ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ
ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ። ‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ›› ት.ኢሳ 58÷3 https://youtu.be/csxxAMGtC4I ለመቀላቀል http://t.me/ortodoxtewahedo
显示更多📈 Telegram 频道 ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ 的分析概览
频道 ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ (@ortodoxtewahedo) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 62 243 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 822,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 511 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 62 243 名订阅者。
根据 03 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -507,过去 24 小时变化为 -42,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 5.37%。内容发布后 24 小时内通常能获得 2.36% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 341 次浏览,首日通常累积 1 471 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 20。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ።
‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ››
ት.ኢሳ 58÷3
https://youtu.be/csxxAMGtC4I
ለመቀላቀል
http://t.me/ortodoxtewahedo”
凭借高频更新(最新数据采集于 04 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
数据加载中...
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 03 七月 | 0 | |||
| 02 七月 | +7 | |||
| 01 七月 | +3 |
| 2 | #ሰኔ ፳(20) #ሕንጸታ_ቤታ
👉በሀገረ እስራኤል፣ ቂሣርያ ከተማ፣ ፊልጵስዩስ በምትባል ሥፍራ የመጀመሪያዋ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን የታነጸችበት ዕለት ሰኔ ፳ ‹‹ሕንጸታ ቤታ›› የተከበረ ነው፤ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያለ እንጨት፣ ያለ ጭቃና ያለ ውኀ በሦስት ድንጋዮች ቤተ ክርስቲያኗን ያነጸበት ዕለት ነውና፡፡
👉ሐዋርያው ጳውሎስና በርናባስ አሕዛብን ሰብከውና ብዙዎችን አሳምነው ከመለሱ በኋላ ሕዝቡ ቅዱስ ቊርባንን የሚቀበሉበት ቤተ ክርስቲያን ስላልነበረ በጸሎትና በሱባኤ ጌታችን ኢየሱስን እንዲማጸኑ ሕዝቡን አዘዙ፤ ጌታችንም በሱባኤው ፍጻሜ ላይ ለሐዋርያቱ ተገልጾ በመላው ሀገር እስከ ፊልጵስዩስ ድረስ በደመና ከሰበሰባቸው በኋላ ባረካቸው፤ እንዲህም አላቸው፤ ‹‹ይህች ዕለት በእናቴ በማርያም ስም በአራቱ ማእዘነ ዓለም አብያተ ክርስቲያናት እንዲታነፁ የፈቀድኩባት ናት፡፡›› ከዚያም ጌታችን የቤተ ክርስቲያኗን ቦታና መሠረት ወስኖ ንዋየ ቅዱሳቷ፣ አልባሳቷንና መሠዊያዋን ካዘጋጀ በኋላ በዚያ ሥፍራ የነበሩትን ሦስት ድንጋዮች የተራራቁትን አቀራርቦ፣ ጥቃቅኑን ታላላቅ አድርጎ ቁመቱን በ፳፬፣ ወርዱን በ፲፪ ክንድ ለክቶ ለቅዱሳን ሐዋርያት ሰጥቷቸዋል፡፡
ልመናዋ በረከቷ ይደርብን! | 2 545 |
| 3 | 没有文字... | 3 198 |
| 4 | ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
ቤተ ክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ
የተሰጠ መግለጫ።
አዲስ አበባ የካቲት ፰ ቀን ፲፱፻፶፱ ዓ.ም.
በትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት ታተመ።
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
ቤተ ክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ
የተሰጠ መግለጫ
****
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ስለ መነኮሳት የገዳማዊነት ኑሮ ከዚህ የሚከተለውን ውሳኔ እንዲገለጥ አዟል።
ምንኩስና ከዓለማዊ ሐሳብ ተለይቶ በመንፈሳዊ ዓላማ ጸንቶ ራሱን ለተቀደሰ ተግባር ብቻ ቆርጦ የሚያውልበት ልዩ የሕይወት ጐዳና ስለሆነ የምንኩስናን ማዕርግ የተቀበሉ ሁሉ ይህንን ተረድተው በአኗኗራቸው ስለ መነኮሳት የገዳማዊነት ኑሮ የተወሰነውን መፈጸም አለባቸው። በማንኛውም ዓይነት ማዕርግ የሚገኝ መነኮስ በልዩ ፈቃድ፤ በመልእክትና በታወቀ ሥራ ምክንያት ካልሆነ በስተቀር ኑሮው በገዳም ውስጥ የተወሰነ መሆን ሲገባው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አንዳንድ መነኮሳት ያለፈቃድና ያለ በቂ ምክንያት መኖሪያቸውን በከተማ አድርገው ሲዘዋወሩ በመታየታቸው፤ ይህ አድራጎት የምንኩስናን ማዕርግ ዝቅ የሚያደርግ በመሆኑ ሁኔታው የሚሻሻልበትን መፈጸም አስፈላጊ ሆኗል።
ስለዚህ የቀድሞውን ሕገ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ምንኩስናን፤ እንዲሁም የገዳማዊነትን የአኗኗር ደንብ በመጠበቅ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በ፲፱፻፶፮ እና ፶፱ ዓመተ ምሕረቶች በወጣው በ፪ኛው ሲኖዶስ በ፲፩ኛው፣ በ፲፫ኛው፣ በ፲፭ኛውና በ፲፱ኛው አንቀጾች እንዲሁም በ፫ኛው ሲኖዶስ በ፬ኛው ክፍል የወሰነውን መሠረት በማድረግ ከዚህ የሚከተለው የአፈጻጸም ውሳኔ ተሰጥቷል።
ውሳኔ
፩ኛ/ ሕገ ምንኩስናን የተቀበሉ ሁሉ ገዳማውያን ሊሆኑ ስለሚገባ በቂ ማስረጃ ባለው መልእክት ወይም መደበኛ በሆነ የተፈቀደ ሥራ ካልሆነ በስተቀር፤ በግል ፍላጎት ብቻ በከተማና ከገዳም ውጭ በሆነ ሥፍራ የሚገኝ መነኮስ ቢኖር ይህ መግለጫ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ አንድ ወር ድረስ ወደ ገዳሙ ወይም ወደሚፈልገው ገዳም እየተመለሰ እንዲገባ ተወስኗል።
፪ኛ/ ይህ ውሳኔ በሚፈጸምበት ጊዜ ችግር እንዳይደርስባቸው በከተማ ውስጥ ወይም ከገዳም ውጭ በሆነ ሥፍራ ለመገኘት የሚያስችለው ተገቢው ፈቃድ ያላቸው መነኮሳት ይህንኑ የሚያረጋግጠውን የጽሑፍ ማስረጃቸውን ለመንበረ ፓትርያርክ ወይም ለሀገረ ስብከት መንበረ ሊቀ ጳጳስ ጽሕፈት ቤቶች ወይም በየአቅራቢያው ለሚገኘው ቤተ ክህነት እያቀረቡ ለፈቃዱ ማረጋገጫ የሚሆነውን ጽሑፍ እንዲቀበሉ ያስፈልጋል።
፫ኛ/ ማንኛውም ሥርዓተ ምንኩስናን የተቀበለ መነኮስ ከገዳም ወጥቶ በከተማ ወይም በሌላ ሥፍራ ለመገኘት የሚያስፈልግበት ምክንያት ቢገጥመው መንበረ ፓትርያርኩ ወይም የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ የሚያውቀውና የሚስማማበትን ፈቃድ ከገዳሙ መምህር በደንበኛ ጽሑፍ ማግኘትና ይህንኑ ይዞ ሲጠየቅ ማሳየት ግዴታው ነው።
፬ኛ/ ማንኛውም መነኮስ ከላይ በ፫ተኛው ተራ ቍጥር በተመለከተው መሠረት ተገቢ ፈቃድ ሊያገኝ የሚችለው ለመልእክትና ለመደበኛ የታወቀ ሥራ ጉዳይ ብቻ ስለሆነ በማናቸውም ዓይነት ምክንያት በከተማ ወይም ከገዳም ውጭ በሆነ ሥፍራ ያለ ፈቃድ እንዳይገኝ በጥብቅ ተከልክሏል።
