የወራቤ ሰለፊዮች መገናኛ
Open in Telegram
📝👉በአላህ ፍቃድ በዚህ ቻነል በወራቤ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ መድረሳዎች የሚሰጡ የሰለፊዮች ደርስ ፣ሙሃደራ እንዲሁም መልእክቶች የሚተላለፉበት ይሆናል !!! https://t.me/ibnbaz1212
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
3 101
Subscribers
No data24 hours
+317 days
+44830 days
Posts Archive
3 101
Repost from አብራር አወል ( Abu ubeyda)
ልዩ አዲስ ሙሃዶራ
ሱናን አጥብቆ መያዝ እና ግዜን በአግባቡ መጠቀም በሚል ሪእስ የተደረገ
ሐምሌ 27/12/2018
🕌 በአል-ወሰጢያህ መድረሳ እና መርከዝ
🎤በዶ/ር ሸይኽ ሁሰይን ቢን ሙሀመድ አስ-ስልጢይ
https://t.me/AbraribnAwal
3 101
📝የሉምዐቱል ኢዕቲቃድ ኪታብ ማብራሪያ
╭─••°─═•°•═─•••─╮
📖 ደርስ ክፍል 009📖
╰─••°─═•°•═─•••─➥
📝የኪታቡን PDF ለማግኘት ➴➷
https://telegram.me/ibnbaz1212/302
🏢በወራቤ ከተማ ዘሞ ባቴ ጤና ጣቢያ ሰፈር ኢብኑ ባዝ መድረሳ ለይ የሚሰጥ ትምህርት
🎙በኡስታዝ አቡ ኑህ
የቴሌግራም ቻነል ➘➷➴➘➷
https://t.me/ibnbaz1212
➥➥➥➥➥➥➥➥➥➥➥
https://t.me/MisbahMohammed_6682
3 101
Repost from 𝐒𝐞𝐦𝐢𝐫 𝐉𝐞𝐦𝐚𝐥 (𝐀𝐛𝐮 𝐇𝐚𝐟𝐬𝐚𝐡)
🛑 ቡድንተኝነት (ሂዝቢይየህ) እንዲሁም የወላእ እና በራእ መበላሸት...
በዚህ ዘመን እጀግ በጣም አውዳሚና አደገኛ ከሆኑ ቢድዓዎች መካከል ወደ ዳዕዋው መድረክ ሙብተዲዕ በሆኑ አንጃዎች እና ቡድኖች ሰርጎ የገባው ውዴታቸው፣ጥላቻቸው፣እንዲሁም ዳዕዋቸው ለአላሁ ሱብሃነ ወተዓላ ሳይሆን፣ ለቡድናቸው ወይም ለፓርቲያቸው፣ለፖለቲካ አይዲዮሎጂያቸው፣ለሱፊይነታቸው ለሸይኻቸው—የነሱ ሸይኻቸው ያለምንም ቅድመሁኔታዎች ወይም ያለምንም ጥያቄ፣ በል እንዲያውም ሸይኻቸው በግልፅ መረጃዎች የመጡበትን ቢቃረን ወይም ቢጥስ ንግግሩ ተቀባይነት አለው።
ስለዚህ የቢድዐህ ሰዎች "ወላእ እና በራእ" ቁርኣንና ሱንናን እንዲሁ ዐቂዳ፣ተውሒድና መንሐጅን መሠረት ያደረገ አይደለም። እንዲህ አይነት ተሀዙብን አላህ በቁርኣኑ በብዙ በታዎች ላይ ያወገዘበትና የኮነነበት ነው፤እንዲሁ በተረጋገጡ በሶሒህ ሐዲሶች ላይ የተወገዘበት ነው።
አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ሙእሚኖችን ገመዱን አጥብቀው እንዲይዙ፣ በዛው ላይ አንድ እንዲሆኑና እንዳይከፋፈሉ አዝዟል። ስለዚህ፣ ወዳጅነታችን እና ጥላቻችን በእውነት ላይ—ማለትም በቁርኣን እና በሱና ላይ በመጣበቅ ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት።
አንድ ሰው የአህሉስ-ሱናን 'አቂዳ' (እምነት) የሚቃወም ከሆነ፣ የሱን ተቃውሞውን አሽቀንጥረን እንጥለዋለን፣ከሱም እንርቃለን፣ ስህተቶቹን እንዲያስተካክል እና ወደ እውነት እንዲመለስ ለእሱንም ሆነ ለከታዮቹን ጥሪ እናደርጋለን። በተመሳሳይም፣ሱናን እና የሶሃባዎችን መንገድ የሚቃወም ከሆነ፣ ያንን ተቃውሞ እንጥላለን፣ እናስተካክለዋለን፣ ተቃውሞውን የማያስተካክል ከሆነ፣ ቀደምት ሰለፎች ከነበሩበት መንሐጅ (መንገድ) በሚታወቀው መሠረት ከሱ እንርቃለን።
