ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ
ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ። ‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ›› ት.ኢሳ 58÷3 https://youtu.be/csxxAMGtC4I ለመቀላቀል http://t.me/ortodoxtewahedo
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ analitikasi
ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ (@ortodoxtewahedo) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 60 123 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 834-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 555-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 60 123 obunachiga ega bo‘ldi.
02 Sentabr, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -1 001 ga, so‘nggi 24 soatda esa -34 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 3.10% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 1.48% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 1 864 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 890 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 7 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ።
‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ››
ት.ኢሳ 58÷3
https://youtu.be/csxxAMGtC4I
ለመቀላቀል
http://t.me/ortodoxtewahedo”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 03 Sentabr, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 03 Sentabr | 0 | |||
| 02 Sentabr | 0 | |||
| 01 Sentabr | 0 |
| 2 | Matn yo'q... | 536 |
| 3 | #አማኑኤል 28
#እግዚአብሔር ከኛ ጋር ሆነ
እኛ ከእርሱ ጋር መሆን ቢያቅተን እርሱ ከእኛ ጋር ሊሆን ልዑል ባህርዪን ዝቅ አድርጎ ከእኛ ጋር ሆነ። በባህርያችን ጎስቁለን የተፈጠርንለትን አምላካዊ መልክ ብናጎድፈው የሰውን አእምሮ በሚፈታተን የተዋህዶ ምስጢር እርሱ ሰው ሆነ።
እኛ አምላክን ወደ መምሰል ከፍ ማለት ቢያቅተን ይህን ክፍተት ያደላድል ዘንድ አምላክ ሰው ሆነ። ሰማያትን እንደ መጋረጃ የሚጠቀልላቸው እርሱን በጨርቅ ጠቀለሉት። ከአለት ውሀን ያፈለቀው አምላክ ከእናቱ ጡትን ለምኖ አለቀሰ።
በላይ ያሉ መላእክትን የሚልካቸውን ንጉስ ማርያምና ዮሴፍ ውሀ ለመቅዳት፣እንጨት ለማምጣት ላኩት።እርሱም በፍቅር ተላካቸው። ከመቅደሱ አገልጋዮች ይልቅ የተናቁትን ሰዎች ሐዋርያት አድርጎ መረጣቸው።
ከቀራጮችና ከሐጢአተኞች ጋር ተቀመጠ።ከእነርሱም ጋር በላ ጠጣ። ሰዎች የተፀየፋቸውን በመቃብር ስፍራ የተጣሉት በምህረቱ ጎበኘ። ከሰርገኞች ጋር ተደሰተ።
ከኀዘንተኞችም ጋር አለቀሰ። እስከመጨረሻም ከእኛ ጋር እንደሆነ እንረዳ ዘንድ የእኛን የሞት ፅዋ ተጎነጫት። መስቀል ላይም ከወንበዴዎች ጋር ተቆጠረ።
በሲኦልም አልተወንም።ከእኛው ጋር ነበር።በገነት መቆየት ያልቻለውን አዳም እስከ ሲኦል ተከተለው። ከዚያም አውጥቶ ወደ ቀደመ ክብሩ መለሰው።
"ከፍ ባልሁ ጊዜ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ" ያለ አምላክ እኛነታችንን ከእርሱ ጋር ከፍ አድርጎ በዘለዓለማዊ ክብር በአብ ቀኝ አስቀመጠው። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ የተባለውም ተፈጸመ።
እኛም ከእርሱ ጋር ለመሆን ያብቃን!!