፭ኛ/ በዚህ ውሳኔ መሠረት ሳይፈጽም የሚገኝ መነኮስ በከተማ ውስጥ ወይም ከገዳም ውጭ በሆነ ሥፍራ በምንም ምክንያት ያለፈቃድ ቢገኝ በሕግ አስከባሪዎች ተገቢው የሚፈጸምበት ከመሆኑም በላይ ይህንን የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ባለማክበሩ ማዕርገ ምንኩስና የሌለው መሆኑን አስቀድሞ ማወቅ አለበት።
ይህንን የቅዱስ ሲኖዶስ የአፈጻጸም ውሳኔ ተከታትለው እንዲያስከብሩና እንዲያስፈጽሙ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለሥልጣኖች ሁሉ እንዲያውቁትና ትእዛዝ እንዲደርሳቸው ተደርጓል። ይህ ውሳኔ የተሰጠው ማዕርገ ምንኩስና እንዲጠበቅና የገዳማዊነት ኑሮም በታወቀው ሥርዓት ተከብሮ እንዲኖር፤ ይልቁንም መነኮሳት በተቀበሉት መንፈሳዊ ማዕርግ የሚፈለግባቸውን መልካም አገልግሎት በትክክል ለማበርከት እንዲችሉ ለማድረግ መሆኑን ሕዝበ ክርስቲያኑ ሁሉ እንዲያውቀው እናሳስባለን። | 3 019 |
| 5 | የአለቃ ገ/ሐናን ታሪካቸውን እና እማይጠገቡ ቀልዶቻቸውን ማግኘት ማንበብ ለምትፈልጉ ከታች ባሉት ሊንኮች ይቀላቀሉን
👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/+T4nCtrKz_-DWg9aJ
https://t.me/+T4nCtrKz_-DWg9aJ | 369 |
| 6 | የአለቃ ገ/ሐናን ታሪካቸውን እና እማይጠገቡ ቀልዶቻቸውን ማግኘት ማንበብ ለምትፈልጉ ከታች ባሉት ሊንኮች ይቀላቀሉን
👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/+T4nCtrKz_-DWg9aJ
https://t.me/+T4nCtrKz_-DWg9aJ | 274 |
| 7 | በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው የኦንላይን ጉባኤ እንሆ የመክፈቻው መርሃ ግብር ጀምሮል ላይቭ ግቡ
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=efb89d42527b78e228
በቤተ ቅዱስ ሚካኤል መንፈሳዊ የበጎ አድራጎት ማህበር አዘጋጅነት ከሰኔ 12 / ጀምሮ እስከ ሰኔ 14/ የሚቆየው ልዩ ጉባኤ መርሃ ግብር መክፈቻው ዛሬ ጀምሮል ላይቭ ቻት ግቡ እንዳይ መልታችሁ ከታች በለው ሊንክ ግቡ 😍
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=4c5c2254a5a28151f0
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=4c5c2254a5a28151f0
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12
ለወዳጆችሁ ሼር ሼር ሼር አድርጉ🙏🙏
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=efb89d42527b78e228 | 291 |
| 8 | ሰኔ 12 ለምን ይከበራል ቢሉ ?
መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ዝክር ይወዳል። በስሙ የተራቡትን ለሚያበሉ የታረዙትን ለሚያለብሱ የተጠሙትን ለሚያጠጡ በዓሉን በክብር በደስታ ለሚያከብሩ ሁሉ ምልጃው ፈጣን የችግረኞች ረዳት ታማኝ። ጽኑዕ ኃያል መልአክ ነው።
1.የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል #ሲመቱ ወይም የ #ተሾመበት ዕለት ነው።
2.በስሙ የታነጸ ቤተ ክርስቲያን የከበረበት #ቅዳሴ_ቤቱ ነው።