አንድ ሙብተዲዕ ከተዘፈቀበት ቢድዐው ተውባ ካደረገ፣ ከዚህ በፊት ሲቃወም የነበረውን ሐቅ ከተወ፣ካስተካከለ እና ካብራራ—ከዚያም በቁርኣን እና በሱና ላይ የሶሃባዎችን መንገድ (ረዲየላሁ ዐንሁም) በመከተል አጥብቆ ከያዘ፣ ያኔ ለእሱ የነበረን ጥላቻ ባደረገው ተውባ እንዲሁም በሐቅ ላይ በመጣበቁ ምክንያት፣ከዚህ በፊት ለሱ የነበረን ጥላቻ በወዳጅነት ይቀየራል።
ይህ የሚያሳየው ከዚህ በፊት የነበረን ጥላቻ፡ በግል ምክንያቶች፣ በዘር፣ በብሔር፣ በጎሳ፣ በሀብት፣ በድሎት ወይም በድህነት ላይ ሳይሆን፣ይልቁንም፣ለሰዎች ያለን ፍቅር እና ጥላቻ ከቁርኣን እና ከሱና ጋር ያላቸው ቁርኝት ወይም ከነሱ (ከቁርኣንና ሱንና) መራቅ ላይ የተመሠረተ ነው።
የቡድንተኞች ቡድኖች እነዚህን መርሆች አይከተሉም፣ ምክንያቱም ወዳጅነታቸውንና ጥላቻቸው የተመሰረተው: በቡድናቸው፣ በፓርቲያቸው ወይም በሸይኻቸው ላይ ነውና። ወዳጅነታቸው እና ጥላቻቸው የሚሽከረከረው በፈጠሯቸው (በፈበረኳቸው) መርሆች፣ ከፍ ባሉ ግለሰቦች እና በቡድንተኝነት ወዳጅነቶች ዙሪያ ነው።
ለምሳሌ ዐሻኢራዎች እና ዲዮባንዲያዎች፣ አላህ ከሰባት ሰማያት በላይ፣ ከዐርሹ በላይ፣ ከፍጥረት የተለየና የላቀ እንደሆነ የሚያረጋግጡትን ይጠላሉ፣ ይቃወማሉ እንዲሁም ምላሽ ይሰጣሉ—አላህ ከርሽ በላይ መሆኑ፣በቁርኣንና በሱና የተረጋገጠ እንዲሁ የነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እና የባልደረቦቻቸው እምነት ሆነ ሳለ።
እነዚህ ቡድኖች፡ ኪታብን (ቁርኣንን)፣ ሱናን እና የሶሃባዎችን መንገድ የሚቃወሙ መርሆችን ይዘው ይቆያሉ፣ እናም በእነዚህ አንጃዎች ላይ "አል-ወላእ ወል-በራእ" (ወዳጅነትና ጥላቻ) ያቋቁማሉ።
ለምሳሌ፣ "አል-ኢኽዋን አል-ሙስሊሙንን" ተመልከት፡- መርሆቻቸውና ተግባሮቻቸው ከቁርኣን እና ከሱና ጋር ቢቃረኑም፣ ተከታዮቻቸው ግን መርሆቻቸውን ለሚክዱ፣ ስህተታቸውን እንዲያስተካክሉ እና ቁርኣንን እና ሱናን እንዲከተሉ ለሚጠሯቸው ሰዎች ይቃወማሉ...በተመሳሳይም ተብሊጎች፣ ሱፊዮች..."ወዳጅነታቸው እና ጥላቻቸው" ለጀማዓቸው፣ለሸይኻቸው፣...ለተፈበረኩ አዝካሮቻቸው ነው።
ይህ የቢደዐህ እና የሂዝቢየህ አንጃዎች ዐበይት መታወቂያ ነው። "ወዳጅነታቸው እና ጥላቻቸው" የሚሽከረከረው በቡድኖቻቸው መርሆዎች ላይ ነው እንጂ አላህ ባወረደው በቁርኣን ላይ አይደለም። ይህ ተግባር ደግሞ፣የሱኒዮች (የሰለፊዮች) አይደለም—አላህ ወደ እውነት የመራው፣በልቡ ውስጥ የምሪትን ብርሃን ያደረገለት ሰውማ፣ሐቅን ይቀበላል፤ለሐቅ እጅ-እግር ይሰጣል፤ ባጢልን ይርቃል።
ሙእሚን በግለሰቦች፣ቡዙ ቁጥር ባላቸው አንጃዎች አይጣበቅም። እሱ ሚጣበቀው በአላህ ቁርኣን፣በመልእክተኛው (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሱንና እንዲሁ በሶሃቦች (ረዲየላሁ ዐንሁም) መንገድ ነው።
የሱ "ወዳጅነት እና ጥላቻ" ለአላህ ብሎ ነው። ለአላህ ብሎ ይሰጣል ለአላህ ብሎ ይከለክላል፣ወዳጅነት እና ጥላቻን ሚመሰርተው በእውነት ላይ ተመርኩዞ ነው እንጂ፣ ውሸት በሆነው በሂዝቢይነት (በቡድንተኝነት) ወይም ግለሰቦች ላይ አይደለም። አላህ ኢስቲቃመህ እንዲለግሰን እንማፀነዋለን።
✍ 𝐀𝐛𝐮 𝐊𝐡𝐚𝐝𝐞𝐞𝐣𝐚 (𝐌𝐚𝐲 𝐀𝐥𝐥𝐚𝐡 𝐩𝐫𝐞𝐬𝐞𝐫𝐯𝐞 𝐡𝐢𝐦)
📝 𝐀𝐦𝐡𝐚𝐫𝐢𝐜 𝐓𝐫𝐚𝐧𝐬𝐥𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧: 𝐀𝐛𝐮 Hafsah
https://t.me/semirEnglish
3 101
Repost from ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa
አዲስ 👉 ይደመጥ!!