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
📖📖📖📖📖📖📖📖📖 | 448 |
| 4 | ይህችውም የወርቅ መሰላል የድንግል ማርያም ምሳሌ ናት::
"አንቲ ውዕቱ ሰዋስው ዘርእየ ያዕቆብ" እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም (ውዳሴ ማርያም ዘሠሉስ)
ተነስቶም "ዛቲ ይእቲ ኈኅታ ለሰማይ: ዝየ ይትሐነጽ ቤተ እግዚአብሔር - ይ
ህች የሰማይ ደጅ ናት: ቤተ እግዚአብሔርም ይታነጽባታል::" ብሎ ትንቢት ተናግሯል::
ይህ ቅዱስ አባት ለድንግል ማርያም ቅድመ አያት ከመሆኑ ባሻገር ነቢያትን: ካህናትን: ነገሥታትንና መሣፍንትን ወልዷል:: ከሁለቱ ሚስቶቹ (ልያና ራሔል) : ከሁለቱ ደንገጥሮች አሥራ ሁለት ልጆችን ወልዷል::
ከአጐቱ ከላባ ዘንድ ለሃያ አንድ ዓመታት አገልግሎ: ሃብት ንብረቱን ጠቅልሎ ወደ ርስቱ ከነዓን ሲመለስ ለብቻው ራቅ ብሎ ይጸልይ ገባ:: በዚያም እግዚአብሔር ሲታገለው አደረ:: (ይኸውም የፍቅርና የምሥጢር ነው::) ለጊዜው ጌታ ያዕቆብን "ልቀቀኝ?" ቢለው "ካልባረከኝ አለቅህም?" አለው:: ጌታም ስሙን "እሥራኤል" ብሎ ባርኮታል::
ቅዱስ ያዕቆብ በስተእርጅና ብዙ መከራ አግኝቶታል:: ልጁን ዮሴፍን ወንድሞቹ ሽጠው "አውሬ በላው" ብለውታልና በለቅሶ ዓይኑ ጠፋ:: በረሃብ ምክንያትም በመቶ ሰላሳ ዓመቱ ከሰባ አምስት ያህል ቤተሰቦቹ ጋር ወደ ግብጽ ወረደ:: በዚያም ለሰባት ዓመታት ኑሮ በመቶ ሰላሳ ሰባት ዓመቱ ዐርፏል:: ልጆቹም ቀብረውታል::
††† በሰማይና በምድር ከሞላው ከአባቶቻችን በረከት ፈጣሪያቸው አብዝቶ: አትርፎ: አትረፍርፎም ያድለን::
††† ነሐሴ 28 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ አብርሃም (የአባቶች አለቃ)
2.ቅዱስ ይስሐቅ (የአባቶች አለቃ)
3.ቅዱስ ያዕቆብ (የአባቶች አለቃ)
††† ወርኀዊ በዓላት
1.አማኑኤል ቸር አምላካችን
2.ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ
3.ቅዱስ ቴዎድሮስ ሮማዊ
4.ቅዱሳን እንድራኒቆስና አትናስያ
††† "አብርሃምንና ይስሐቅን: ያዕቆብንም: ነቢያትንም ሁሉ በእግዚአብሔር መንግስት ባያችሁ ጊዜ: እናንተ ግን ወደ ውጭ ተጥላችሁ ስትቀሩ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል::" †††
(ሉቃ. ፲፫፥፳፰)
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
በ facbook ይቀላቀሉን
https://www.facebook.com/profile.php?id=100050228150764 | 252 |
| 5 | ††† እንኳን ለአበው ቅዱሳን አብርሃም: ይስሐቅ እና ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††