3. ቅድስት #አፎምያ ዝክሩን የምትዘክር ወዳጁን ከሳጥናኤል ያዳነበት ዕለት ነው።
4.ምስኪኑ ታዛዡ ልጅ የኃለኛ ስሙ #ባህራን በጎረቤቱ ባለጸጋው ምክንያት የታወጀበት የሞት ደብዳቤ ለውጦ ያዳነው ዕለትም ነው።
ከዚህ በተጨማሪ
ይህ ሰኔ 12 ጻድቁ የኢትዮጵያ ንጉስ ላሊበላ ዕረፍቱም ነው።በመላእክት ዕርዳታ 10 ቤተመቅደስን ያነጸው ቅዱስ ላሊበላ ያረፈት ዕለትም ነው።
ሰፋ ያለ ዝርዝር ታሪኩን ስንክሳር ላይ ያገኙታል።
እንኳን ለገናናው መልአክ ለቅዱስ ሚካኤል በዓል በሰላም በጤና እና በፍቅር አደረሳችሁ። ካልታሰበ መከራ ይሰውረን አሜን። | 6 711 |
| 9 | 没有文字... | 4 159 |
| 10 | 没有文字... | 3 533 |
| 11 | “ቅዱስ ሚካኤል «ቅዱስ» ማለት ልዩ፥ ክቡር ማለት ነው፤ ሚካኤል ማለት ደግሞ «መኑ ከመ አምላክ፥ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው?» ማለት ነው።
#ሚካኤል የሚለው ስም ቃሉ #የዕብራይስጥ ነው፤
#ሚ - የሚለው «መኑ» ማለት ነው፥
#ካ - የሚለው «ከመ» ማለት ሲሆን፥
#ኤል - ማለት ደግሞ «አምላክ» ማለት ነው።
ይህን ማለትም የቅዱስ ሚካኤልን ስም በጠራን ቊጥር የምንመሰክረው ስለ እግዚአብሔር ነው፤
በመሆኑም እግዚአብሔርን በባሕርይ የሚመስለው፥ በሥልጣንም የሚተካከለው፥ በምድርም በሰማይም እንደሌለ የሚናገር ልዩ፥ ክቡር ስም ነው።
የነቢያት አለቃ ሙሴ ባሕረ ኤርትራን ለሁለት ከፍሎ ሕዝቡን ያሻገረለትንና ፈርዖንን ከነሠራዊቱ ያሰጠመለትን አምላክ እግዚአብሔርን በመዝሙር ሲያመሰግን፥ «አቤቱ በአማልክት መካከል (በስም አማልክት ከሚባሉ፥ በስመ አማልክት ከሚጠሩ፥ አንድም አማልክት ዘበጸጋ ከተባሉ ከነቢያት ከካህናት መካከል) አንተን የሚመስል ማነው? በቅዱሳንም ዘንድ እንደ አንተ የከበረ ማነው?» ብሏል። ዘጸ ፲፭፥፲፩። ቅዱስ ዳዊትም፦ «አቤቱ፥ ከአማልክት የሚመስልህ የለም፤» ብሏል። መዝ ፹፭፥፰
እግዚአብሔር ግን ኢያሱን አስነስቶ አረጋግቷቸዋል:: ቅዱስ ሚካኤል 40ውን ዘመን እሥራኤልን ደመና ጋርዶ: መና አውርዶ: ክንፉን ዘርግቶ: ጠላትን መክቶ ከሙሴ ጋ እንደ መራቸው ከኢያሱ ጋርም ይሆን ዘንድ ከሰማይ ወረደ::
+በኢያሪኮ አካባቢም የተመዘዘ ሰይፉን ይዞ በግርማ ለኢያሱ ታየው:: ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ "አንተ ከእኛ ወገን ነህን? ወይስ ከጠላቶቻችን?" ሲል ጠየቀው:: ቅዱስ ሚካኤልም መልሶ "እረዳህ ዘንድ እነሆ የሠራዊት አለቃ ሆኜ ተሹሜ መጥተቻለሁ" አለው ረድኤቱ አይለየን።
ምሕረቱ ፥ ርኅራኄው ፥ ይቅርታው ባህሪው የሆነ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ለኛም ምሕረት ይቅርታን ያድለን ዘንድ ከጌታህ አማልደን” | 3 208 |
| 12 | የመላእክት አለቃ
ቅዱስ ሚካኤል የመላእክት ሁሉ አለቃ ወይም "ሊቀ መላእክት" ተብሎ ይጠራል። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዳንኤል መጽሐፍ፣ በይሁዳ መልእክትና በዮሐንስ ራእይ ላይ ስሙ ተጠቅሶ እናገኘዋለን። በተለይም በሰማይ ሰልፍ በሆነ ጊዜ ሳጥናኤልን ድል አድርጎ የጣለ የሰራዊት አለቃ እንደሆነ ይታወቃል።
አማላጅና ጠባቂ
ምእመናን ቅዱስ ሚካኤልን የሚወዱት በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ነው፦
• ፈጣን ረዳትነት፦ ከእግዚአብሔር ዘንድ ለምህረትና ለበረከት የሚላክ፣ አማላጅ መልአክ እንደሆነ ይታመናል።
