ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ
ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ። ‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ›› ት.ኢሳ 58÷3 https://youtu.be/csxxAMGtC4I ለመቀላቀል http://t.me/ortodoxtewahedo
显示更多📈 Telegram 频道 ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ 的分析概览
频道 ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ (@ortodoxtewahedo) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 62 633 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 810,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 503 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 62 633 名订阅者。
根据 11 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -770,过去 24 小时变化为 -23,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 5.45%。内容发布后 24 小时内通常能获得 N/A% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 411 次浏览,首日通常累积 0 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 25。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ።
‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ››
ት.ኢሳ 58÷3
https://youtu.be/csxxAMGtC4I
ለመቀላቀል
http://t.me/ortodoxtewahedo”
凭借高频更新(最新数据采集于 12 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
数据加载中...
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 12 六月 | +5 | |||
| 11 六月 | 0 | |||
| 10 六月 | +14 | |||
| 09 六月 | +1 | |||
| 08 六月 | 0 | |||
| 07 六月 | +25 | |||
| 06 六月 | 0 | |||
| 05 六月 | +7 | |||
| 04 六月 | +8 | |||
| 03 六月 | +7 | |||
| 02 六月 | 0 | |||
| 01 六月 | 0 |
| 2 | ቤተ ክርስቲያን፡- የመንግሥተ ሰማያት በር ናት “ዛቲ ይእቲ ኆኅታ ለሰማይ (ይህች የሰማይ ደጅ ናት) /ዘፍ 28÷17/”
በዚህ መሠረት ለእኛም በ40 ቀንና በ80 ቀን የተሰጠን ጸጋመንፈስ ቅዱስ እንዳይለየን ሕጉን ትእዛዙን መጠበቅና ጧት ማታ ወደ ቤተ ክርስቲየን መገስገስ ይገባል፡፡
ለዚህም የእግዚአብሔር ቸርነት" የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና የቅዱሳን ተራዳኢነት አይለየን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር | 3 612 |
| 3 | #በዓለ_ጰራቅሊጦስ
“ኢየኀድገክሙ ዕጓለ ማውታ ትኩኑ”
“ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም”
/ዮሐ.14÷18/
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከምታከብራቸው ዘጠኝ ዐበይት (ታላላቅ) በዓላት መካከል አንዱ የጰራቅሊጦስ በዓል ነው፡፡
ጰራቅሊጦስ፡- ቃሉ ግሪክ ነው፡፡ ጰራቅሊጦስ ማለት መጽንዒ በእምነት የሚያጸና፣ መንጽሒ ከኃጢአት የሚያነጻ፣ ናዛዚ ያዘኑትን የሚያረጋጋ፣ መስተፍሥሒ፣ ያዘኑትን የሚያስደስት፣ ከሣቲ ምስጢርን የሚገልጽ ማለት ነው፡፡
ጰራቅሊጦስ፡- መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ የጰራቅሊጦስ በዓል ታሪክ እንደሚከተለው ተገልጿል፡፡
