን ዓለም አሸዋ ያህል የበዛ ቢሆን እንኳ አላህ ወንጀሎችህን በሙሉ ይምርሃል። > እና ይሄ ከባድ ነው? እንግዲያውስ ከአላህ ጋር ኑር!" >

"ከከሀዲያን እና ከቢድዓ ባለቤቶች ጋር በአደባባይ ወይም በየቲቪ ቻናሎቹ የሚደረጉ ይፋዊ ክርክሮች፤ ይህ ከሰለፎች  የዳዕዋ መንገድ ነውን? ውጤቱስ ምንድን ነው?! ይህንን በተመለከተ፤ ከሰለፎች (አላህ ይዘንላቸውና) በሰፊው የተነገረውና የታወቀው መንገድ፡ ከቢድዓ ባለቤቶች ጋር ከመቀማመጥ፣ እነሱን ከመስማት፣ ከእነሱ ጋር ከመከራከርና ክርክር ከመግጠም መራቅ ነው። ለዚህም ምክንያቱ፦ * አንደኛ፦ ክርክር ልብን ያደክማል፣ ቂምና በቀልንም ያወርሳል። * ሁለተኛ፦ ሰሚው  (ሰፊው)ማህበረሰብ እውነቱ የትኛው እንደሆነ መለየት ላይችል ይችላል። በተለይም የቢድዓው ባለቤት አቀራረቡ የተዋጣለትና አንደበተ ርቱዕ ከሆነ፣ እንዲሁም የሱናው ባለቤት ደግሞ የማስረዳት አቅሙ ደካማ ከሆነ፤ ይፋዊው ክርክር ለሰፊው ህዝብ ፈተና (ፊተና) መሆን ይጀምራል። ህዝቡም ጥመትን እውነት ነው ብሎ ሊከተል ይችላል። ስለዚህ ሰለፎች ይከለክሉ የነበሩት ለዚህ ነው።" "አላህ ይጠብቃችሁና፤ በዚህ ዘመን በሳተላይት የቲቪ ቻናሎች ላይ የሚደረጉ የክርክር መድረኮችን በተመለከተ፦ እነዚህ መድረኮች አብዛኛውን ጊዜ ከጥቅማቸው ይልቅ ጉዳታቸው ያመዝናል። ለምን ቢባል? * አንደኛ፦ ጥያቄዎችንና ጥርጣሬዎችን (ሹብሃቶችን) ወደማያውቁትና ንፁህ ወደሆኑት የሰፊው ህዝብ ልቦች ውስጥ ያስርጻሉ። አንድ ተራ ሙስሊም በቤቱ ተቀምጦ ሳለ፣ ከዚህ በፊት ሰምቶት የማያውቀውንና በጭንቅላቱ ውስጥ ጨርሶ ያልነበረን ጥርጣሬ (ሹብሃ) በነዚህ መድረኮች አማካኝነት እንዲሰማ ይደረጋል። ከዚያም ያ ጥርጣሬ ልቡ ውስጥ ይፈጠራል። በክርክሩ ላይ ለቀረበው ጥርጣሬ የተሰጠው ምላሽ በቂ ባይሆን ወይም ግልጽ ባይሆንለትስ?! ያ ሰው ጥርጣሬው ልቡ ውስጥ እንደታተመ ይቀራል ማለት ነው። ይህ ደግሞ ትልቅ አደጋ ነው። * ሁለተኛ፦ እነዚህ መድረኮች ለቢድዓ ባለቤቶችና ለጠማሞች የራሳቸውን መርዝና ጥመት የሚረጩበት ሰፊ መድረክና ነፃ ማስታወቂያ ይሆኑላቸዋል። መቼም ቢሆን ሊያገኙት የማይችሉትን ሰፊ ህዝብ በእነዚህ ቻናሎች አማካኝነት ያገኛሉ። ስለዚህ ትክክለኛውና ጥንቃቄ የተሞላበት መንገድ፡ እውነትንና ሱናን በራሱ ጥራቱና ውበቱ ለህዝቡ ማስተማር ነው። የጠማሞችን ጥርጣሬ ግን ስማቸውን ሳያነሱና መድረክ ሳይሰጧቸው፣ እውነቱን ጠንካራ በሆነ መረጃ በማብራራት ማፍረስ ይገባል።" ሸይኽ ዶ/ር ሳሊህ አስ-ሰንዲ