🔷 ልዩ ተከታታይ ኮርስ
ርእስ:- ሺዐቱ ሸይጧን!!
በታላቁ ዓሊም ሸይኽ ሙሀመድ ቢን ሰዒድ ረስላን (ሀፊዘሁላህ) የተዘጋጀ
Pdf↘️↘️
https://t.me/IbnShifa/6377
⏯ ክፍል 29
🎙በኡስታዝ አቡ ሙዓዝ - ታጁዲን (ሀፊዘሁላህ)
ኮርሱ የሚሰጠው በ t.me/ibnshifa ቴሌግራም ቻናል ዘውትር እሮብና ሀሙስ ከምሽቱ:- 4:00 ጀምሮ ነው፣ በሰኣቱ ቀጥታ ተከታተሉ
#Join ⤵️⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa
Follow Ibn Shifa's WhatsApp Channel: ⤵️⤵️ https://whatsapp.com/channel/0029VbAU7moHgZWXXXnNiL3f
3 101
🌸 ጥያቄ 🌸
📖 ወደ አድ ሕዝቦች ተውሒድን እንዲሰብክ የተላከው ነብይ ማነው?
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
✅ ትክክለኛውን መልስ በመጫን
📲 ወደ ሰለፊዮች ቻናል ይቀላቀሉ!
3 101
Repost from አቡ ኑህ አስ'ስልጢይ [ Misbah Mohammed ]
🚫
በአንፃራዊነት ከኢብራሂም ቱፋ ንግግር ይልቅ የመሐመድ ሐሚድን ንግግር ለሙስሊሞች እጅግ አደገኛ ንግግር ነው !➧የኢብራሂም ቱፋ ንግግር በስልጣን ስካር የተነሳ የተናገራው መሆኑን ስለሚያውቁ ሙስሊሞች በንግግሩ አይሸወዱበትም እንዲሁም የሐገራችን ጠቅላይ ሚኒስተር አቢይ አህመድ ሙስሊም ከነበረ በኋላ ወደ ኩፍር እምነት የገባ ሙርድ ካፊር መሆኑንን ጠንቅቀው የሚያውቁ ከመሆኑ አንፃር የአላህ ወዳጅ ወሊይ ነው በሚለው የጠመመው ኢብራሂም ቱፋ ንግግር በሙስሊሞች ለይ ብዙም ተፅኖ አይፈጥርባቸውም ! ➧የመሐመድ ሐሚድን ንግግር ግን በሀገራችን በየቦታው ተሰራጭቶ ያለው አላህ ያለቦታ ነው ያለው የሚለው የአሀሸባሾችን እምነት የሚደግፈውን የሰይድ ቁጥብን መፅሐፍ ዚላሉል ቁርኣንን ደጋግሞ እየነሳ በማወደስ ነበር ያስተዋውቀው የነበር ። ➢በሐገራችን እያቆጠቆጠ ያለውን የሺዓ እምነት የሚደግፈውን ሰይድ ቁጥብን ርዕስ አድርጎ ይዞት እንደ እስላም ጀግና አስተዋውቆታል ። በጥቅሉ በነዚህና በሌሎችንም ምክንያቶች የተነሳ የሙሐመድ ሐሚዲን ንግግር ከኢብራሂም ቱፋ ንግግር የበሳ ለሙስሊሞች አደገኛ መሆኑን እንረዳለን ። የእነ ኤሊያስ አህመድ መጅሊስ ሰዎች በዚህ መልኩ በየግዜው የኩፍር ተግባራትንና ንግግሮችን መናገርን ቀጥለውበታል ። ➼የኔ ጥቆማ በነ ኤሊያስ አህመድ ለተሸወዱ ሙስሊሞች ፤የኔ ኤሊያስ አህመድና ባልደረቦቹ ከመጅሊስ ሰዎች የምንጨመረው አደጋቸውን ለመከላከል ነው ብለው እየተናገሩ አልነበረም ?። ➨ መጅሊስ ውስጥ በመግባታቸው ከነዚህ ጠማሞች ጋር አንድ መሆናቸውን በማወጅ ሀቅ ለይ እንዳሉ በመመስከር እየወደሱዋቸው በተቃራኒው ሰለፊዮች እያባረሩ መስጂዳቸውንና መድረሳቸውን እየቀሙ ከማሰቃየት በስተቀር የት አለ ከአህባሾችንና ከእኽዋኖችን ጥሜት ያስቀሩት ወይም የቀነሱት አደጋ ? ➨የት አላህ ለሙስሊሞች ያመጡት ጥቅም ?