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም የሚሠራውን ሥራ ከጨረሰ በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያትን ወደ አባቴ እሄዳለሁ (አርጋለሁ) ሲላቸው ደነገጡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም መደንገጣቸውን አይቶ“ኢይደንግጽክሙ ልብክሙ እመኑ በአግዚአብሔር ወእመኑ ብየ እስመ ውስተ ቤተ አቡየ ብዙኅ ማኅደር ወምዕራፍ ቦቱ” (ልባችሁ አይደንግጥባችሁ በእግዚአብሔር እመኑ በእኔም እመኑ በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ ማለት፡- በአባቴ ቤት በመንግሥተ ሰማያት ብዙ ማዕርገ ሀብታት አለ) (ዮሐ.14÷1) እንዲሁም /በዚሁ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 14÷18/ “ኢየኀድገክሙ ዕጓለ ማውታ ትኩኑ” (ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም) ሲል መድኃኒታችን ኢየሱሰ ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን አጽናንቷቸዋል፡፡
/በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 24 ቁጥር 49/ ላይም እንደተጻፈው የሰላም አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ሊያርግ ሲል ቅዱሳን ሐዋርያትን “አንትሙሰ ንበሩ ሀገረ ኢየሩሳሌም እስከ ትለብሱ ኃይለ እምአርያም” (እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ተቀመጡ) አላቸውና ዐረገ በሐዋ.ሥራ ምዕራፍ 2- ከቁጥር 1 ጀምሮ እንደተጻፈው እነርሱም ይህን አምላካዊ ቃል መሠረት በማድረግ በኢየሩሳሌም በጽርሐ ጽዮን በማርቆስ እናት በማርያም ቤት ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው ተሰብስበው ሳሉ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዐረገ በአሥረኛው ቀን በተነሣ በሃምሳኛው ቀን ጧት በሦስት ሰዓት ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል ወረደላቸው፡፡
ከዚህ በኋላ ፍርሃት ከውስጣቸው ወጣ መንፈሳዊ ድፍረት አገኙ፡፡ አንድ የዕብራይስጥ ቋንቋ ብቻ ነበር የሚያውቁት ሰባ አንድ ዓይነት ቋንቋ (የአገሩ ሁሉ ቋንቋ) ተገለጸላቸው፡፡ ከእነርሱ ቋንቋ ጋር በሰባ ሁለት ዓይነት ቋንቋ ተናገሩ፡፡
የአገሩ ሁሉ ቋንቋ የተገለጸላቸውም ሁሉንም በአገሩ ቋንቋ እንዲያስተምሩ ነው፡፡ ከተለያየ ክፍለ ዓለም የመጡ ሰዎች ነበሩና እነዚህ የገሊላ ሰዎች አይደሉምን? እንዴት የእኛን አገር ቋንቋ ሊናገሩ ቻሉ? በማለት ተገረሙና አመንትተው እርስ በርሳቸው እንጃ ይህ ምን ይሆን? አሉ፡፡ ሌሎች ግን ጉሽ የወይን ጠጅ ጠጥተው ሰክረው ነው አሉ፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ጴጥሮስ ከአሥራ አንዱ ጋር ቆመ ድምፁንም ከፍ አድርጎ እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፡-የይሁዳ ሰዎች በኢየሩሳሌምም የምትኖሩ ሁላችሁ፡- ይህ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን ቃሎቼንም አድምጡ፡፡
ለእናንተ እንደመሰላችሁ እነዚህ የሰከሩ አይደሉም ከቀኑ ገና ሦስተኛ ሰዓት ነውና፡፡ ነገር ግን ይህ በነቢዩ ኢዩኤል የተነገረው ይፈጸም ዘንድ ነው፡- ይህም “እግዚአብሔር ይላል፡- በኋለኛይቱ ቀን እንዲህ ይሆናል ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፣ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፣ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ፡፡
ደግሞም በዚያች ወራት በወንዶችና በሴቶች አገልጋዮች ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ትንቢትም ይናገራሉ፡፡ ድንቆችንም በላይ በሰማይ ተአምራትን በታች በምድርም ምልክቶችን ደምን እሳትንና ጢስንም እሰጣለሁ የምትገለጠው ታላቅዋ የእግዚአብሔር ቀን ሳትመጣ ፀሐይ ወደ ጨለማ ጨረቃም ወደ ደም ይለወጣል፡፡
የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል” /ኢዩ.2÷28-32/ ይህን መሠረት በማድረግ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ ልብን የሚነካ ትምህርት ሰጠ፡፡ ሕዝቡም ቅዱስ ጴጥሮስ በሰጠው ትምህርት ልባቸው ተከፈተ ቅዱስ ጴጥሮስንና ሌሎቹንም ሐዋርያት ወንድሞች ሆይ ምን እናድርግ? አሉአቸው፡፡
“ቅዱስ ጴጥሮስም ንስሓ ግቡ ኃጢአታችሁም ይሠረይ ዘንድ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ ኃጢአታችሁም ይሠረይላችኋል የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ፡፡ የተስፋው ቃል ለእናንተና ለልጆቻችሁ አምላካችንም ወደ እርሱ ለሚጠራቸው በሩቅ ላሉ ሁሉ ነው፡፡ ስለዚህ ራሳችሁን ከዚህ ክፉ ዓለም አድኑ” ብሎ መከራቸው፡፡ በዚችም ዕለት ሦስት ሺህ ሰዎች አምነው ተጠመቁ፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው የሞቱና የትንሣኤው ምስክሮች ሆኑ፡፡
የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ በነሱ ላይ ሲያድር ለቤተክርስቲያን ጉዞ አዲስ ምዕራፍ ተከፈተ፡፡ ይህ የጰራቅሊጦስ በዓል በግሪኮች ቋንቋ ጰንጠቆስጤ ይባላል፡፡ ጰንጠቆስጤ ማለት ሃምሳኛ ማለት ነው፡፡ ጌታችን ከተነሣ በኋላ ሃምሳኛው ቀን ነው፡፡ ይህም ዕለት በዓለ ሃምሳ፣ በዓለ ጰራቅሊጦስ ነው፡፡
እንዲሁም ታላቁ ሊቅ ቅ/ዮሐንስ አፈወርቅ ይህን በዓል በሚገባ አነጋገር “የቤተክርስቲያን የልደት ቀን” ብሎታል፡፡ ይህ በዓል በብሉይ ኪዳን የእሸት በዓል (በዓለ ሰዊት) ይባላል፡፡
እስራኤል የነጻነት በዓላቸውን ከሚያከብሩበት ከበዓለ ፋሲካ ጀምረው ሃምሳውን ቀን በዓል አድርገው ይሰነብታሉ፡፡ በሃምሳኛው ቀን በዓለ ሰዊትን (የእሸት በዓላቸውን) ያከብራሉ፡፡
በሀገራቸው ከመጋቢት እስከ ግንቦት ያለው ወቅት በሀገራችን ከመስከረም እስከ ኅዳር እንዳለው የእሸት ወራት (የጸደይ ወራት) ነውና የእሸት በዓላቸውን የሚያከብሩት በኦሪት ዘሌዋውያን /ምዕራፍ 23÷10-17/ በታዘዘው መሠረት ማንኛውም እስራኤላዊ ገበሬ ከዘራው ሁሉ በየአይነቱ እሸቱን ቆርጦ ተሸክሞ ወደ ምኵራቡ ይመጣል፡፡ በቤተ መቅደስ የሚያገለግለው ካህን ተቀብሎ ባርኮ ጸልዮ የሚጠበሰው እየተጠበሰ የሚታሸው እየታሸ በማኅበር አንድነት ይበላል፡፡ ይህም “ቀዳምያት” ይባላል፡፡
የመጀመሪያው ማለት ነው፡፡ ከማንኛውም በረከት የመጀመሪያው በእግዚአብሔር ፊት መቅረብ፣ ለእግዚአብሔር መሰጠት እንዳለበት ታዟልና፡፡
በዚህ መሠረት ከበዓለ ጰራቅሊጦስ የምንማረው፡- ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን “እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ተቀመጡ” ባላቸው መሠረት በኢየሩሳሌም ተቀምጠው ተስፋውን ሲጠባበቁ መንፈስ ቅዱስ ወርዶላቸዋል፡፡
ዛሬም መንፈስ ቅዱስ የሚወርድባት ኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ናት “ሚ መጠን ግርምት ዛቲ ዕለት ወዕፅብት ዛቲ ሰዓት እንተ ባቲ ይወርድ መንፈስ ቅዱስ እመልዕልተ ሰማያት (ይህች ቀን ምን ያህል የምታስፈራ ናት? ይህች ሰዓት ምን ያህል የምታስጨንቅ ናት? መንፈስ ቅዱስ ከሰማየ ሰማያት የሚወርድባት) /ሥርዓተ ቅዳሴ/ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ እንደ ወረደላቸው ለእኛም ሁል ጊዜ ይወርድልናል እንዲወርድልንም ሁል ጊዜ ወደ ቤተክርስቲያን መሄድ ይገባል፡፡ ከቤተክርስቲያን ተለይቶ ጽድቅ የለም፡፡” | 3 515 |
| 4 | ✝እውነት ለዘለዓለም ታሸንፋለች✝
Size:-68.7MB
Length:- 1:14:13
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
http://t.me/abagebrekidan
http://t.me/abagebrekidan | 2 552 |
| 5 | 没有文字... | 3 161 |
| 6 | 👑🌿እንኳን #ለግንቦት 21 ቀን የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የመገለጥ በዓል (ደብረ ምጥማቅ) በሠላም አደረሰን|አደረሳችሁ🙏🍇🙏
🍒የአርያም ንግሥት: የሰማይና የምድር እመቤት: የሰውነታችንም መመኪያ ቅድስት ድንግል ማርያም በዚች ዕለት በምድረ ግብፅ ለተከታታይ ቀናት ተገልጻለች::