«አላህ (ሱብሓነሁ ወተዓላ) እንዲህ ይላል፦ "ከሥራም ወደሠሩት እንመጣለን፤ የተበተነም ትቢያ እናደርገዋለን።" *(ሱረቱ አል-ፉርቃን፡ 23)* ፉደይል የተባሉት ታላቅ ዓሊም ይህንን የቁርዓን አንቀጽ አስመልክተው ሲናገሩ፦ "ከማያስቡትም ከአላህ ዘንድ ለእነሱ ግልጽ ሆነላቸው።" *(ሱረቱ አዝ-ዙመር፡ 47)* እንዲህ አሉ፦ "መልካም ሥራዎችን የሠሩ መስሏቸው ነበር፤ ነገር ግን (በትንሣኤ ቀን) ሲያዩት ወንጀል ሆኖ አገኙት።" እነዚህ ሥራዎች (በውስጣቸው ለአአሏህ ብቻ ያልጠሩ) ጉድለት ያለባቸው ሥራዎች ናቸው። ለአላህ ብሎ የሚሠራ ይመስላል፤ ነገር ግን በእውነታው ለራሱ ስምና ዝና (ወይም ለሌላ ምድራዊ ጥቅም) ነው የሠራው። ለአላህ ብሎ በተገቢው መንገድ አላጠራውም። ይህ ሰው (በቂያማ ቀን) ወንጀል እንጂ መልካም ምንዳ አይኖረውም። እሱ ግን መልካም ሥራ የሠራ መስሎት ነበር። ለምን? ምክንያቱም ቀደም ሲል እንደጠቀስኩት ራሱን በትክክል አያውቅም ነበር። ራሱን በአግባቡ የሚያውቅና አላህ ከራሱ (ከነፍሱ) ክፋት እንዲጠብቀው የሚለምን ሰው፣ ነፍሱ አታታለውም። ይህ (የተሸወደው) ሰው ግን መልካም ሥራ የሠራ መስሎት ይመጣል፤ ነገር ግን በእውነቱ ለአላህ ብሎ አልሠራም፣ ለራሱ ስሜት ሲል ነው የሠራው። በዚህም ምክንያት የሠራው ሥራ ሁሉ "የተበተነ ትቢያ" (ዋጋ ቢስ) ሆኖ ይቀራል።»

"የተባሉትን ቃል ለወጡ" — የሲፋት ማዛባት አደገኝነት
አሰላም ዓለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ የአላህን ሱብሃነሁ ወተዓላ ባህሪያት (ሲፋት) የሚቀይሩና ትክክለኛ ትርጉማቸውን የሚያዛቡ የብድዓ (የፈጠራ) ሰዎች፤ የአላህ عز وجل የሚከተለው ቃል በእነሱ ላይ ይፈጸማል፦ > "እነዚያ የበደሉት ሰዎች የተባሉትን ቃል ካልሆነ ሌላ ቃል ለወጡ።" *(አል-በቀራህ፡ 59)* > * "አር-ራህማን ከዐርሹ በላይ ከፍ አለ (ኢስተዋ)" ሲባሉ፤ እነሱ ግን፦ "አይደለም፣ ተቆጣጠረ (ኢስተውላ)" አሉ። የተባሉትን ቃል ወደ ሌላ ቃል ለወጡ። * "ይልቁንም ሁለት እጆቹ የተዘረጉ ናቸው" ሲባሉ፤ እነሱ ግን፦ "አይደለም፣ (እጅ ማለት) ጸጋውና ችሮታው ነው" አሉ። የተባሉትን ቃል ወደ ሌላ ቃል ለወጡ። * "የጌታህም ፊት (ዛት) ቀሪ ነው" ሲባሉ፤ እነሱ ግን፦ "አይደለም፣ (ፊት ማለት) የጌታህ ማንነት (ዛት) ብቻ ነው" አሉ። የተባሉትን ቃል ወደ ሌላ ቃል ለወጡ። * "ጌታችን ወደ ቅርቢቱ ሰማይ ይወርዳል፤ ለክብሩና ለግርማ ሞገሱ በሚገባ ሁኔታ" ሲባሉ፤ እነሱ ግን፦ "አይደለም፣ ትዕዛዙ ወይም እዝነቱ ወይም ከመላእክቱ አንዱ መልአክ ነው የሚወርደው" አሉ። እነዚያ የበደሉት ሰዎች የተባሉትን ቃል ባልሆነ ሌላ ቃል ለወጡ። * "ጌታህም (ለመፍረድ) በመጣ ጊዜ" ሲባሉ፤ እነሱ ግን፦ "አይደለም፣ የጌታህ ትዕዛዝ መጣ" አሉ። በሌሎችም ማዛባቶቻቸው ሁሉ ላይ የአላህ عز وجل ቃል ይገጥማቸዋል፦ > "እነዚያ የበደሉት ሰዎች የተባሉትን ቃል ካልሆነ ሌላ ቃል ለወጡ።" > ወሰላሙ ዓለይኩም አሽይኽ ወሊድ አስ–ሱዐይዳን

