የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)
ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡ አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን! ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን! ♻: https://api.whatsapp.com/send?phone=
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official) analitikasi
የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official) (@sultan_54) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 13 503 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 6 549-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 504-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 13 503 obunachiga ega bo‘ldi.
25 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 1 ga, so‘nggi 24 soatda esa -2 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 18.42% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 5.84% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 2 487 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 789 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 30 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡
አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን!
ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን!
♻: https://api.whatsapp.com/send?p...”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 26 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
"ዐብዱረዛቅ አል-በድር አባቱ ሸይኼ ነው፣ እሱ ደግሞ ተማሪዬ ነው፤ ዛሬ ግን እሱ ከእኔ ይበልጣል" ብለዋል።የሕይወት ታሪካቸውንና ትምህርቶቻቸውን ያስተዋለ ሰው አላህ የሰጣቸውን የብስለት አእምሮ፣ ጥበብና ቀጥተኛ አካሄድ በግልጽ ይመለከታል። እውቀትን ከተግባር፣ ዐቂዳን ደግሞ ነፍስን ከማጥራት(ተዝኪየቱ አን ነፍስ) ጋር ለማገናኘት ያላቸው ልዩ ትኩረት ይታያል፤ በዚህም የተነሳ የትምህርት መጃሊሶቻቸው በትህትና እና በሰኪና (በመረጋጋት) የተሞሉ ናቸው። በዒልማቸው በሳዑዲ ዓረቢያ ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ በርካታ ሕዝብ ተጠቃሚ ሆኗል። ታዋቂ ማብራሪያዎቻቸውና ትምህርቶቻቸው (ሸርሆች) ሸርሕ አል-ቀዋዒድ አል-ሙሥላ (شرح القواعد المثلى) ሸርሕ አል-ከሊም አጥ-ጦይብ (شرح الكلم الطيب) ሸርሕ ቀዋዒድ አል-አስማእ አል-ሑስና (شرح قواعد الأسماء الحسنى) ሸርሕ ሐሺየት ኢብን አቢ ዳውድ (شرح حاشية ابن أبي داود) የዋሲጢያህ፣ የሉምዐቱል ኢዕቲቃድ፣ የመሳኢል አል-ጃሂሊያህ እና የሌሎች ሰለፎች የዐቂዳ ኪታቦች ማብራሪያ። የሪያዱ አስ-ሷሊሒን፣ የተጅሪድ አስ-ሶሪሕ፣ የሙኽተሰር ሶሒሕ ሙስሊም እና የአርበዒን አል-ነወዊያህ ማብራሪያ። በስነ-ምግባርና በባህሪ ዙሪያ ጠቃሚ ትምህርቶች አሏቸው፤ ከእነዚህም፦ የአድ– ዳእ ወድ-ደዋእ ፣ የአኽላቅ ሐመለቲል ቁርዓን እና የዋቢል አስ-ሰዪብ ማብራሪያዎች። ታዋቂ መጽሐፎቻቸው ፦ ፊቅህ አል-አድዒያህ ወል-አዝካር (فقه الأدعية والأذكار) አል-ሐጅ ወተህዚብ አን-ኑፉስ (الحج وتهذيب النفوس) ተዝኪረቱል ሙእተሲ ሸርሕ ዐቂዳህ ዐብደልገኒ አል-መቅዲሲ (تذكرة المؤتسي) ዲራሰቱ አሠር አል-ኢማም ማሊክ ፊ ባብ አል-ኢስቲዋእ (دراسة أثر الإمام مالك) ተዕዚም አስ-ሶላት (تعظيم الصلاة) በሐዲስ፣ በፊቅህ፣ በዐቂዳና በስነ-ምግባር ዙሪያ የተሰሩ ምርምሮችና ጥናቶች። ፊቅህ አል-አስማእ አል-ሑስና (فقه الأسماء الحسنى) እነዚህና ሌሎች ጠቃሚ መጽሐፎች ያሏቸው ሲሆን፣ በቅርቡ መጽሐፎቻቸውና መልዕክቶቻቸው በሙሉ በአንድ ጠቃሚ ጥራዝ ተሰብስበው ታትመዋል። ማጠቃለያ፦ እሳቸው አላህ እውቀትንና ተግባርን፣ ማስረጃንና ርህራሄን፣ ሱናንና መልካም ስነ-ምግባርን በአንድ ላይ የሰበሰበላቸው ሸይኽ ናቸው። በመሆኑም ለአስተማሪ ዳዒና መካሪ ዓሊም ምርጥ ምሳሌ ናቸው። የእውቀት ፈላጊዎች ወደ መጽሐፎቻቸው እንዲዞሩ፣ ትምህርቶቻቸውን እንዲያዳምጡ እና ዐቂዳን በማረጋገጥ፣ ነፍስን በማጥራትና በመልካም አስተዳደግ ረገድ ካላቸው ጠንካራ አካሄድ እንዲጠቀሙ እንመክራለን። አላህ ሸይኹን ይጠብቃቸው፣ በእድሜያቸውና በእውቀታቸው ላይ በረከትን ያድርግላቸው፣ እስልምናንና ሙስሊሞችንም በእሳቸው ይጠቅም ዘንድ እንለምነዋለን።
"አላህ መሸጥን ፈቀደ፤ ወለድን ግን እርም አደረገ።" (አል-በቀራህ፡ 275)እንዲሁም አላህ እንዲህ ብሏል፦
"እናንተ ያመናችሁ ሆይ! እስከ ታወቀ ጊዜ ድረስ ባለ እዳ በተዋዋላችሁ ጊዜ ጻፉት።" (አል-በቀራህ፡ 282)ይህ ገዥ ዕቃው በሁለት የተለያየ ዋጋ ቀረበለት ማለት ነው፤ በጥሬ ገንዘብ (በካሽ) የሚከፈል ዋጋ እና በጊዜ ገደብ (በክሬዲት) የሚከፈል ዋጋ። ለምሳሌ የጥሬ ገንዘቡ ዋጋ 100 ነው እንበል፤ የጭልፊቱ ዋጋ ደግሞ 150 ነው፤ እሱም በዚያው በተቀመጡበት መጅሊስ ከቦታው ሳይበተኑ የክሬዲቱነረ (የ150ውን) መረጠ። ከዚያም ዕቃውን ይዞ ሄደ። በዚህ ጊዜ በእሱ እዳ ላይ 150 ዲናር በትክክልና በግልጽ ተቀምጦ ጸና። ይህ ዓይነቱ ሽያጭ ምንም ችግር የሌለበት ትክክለኛ ሽያጭ ነው። ምክንያቱም ገዢው በዚህ ወይም በዚያኛው ዋጋ ለመግዛት ምርጫ ተሰጥቶታል። ይህ ደግሞ በምንም መልኩ ከወለድ (ሪባ) ጋር አይገናኝም። ምክንያቱም ወለድ ማለት "ብርን በብር" (ገንዘብን በገንዘብ) ላይ ጨምሮ መሸጥ ማለት ነው። እዚህ ጋር ግን እየተሸጠ ያለው ዕቃ ነው፤ ዕቃን ደግሞ በጥሬ ገንዘብ ሲሆን በዚህ ዋጋ፣ በጊዜ ገደብ ሲሆን ደግሞ በዚያ ዋጋ መሸጥ ሙሉ በሙሉ የተፈቀደ ነው። እንዲሁም ይህ ሽያጭ ነቢዩ (ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም) ከከለከሉት "በአንድ ሽያጭ ውስጥ ሁለት ሽያጭ ማድረግ" (بيعتين في بيعة) ከሚለው ክልከላ ውስጥ አይገባም። ምክንያቱም እዚህ ጋር የተፈጸመው አንድ ሽያጭ ብቻ ነው። ሰውየው በሁለት አማራጮች መካከል ምርጫ ተሰጥቶት አንደኛውን መርጦ በአንዱ ላይ ብቻ ተስማምቶ ወጥቷልና።
የአላህ መልእክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ «የጠራችሁን ሰው ጥሪ ተቀበሉ (እሺ በሉ)፣ ስጦታን አትመልሱ፣ ሙስሊሞችንም አትምቱ።» (አህመድ ዘግበውታል፣ አልባኒም ሰሂህ ነው ብለውታል)የሐዲሱ ማብራሪያ (የግርጌ ማስተዋሻ) «የጠራችሁን ሰው ጥሪ ተቀበሉ»፦ ይህ የሰርግ ድግስም ይሁን ሌላ ማንኛውም ዓይነት ምግብ ላይ እንዲገኝ የጠራውን ሰው ጥሪ ምላሽ እንዲሰጥ የታዘዘበት ነው። «ስጦታን አትመልሱ»፦ ይህ ደግሞ ሁለተኛው ትዕዛዝ ሲሆን፣ የቀረበን ስጦታ ባለመመለስ መካከል ላይ ፍቅርና መተሳሰር እንዲኖር ያደርጋል። «ሙስሊሞችንም አትምቱ»፦ ይህ ሦስተኛው ትዕዛዝ ሲሆን፣ ያለ ምንም (ሸሪዓዊ ቅጣት) ወይም ያለ አግባብ ሙስሊሞችን ከመምታትና ከመበደል መቆጠብን ያዛል። መሠረቱ ግን ከእነሱ ጋር በቃልም ሆነ በተግባር በደግነትና በለስላሳነት መኖር ነው።
"ሰዎች ከሸሪዓዊ አውራዶች (የጠዋትና የማታ ዚክሮች) በዘነጉ ጊዜ፤ በእነሱ ላይ ጅን በዛባቸው፣ ተጫወተባቸውም (አላገጠባቸውም)።"• ሊቃኡል ባቢል መፍቱህ (197)
የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፦ "ሁለት ጸጋዎች አሉ፤ ከሰዎች አብዛኛዎቹ በእነሱ (በአጠቃቀማቸው) ይሸወዳሉ ፦ እነሱም ጤና እና ትርፍ ጊዜ ናቸው።" (ቡኻሪ ዘግበውታል)