🌿ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድረ ግብፅና ኢትዮዽያ በተሰደደ ጊዜ ከድንግል እናቱ: ከዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ዛሬ ደብረ ምጥማቅ በሚባለው ቦታ ላይ አርፎ ነበር:: ቦታውን ባርኮ ለዘለዓለም ያንቺ መገለጫ ይሁን ብሎም ቃል ኪዳን ገብቶላት ነበር::
🍒ጊዜው በደረሰ ሰዓት ደብረ ምጥማቅ ተገድሞ የበርካታ መነኮሳት ቤት ሆነ:: እመቤታችንም በልጇ ፈቃድ ግንቦት 21 ቀን አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን አስከትላት መጣች::
🌿በዚያ ሕዝበ ክርስቲያንም: አሕዛብም ተሰብስበው ለ5 ቀናት ከእመ ብርሃን ጋር ይሰነብታሉ:: እንግዲህ ልብ በሉት:- እንኳን የአርያም ንግስት: የአምላክ እናቱ እመቤታችንን ይቅርና በዚሕ ዓለም ሰይጣን ቤቱ ያደረጋቸውን: የመዝናኛው ኢንዳስትሪ ዝነኛ ሰዎችን ለማየት የዘመናችን ሰው እንዴት እንደሚቸኩል::
🍒እመቤታችንን በአካል መመልከት አይደለም ስሟን መጥራት ነፍስን ከሥጋ መለየት የሚችል ጣዕምና ደስታ አለው:: ባይሆን ይሔ ለሚገባውና ላደለው ብቻ ነው::
🌿የደብረ ምጥማቅና የአካባቢዋ ሰዎች ከእመቤታችን ጋር የሚቆዩባቸው ቀናት የዘለዓለም የሕይወት ስንቅ የሚይዙባቸው ናቸው:: ፈልገው የሚያጡት: ጠይቀው የማይፈጸምላቸው ምንም ነገር አልነበረም:: ነቢያት: ሐዋርያት: ጻድቃን: ሰማዕታት: ደናግል: መነኮሳት: መላዕክትና ሊቃነ መላእክት ለድንግል ማርያም ሲሰግዱ ይታዩ ነበርና:: እመ ብርሃንም እየመላለሰች ትባርካቸው ነበር::
🍒እነዚያ እርሷን ያዩ ዐይኖች: በፊቷ የቆሙ እግሮች ክብር ይገባቸዋል:: 5ቱ ዕለታት ሲፈጸሙ ሕዝቡ እመቤታችንን በዕንባ ይሰናበቷታል:: እመ ብርሃንም በብርሃን መስቀል ባርካቸው ከቅዱሳኑ ጋር ታርጋለች::
👑🌿የእመቤታችን ፍቅር፣ በረከትና ምልጃ አይለየን!🙏 | 3 115 |
| 7 | ምንኩስና_ምን_ማለት_ነው_አዲስ_እጅግ_ድንቅ.m4a | 3 552 |
| 8 | 没有文字... | 6 032 |
| 9 | 没有文字... | 0 |
| 10 | በዓለ ዕርገት ደረሰ " እንኳን አደረሳችሁ:: የሐሙስ ሰዎች ይበለን::
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን3🙏
☦️በዓል ዕርገት ( ዕርገተ ክርስቶስ)☦️
👉 በዓለ ዕርገት (ዕርገተ እግዚእ)ሐዋርያዊቷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከምታከብራቸው ከ፱ኙ ዐበይት የጌታ በዓላት መካከል የሥጋ ዕርገት በማህጸን የቃል እርገት በ፵ ቀን (በዓለ ዕርገት) አንዱ ነው🙏
🥀 በዓለ ዕርገት ከዓመት ዓመቱ ከፍ ዝቅ ብሎ ይዉላል የዘንድሮ ማለትም 2018 በዓለ ዕርገት ግንቦት (13) ሐሙስ ቀን ይዉላል
<በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፡፡(መዝ 67-68፡33)
👉ዕርገት> የሚለው ቃል ዐረገ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ከፍ ከፍ አለ ፣ ወደ ሰማይ ወጣ ማለት ነው፡፡
< ለምሳሌ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በአንቀጸ ብርሃን ላይ በስምሽ በመለመን በመማጸን የሰው ልጆችን ጸሎት ያሳርጋሉ እንዲል፡፡
🥀እንዲሁም በእሑድ ውዳሴ ማርያም ላይ :-
ራሱን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ያሳረገ እንዳለ፡፡
↔️ ደግሞም የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር በመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ" በማለት ዐረገ የሚለውን ቃል በአማርኛ (ወጣ) በማለት ይገልጸዋል::(ራእይ 8:4)
👉ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዓርብ ሞቶ ድሕነትን ከፈፀመ በኋላ በሦስተኛው ቀን የሞትን መውጊያ ሰብሮ ተነሣ፡፡
🥀ከዚህ በኋላ በሞቱ ቀቢጸ ተስፋ ይዟቸው የነበረውን ሐዋርያትና አርድዕትን በተደጋጋሚ ትንሣኤዉን በመግለጥ ያጽናናቸው ነበር፡፡
↔️ጌታችን ከሞት ከተነሣ ከኋላ ለ12ቱ" ሐዋርያት ኪዳንንና ትምሕርተ ሕቡዓትን በዝርዝር አስተምሯቸዋል፡፡