ኧረ ተው እንንቃ ሙሪድነት ይብቃ ለእስልምና በእስልምና እንስራ በእስልምና ስም በእስልምና ለይ አንስራየሰዎቹን አደገኛ አካሄዶችን እያየን አንሸወድ ለሐበሻ ዲን ወዳድ ሙስሊሞች ሀቅን ከሀቀኞች መሆን በማድረስ አማናችንን እንወጣ። 📝ተጨማሪ ትምህርቶችን ለማግኘት የቴሌግራም Channeሉን ይቀላቀሉ !!! https://t.me/MisbahMohammed_6682
3 101
Repost from አቡ ኑህ አስ'ስልጢይ [ Misbah Mohammed ]
🚫ሰይድ ቁጥብ የእኽዋኖች መሪ !
⛔️የመሐመድ ሐሚድን በአዲስ መልክ የጥሜት ሰበካ ዘመቻ !
ሰይድ ቁጥብ ማለት ግብፅ ለይ ተወልዶ እዛው የሀገሩ መንግስት በሽብር ወንጀል ይዞ አስሮት እስር ቤት እንዳለ በጥፋቱ በሒጅራ አቆጣጠር በ1386 የተገደለ የእኽዋኖች ጥሜት አዳሽ የነበረ የኩፍር አይነቶች ሁሉም የተሰበሰቡበት በሙስሊሞች ለይ ከከሓዲያን በለይ አደገኛ ግለሰብ ነበር።
➷ሰይድ ቁጥብ ከሉበት ኩፍሪያት ቢደዐዎች መካከል ➴፦
➠ሰይድ ቁጥብ አላህ ሁሉም ቦታ ነው ያለው ብሎ ያምናል
➢ሰይድ ቁጥብ ቁርኣን መኽሉቅ ነው ብሎ ያምናል
➥ሰይድ ቁጥብ ሶሃባዎችን ይሳደባል
➨ሰይድ ቁጥብ ሙስሊሞችን በሙሉ ካፊር ሆነዋል ብሎ ይነገራል
➼የእኽዋኖች መሪ የነበረው ሰይድ ቁጥብ
የሺአዎችን ፣ የጀሕሚያዎችን ፣ የሙዕተዚላዎችን ፣ የአሻዒራዎችን እነ የተከፊሮችን የክህደት ቢድዐዎችን የሚከተል(የሚደግፍ) የነበረ አደገኛ የሙስሊሞች ጠላትነትን ግልፅ ያደረገ ሰው ነው። እነ ሸይኽ ኢብኑ ዑሰይሚን አላህ ይዘንላቸውና ስለ ኩፍሪያት ቢደዐዎቹ ከወሩ በኋለ በሕይወት ቢኖር ጥረቶቹን ነግረነው እንዲቶብት እናደርግ እነ እምቢ ከለ እንዲገደል ይደረግ ነበር ይላሉ።
➽የሐገራችን የእኽዋነል ሙስሊሚን የቢደዐህ ቡዱን መሪ ከሆኑ አንዱ መሐመድ ሐሚዲን ይህንን የጥሜታቸው አሚር የነበረውን ሰይድ ቁጥብን ሰሞኑን ስሙን አንስቶ ለሙስሊሞች ብዙ ስራዎችን የሰራ የጊዜው ደግ ዓሊም እንደነበረ ይነገርለታል ።
➷መጅሊስ አካባቢ ያሉ እኽዋኖች ለተራ ሙስሊሞች የተደበቀ ማንነታቸውን በደምብ ግልጽ እያደረጉ ነው ።
ባለፈው መሪያችን ነው የሚሉት ሙፍቲው ኢብራሂም ቱፋ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ነቢይ ነው እንዳንለው ከነቢያችን ﷺ በኋላ ነቢይ የለም ስለዚህ አቢይ አህመድ የአላህ ወሊይ ነው ብሎ በመናገር አደገኛ የኩፍር ንግግርን በአደባባይ ተናግሯል ።
3 101
Repost from አብራር አወል ( Abu ubeyda)
🔖አስደሳች ሰበር ዜና
━━━━━━━ ━━━━━━━
📢 ለአል-ወሰጢያ መድረሳ እና መርከዝ አካባቢ ነዋሪዎችና ደርስ ተከታታዮች በሙሉ!
~ ዛሬ እሮብ ነሓሴ 27/2018 ከወትሮው ለየት ያለ ታላቅ ወቅታዊ የደዕዋ ፕሮግራም ተዘጋጅቷል።
🎙 ተጋባዥ እንግዳችን፦
└─
ዶ/ር ሸይኽ ሁሰይን ቢን ሙሀመድ አስ-ስልጢይ(ሀፊዘሁላህ)📌 የደዕዋው ርዕስ፦ └─ «በግዜው ይገለፃል» ⏰ ሰዓት፦ [ ከመغሪብ እስከ ኢሻ ] 📍 ቦታ፦ [ አለም ባንክ - ስልጤ ሰፈር በአል-ወሰጢያ መድረሳ ] 📲 ለሌሎችም ሼር (Share) በማድረግ የኸይር ሥራው ተካፋይ ይሁኑ! https://t.me/AbraribnAwal https://t.me/AbraribnAwal
3 101
Repost from ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa
አህመዲን ጀበል "በቱፋ ላይ ስህተቱ የተከሰተው ከደስታ ብርታት የተነሳ ነው" ብሎ ለሞገተበት የተሳሳተ ፅሁፍ የተሰጠ ገላጭ የሆነ ምላሽ!!
—————
ሸይኽ ጧሀ ኸድር አል-ጂሚ (ሀፊዘሁላህ) እንዲህ አሉ:-
ከአህመዲን ጀበል ስህተት የመጅሊሳቸው መሪ ቱፋ የነቢይነትን መዕረግ ለመስጠት የተጣጣረበትን ስህተት በሚዛናዊነት ግርዶሽ ከደስታ ብዛት የተሳሳተ ለማስመሰል መሞከሩ ነው። አስቀያሚ የሆነን መንገድ በመጓዝ በፈጣጣነት ያለ ሀፍረት "ከደስታ ብዛት ነው የተሳሳተው" በማለት በእራሱ ላይ በመሀይምነቱ ፈርዷል። ይህ ደግሞ ግልፅ የሆነ ውሸት ነው፣ የመጅሊሱም መሪ ይህን አይሞግትም የአዕምሮ ባለቤት የሆነውም ሰው የሚቀበለው ነገር አይደለም።
1, ከነቢዩ ﷺ የመጣው "ከደስታ ብዛት ተሳሳተ" የሚለው ሀዲስ፣ አላህ ጥላው የጠፋችውን ግመሉን ስለመለሰለት በዋለለት ፀጋ አላህን ማመስገንና ማላቅ ፈልጎ ነው ምላሱ የቀደመው። እንዲህ ያለው ነገር ደግሞ በድንጋጤ አለያም በደስታ በአንድ ወይም በሁለት ቃላት በምላስ መከርበትና የቃላት ቦታ መለዋወጥ ምክንያት ሊከሰት የሚችል ነው።
ይህ ደግሞ ከመጅሊስህ መሪ በተቃራኒ ነው፣ የመጅሊስህ መሪ በሙሉ አገባብና አውዱን የጠበቀ የቃላት አሰካክ ተጠቅሞ ነው ይህን ቃል የተናገረው። ደስታውም ለሰዎች ከመከቱ'ል ሙከረመህ እንደምትክ ሆኖ ለሀጅ ጉዞ እንዲያገለግል ታቅዶ በተሰራ ስፍራ ነው።
2, ሌላው በሀዲስ የመጣው "ከደስታ ብዛት የተነሳ የተሳሳተው" ትክክለኛ ነገር ሊናገር ፈልጎ ነው እንጂ ቀድሞውኑ ስህተት ሊናገር አልነበረም።
3, ይህ ባሪያ ከሚፈልገው በተቃራኒ የተከሰተ የምላስ ወለምታ ነው፣ ይልቁንም ባሪያው የፈለገው ከመጅሊስህ መሪ በተቃራኒው ነበር። ለመሆኑ ጠ/ሚሩን የነቢይነት ማእረግ እንደሚገባው ከመናገር ተቃራኒ ነበር የፈለገበት? ለዚያ ነው እንዴ መልክተኝነት (ነቢይነት) ስለተደመደመ ወሊይነት ይገባሃል ያለው? አንተ የአደም ልጅ አዕምሮ ባለቤት ሆይ! እዚህ ጋር መናገር የፈለገው ከዚህ ሌላ ሆኖ ሳለ የተሳሳተው ቃል አለን? በተለይ የመጅሊሱን መሪ ንግግር ያደመጣችሁ የኦሮሚኛ ተናጋሪዎች ሆይ! እስቲ ንገሩን?