†††በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††
††† እኒህ ቅዱሳን ከሰው ወገን እጅግ ክቡራን ከመሆናቸው የተነሳ መንግስተ ሰማያት በእነርሱ ስም ተጠርታለች:: ጽድቃቸውና ክብራቸው እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነውና ጽፈንም: ተናግረንም አንፈጽመውም:: እንዲሁ "ዕጹብ! ዕጹብ!" እያልን ፈጣሪያቸውን ከማመስገን በቀር::
††† ቅዱስ አብርሃም ርዕሰ አበው †††
††† የሃይማኖት: የደግነት: የምጽዋት: የፍቅር አባት የሆነው አብርሃም በቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት አባቱ ታራ ጣዖትን ይጠርብና ይሸጥ ነበር:: ሽጦ ገንዘብ የሚያመጣለት ደግሞ ልጁ አብርሃም ነበር::
በዚያ ወራት አብርሃም እውነተኛውን አምላክ ፍለጋ ገብቶ ነበር:: አንድ ቀን ጣዖቱን ሊሸጥ ወደ ገበያ እየሔደ የተሸከመውን እንጨት ይመራመረው ገባ:: "አሁን ይሔ ምኑ ነው አምላክ!" እያለም ያደንቅ ገባ:: መንገድ ላይም ደክሞት ካረፈበት "ለምን አልጠይቀውም?" በሚል አናገረው::
"እርቦኛል አብላኝ?" አለው:: መልስ የለም:: "እሺ አጠጣኝ?" አለው:: አሁንም ያው ነው:: "ባይሆን እሺ አጫውተኝ?" አለው:: ጣዖቱ ተራ እንጨት ነውና መልሱ ዝምታ ነበር:: ከዚያ ተነስቶ ወደ ገበያው ሲደርስ "ዓይን እያለው የማያይ: ጆሮ እያለው የማይሰማ አምላክ የሚገዛ?" እያለ ይጮህ ጀመር::
ይህን ሲሰሙ አንዳንዶቹ "የታራ ልጅ አብዶ" ሲሉ ሌሎቹ ደግሞ "እሱ ያቀለለውን ማን ይገዛዋል::" ብለውት ሔደዋል:: ሲመለስም ጣዖቱን ተመልክቶ አብርሃም እንዲህ አለ:: "አንተ ቀድሞውን በዕለተ ሠሉስ የተፈጠርክ ዕፅ ነህ::" ብሎ ሰባበረው::
ወደ ቤቱ ሲመለስም ሁሉንም ጣዖታት ሠባበራቸው:: የመንግስተ ሰማያት አበጋዝ: የእግዚአብሔር ወዳጅ አባታችን አብርሃም የሕዝብና የአሕዛብ አባት የሆነው አብርሃም እግዚአብሔርን አምልኮ: ጣዖታትን ሰብሮ ወደ ከነዓን ከወጣ በኋላ ብዙ ችግርን አሳልፏል:: በረሃብ ምክንያት ከአንድም ሁለት ጊዜ ወደ ግብጽና ፍልስጥኤም ተሰዷል:: በዚያ ግን ፈጣሪው አክብሮታል::
ሁለቱ ነገሥታት (ፈርኦንና አቤሜሌክ) ሣራን እንነካለን ቢሉ ተግሣጽ ደርሶባቸዋል:: ነቢይ ነውና በአብርሃም ጸሎት ተፈውሰዋል:: ቅዱስ አብርሃም ከደግነቱ የተነሳ በኬብሮን (በተመሳቀለ መንገድ) ላይ ድንኳን ሠርቶ እንግዳ ይቀበል ነበር:: ምሥክር ሳይዝም እህል አይቀምስም ነበር::
ሰይጣን ከፍቶ እንግዳ ቢያስቀርበት ያለ ምግብ ለሦስት ቀናት ቆይቷል:: በፍጻሜውም ሥላሴ በእንግድነት መጥተውለት በክብር ላይ ክብር: በጸጋ ላይ ጸጋ: በጣዕም ላይ ጣዕም ተጨምሮለታል:: እርሱ የሥላሴን እግር ያጥብ ዘንድ: በጀርባውም ይሸከማቸው ዘንድ አድሎታልና:: ሥላሴም በቤቱ ተስተናግደው: ልደተ ይስሐቅን አብሥረውታል:: ጻድቁ ሰውም በፈጣሪው ፊት ስለ ሰዶምና ገሞራ ለምኗል::