የተከበሩ ዶክተር ሸይኽ አሕመድ ኢብኑ ጧሊብ በሸሪዓ እና ኢስላማዊ ጥናቶች ክፍል የዶክትሬት (PhD) ዲግሪያቸውን በከፍተኛ ማዕረግ ( Excellent) ከመጀመሪያ ደረጃ ክብር (First-Class H
የተከበሩ ዶክተር ሸይኽ አሕመድ ኢብኑ ጧሊብ በሸሪዓ እና ኢስላማዊ ጥናቶች ክፍል የዶክትሬት (PhD) ዲግሪያቸውን በከፍተኛ ማዕረግ ( Excellent) ከመጀመሪያ ደረጃ ክብር (First-Class Honors) ጋር በማግኘታቸው እንኳን ደስ አሎት እንላለን። ​አላህ ይጠብቃቸው፣ በእሳቸው (ዒልም) ሌሎችን ይጠቅም ዘንድ እመኛለሁ።

​"ቁርኣን ላይ ያሉ አሻሚ ነጥቦችን (ሙተሻቢሃትን) በመምዘዝ የሚከራከሯችሁ ሰዎች ወደፊት ይመጣሉ። እናንተ ግን በሱና ሞግቷቸው/ያዟቸው፤ ምክንያቱም የሱና ባለቤቶች የአላህን መጽሐፍ (ቁርኣንን) ይበ
"ቁርኣን ላይ ያሉ አሻሚ ነጥቦችን (ሙተሻቢሃትን) በመምዘዝ የሚከራከሯችሁ ሰዎች ወደፊት ይመጣሉ። እናንተ ግን በሱና ሞግቷቸው/ያዟቸው፤ ምክንያቱም የሱና ባለቤቶች  የአላህን መጽሐፍ (ቁርኣንን) ይበልጥ አዋቂዎች ናቸውና።" (ዑመር ኢብኑ አል ኸጧብ) — ዳሪሚይ የዘገቡት

«የኸዋሪጆች ፈለግ እና የመገለል አባዜ» "አ’ትተመዩዝ" “አል ኢንዒዛል" > ከሙስሊሙ ማህበረሰብ (ጀማዐ) ተለይቶ መውጣትንና 'ልዩ ነኝ' ባይነትን (ኢንዒዛልን) በመጀመርያ የፈጠሩት ኸዋሪጆች ናቸው። ይህን ያደረጉትም በ'ሐሩራእ' የራሳቸውን ማህበረሰብ በመመስረትና ወደ እነሱ መሰደድን ግዴታ በማድረግ ነበር፤ ወደ እነሱ ያልተሰደደውንም በኩፍር ፈረጁት። ታዲያ ከሰዎች ተገልሎና ተለይቶ እየኖረ 'ሰዎችን አስገነዝባለሁ (አስተካክላለሁ)' የሚል ሰው ነገር ግራ የሚያጋባ ነው፤ ከማህበረሰቡ ጋር ሳትቀላቀልና ሳትኖር እንዴትስ ሰዎችን ወደ በጎ መንገድ ልትጣራ ትችላለህ?!" > ###ከሰዎች መገለል (በአካልም ሆነ በስሜት) እና ራስን እንደ ብቸኛ ትክክለኛ አድርጎ መቁጠር ለጽንፈኝነት የመጀመሪያው በር ነው። መልክተኛው ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «ከሰዎች ጋር የሚቀላቀልና በነርሱ አዛ ላይ የሚታገስ አማኝ፣ ከሰዎች ጋር የማይቀላቀልና በነርሱ እንግልት ላይ ከማይታገሰው ይበልጣል»። ስለሆነም በዳዕዋ ላይ ዋናው መሠረት ሰዎችን መቅረብ፣ መደባለቅና መታገስ እንጂ መገለልና መኮራት አይደለም።