4, በተለምዶ የሰዎችን ሁኔታዎች በማወቅ ልምድ ያላቸው የፍርድ ቤት ዳኞች አንድ ሰው በሆነ ጥፋት ላይ በተደጋጋሚ በመውደቁ ምክንያት በድጋሚ ጥፋት ላይ ሲያገኙት "የፈለግኩበት ሌላ ነው… አስቤበት አይደለም…" ብሎ ሲሞግት ጥፋት ላይ የወደቀው የምር ድንገት ሳያስብ አምልጦት ይሁን አይሁን በጥንቁቅነቱና ባለው ራሱን መቆጣጠር ያውቁታል፣ የምር እንደሞገተው ከሆነ ይቀበሉታል፣ አለያ ግን ውድቅ ያደርጉበታል። [ይህን ዒራቂ የተናገረው ሲሆን አል-ወለዊይም ተቀብሎ በማንሳት አፅንቶታል]
ከዚህ አንፃር ደግሞ የመጅሊስህን መሪ ተጨባጭ ስናየውና ከርሱም የተለመደው ነገር፣ ሸሪዓን በሚፃረር ነገር ላይ መውደቁ ራፊዷዎችን መርዳቱንና ለእነሱም አጋርነቱን መግለፁን ይመስል…፣ ለዲናዊ ጉዳይ ምንም ቦታ አለመስጠቱ… ይህን መከላከልህንና ምክንያቱን እያወቀ የተጋለጠው አካል ሊያጠራህ ፊቱን ወዳንተ አላዞረም። እወቅ ይህ ለዲን ካለህ የሳሳ ግንዛቤ መሆኑ ነው።
አል-ኢማም ኢብኑ'ል ቀይም (ረሂመሁላህ) እንዲህ አሉ:- “ለዚያም ነው አላህ ጥራት ይገባውና ግመሉ ጠፍቶበት ተስፋ ከቆረጠ በኋላ በመገኘቱ የተነሳ ከደስታ ብዛት የተሳሳተውን ሰው ያልያዘው፣ ሲያገኛት ከደስታ ብዛት "አላህ ሆይ! አንተ ባሪያዬ ነህ እኔ ጌታህ ነኝ" ብሎ የተሳሳተው፣ ይህ ቃል ሳያስበው ድንገት በምላሱ ተከሰተ፣ በመሆኑም አላህ በዚህ አልያዘውም፣ ይህ ደግሞ አንድ ቁርኣን የሚቀራ ሰው ድንገት በምላሱ ላይ እንደሚፈጠረው የምላስ ወለምታ ነው።" እንዲህም አሉ:- "የባሪያው የምላስ ፍጥነት ከሚያስበው ተቃራኒ የሚከሰት የምላስ ወለምታ ይሆናል።"
ኢብኑ ሐጀር (ረሂመሁላህ) እንዲህ ብለዋል:- "አንድ ሰው በሆነ ነገር ላይ መናገር ይፈልግና ምላሱ ይቀድመዋል…"
ሸይኽ ኢብኑ ዑሰይሚን (ረሂመሁላህ) እንዲህ አሉ:- "ፈጥኖ ምላሱ በተናገረው ስህተት አይያዝም፣ ምክንያቱም ይህ ከርሱ የተገኘው ንግግር ይህ ሰው ሳያስበው የተናገረው ነው፣ ይልቁንም በምላሱ ቀድሞት ነው የተከሰተውና ከደስታ ብዛት የተሳሳተው። እንዲህ ያለው የምላስ ወለምታ ሰዎችን አይጎዳም፣ ምክንያቱም አስቦበት ስላልሆነ። ሆነ ተብሎ ታስቦበት የሚነገርን ንግግርና ሳይታሰብበት ድንገት በምላስ ወለምታ ምክንያት የሚከሰትን ንግግር መለየት ግድ ይላል።"
✍🏻ትርጉም:- ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa)
#Join ⤵️⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa
Follow Ibn Shifa's WhatsApp Channel: ⤵️⤵️ https://whatsapp.com/channel/0029VbAU7moHgZWXXXnNiL3f
3 101
Repost from የወራቤ ሰለፊዮች መገናኛ
➢የተከበራችሁ የኢብኑ ባዝ መድረሳ ደርስ ተከታታዮች ሰሞኑን ተቋርጦ የነበረው የሉምዐቱል ኢዕቲቃድ ኪታብ ቂርኣት ክፍል ዘጠኝ ነገ እሮብ ከፈጅር በኋላ በአላህ ፍቃድ ይቀጥላል ።
3 101
➢የተከበራችሁ የኢብኑ ባዝ መድረሳ ደርስ ተከታታዮች ሰሞኑን ተቋርጦ የነበረው የሉምዐቱል ኢዕቲቃድ ኪታብ ቂርኣት ክፍል ዘጠኝ ነገ እሮብ ከፈጅር በኋላ በአላህ ፍቃድ ይቀጥላል ።
3 101
ونسمع في هذه الآونةِ ما يَثْقُلُ على الأسماعِ، ويُؤْلِمُ القلوبَ
وقد استمعنا قبلُ إلى كلام سادات ابن كمال، حين قال: إن أهل المجلس عقلاء وفطناء، ناضجون وأذكياء.