አብርሃም በአምልኮው ፍጹም ነውና የሚወደውን ልጁን ይስሐቅን ለመስዋዕት አቅርቧል:: በዚህም የነቢያት: የሐዋርያት: የነገሥታት: የካህናት አባት: ሥርወ ሃይማኖት (የሃይማኖት ሥር) ተብሏል:: ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ አያቱም ተብሏል::
አንድ ቀን እግዚአብሔር መላእክቱን "ብየ አርክ አብርሃም በዲበ ምድር - በምድር ላይ ወዳጄ አብርሃም አለ::" አላቸው:: ያን ጊዜ ዘጠና ዘጠኙ ነገደ መላእክት ፈጣሪያቸውን አመሰገኑ:-
*"አብርሃም አርከ እግዚአብሔር (አብርሃም የእግዚአብሔር ወዳጅ)"
*"አብርሃም ብእሴ እግዚአብሔር (አብርሃም የእግዚአብሔር ሰው)"
*"አብርሃም ገብረ እግዚአብሔር (አብርሃም የእግዚአብሔር አገልጋይ)"
*"አብርሃም ምዕመነ እግዚአብሔር
(አብርሃም የእግዚአብሔር ታማኝ)
*"አብርሃም ፍቁረ እግዚአብሔር (አብርሃም የእግዚአብሔር ተወዳጁ ነው::) እያሉ አሰምተው ተናግረዋል::
አባታችን አብርሃም በክብር: በቅድስናና በሞገስ ከዘፍጥረት እስከ ዮሐንስ ራእይ ድረስ ተጠቅሷል:: ፈጣሪ በስሙ ለቅዱሳን ተለምኗል:: ስለ ክብሩም በሲዖል ውስጥ እንኳ ማረፊያን ሠርቶለታል:: አጋንንትም ሊቀርቡት አልተቻላቸውም:: ያረፈውም ከክርስቶስ ልደት አንድ ሺ ዘጠኝ መቶ ዓመታት በፊት ነው:: እድሜውም መቶ ሰባ አምስት ዓመት ነበር::
*ፍቅሩን የተረዱ ሊቃውንት ድንግል ማርያምን "ሐይመቱ (ድንኳኑ): ተናግዶቱ (እንግድነቱ) ለአብርሃም" ሲሉ አመስግነዋታል::
ሊቁም:-
††† "አብርሃም ፍጹም በሒሩት ወበአምልኮ:
እግዚአብሔር አዕበየከ ወባረከከ ባርኮ:
እስከ ሰመየከ ዲበ ምድር አርኮ::" ብሎ በምሥጢር ገልጾታል::
††† ቅዱስ ይስሐቅ ርዕሰ አበው †††
††† የደግ ዛፍ ፍሬ: የአብርሃም ልጅ ደጉ ይስሐቅ እጅግ ንጹሕ በመሆኑ የወልድ ክርስቶስ ምሳሌ ተብሏል:: የይስሐቅ ልደት እጅግ የተጠበቀ ከመሆኑ ባሻገር የተፈጸመውም በብሥራተ አምላክ ነው:: ስሙንም ያወጡለት ሥላሴ ናቸው:: ቡሩክ ይስሐቅ በብዙ ነገሩ ድንቅ ነው::
ለእርሱ ሃያ ዓመት ለአባቱ መቶ ሃያ ዓመት በሆናቸው ጊዜ ጭንቅ ትዕዛዝ ከፈጣሪ ዘንድ ተሰማ:: አብርሃም ይሰዋው ዘንድ ወደ ደብረ ምሥጢር ይዞት ከወጣ በኋላ መስዋዕቱ እርሱ እንደ ሆነ አወቀ:: ለፈጣሪውና ለአባቱ ይታዘዝ ዘንድ "እሺ" አለ::
በዚያውም ላይ አባቱን "አባ ስንፈራገጥ እንዳልጐዳህ እሠረኝ:: ዓይኔን አይተህ እንዳትራራ በሆዴ አስተኛኝ::" አለው::
አቤት ትሕትና! አቤት መታዘዝ! ወዮ አባታችን ይስሐቅ! ቅንነትህ ምን ይደንቅ! ለዚህ አነጋገርህ አንክሮ ይገባል!