👉መድኃኔዓለም ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣ ጀምሮ እስከ 40 ቀን ድረስ ሐዋርያትን" አርድዕትን በጠቅላላው 120ውን ቤተሰብ ሲያጽናና ቆይቶ ለቅዱስ ጴጥሮስ ታላቅ አባት የመሆን ሥልጣንን ከሰጠው በኋላ 120ውን ቤተሰብ ወደ ደብረ ዘይት ይዞዋቸው ወጣ፡፡
🥀በዚያም ሳሉ ኃይልን እስክትለብሱ ድርስ በኢየሩሳሌም ጸንታችሁ ቆዩ የሚለውን ታላቁን የዕርገት መልእክት አስተላልፎ ከምድር ከፍ አለ፡፡
↔️በመላእክት ምስጋና (በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ) እንዲል ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡
👉ከዐይናቸዉም ተሰወረ ሐዋርያትም ወደላይ አንጋጠው አንገታቸውን አቅንተው ይመለከቱ ነበር፡፡ (ሐዋ 1፡2)
🥀 በዚህ ጊዜ ሁለቱ ብርሐናውያን መላእክት እንዲህ ሲሉ ተናገሯቸው:-
↔️የገሊላ ሰዎች ሆይ! ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ለምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁ እንዲሁ ይመጣል፡፡
👉ይህ ታላቅ የተስፋ ቃል የመላእክት ንግግር ከቅዱስ ዳዊት ትንቢት ጋር የተዛመደ ሲሆን የጌታችን ምጽአት በምሥራቅ በኩል እንደሚፈጸም ያሳያል፡፡
🥀 ሁለቱ መላእክት በንግግራቸው በዚህ ሲሄድ እንዳያችሁት በግርማ ደግሞ በዚህ ይመጣል ብለው ነበር፡፡
↔️በመሆኑም ጌታችን ያረገው በምሥራቅ ነው ደግሞ ለፍርድ የሚመጣው በምሥራቅ ነው ማለት ነው፡፡
☦️ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ለበዓለ ዕርገቱ በሰላም ያድርሰን አሜን3👏
< አምላክ በእልልታ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ፡፡ ዘምሩ ለአምላካችን ዘምሩ ፤ ዘምሩ ፣ ለንጉሣችን ዘምሩ፡፡ እግዚአብሔር ለምድር ሁሉ ንጉሥ ነውና:: በማስተዋል ዘምሩ፡፡ እግዚአብሔር በአሕዛብ ላይ ነገሠ::እግዚአብሔር በቅድስናው ዙፋን ይቀመጣል፡፡(መዝ 47፡5-8)
<እንሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ::እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ፡፡ እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው፡፡ ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ፡፡ እነርሱም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ፡፡(ሉቃ 23፡50-53)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር🙏
ወለወላዲቱ ድንግል🙏
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን3🙏 | 5 836 |
| 11 | 没有文字... | 0 |
| 12 | +++ በዓለ ዕርገት +++
እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ
በዓል እርገት አደረሳችሁ።
#እርገት የጌታችን የመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አበይት በዓላት አንዱ ነው።
"አልቦ ዘዓረገ ውስተ ሰማይ ዘእንበለ ዘወረደ እምሰማይ ወልድ ዕጓለመሕያው" ዮሐ ፫ ፤፲፫
ከሰማይ ከወረደው የሠው ልጅ በቀር ወደ ሠማይ የወጣ የለም
ዕርገት ማለት ወደ ላይ መውጣት ማለት ነው።
ጌታ እየሱስ ክርሥቶሥ ከሙታን ከተነሣ በ፵ ኛው ቀን ወደ ሰማይ ዓርጓል።ዐረገ በስብሀት ውስተ ሰማያት ወነበረ በየማነ አቡሁ ዳግም ይመጽዕ በስብሀት ሕይዎን ወሙታን፡ ጸሎተ ሀይማኖት
ይህውም "እርገት" የሚለው ቃል "ዐረገ" ከሚለው የግዕዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ከታች ወደላይ መውጣት ከፍ ከፍ ማለት ማረግ ማለት ነው።
በዓለ እርገት ጌታችን መድሃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በዚህ አለም የነበረውን የማዳን ስራ ጨርሶ ወደላይ መውጣቱንና በቀደመ ክብሩ በአብ ቀኝ መቀመጡ የሚከበርበት በዓል ነው።
በአሉ የሚውልበት እለት ሀሙስ (ከበአለ ትንሳኤው በአርባኛው ቀን) አይለቅም የጌታችን እርገት ከትንሳኤ በኋላ በአርባኛ ቀን ( ስድስተኛ ሀሙስ) የሚከበረው ቅዱስ ሉቃስ በሃዋርያት ስራ ላይ ዳግም አርባ ቀን እየታያቸው ስል እግዚአብሔር መንግስት ነገር እየነገራቸው በብዙ ማስረጃ ከህመማቱ በኋላ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው። እርገቱም የተፈፀመው ስለ ምፅዓቱ ባስተማረበትና ዳግም ይመጣል ተብሎ በሚጠበቅበት በደብረ ዘይት ተራራ ነው።
መልካም በዓል።
ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://t.me/weludebirhane
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ | 0 |
| 13 | ሥ ጋ ህ ን : አ ፍ ል ሰ ው : በ ው ስ ጡ : ያ ኖ ራ ሉ
ግንቦት 12 ቀን ቅዱስ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቅዱስ ዐፅማቸው ቀድሞ ካረፉበት (ከተቀበረበት) ሥፍራ (ደብረ አስቦ) አሁን ወዳለበት ሥፍራ (ደብረ ሊባኖስ) የተዘዋወረበት ቀን ነው፡፡
ስለ ቀናች ሃይማኖትህ
ስለ ልብህ ንጽሕናና ቅድስና
ስለ ብዙ ጾም ጸሎት ስግደትህ
ሃይማኖትን ለማስተማር መላዋን ኢትዮጵያን ስለመዞርህ
በሰባት ዓመታት ቁመት የአንዱ አገዳ እግርህ ስለ መሰበሩ
ወደ ኢየሩሳሌም ወርደህ ልዩ ልዩ የቅዱሳን ቦታዎች ስለ መሳለምህ
ከአረማውያን ሕዝብ ጋር በሃይማኖት ስትታገል ደምህን ስለ ማፍሰስህ
በማለት የሕይወት አክሊላትን ካቀዳጃቸው በኋላ
ዝክራቸውን በማዘከር መታሰቢያቸውን የሚያደርጉ ሁሉ በዚህ ዓለምም ሆነ በወዲያኛው ዓለም ፍጹም ዋጋና ፍጹም ክብር እንደሚሰጣቸው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለጻድቁ አባታችን ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቃል ኪዳን ገባላቸው ።
#ግንቦት_12_ቀን ደግሞ « በስምህ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ልጆችህ ሠርተው ሥጋህን አፍልሰው በውስጡ ያኖራሉ ›› አላቸው ።
© ✎﹏ዳዊት ተስፋዬ
ግንቦት 12 20 18 ዓ.ም | 0 |
| 14 | +++ አቡነ ተክለሃይማኖት +++
ግንቦት 12"የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት
የፍልሰተ አጽም በዓል አደረሰን ።
" አቡነ ተክለ ሃይማኖት ተክለ ሃይማኖት ማለት የሃይማኖት ተክል፣ ተክለ አብ ተክለ ወልድ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው ፡፡"
ተክል› ማለት ፍሬያማ ዕንጨት፣ ዛፍ፣ ቅመም፣ ቅጠላ ቅጠል፣ የሚበላ፣ የሚሸተት፣ ገነታዊ ዕፅ፣ እንዲሁም ሕግ፤ ስርዓት ማለት ነው ( ማቴ.፲፭፥፲፫ ) ፡፡ ‹ሃይማኖት› ማለት ደግሞ በሀልዎተ እግዚአብሔር፣ እግዚአብሔር የሁሉ አስገኚ መሆኑን፣ በስላሴ አንድነትና ሶስትነት፣ በቅዱሳን ተራዳኢነት ማመን አምኖም መመስከር ማለት ሲሆን ‹ተክለ ሃይማኖት› የሚለው ሐረግም የሃይማኖት ተክል፣ ይኸውም የጽድቅ ፍሬን ያፈራ፣ ከኃጢአት ሐሩር ማምለጫ ዛፍ፣ ምእመናንን በቃለ ወንጌል ያጣፈጠ ቅመም፣ መዓዛ ሕይወቱ የሚማርክ፣ ቢመገቡት ረኃበ ነፍስን የሚያስወግድ ቅጠል፣ የጻድቃን መጠለያ ዕፅ የሚል ትርጉም አለው ፡፡
‹‹ተክለ ሃይማኖት ማለት የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ተክል ማለት ነው›› ሲል የጻድቁን ስም ይተረጉመዋል ፡፡
ጻድቁ አባታችን ሕይወታቸዉን ሙሉ ለእግዚአብሔር በመስጠት፣ እንደ በሬ ተጠምደው፣ እንደ ገበሬ ታጥቀው፣ ይህንን ዓለም ንቀው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው በብሕትውና በመኖራቸው፤ እርሳቸው በአሚነ ስላሴ ጸንተው ሌሎችንም እንዲጸኑና እንዲያምኑ በማድረጋቸው፤ እንደዚሁም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ በመስበክ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድውያነ ስጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የፈወሱ ሰባኬ ወንጌል በመሆናቸው ‹‹ተክለ ሃይማኖት›› ተብለው ይጠራሉ ፡፡
ምግጭ 👉 ገድለ ተክለሃይማኖት
ፃድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሀይማኖት ምልጃ በረከታቸው አይለየን ለሀገራችን ሰላምን ለህዝባችን ፍቅር አንድነትን ያምጡልን አሜን !!