ولكننا اليوم سمعنا من أحدهم، وهو إبراهيم «توفا»، يتطاول على مقام النبوة :يقول «لولا أن خُتمت النبوة بنبينا محمد، لكان هو، ولكن لا يمنعنا أن نقول: هو وليٌّ من أولياء الله». فانظروا إلى هذا الغلو!
فماذا تقولون بعد هذا، وقد كنتم تقولون بجواز الانضمام إلى هؤلاء ومجالستهم، بل كنتم تذمّون من يفاصل عنهم ويتميّز منهم بل كان كثير منكم يقول الخروج من أهل المجلس يعد كالخروج على أئمة المسلمين وستدلوا بقوله تعالى(وأؤلي الأمر منكم -مع أنه قياس مع الفارق
وهل تعذرون عنه بأنه أخطأ من شدة الفرح، كما عذر إلياس أحمد أحدَهم لما قال: «لو جاء نبيُّ الله موسى، ونبيُّ الله عيسى، ونبيُّ الله محمد، لا نجد مثل هذا الحظ أو كماقال
الله المستعان وعليه التكلان
اللهم ثبتنا على الصراط المستقيم
إنك جواد كريم وغفور رحيم
3 101
🔈 አስደሳች ዜና!
ከቢላል ኢብኑ ረባህ የቁርአን ሒፍዝ
እና የተርቢያ ማዕከል
✅ቢላል ኢብኑ ረባህ መርከዝ ባሉት ውስን ቦታዎች ተማሪዎችን በአዳሪ መርሃ-ግብር ተቀብለን ለማስተማር ምዝገባ ላይ እንገኛለን።
⏩ የመመዝገቢያ መስፈርቶች፦
✅ጾታ፦ ለወንዶች ብቻ (አዳሪ)
✅ እድሜ፦ ከ10 - 20 ዓመት
✅ ጤንነት፦ ከማንኛውም ተላላፊ በሽታ ነፃ የሆነ
✅ስነ-ምግባር፦ ለመርከዙ ህግና ደንቦች ተገዢ የሆነ
✅ ፍላጎት፦ ለመቅራት ከፍተኛ ፍላጎት ያለው
✅ክፍያ፦ ወርሃዊ ክፍያን መክፈል የሚችል
📒 የሚሰጡ የትምህርት አይነቶች፦
📖የቁርአን ሒፍዝ (በቃል መያዝ)
📖 የቁርአን ነዘር (ንባብ) እና ሙራጀዓ (ክለሳ)
📖 ቃዒደቱን ኑራኒያ እና የተጅዊድ ትምህርቶች
📖የተለያዩ የዲን ኪታቦች፦📖አቂዳ
📖የመንሀጅ
📖 የተጅዊድ
📖የፊቂህ
📖 የተርቢያ
📖 የሀዲስ ወዘተ ይሰጣሉ
📆ምዝገባ ቀናት፦ ከሰኔ 25-ጳጉሜ5 /2018
🗓ወደ መርከዙ መግቢያ ቀናቶች መስከረም 8-9
📲ለበለጠ መረጃ እና ለምዝገባ፦
0921566720 | 0725566720
🌐 አድራሻ፦ 💡አድራሻ፦ ካራ ቆሬ ወደ ባማ ሆስፒታል በሚወስደው ቅያስ 500 ሜትር ዝቅ ብሎ ውሃ ታንከሩ አጠገብ ቢላል ኢብኑረባህ መርከዝ
https://t.me/bilalibnurebahmedresa
3 101
Repost from 𝐒𝐞𝐦𝐢𝐫 𝐉𝐞𝐦𝐚𝐥 (𝐀𝐛𝐮 𝐇𝐚𝐟𝐬𝐚𝐡)
ስሜቱን (ዝንባሌውን) የሚከተልን ሰው እንዴት መለየት ይቻላል?