• ጠባቂ መላእክ፦ የእስራኤል ዘስጋ (የጥንቶቹ አይሁድ) እና የእስራኤል ዘነፍስ (ክርስቲያኖች) ጠባቂ ተደርጎ ይወሰዳል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ያለዉ ክብር
በኢትዮጵያ በየወሩ በ 12 ቀን ቅዱስ ሚካኤል ይታሰባል። በተለይም በዓመት ሁለት ታላላቅ በዓላት አሉት፦
• ህዳር 12፦ ሳጥናኤል በትዕቢት በወደቀ ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል በምትኩ የተሾመበትና "በሰማይ ሰልፍ የሆነበት" ቀን ተብሎ ይከበራል።
• ሰኔ 12፦ ቅዱስ ሚካኤል ባህራንን ከሞት ያዳነበትና ለሰው ልጆች ምህረትን የሚያሰጥበት ታላቅ በዓል ነው።
በስዕለ አድኖው ላይ የሚታዩ ምልክቶች
በአብዛኛው የቅዱስ ሚካኤል ስዕል ላይ የሚከተሉትን ምልክቶች እናያለን፦
• ሰይፍ፦ የድል አድራጊነቱና ክፉዎችን የመቅጣቱ ምልክት።
• ሚዛን፦ የሰዎችን ስራ የሚመዝን መልአክ መሆኑን ለማሳየት።
• ዲያብሎስ (ዘንዶ)፦ በእግሩ ስር ተረግጦ ይታያል፣ ይህም በክፋት ላይ ያለውን ድል ያሳያል።
የምሕረትና የድል መልአክ
ቅዱስ ሚካኤል "መጋቤ ሐዲስ" እና የሰው ልጆች ሁሉ ጠባቂ ተደርጎ ይታመናል። መጽሐፍ ቅዱስ "ከመላእክት አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ" (ዳን 10፡13) በማለት የእርሱን ረዳትነት ይመሰክራል።
በድርሳነ ሚካኤል የሚጠቀሱ ታዋቂ ተአምራት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን "ድርሳነ ሚካኤል" መጽሐፍ በየወሩ የሚነበቡ የቅዱስ ሚካኤልን ተአምራት ይዟል። ጥቂቶቹ እነሆ፦
• ባህራንና የታሸገው ደብዳቤ፦ አንድ ሀብታም ሰው ድሃውን ባህራንን እንዲገደል ደብዳቤ ጽፎ ቢልከውም፣ ቅዱስ ሚካኤል ግን ደብዳቤውን በመለወጥ ባህራን የሀብታሙን ልጅ እንዲያገባና የሀብቱ ወራሽ እንዲሆን አድርጎታል።
• አፎምያ፦ ሰይጣን በቅዱስ ሚካኤል አምሳል ተገልጦ አፎምያን ሊያስታት ሲሞክር፣ ቅዱስ ሚካኤል ደርሶ እንዳዳናትና ሰይጣንንም እንዳሳፈረው ይነገራል።
• ዱራታኦስና ቴዎብስታ፦ እነዚህ ደግ ሰዎች ለቅዱስ ሚካኤል ዝክር ሲሉ ያላቸውን ሁሉ ሰጥተው በነበረበት ወቅት፣ መልአኩ በሰው አምሳል መጥቶ ቤታቸውን በበረከት እንደሞላው ይተርካል።
ለምን በ12 ቁጥር ይከበራል?
በቤተክርስቲያን ትውፊት መሠረት ቅዱስ ሚካኤል በወደቀው በሳጥናኤል ምትክ የመላእክት አለቃ ሆኖ የተሾመው በ12ኛው ሰዓት (በእለተ እሁድ) ስለሆነ፣ በየወሩ በ12ኛው ቀን ይታሰባል።
በምልጃው የሚታመኑ ነጥቦች
ምእመናን ወደ ቅዱስ ሚካኤል ሲጸልዩ የሚከተሉትን ተስፋዎች ያደርጋሉ፦
• ከክፉ መናፍስት ጥቃት እንዲጠብቃቸው።
• በሞት ጊዜ ነፍስን ተረክቦ ወደ ገነት እንዲያሳርግ።
• በምድር ላይ በረከትንና ረድኤትን እንዲያሰጥ።
ለማጠቃለል፦ ቅዱስ ሚካኤል ለሰው ልጆች የሚራራ፣ በፍርድ ቀን የሚቆም እና በእግዚአብሔር ፊት ስለ ሰው ልጆች ምሕረትን የሚለምን ታላቅ መልአክ ነው። | 3 340 |
| 13 | የኢትዮጵያ መነኮሳት በከተማ እንዲርመሰመሱ
ያደረገብን አንደኛው አግብተው ኑረው ኋላ የእንጦስን በረከት ያግኙ ተብለው መንኩሰው በከተማ መኖር ስለጀመሩ
ሁለተኛ ሚስቱ የሞተችበት ቄስ ክህነቱን ለማስቀጠል ሲል መንኩሶ በቤቱ በከተማ መኖሩ ናቸው!
ከእነዚህ የተቀሰመው ችግር ዛሬ እየመነኮሱ ስራ አስክሀጅ አስተዳዳሪ ጸሐፊ እየሆኑ ለቤተክርስቲያን እና ለክርስትና የውስጥ ደዌ ሆኑ!!