🔸🔶🔸🔶🔸🔶🔶🔶🔸🔶🔸
#ዉሉደ_ብርሃን_ሚድያን_ለመቀላቀል➠
YouTube
https://www.youtube.com/@WuludeBirhan7
Facebook https://www.facebook.com/1880533115515403/posts/2831103630458342/?app=fbl
Telegram
https://t.me/weludebirhane
Tiktok https://www.tiktok.com/@weludebirhan1?_t=ZM-8t8Bq1Nt0vV&_r=1
ዌብሳይታችንን
https://wuludebrihan.org.et
Phone
+251907777037
🎞 ገፆቹን #Like , #Follow , #Subscribe እንዲሁም የሚለጠፉትን #Share , #Like ማድረግ እንዳይረሳ | 0 |
| 15 | 没有文字... | 4 077 |
| 16 | 没有文字... | 5 232 |
| 17 | ከሰው ፡ ዐይን ፡ ተሰወረ ፡ አኗኗሩም ፡ ከሰማይ ፡ መላእክት ፡ ጋር ፡ ሆነ
#ግንቦት_11_ቀን_ቅዱስ_ያሬድ ደብረ ሐዊ ከተባለው በሰሜን ተራራና ጫካ ውስጥ ብዙ ዓመታትን በምናኔ ካሳለፈ በኋላ ሞትን ሳይቀምስ ከዚህ ዓለም የተሠወረበት ቀን ነው ።
ቅዱስ ያሬድ በዚህ ዓለም የኖረበት ጠቅላላ ዕድሜው ሰባ ዐምስት ዓመት ነዉ በቅዱስ ያሬድ ታሪክ ውስጥ አከራካሪ ትረካዎች አሉ ይህውም በዕረፍቱና በዕርገቱ መካከል የሚነገረው ትረካ ነው።
አንዳንድ ሊቃውንት ቅዱስ ያሬድ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየ መቃብሩም እንደተሠወረ ሲናገሩ ሌሎች ሊቃውንት ደግሞ እንደ ሄኖክና እንደ ኤልያስ ሞትን ሳይቀምስ እንደተሠወረ ይናገራሉ ፡፡
ሞቷል የሚሉት ሊቃውንት በስንክሣሩ ላይ ‹‹ በዚች ዕለት የሱራፌል አምሳያቸው የሆነ ማሕሌታይ ያሬድ ዐረፈ ፤ ከዚህ በኋላ ወደ ሰሜን ገዳም ሔዶ በዚያ በሰላምም ተቀመጠ ›› የሚለውን ገጸ ንባብ ይዘው ሞቷል የሚሉ አሉ ነገር ግን ይሄ ገጸ ንባብ በሞት መለየቱን አያመለክትም ።
ምክንያቱም ‹‹ ጌታችን ከሥራው ሁሉ ዐረፈ ›› እንደሚለው ፤ ቅዱስ ያሬድም በድጓው ‹‹ በጎዳና ካገኘኝ ድካም ሰውነቴ ዐረፈች ›› ብሎ በተናገረው መሠረት ሰው እንደሚያርፍ ቅዱስ ያሬድም ማስተማሩን ፤ ከሰው ጋር መለየቱን ፤ ከዓይነ ሞት መሠወሩንና ከተጋድሎው ማረፉን የሚያመለክት ነው እንጂ መሞቱን አያመለክትም ብለው የሚከራከሩ ሊቃውንት አሉ ።
ስለዚህ ቅዱስ ያሬድ ሞቷል ብለው የሚከራከሩ ሊቃውንት ከሞተ መቃብሩ የት ነው ሲባሉ መቃብሩ ተሠውሯል ይላሉ ፤ የመቃብሩ መሠወር ለምን አስፈለገ ተብለው ሲጠየቁ ልክ እንደ ሙሴ መቃብር ተሠውሯል ይላሉ ነገር ግን የሙሴ መቃብር የተሠወረበት የራሱ የሆነ ዓላማና ምክንያት ነበረው ።
እርሱም ምንድነው ቢሉ እስራኤላውያን ቅዱስ ሙሴን በብዙ ይወዱት ነበርና እንዳያመልኩት ምክንያት ለማሳጣት እግዚአብሔር ይህን እንዳደረገ ሊቃውንት ይናገራሉ ፤ የቅዱስ ያሬድ መቃብር መሠወሩ ግን ምሥጢሩ ምንድ ነው ? ለሚለው ጥያቄ በቂ መልስ ስለሌለ ሞትን ሳይቀምስ እንደነ ኤልያስ ተሠውሯል የሚለው አብላጫውን ድምፅ ይዞ በብዙ ቤተ ጉባኤዎች የሚነገረው መሠወሩ ነው ፡፡
ድርሳነ ዑራኤልም ‹‹ ከሰው ዐይን ተሰወረ ፤ አኗኗሩም ከሰማይ መላእክት ጋር ሆነ ›› በማለት እንደነ ኤልያስ ከነሥጋው ማረጉን አስረግጦ ይናገራል ፡፡( የሰኔ ድርሳነ ዑራኤል ምዕራፍ 2 ፥ 50 )