## ልጆችን የመውለድ ጉጉትና ትሩፋት! ኢብኑል ቀዪም (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦ *«ልጅን ለመውለድ ለመውደድና ለመመኘት ካደረጉኝ ነገሮች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡»* ● ሙስሊም በሶሒሃቸው ከአቡ ሐሳን ይዘው እንደዘገቡት እንዲህ ብሏል፦ «ሁለት ወንድ ልጆቼ ሞቱብኝ። ለአቡ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ አልኳቸው፡— "ስለ ሙታኖቻችን ልባችንን የሚያረጋጋና የሚያስደስት ከረሱል ﷺ የሰማኸው ሐዲሥ አለህን?" እሳቸውም፦ "አዎ፤ 'ሕጻናቶቻቸው የጀነት ትናንሽ አሳዎች (ደዓሚስ) ናቸው። ከእነርሱ አንዱ አባቱን — ወይም ወላጆቹን — ያገኝና እኔ አሁን ያንተን ልብስ ጫፍ እንደያዝኩት የልብሱን ወይም የእጁን ጫፍ ይይዛል። አላህ እርሱንም አባቱንም ጀነት እስኪያስገባቸው ድረስ በፍጹም አይለቀውም' አሉ" አሉ።» ● ከሙዓዊያህ ኢብኑ ቁ‘ርራህ፣ እርሱም ከአባቱ እንደዘገበው፦ «አንድ ሰው ልጅን አስከትሎ ወደ ነቢዩ ﷺ ይመጣ ነበር። ነቢዩም ﷺ፦ "ትወደዋለህን?" አሉት። ሰውየውም፦ "የአላህ መልክተኛ ሆይ! እኔ እሱን እንደምወደው ሁሉ አላህም ይውደዳችሁ!" አላቸው። ከዕለታት አንድ ቀን ነቢዩ ﷺ ሰውየውን አጡትና፦ "የእገሌ ልጅ ምን ሆነ?" ብለው ጠየቁ። ሰዎቹም፦ "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ልጁ ሞተበትኮ" አሏቸው። ነቢዩም ﷺ ለአባቱ እንዲህ አሉት፦ "ከጀነት በሮች ወደ አንዱ ስትመጣ እርሱ በዚያ በር ላይ እየተጠባበቀህ ማግኘትህን አትወድምን?" አንድ ሰውም፦ "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ይህ ለእሱ ብቻ የተለየ ነው ወይስ ለሁላችንም?" ሲል ጠየቀ። እሳቸውም፦ "አይደለም፤ ለሁላችሁም ነው" አሉ።» ● ኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ ብለዋል፦ «የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ አሉ። "ከኡመቴ (ህዝቦቼ) መካከል ሁለት ልጆች ቀድመውት የሄዱለት ሰው ጀነት ይገባል።" ዓኢሻም (ረዲየላሁ ዐንሃ)፦ "አባቴና እናቴ ፊዳ ይሁኑልህና፤ አንድ ልጅ ቀድሞት የሄደስ?" ስትል ጠየቀች። እሳቸውም፦ "አንቺ የተመራሽው (የተባረክሽው) ሆይ! አንድ ልጅ ቀድሞት የሄደም ቢሆን (ያው ነው)" አሉ። እሷም፦ "ከኡመትህ መካከል ምንም ልጅ ቀድሞት ያልሄደስ?" ስትል ጠየቀች። እሳቸውም፦ "እኔ ለኡመቴ ቀዳሚ ነኝ፤ እኔን በማጣት እንደደረሰባቸው ያለ መከራ በፍጹም አይደርሰባቸውም" አሉ።» ምንጭ፦ *ቱሕፈቱል መውዱድ ቢአሕካሚል መውሉድ (ገጽ 13 - 15)*

(الرَّحْمَنُ عَلَى الْعَرْشِ اسْتَوَى) «እናንተ መልካም ሰዎች ሆይ! “አላህ በዐርሹ ላይ ከፍ አለ (ኢስተዋ)” የሚለውን የቁርኣን ቃል — ቁርኣን በወረደበትና በዐረብኛ ቋንቋ የታወቀውን “ከፍ አለ፣ ከላይ ሆነ” የሚለውን ትርጉም — ለምን አትቀበሉም? ለምንስ ትክዳላችሁ? እነርሱም (አሻዒራዎች/ሙዕተዚላዎች) ሲመልሱ፦ “ምክንያቱም ‘ኢስቲዋእ’ (በዐርሽ ላይ መሆን) የፍጡራን ባህሪ ነው፤ እኛ ደግሞ በዐርሽ ላይ የሚሆንን (የሚቀመጥን) አካል ከፍጡር ውጭ አናውቅም፤ ስለዚህ ይህንን ካረጋገጥን አላህን ከፍጡር ጋር አመሳሰልን (ተሽቢህ አደረግን)” ማለት ነው ይላሉ። እሺ! መልካም፣ ችግር የለውም። ታዲያ ይህንን የቁርኣን አንቀጽ ምን ልታደርጉት ነው? ስንላቸው ምን ይላሉ መሰላችሁ? “በትርጉም እናቆለምመዋለንን (እናውለዋለን)፤ ትርጉሙም ‘ኢስቲላእ’ (በኃይል መቆጣጠር/ማሸነፍ) ነው እንላለን” ይላሉ። እኛም በነርሱው መመዘኛ (ሎጅክ) እንመልስላቸዋለን፦ እኛም እኮ በኃይል የሚቆጣጠርንና የሚያሸንፍን አካል ከፍጡር ውጭ አናውቅም! (አንድን ነገር በኃይል የሚቆጣጠረው ፍጡር ነው)። ታዲያ አሁንም እናንተ አላህን ከፍጡር ጋር አላመሳሰላችሁምን? እናንተ ራሳችሁ ፈጣሪን ከፍጡራን ጋር አመሳሳዮች (ሙሸቢሃ) አደላችሁም? ለመሆኑ እናንተ የአንዱን ገጣሚ ስንኝ ጠቅሳችሁ፦ *“ቢሽር የተባለው ሰው ያለ ሰይፍና ደም መፋሰስ በኢራቅ ላይ ‘ኢስተዋ’ (ተቆጣጠረ)”* የምትሉትን አታውቁም? እዚህ ጋ ‘ኢስተዋ’ ማለት በናንተ ትርጉም ‘ኢስቲላእ’ (ተቆጣጠረ) ማለት አይደል? ታዲያ ቢሽር የተባለው ፍጡር እኮ ነው የተቆጣጠረው! ስለዚህ አሁንም እናንተ አላህን ከፍጡር ጋር ወደማሳሰል (ተሽቢህ) ውስጥ ወድቃችኋል። በዚህ ጊዜ፦ “አይ ወንድማችን! አንተ በስህተት ነው የተረዳኸን፤ እኛ እኮ የፈለግነው ለአላህ ክብርና ልቅና የሚመጥን፣ ከፍጡራን ቁጥጥር ጋር የማይመሳሰል ‘መቆጣጠር’ (ኢስቲላእ) ነው” ካሉን፤ እኛም እንዲህ እንላለን፦ “ሱብሓነላህ! ታላቅና ምስጉን ለሆነው አላህ ጥራት ይገባው!” እኛስ (አህሉሱናዎች) መጀመሪያውኑ ምን አልን? አላህ ለአምላክነቱና ለታላቅነቱ የሚመጥን፣ ከፍጡራን መሆን ጋር የማይመሳሰል “በዐርሹ ላይ ከፍ ማለት” (ኢስቲዋእ) አለው ነው ያለነው። ስለዚህ በእኛ አቋም ላይ የምትሰጡትን ማንኛውንም (የተሳሳተ) መልስ፣ እኛ በናንተ ቃልና መከራከሪያ ራሳችሁን መልሰን እንረታችኋለን (እንመክትባችኋለን)።» ታላቁ የዘመናችን የዐቂዳ  ዓሊም ሸይኽ ሷሊሕ አስ-ሰንዲ

የኡስታዝ ሳዲቅ ሙሐመድ (አቡ ሐይደር) መልእክት፣ ​📌 ከሐዲሥ ማስተባበል ጀርባ ያለው አስፈሪው እውነታ!
የኡስታዝ ሳዲቅ ሙሐመድ (አቡ ሐይደር) መልእክት፣ ​📌 ከሐዲሥ ማስተባበል ጀርባ ያለው አስፈሪው እውነታ!