መ/ር ኀይለማርያም ዘቦሩ ሜዳ
#ሠናይ_ሚዲያ | 3 329 |
| 14 | 没有文字... | 8 340 |
| 15 | ቤተ ክርስቲያን፡- የመንግሥተ ሰማያት በር ናት “ዛቲ ይእቲ ኆኅታ ለሰማይ (ይህች የሰማይ ደጅ ናት) /ዘፍ 28÷17/”
በዚህ መሠረት ለእኛም በ40 ቀንና በ80 ቀን የተሰጠን ጸጋመንፈስ ቅዱስ እንዳይለየን ሕጉን ትእዛዙን መጠበቅና ጧት ማታ ወደ ቤተ ክርስቲየን መገስገስ ይገባል፡፡
ለዚህም የእግዚአብሔር ቸርነት" የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና የቅዱሳን ተራዳኢነት አይለየን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር | 5 903 |
| 16 | #በዓለ_ጰራቅሊጦስ
“ኢየኀድገክሙ ዕጓለ ማውታ ትኩኑ”
“ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም”
/ዮሐ.14÷18/
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከምታከብራቸው ዘጠኝ ዐበይት (ታላላቅ) በዓላት መካከል አንዱ የጰራቅሊጦስ በዓል ነው፡፡
ጰራቅሊጦስ፡- ቃሉ ግሪክ ነው፡፡ ጰራቅሊጦስ ማለት መጽንዒ በእምነት የሚያጸና፣ መንጽሒ ከኃጢአት የሚያነጻ፣ ናዛዚ ያዘኑትን የሚያረጋጋ፣ መስተፍሥሒ፣ ያዘኑትን የሚያስደስት፣ ከሣቲ ምስጢርን የሚገልጽ ማለት ነው፡፡
ጰራቅሊጦስ፡- መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ የጰራቅሊጦስ በዓል ታሪክ እንደሚከተለው ተገልጿል፡፡
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም የሚሠራውን ሥራ ከጨረሰ በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያትን ወደ አባቴ እሄዳለሁ (አርጋለሁ) ሲላቸው ደነገጡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም መደንገጣቸውን አይቶ“ኢይደንግጽክሙ ልብክሙ እመኑ በአግዚአብሔር ወእመኑ ብየ እስመ ውስተ ቤተ አቡየ ብዙኅ ማኅደር ወምዕራፍ ቦቱ” (ልባችሁ አይደንግጥባችሁ በእግዚአብሔር እመኑ በእኔም እመኑ በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ ማለት፡- በአባቴ ቤት በመንግሥተ ሰማያት ብዙ ማዕርገ ሀብታት አለ) (ዮሐ.14÷1) እንዲሁም /በዚሁ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 14÷18/ “ኢየኀድገክሙ ዕጓለ ማውታ ትኩኑ” (ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም) ሲል መድኃኒታችን ኢየሱሰ ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን አጽናንቷቸዋል፡፡
/በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 24 ቁጥር 49/ ላይም እንደተጻፈው የሰላም አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ሊያርግ ሲል ቅዱሳን ሐዋርያትን “አንትሙሰ ንበሩ ሀገረ ኢየሩሳሌም እስከ ትለብሱ ኃይለ እምአርያም” (እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ተቀመጡ) አላቸውና ዐረገ በሐዋ.ሥራ ምዕራፍ 2- ከቁጥር 1 ጀምሮ እንደተጻፈው እነርሱም ይህን አምላካዊ ቃል መሠረት በማድረግ በኢየሩሳሌም በጽርሐ ጽዮን በማርቆስ እናት በማርያም ቤት ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው ተሰብስበው ሳሉ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዐረገ በአሥረኛው ቀን በተነሣ በሃምሳኛው ቀን ጧት በሦስት ሰዓት ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል ወረደላቸው፡፡
ከዚህ በኋላ ፍርሃት ከውስጣቸው ወጣ መንፈሳዊ ድፍረት አገኙ፡፡ አንድ የዕብራይስጥ ቋንቋ ብቻ ነበር የሚያውቁት ሰባ አንድ ዓይነት ቋንቋ (የአገሩ ሁሉ ቋንቋ) ተገለጸላቸው፡፡ ከእነርሱ ቋንቋ ጋር በሰባ ሁለት ዓይነት ቋንቋ ተናገሩ፡፡