ስለዚህ ሊቁ ቅዱስ ያሬድን ከሃይማኖታዊ ሚዛን ወጥተን ስንመለከተው ሀገራዊ ፣ ባህላዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ ፣ ሥልጣኔያዊ ፋይዳና ፍልስፍናዊ ድርሻ ያለው እንደሆነ እንገነዘባለን ፡፡
ቅዱስ ያሬድ ሃይማኖታዊ እሴት ያበረከተ ዘማሪ ብቻ ሳይሆን እጅግ ብዙ መጠነ ሰፊ ጉዳዮች የጻፈ የቀመረ ያረቀቀ ሊቅ ነው ፤ ስለሆነም ብሔራዊ መኩሪያችን ነው ።
© ✎﹏ዳዊት ተስፋዬ
ግንቦት 10 20 18 ዓ.ም | 3 782 |
| 18 | 没有文字... | 3 290 |
| 19 | ለኢትዮጵያ ፡ውበቷ ፡የኩራት ፡መቀነቷ ፡ሊቁ ፡ቅዱስ :ያሬድ
ታህሳስ 11 ቀን ቅዱስ ያሬድ ከሰማይ ዜማ የተቀበለበትን ቀን ቅድስ ቤተ ክርስቲያን በዓልን ሰርታ በታላቅ ድምቀት ታከበርዋለች ።
ያሬድ ሲታስብ በሁላችን ኅሊና ውስጥ ወይም በሁላችንም ዕውቀት ውስጥ የሚመጣው #ዜማ የሚለው ቃል ነው ።
የቅዱስ ያሬድ ዝርዝር ታሪክና ያበረከተው ሰፊ አስተዋፅኦ በተወሰነ ካህናትና ምእመናን ቢታወቅም በአብዛኛው ምእመናን ዘንድ ግን ስለቅዱስ ያሬድ ያለን ግንዛቤና መረጃ በጣም ውሱን ነው ፡፡
ስለዚህ የቤተ ክርስቲያናችን ብርሃን የሀገራችን ወርቃማ ሀብት ስለሆነው ታላቅ ሊቅ ይመለከተኛል በምንለው በተዋሕዶ ልጆች እንኳን የጠለቀ ግንዛቤ አለመኖሩ ሥራዎቹ ከቤተ ክርስቲያንም አልፎ ለሀገር ፣ ከሀገርም አልፎ ለዓለም እንዳይተርፍ አድርጎታል ።
ቅዱስ ያሬድ ለነፍስም ለሥጋም በሰማይ ለሚጠብቀን ሕይወታችንም ሆነ በምድር ላለው ሕይወታችንም የሚሆን ቁስለ ነፍስን የሚያክም አጥንትን የሚያለመልም ድንቅ ድርሰቶችን አበርክቶልናል ፡፡
ዛሬ በሠለጠኑ ሀገሮች የነበሩ ፈላስፎች ሥራዎቻቸውን በዓለም መድረክ ስላስተዋወቁላቸው መካነ መቃብሮቻቸውና ይገለገሉበት የነበረው ቁሳቁስ ሳይቀር እየተጎበኙ ለሀገራቸው በሕይወት እያሉ ካበረከቱት ጥቅም በላይ ከሞቱ በኋላ ያበረከቱት ጥቅምና አገልግሎት እየበለጠ ሄዷል ፡፡
በዚህ መልኩ የሰለጠኑ ሀገሮች የቱሪስቶቻቸውን ፍሰት ከጨመሩበት መንገዱች አንዱ የሊቃውንቶቻቸውን ታሪክ ማስተዋወቅ ነው ።
ቅዱስ ያሬድ በመንፈስ ቅዱስ ቃኝነት ያበረከተልን በዓለም ተወዳዳሪ የሌለውን ይህን ዜማ በከፍተኛ ተጋድሎ ጠብቀው ከትውልድ ወደ ትውልድ በማስተላለፍ እስካሁን ላደረሱልን የኢትዮጵያ ሊቃውንት አባቶቻችን ከፍተኛ የሆነ አድናቆትና ምስጋና ሊሰጣቸው ይገባል ።
የአሁኑ ትውልድም ለዘመናት ተጠብቆ የኖረውን ዜማና ባህል ዘመኑ በሚጠይቀው ሁኔታ ተንከባክቦ ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ ይጠበቅበታል ።
የዝማሬ ፣ የፍልስፍና ፤ የስነ ከዋክብት ፤ የሕግ የታሪክ ፣ የመልክዐ ምድርና የቋንቋ ሊቅ የሆነው ቅዱስ ያሬድ ዛሬ ዓለም ለደረሰበት የዜማ ፣ የተፈጥሮ ሳይንስና የማኅበራዊ ሕይወት ፍልስፍናም መሠረት ነው ሊያስብል የሚያስችሉ ሰማያዊ ሰነዶችን ትቶልን ሄዷል
#ከቅዱስ_ያሬድ_ረድኤት_በረከትን_ያሳትፈን
© ✎﹏ዳዊት ተስፋዬ
ታኅሣሥ 11 20 18 ዓ.ም | 3 559 |
| 20 | ✝የእግዚአብሔር ሰው✝
Size:-77.2MB
Length:- 1:23:23
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
http://t.me/abagebrekidan
http://t.me/abagebrekidan | 3 963 |
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