🌷ሰባሑል ኸይር! ነቢያችን አዩብ (ዐለይሂ-ሰላም) በከባድ የድካምና የበሽታ ፈተና ወቅት ጌታቸውን በተማፀኑ ጊዜ፣ ብዙ የተንዛዙ ቃላትን ወይም ረዣዥም ዓረፍተ ነገሮችን አልተጠቀሙም። ይልቁኑ የዓመታት ስቃያቸውንና ሙሉ ታሪካቸውን በጥቂት፣ እውነተኛና ሙሉ እምነት (የቅንነት ስሜት) በሞላባቸው ቃላት እንዲህ በማለት አሳጠሩት፦ ”وَأَيُّوبَ إِذْ نَادَىٰ رَبَّهُ أَنِّي مَسَّنِيَ الضُّرُّ وَأَنتَ أَرْحَمُ الرَّاحِمِينَ“ > « አዩብም (አለ፦)እኔን መከራ አገኘኝ፤ አንተም ከአዘኞች ሁሉ ይበልጥ አዛኝ ነህ።» *(አል-አንቢያእ፡ 83)* > የሚፈልጉትንና ያሰቡትን በግልጽ የሚያሳይ፣ አላህ በላኡን እንዲያነሳላቸው የሚማጸን ቀጥተኛና ቀላል መግለጫን ተጠቀሙ። የዓለማቱ ጌታ የሆነው አላህም ምላሽ ሰጣቸው፦ { فَاسْتَجَبْنَا لَهُ فَكَشَفْنَا مَا بِهِ مِن ضُرٍّ ۖ} > «ለእርሱም ዱዓውን ተቀበልነው፤ ከእርሱም የነበረውን መከራ አስወገድንለት።» *(አል-አንቢያእ፡ 84)* > አላህ ካንተ የሚፈልገው በዱዓህ ላይ የቃላት ውበትና የቋንቋ ብቃትን (በላጋን) አይደለም፤ ይልቁኑ እውነተኛና ቅን የሆነን ልብ ነው! በልብህ ውስጥ ያለውን ስቃይ፣ ግራ መጋባትና ስብራት ይዘህ ወደ እርሱ ዱዓ አድርግ፤ በውስጥህ ያለውን እሮሮ ለእርሱ ብቻ አዋየው። እርሱ (ሱብሓነሁ ወተዓላ) ሁሉንም ነገር ያስተካክላል፣ የተሰበሩ ልቦችንም ይጠግናል። #መልካም_ማለዳ

የጁምዓ ኹጥባ መልክት የነቢዩ ﷺ ሱና በኢስላም ያለው ቦታና ምንጭነቱ 📜✨ ውድ ወንድሞች! የነቢዩ ﷺ ሱና የኢስላም ሁለተኛው ዋና የሸሪዓዊ የዕውቀት ምንጭ ነው። ሱና የቁርኣን ማብራሪያና የነቢዩ ﷺ ተግባራዊ ሕይወት በመሆኑ፣ ያለ እሱ እስልምናን በትክክል መረዳትም ሆነ መተግበር አይቻልም። የሱና ደረጃ በኢስላም አላህ ሱብሃነሁ ወተዐላ ቁርኣንን አጠቃላይ የሆኑ ሕግጋት(ሙጅመል)አድርጎ ሲያወርደው፣ ሱና ደግሞ ዝርዝር ማብራሪያ (ሙበዪን)እንዲሆን አድርጎታል። * ለምሳሌ በቁርኣን፦ አላህ ሶላት እንድንሰግድ አዟል። * በሱና ግን፦ እንዴት እንደምንሰግድ፣ ስንት ረከዓ እንደምንሰግድና የሶላት አሰጋገድ ነቢያችን ﷺ *“እኔ ስሰግድ እንዳያችሁኝ ስገዱ”* በማለት በተግባር አሳይተውናል። ሱናን የመከተል ግዴታ (የሱና ሁጃነት) የነቢዩን ﷺ ሱና መቀበልና መከተል በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ መሆኑን ቁርኣን በግልጽ አስቀምጧል፦ 1. አላህን መታዘዝ ነቢዩን ﷺ ከመታዘዝ ጋር የተያያዘ ነው፦ > «መልእክተኛውን የሚታዘዝ በእርግጥ አላህን ታዝዟል።» [አን-ኒሳእ: 80] > 2. ነቢዩን ﷺ አለመታዘዝ ለቅጣት ይዳርጋል፦ > «እነዚያም