የአገሩ ሁሉ ቋንቋ የተገለጸላቸውም ሁሉንም በአገሩ ቋንቋ እንዲያስተምሩ ነው፡፡ ከተለያየ ክፍለ ዓለም የመጡ ሰዎች ነበሩና እነዚህ የገሊላ ሰዎች አይደሉምን? እንዴት የእኛን አገር ቋንቋ ሊናገሩ ቻሉ? በማለት ተገረሙና አመንትተው እርስ በርሳቸው እንጃ ይህ ምን ይሆን? አሉ፡፡ ሌሎች ግን ጉሽ የወይን ጠጅ ጠጥተው ሰክረው ነው አሉ፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ጴጥሮስ ከአሥራ አንዱ ጋር ቆመ ድምፁንም ከፍ አድርጎ እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፡-የይሁዳ ሰዎች በኢየሩሳሌምም የምትኖሩ ሁላችሁ፡- ይህ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን ቃሎቼንም አድምጡ፡፡
ለእናንተ እንደመሰላችሁ እነዚህ የሰከሩ አይደሉም ከቀኑ ገና ሦስተኛ ሰዓት ነውና፡፡ ነገር ግን ይህ በነቢዩ ኢዩኤል የተነገረው ይፈጸም ዘንድ ነው፡- ይህም “እግዚአብሔር ይላል፡- በኋለኛይቱ ቀን እንዲህ ይሆናል ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፣ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፣ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ፡፡
ደግሞም በዚያች ወራት በወንዶችና በሴቶች አገልጋዮች ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ትንቢትም ይናገራሉ፡፡ ድንቆችንም በላይ በሰማይ ተአምራትን በታች በምድርም ምልክቶችን ደምን እሳትንና ጢስንም እሰጣለሁ የምትገለጠው ታላቅዋ የእግዚአብሔር ቀን ሳትመጣ ፀሐይ ወደ ጨለማ ጨረቃም ወደ ደም ይለወጣል፡፡
የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል” /ኢዩ.2÷28-32/ ይህን መሠረት በማድረግ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ ልብን የሚነካ ትምህርት ሰጠ፡፡ ሕዝቡም ቅዱስ ጴጥሮስ በሰጠው ትምህርት ልባቸው ተከፈተ ቅዱስ ጴጥሮስንና ሌሎቹንም ሐዋርያት ወንድሞች ሆይ ምን እናድርግ? አሉአቸው፡፡
“ቅዱስ ጴጥሮስም ንስሓ ግቡ ኃጢአታችሁም ይሠረይ ዘንድ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ ኃጢአታችሁም ይሠረይላችኋል የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ፡፡ የተስፋው ቃል ለእናንተና ለልጆቻችሁ አምላካችንም ወደ እርሱ ለሚጠራቸው በሩቅ ላሉ ሁሉ ነው፡፡ ስለዚህ ራሳችሁን ከዚህ ክፉ ዓለም አድኑ” ብሎ መከራቸው፡፡ በዚችም ዕለት ሦስት ሺህ ሰዎች አምነው ተጠመቁ፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው የሞቱና የትንሣኤው ምስክሮች ሆኑ፡፡
የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ በነሱ ላይ ሲያድር ለቤተክርስቲያን ጉዞ አዲስ ምዕራፍ ተከፈተ፡፡ ይህ የጰራቅሊጦስ በዓል በግሪኮች ቋንቋ ጰንጠቆስጤ ይባላል፡፡ ጰንጠቆስጤ ማለት ሃምሳኛ ማለት ነው፡፡ ጌታችን ከተነሣ በኋላ ሃምሳኛው ቀን ነው፡፡ ይህም ዕለት በዓለ ሃምሳ፣ በዓለ ጰራቅሊጦስ ነው፡፡
እንዲሁም ታላቁ ሊቅ ቅ/ዮሐንስ አፈወርቅ ይህን በዓል በሚገባ አነጋገር “የቤተክርስቲያን የልደት ቀን” ብሎታል፡፡ ይህ በዓል በብሉይ ኪዳን የእሸት በዓል (በዓለ ሰዊት) ይባላል፡፡
እስራኤል የነጻነት በዓላቸውን ከሚያከብሩበት ከበዓለ ፋሲካ ጀምረው ሃምሳውን ቀን በዓል አድርገው ይሰነብታሉ፡፡ በሃምሳኛው ቀን በዓለ ሰዊትን (የእሸት በዓላቸውን) ያከብራሉ፡፡
በሀገራቸው ከመጋቢት እስከ ግንቦት ያለው ወቅት በሀገራችን ከመስከረም እስከ ኅዳር እንዳለው የእሸት ወራት (የጸደይ ወራት) ነውና የእሸት በዓላቸውን የሚያከብሩት በኦሪት ዘሌዋውያን /ምዕራፍ 23÷10-17/ በታዘዘው መሠረት ማንኛውም እስራኤላዊ ገበሬ ከዘራው ሁሉ በየአይነቱ እሸቱን ቆርጦ ተሸክሞ ወደ ምኵራቡ ይመጣል፡፡ በቤተ መቅደስ የሚያገለግለው ካህን ተቀብሎ ባርኮ ጸልዮ የሚጠበሰው እየተጠበሰ የሚታሸው እየታሸ በማኅበር አንድነት ይበላል፡፡ ይህም “ቀዳምያት” ይባላል፡፡