ሸይኽ ሷሊሕ አል-ፈውዛን (ሀፊዘሁላሁ ተዓላ) እንዲህ አሉ፦
❝...እውነትን ለሚፈልግና ስህተት ለሰራ ሰው በዚህ ማስረጃ ላይ ተሳስተሃል፣ በሱንና ላይ ስህተት ሰርተሃል ብትለው፣ እሱ ይህን ይቀበላል፤ምክንያቱም የእሱ አላማና ግብ እውነትን (ሐቅን) መፈለግ ነውና፣ የራሱን አስተያየት የበላይ ማድረግ አይደለም።
ሆኖም ግን፣ ዝንባሌውን ለሚከተል ሰው ስህተት ሰርተሃል ብትለው፣ይናደዳል እና በጣም ሀይለኛም ይሆናል፤ይህ ዝንባሌዎችን እንዳሁም ስሜቶችን የሚከተሉ ሰዎች መለያ (መታወቂያ) ምልክት ነው። እያንዳንዳቸው የራሳቸውን ዝንቤሌዎችና ፍላጎቶቻቸውን የበላይ ማድረግ ይፈልጋሉ።❞
📚 [ሸርሕ አስ-ሱንና አል-በርበሃሪ፣ (ገጽ: 56)]https://t.me/semirEnglish
3 101
Repost from طه خضر أبوعبد الله
الرد الكاشف لأباطيل Ahmedin ودعوى الخطأ من شدة الفرح
من مغالطة المدعو Ahmedin Jebel-አሕመዲን ጀበል
محاولته تبرير تطاول - رئيس مجلسه تفا - على مقام النبوة تحت ستار الإنصاف ونادى على نفسه بالجهل كعادته وسلك مسلكا شنيعا وادعى بلا خجل أنه: "أخطأ من شدة الفرح" وذلك كذب صريح لا يدعيه رئيس مجلسه ولا يقره عاقل.
يوضحه:
1/ أن الذي ورد فيه قول النبي الكريم صلى الله عليه وسلم: "أخطأ من شدة الفرح"
أراد أن يحمد الله بما أنعم عليه من رد راحلته وأن يعظمه فسبق لسانه إلى ذلك ومثله يحصل في اللفظة واللفظتين بانقلاب كلمة واحدة بدلا عن أختها قد ندت عن اللسان عند الذهول التام والدهشة
بخلاف رئيس مجلسه جاء بها في سياق منتظم وألفاظ متسقة وترتيب فكري ينافي الذهول والدهشة وفرحته نابعة عن إحياء بديل عن مكة المكرمة للحج إليها.!
2/ أن المخطئ هو من أراد الصواب فصار إلى غيره وقصد الصواب فأخطأ.
3/ أن هذا من سبق اللسان بما لا يريده العبد بل يريد خلافه.
بخلاف رئيس مجلسك فهل يريد إلا بيان أهليته لمقام النبوة لولا ختم الرسالة فاستحق الولاية؟
فهل هناك لفظة أخطأها وأراد غيرها يا عقلاء بني آدم؟
ويا من تتحدث باللغة الأورومية خاصة؟
4/ أن الذي جرت به عادة الحكام الحذاق منهم اعتبار حال الواقع منه ذلك، فإن تكرر منه ذلك وعرف منه وقوعه في المخالفات وقلة المبالات بأمر الدين لم يلتفتوا إلى دعواه ومن وقع منه ذلك فلتة وعرف بالصيانة، والتحفظ قبلوا قوله في ذلك. قاله العراقي ونقله الولوي وأقره.
وواقع حال رئيس مجلسك وما عرف منه من وقوعه في المخالفات كمناصرته لأهل الرفض وتضامنه معهم ورأى قلة مبالاته بأمر الدين وعلم الباعث على ذلك وسببه لم يلتفت لتبريرك المفضوح وعلم أنه من رقة دينك.
قال الإمام ابن القيم: ولهذا لم يؤاخذ الله سبحانه الذي اشتد فرحه بوجود راحلته بعد الإياس منها، فلما وجدها أخطأ من شدة الفرح، وقال: اللهم أنت عبدي وأنا ربك، فجرى هذا اللفظ على لسانه من غير قصد، فلم يؤاخذه به، كما يجري الغلط في القرآن على لسان القارئ.
وقال: وسبق اللسان بما لا يريده العبد بل يريد خلافه.
وقال ابن حجر: وهو من يريد أن يلفظ بشيء فيسبق لسانه إليه.
وقال ابن عثيمين: فلم يؤاخذ لأن هذا القول الذي صدر منه غير مقصود له، بل سبق على لسانه فأخطأ من شدة الفرح، فمثل هذا لا يضر الإنسان، لأنه ما قصده، فيجب أن نعرف الفرق بين قصد الكلام وعدم قصد الكلام.