ትእዛዙን የሚጥሱ መከራ እንዳትደርስባቸው ወይም አሳማሚ ቅጣት እንዳያገኛቸው ይጠንቀቁ።» [አን-ኑር: 63] > 3. ያለ ሱና ኢስላም ሙሉ አይሆንም፦ > «በጌታህም እምላለሁ በመካከላቸው በተከራከሩበት ነገር ፈራጅ እስከሚያደርጉህ... ድረስ አላመኑም።» [አን-ኒሳእ: 65] > ### 3️⃣ ሱናን ከማጣጣል መጠንቀቅ! ነቢያችን ﷺ ከብዙ ዓመታት በፊት እንዲህ ሲሉ አስጠንቅቀዋል፦ > *“አዋጅ! እኔ ቁርኣንና መሰሉ ን(ሱና) ተሰጥቶኛል። አንድ በአልጋው ላይ የተደገፈ ሰው ‘ቁርኣንን ብቻ ያዙ፤ በሱ ውስጥ ያገኛችሁትን ሐላል ሐላል በሉ፣ ሐራምንም ሐራም በሉ’ የሚልበት ጊዜ ሊመጣ ይቀርባል።”* [አቡ ዳውድ] > ዛሬ ላይ “ቁርኣን ብቻ ይበቃል፣ ሱና አያስፈልግም” የሚሉ አካላትን ስናይ የነቢዩ ﷺ ንግግር በተግባር ሲፈጸም እንመለከታለን። ሱናን መተው ማለት የዲንን ሙሉ ለሙሉ ክፍል ማፍረስ ማለት ነው። ምክንያቱም የዘካ ስሌት፣ የሐጅ ስነ-ስርዓት፣ የጋብቻና የንግድ ሕግጋት በዝርዝር የሚገኙት በሱና ውስጥ ብቻ ነው። 📌 ዋና መልእክት፦ የነቢያችን ﷺ እያንዳንዱ ንግግር ከአላህ ዘንድ የወረደ ወህይ ነው። ዲናችንን ከቢድዓና ከመጠራጠር ለመጠበቅ የነቢዩን ﷺ ሱና አጥብቀን እንያዝ፤ በሕይወታችንም ላይ እንተግብረው። *አላህ በሱና ላይ ቀጥ የምንል ያድርገን!* 🤲

ነቢዩ () የሚናገሩት ነገር ሁሉ ከራሳቸው ስሜት የመነጨ ሳይሆን ከአላህ የተላለፈላቸው ወሕይ  በመሆኑ፣ ሐዲሳቸውን መከተል ራሱን አላህን የመከተል ያህል ነው። ታላቁ የሶሪያ እና የሻም ምድር ፈቂህ እና የሐዲስ ሊቅ የሆኑት ኢማም አል-አውዛዒ የተነገሩት እጅግ ውብና ጥልቅ የሆነ ምክር፦
'አቡ ሙሐመድ ሆይ! ከአላህ መልክተኛ (ﷺ) ሐዲስ በደረሰህ ጊዜ፣ ከዚያ ውጭ በሆነ ሌላ ነገር እንዳታስብ (ሐዲሱን እንዳትጠራጠር)። [አቡ ሰህል ደግሞ፦ 'ከእሱ ውጭ ሌላ ንግግርንም እንዳትናገር (በገዛ አስተያየትህ እንዳትቃወመው)' በማለት ጨምረውታል]፤ ሙሐመድ (ﷺ) እኮ ከጌታቸው ዘንድ መልዕክትን  አድራሽ ብቻ ነበሩና።'"[ምንጭ፦ አል-ላልካኢ፣ ሸርሕ ኡሱል އިዕቲቃድ አህሊስ-ሱና ወል-ጀማዓ (ቅጽ 3 / ገጽ 478)]

## ​የ"ቁርአንዮች" ትልቁ ተቃርኖ፡ መጽሐፉን አግዝፎ ህጎቹን ማግለል! በዘመናዊው እስላማዊ የሃሳብ መድረክ ላይ፣ የነቢዩን ሱና (ሐዲስ) ከእስልምና ድንጋጌዎች በማራቅ "በቁርአን ብቻ እንብቃቃለን" የሚሉ ወገኖች ብቅ እያሉ ሲሆን፣ ተከታዮቻቸውም "ቁርአንዮች" (قرآنيون) በመባል ይታወቃሉ። ምንም እንኳን ስማቸው ሙሉ ሕይወታቸውና እውቀታቸው በአላህ መጽሐፍ ዙሪያ ብቻ ያጠነጠነ እንደሆነ ቢያሳይም፣ ተጨባጭ እውነታው ግን ከሚያስተጋቡት መፈክርና ከተግባራዊ እንቅስቃሴያቸው መካከል ሰፊ ልዩነት እንዳለ ያረጋግጣል። በዚህ ቡድን