††† "ሰላም ለይስሐቅ ዘኢያግዘፈ ክሳዶ:
ለደኒን ወለተሐርዶ"
እንዲል::
ቸር ፈጣሪ ግን የአብርሃምን አምልኮ: የይስሐቅን ንጹሕ መታዘዝ ለዓለም ገለጠ እንጂ እንዲሞት አላደረገም:: ቅዱስ ይስሐቅ በዚህች ዓለም ለመቶ ሰማንያ ዓመታት: በትዳር ደግሞ ለመቶ ሃያ ዓመታት ቆይቷል:: ከቅድስናው የተነሳ በእነዚህ ጊዜያት ከአንድ ቀን በቀር ከሚስቱ ርብቃ ጋር አልተኛም:: በዚህቺው ዕለትም ያዕቆብና ኤሳው ተጸንሰዋል::
እግዚአብሔር በመቶ ሰማንያ ዓመቱ ወደ ሰማይ ይዞት ወጣ:: በዚያም ግሩም ምሥጢርን ተመለከተ:: በእሳት መጋረጃ መካከል አብርሃምን አየው:: ከአምላክ ዙፋንም እንዲህ የሚል ቃል ወጣ::
*"ወዳጄን ይስሐቅን የሚያከብረውን አከብረዋለሁ::
*ልጁን አምኖ "ይስሐቅ" ብሎ የሚጠራውን
*በስሙ ለነዳያን የሚራራውን
*ለቤቱ እጣን ያመጣውን
*በዚህች ሌሊት በጸሎት የተጋውን
*'አምላከ ይስሐቅ' እያለ መቶ (100) ጊዜ የሰገደውን
*ዜና ይስሐቅን የጻፈውን: ያነበበውን ሁሉ በመንግስተ ሰማያት ዋጋውን እከፍለዋለሁ::
ይህንንም ልጁ (አባታችን ያዕቆብ) ተመልክቶ ከትቦታል:: ቅዱስ ይስሐቅም ከንጽሕናው ሳይጐድል በበረከት እንዳጌጠ ዐርፏል::
††† ወገኖቼ! ከላይ ካነበባችሁት መርጣችሁ አንዷን በእምነት እንድትፈጽሙ አደራ እላለሁ!
††† ቅዱስ ያዕቆብ ርዕሰ አበው †††
††† የአባቶች አለቃ የተሰኘ ቅዱስ ያዕቆብ ለሁለቱ ታላላቅ አባቶቹ እርሱ ሦስተኛቸው ነው:: እነርሱን መስሎ: እነርሱንም አህሎ በጐዳናቸው ተጉዟል:: በፈቃደ እግዚአብሔር ብኩርናን ከኤሳው ተቀብሎ ወደ ሶርያ ሲሸሽ ቤቴል (ፍኖተ ሎዛ) ላይ ድንጋይ ተንተርሶ በተኛበት ግሩም ራዕይን አይቷል:: | 215 |
| 6 | 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
እንኳን አደረሳችሁ የቸሩ
መድሐኒአለም ልጆች
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
📖📖📖📖📖📖📖📖📖 | 227 |
| 7 | #መልክአ መድሐኔአለም
መድኀኔዓለም ተወከፍ እንተ አቅረብኩ ንስቲተ፤ ዘሰተይከ በእንቲአየ ከርቤ ወሐሞተ፤ በሞተ ዚአከ ከመ ትቅትል ሞተ፡፡ ትርጕም፤ ፈጣሪዬ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ሆይ ፤ በሞትህ ሞትን ታጠፋው ዘንድ ከርቤ የተቀላቀለበትን መራራ ሐሞትን ስለኔ ሕይወት የጠጣህ የአቀረብኳትን አነስተኛ የምስጋና መባ በቸርነትህ ተቀበል፡፡
(መልክአ መድኀኔ ዓለም ለዝክረ ስምከ)
ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
📖📖📖📖📖📖📖📖📖. | 229 |
| 8 | በእምነት ከመያይመስሉን ጋር ማድረግ የሌለብን ነገሮች። | 234 |
| 9 | Matn yo'q... | 236 |
| 10 | ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ምስለ ኖኅ
ኪዳነ ዘአቀምከ፤ ለደቂቀ እስራኤል መና ዘአውረድከ፤
ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወበጽጌያት ምድረ አሠርጎከ፤ ወሥነ
ገዳምኒ ምስለ ቅዱሳኒከ፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወከመ
ወሬዛ ኃየል መላትሒሁ ጉርዔሁ መዓርዒር አምሳሉ
ዘወይጠል፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ሰማየ ወምድረ ዘአንተ
ፈጠርከ፤ ፀሐየ ወወርኀ ዘአስተዋደድከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ፤ በከዋክብት ሰማየ ዘከለልከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ፤ ወበጽጌያት ምድረ አሠርጎከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ፤ ቀደሳ ወአክበራ አዕበያ ለሰንበት፤ ወአልዓላ
እምኵሉ ዕለት፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወኵሉ ይሴፎ ኪያከ፤
#ትርጉም
ከኖኅ ጋር ቃል ኪዳን የገባህ እንዳንተ ይቅር ባይ ማነው
ለእስራኤል ልጆች መናን ያወረድክ፤ ምድርን በአበቦች
ያስጌጥክ፤ እንዳንተ ይቅር ባይ ማነው ? የምድረ በዳውን
አራዊት ከወዳጆችህ ጋር ያስማማህ እንዳንተ ያለ ይቅር ባይ