የመጀመሪያው ማለት ነው፡፡ ከማንኛውም በረከት የመጀመሪያው በእግዚአብሔር ፊት መቅረብ፣ ለእግዚአብሔር መሰጠት እንዳለበት ታዟልና፡፡
በዚህ መሠረት ከበዓለ ጰራቅሊጦስ የምንማረው፡- ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን “እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ተቀመጡ” ባላቸው መሠረት በኢየሩሳሌም ተቀምጠው ተስፋውን ሲጠባበቁ መንፈስ ቅዱስ ወርዶላቸዋል፡፡
ዛሬም መንፈስ ቅዱስ የሚወርድባት ኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ናት “ሚ መጠን ግርምት ዛቲ ዕለት ወዕፅብት ዛቲ ሰዓት እንተ ባቲ ይወርድ መንፈስ ቅዱስ እመልዕልተ ሰማያት (ይህች ቀን ምን ያህል የምታስፈራ ናት? ይህች ሰዓት ምን ያህል የምታስጨንቅ ናት? መንፈስ ቅዱስ ከሰማየ ሰማያት የሚወርድባት) /ሥርዓተ ቅዳሴ/ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ እንደ ወረደላቸው ለእኛም ሁል ጊዜ ይወርድልናል እንዲወርድልንም ሁል ጊዜ ወደ ቤተክርስቲያን መሄድ ይገባል፡፡ ከቤተክርስቲያን ተለይቶ ጽድቅ የለም፡፡” | 6 433 |
| 17 | ✝እውነት ለዘለዓለም ታሸንፋለች✝
Size:-68.7MB
Length:- 1:14:13
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
http://t.me/abagebrekidan
http://t.me/abagebrekidan | 3 672 |
| 18 | 没有文字... | 4 537 |
| 19 | 👑🌿እንኳን #ለግንቦት 21 ቀን የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የመገለጥ በዓል (ደብረ ምጥማቅ) በሠላም አደረሰን|አደረሳችሁ🙏🍇🙏
🍒የአርያም ንግሥት: የሰማይና የምድር እመቤት: የሰውነታችንም መመኪያ ቅድስት ድንግል ማርያም በዚች ዕለት በምድረ ግብፅ ለተከታታይ ቀናት ተገልጻለች::
🌿ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድረ ግብፅና ኢትዮዽያ በተሰደደ ጊዜ ከድንግል እናቱ: ከዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ዛሬ ደብረ ምጥማቅ በሚባለው ቦታ ላይ አርፎ ነበር:: ቦታውን ባርኮ ለዘለዓለም ያንቺ መገለጫ ይሁን ብሎም ቃል ኪዳን ገብቶላት ነበር::
🍒ጊዜው በደረሰ ሰዓት ደብረ ምጥማቅ ተገድሞ የበርካታ መነኮሳት ቤት ሆነ:: እመቤታችንም በልጇ ፈቃድ ግንቦት 21 ቀን አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን አስከትላት መጣች::
🌿በዚያ ሕዝበ ክርስቲያንም: አሕዛብም ተሰብስበው ለ5 ቀናት ከእመ ብርሃን ጋር ይሰነብታሉ:: እንግዲህ ልብ በሉት:- እንኳን የአርያም ንግስት: የአምላክ እናቱ እመቤታችንን ይቅርና በዚሕ ዓለም ሰይጣን ቤቱ ያደረጋቸውን: የመዝናኛው ኢንዳስትሪ ዝነኛ ሰዎችን ለማየት የዘመናችን ሰው እንዴት እንደሚቸኩል::
🍒እመቤታችንን በአካል መመልከት አይደለም ስሟን መጥራት ነፍስን ከሥጋ መለየት የሚችል ጣዕምና ደስታ አለው:: ባይሆን ይሔ ለሚገባውና ላደለው ብቻ ነው::
🌿የደብረ ምጥማቅና የአካባቢዋ ሰዎች ከእመቤታችን ጋር የሚቆዩባቸው ቀናት የዘለዓለም የሕይወት ስንቅ የሚይዙባቸው ናቸው:: ፈልገው የሚያጡት: ጠይቀው የማይፈጸምላቸው ምንም ነገር አልነበረም:: ነቢያት: ሐዋርያት: ጻድቃን: ሰማዕታት: ደናግል: መነኮሳት: መላዕክትና ሊቃነ መላእክት ለድንግል ማርያም ሲሰግዱ ይታዩ ነበርና:: እመ ብርሃንም እየመላለሰች ትባርካቸው ነበር::
🍒እነዚያ እርሷን ያዩ ዐይኖች: በፊቷ የቆሙ እግሮች ክብር ይገባቸዋል:: 5ቱ ዕለታት ሲፈጸሙ ሕዝቡ እመቤታችንን በዕንባ ይሰናበቷታል:: እመ ብርሃንም በብርሃን መስቀል ባርካቸው ከቅዱሳኑ ጋር ታርጋለች::
👑🌿የእመቤታችን ፍቅር፣ በረከትና ምልጃ አይለየን!🙏 | 4 734 |
| 20 | ምንኩስና_ምን_ማለት_ነው_አዲስ_እጅግ_ድንቅ.m4a | 5 488 |
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