ላይ የሚታዩትን ዋና ዋና ተቃርኖዎች በሚከተሉት ነጥቦች ማጠቃለል ይቻላል፡ ### 1. ሙሉውን ቁርአን በቃል የመሸምደድ (ሒፍዝ) እጥረት ሃይማኖቴን በአንድ መጽሐፍ ብቻ እገድባለሁ ከሚል ወገን የሚገርመው ነገር፣ በመሪዎቻቸውም ሆነ በተከታዮቻቸው መካከል ሙሉውን ቁርአን በልቡ የሸመደደ (ሓፊዝ) ሰው ፈጽሞ አለመገኘቱ ነው። የአህሉ-ሱና ወል-ጀማዓ ዓለም በሁሉም የዕድሜ ክልል በሚገኙ በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ የቁርአን ሓፊዞች የተሞላ ሲሆን፣ ይህ ቡድን ግን እንከላከልለታለን የሚሉትን የመለኮታዊ ቃል ጽናትና መሠረት ይጎድላቸዋል። ### 2. የተጅዊድና ትክክለኛ አቀራረብ ደንቦችን ችላ ማለት ቁርአን የወረደው በድምጽ ተነቦ ሲሆን፣ ወደ እኛ የተላለፈውም ልክ በጽሑፍ እንደተላለፈው ሁሉ ትውልድ በትውልድ ባስተላለፈው (ተዋቱር) የድምጽ ጥበቃ ጭምር ነው። ሆኖም ግን፣ "ቁርአንዮች" ለተጅዊድና ለፊደላት መውጫ (መኻሪጅ) ህጎች ምንም ዓይነት ትኩረት እንደማይሰጡ በግልጽ ይስተዋላል። ይልቁንም ኡማው (የእስልምና ማህበረሰብ) ከትውልድ ወደ ትውልድ ያሸጋገረውን ሥርዓት በጣሰ መልኩ እንደ ተራ ጽሑፍ ያነቡታል። ይህ ችላ ባይነታቸው የሚያሳየው ለቁርአን ያላቸው አቀራረብ የአምልኮና የስርዓተ-ተልዕኮ ሳይሆን፣ ዘመናዊ (ሀዳሲ) የሆነ ምሁራዊ እይታ ብቻ መሆኑን ነው። ### 3."ዑሉሙ አል ኣላህ" እውቀቶች(علوم الآلة) መራቅ ቁርአንን በትክክል ለመረዳትና ድንጋጌዎቹን ለመገንዘብ፣ የእስልምና ሊቃውንት "ዑሉሙ አል ኣላህ" በመባል የሚታወቁ ጥብቅ የሆኑ መሠረታዊ ሕጎችን አስቀምጠዋል። እነዚህም፡- (የአረብኛ ሰዋስው (ናህው እና ሳርፍ)፣ በላጋህ ፣ ኡሱል አል-ፊቅህ  እና የተፍሲር ሕጎች) ናቸው። * የሱና አስተባባዮች እነዚህን እውቀቶች ሙሉ በሙሉ ያጣሉ፤ * በእነዚህ ምትክ "ዘመናዊ ንባብ" (القراءة المعاصرة) በሚል ስም በምዕራባውያን አስተሳሰብ ወይም በግል ስሜታዊ ምክንያታዊነት ላይ ይመረኮዛሉ፤ * የእነዚህ መሣሪያዎች መቅረት የአረብኛ ቋንቋ ሰዋስው ወደ መጣስና ቁርአን ከወረደበት የአረብኛ ልሳን መሠረታዊ ህግጋት ጋር የሚጋጭ ላዩን ብቻ የሆነ ደካማ ግንዛቤ ላይ እንዲወድቁ ያደርጋቸዋል። > ማጠቃለያ፡ > የሱና አስተባባዮችን "ቁርአንዮች" ብሎ መጥራት እውነታውን የማይገልጽ ዘይቤያዊ አገላለጽ ብቻ ነው። ምክንያቱም ቁርአንን ከመሸምደድ የራቀ፣ ተጅዊዱን ችላ ያለ እና እሱን ለመረዳት የሚያስፈልጉትን የቋንቋና የመሠረታዊ (ኡሱል)እውቀቶች ያጣ አካል እንዴት "ቁርአንን ተከታይ ነኝ" ሊል ይችላል? ይህ ጥሪ የተመሠረተው መጀመሪያ ሱናን በማፍረስ ላይ እንጂ፣ ቁርአንን የሚያገለግል እውነተኛ የእውቀት ግንባታ ላይ አይደለም። >