ማነው፤ ጉንጮቹ እንደ ዋልያ እንቦሳ ፈጣኖች ናቸው፤
አንደበቱ ጣፋጭ ነው፤ ተወዳጅነቱ እንደ ፌቆ ግልገል ነው፤
ሰማይና ምድርን የፈጠርክ፤ ፀሐይና ጨረቃን ያስማማህ፤
ሰማይን በከዋክብት የሸፈንክ፤ ምድርን በአበቦች ያሸበረቅህ፤
ሰንበትን ያከበርካት ከዕለታትም ለይተህ ከፍከፍያደረግኻት፤
አቤት!! እንዳንተ ይቅር ባይ ማንም የለምና ኹሉም አንተን
ተስፋ ያደርጋሉ።
#እንኳን_ለዓለም_ጌታ_ለፍጥረታት_አምላክ_ለነገስታት_ንጉስ_ልዑለ_ባህሪ_ለሆነው_ለአምላካችን_ለመድሐኒታችን_መድኃኒዓለም_ወርሀዊ_በዓል_አደረሰን !
< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo | 417 |
| 11 | #ነሀሴ 26 በዓለ ፅንሰቱ ለወላዴ አእላፍ አቡነ ኢየሱስ ሞአ ዘ ሃይቅ እስጢፋኖስ ወ አቡነ ሀብተ ማርያም ጻድቅ
"+ እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና:: ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና:: ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል . . .
ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ:: የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል::
አንደበቱም ፍርድን ይናገራል:: የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው:: በእርምጃውም አይሰናከልም:: +"+
(መዝ. 36:28-31)
"+ ለመንጋው ምሳሌ ሁኑ እንጂ ማሕበሮቻችሁን በኃይል አትግዙ:: የእረኞችም አለቃ በሚገለጥበት ጊዜ የማያልፈውን የክብርን አክሊል ትቀበላላችሁ:: እንዲሁም ጐበዞች ሆይ! ለሽማግሌዎች ተገዙ:: ሁላችሁም እርስ በርሳችሁ እየተዋረዳችሁ ትሕትናን እንደ ልብስ ታጠቁ:: እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማልና:: ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል::
+ (1ዼጥ. 5:3)
#ስንክሳር ዘወርሃ ሐምሌ
ሰው ሁሉ ለመናገር የዘገየ ለመስማት የፈጠነ ይሁን !
(ያዕቆብ 1፥19)
< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo | 1 538 |
| 12 | † ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል:: ጻድቅን በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል:: †††
(ማቴ.10:40)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
በ facbook ይቀላቀሉን
https://www.facebook.com/profile.php?id=100050228150764 | 2 266 |
| 13 | ✝✞✝ #ግብጽ (እስክንድርያ), (EGYPT, ALEXANDRIA) ውስጥ የሚገኝ የቅዱስ #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ✝✞✝
☞ዛሬ በድምቀት በዓላቸው በግብጻውያንም ይከበራል!
✝ በረከታቸው ይደርብን ✝✞
" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል:: አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
በ facbook ይቀላቀሉን
https://www.facebook.com/profile.php?id=100050228150764 | 1 699 |
| 14 | #ነሀሴ 24
#አቡት ተክለሃይማኖት
#ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ
< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
በ facbook ይቀላቀሉን
https://www.facebook.com/profile.php?id=100050228150764 | 1 605 |
| 15 | Matn yo'q... | 2 803 |
| 16 | መፍትሄውን መናገር አይጠበቅብኝም! ስለሆነም ትውልዱ የሚያንቀላፋበት ዘመን እንዲያበቃ አሳስባለው:: ሀገርም ቤተክርስቲያንም ታላቅ የጥፋት ዘመን ላይ ናቸውና እንንቃ እንዘጋጅ!
ቅድስት ሀገራች ኢትዮጵያ የትናንት ቅርስ ብቻ አይደለችም፤ የነገ ትውልድም ናትና እንጠብቃት!
ድል ለኢትዮጲያ፤ ድል ለቤተክርስቲያን!
ቆሞስ አባ ጳውሊ | 2 149 |
| 17 | በአሁኑ ወቅት ሀገራችን ኢትዮጵያ በታሪኳ አይታው የማታውቀው ውስብስብ እና ጥልቅ መከራ ውስጥ ትገኛለች። ዛሬ በፊታችን የቆመው ጉዳይ የአንድ የፖለቲካ ፓርቲ ወይም የአንድ ትውልድ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ የቀድሞዎቹ አያቶቻችንና የእኛ የማንነት፣ የታሪክ፣ የባህል፣ የእምነት፣ የቀጣዩም የትውልድ ቅርስና የሀገር የወደፊት አቅጣጫ ጉዳይ ነው። በየዕለቱ በሚመጡልን ጊዜያዊ አጀንዳዎች ብቻ ተጠምደን ከእጃችን በቀስታ የሚወጡትን ትልልቅ ነገሮች እንዳንረሳ ኢትዮጵያ ነገ እንዴት ያለች ሀገር ትሆናለች? ብለን ራሳችንን ልንጠይቅ ይገባል። በቅርቡ መንግሥት ለጥፋት ዓላማ ያዘጋጃቸው በተሰብሳቢዎች በሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ውይይቶች ውስጥ የብሔራዊ ምልክቶች፣ ቋንቋ፣ የዘመን አቆጣጠር እና የታሪክ ትርክቶች ሆነው የተነሱ መሆናቸው ይታወቃል። ከእነዚህም መካከል ዓመተ ምሕረት የሚለው ይወገድ የሚሉ ሐሳቦች መቅረባቸው ታሪካዊና ባህላዊ መሰረታችንን ለመሸርሸር የሚደረጉ ጥረቶች እንደሆኑ መታወቅ አለበት። ኮሚሽኑ እነዚህ የውይይት ሐሳቦች የመጨረሻ ውሳኔዎች እንዳልሆኑ እና ሂደቱ ምክረ ሐሳብ ለማቅረብ እንደሆነ ቢገልጽም የተነሳው ሐሳብ ከሀገር ማንነት ጋር ሲያያዝ ሕዝቡ በንቃት መከታተል ያለበት ጉዳይ ነው። መንግሥት ይህንን ጉዳይ እንዲነሳና አጀንዳ እንዲሆን ካደረገ በኋላ ዝም የማለት ማታለል ቢያደርግም በተግባር እየቀየሩት ነው:: አጠቃላይ ከመንግሥት የሚወጡ የጥፋት አጀንዳዎች ህዝብን በማያስነቃ መልኩ ተግባራዊ እያደረጉት ነው:: በበርካታ የአድስ አበባና የኦሮምያ ክልል በአውሮፓዊያን አቆጣጠር መቁጠር ከተጀመረ ቆይቷል:: በሚዲያ እንኳን የብልጽግና አክቲቪስቶች በሙሉ መልእክት ሲያስተላልፉ የሚጠቀሙት የአውሮፓዊያንን ዘመን አቆጣጠር ነው:: ዓመተ ምሕረት የሚለው አጠራር ከክርስቲያናዊ የታሪክ አተረጓጎም፣ ከግዕዝ ፊደል እና ከኢትዮጵያ ረጅም የጽሑፍ ታሪክ ጋር የተያያዘ በመሆኑ ይህ ቃል ሲነሳ ሕዝቡ በቀላሉ እንዳያልፈውና ለምን? ብሎ እንዲጠይቅ አሳስባለሁ:: ዘመኑን ወደ ዓመተ ፍዳ መመለስ ይቻላልን? ብልጽግና ህዝብን በጨለማ ውስጥ ስላኖረው ዘመኑ የምሕረት አይደለም ብሎ አስቦ ይሆን? ምክንያቱን በደንብ ይገባናል! ኢትዮጵያን ማን እያፈረሳት ለምንስ እንደሆነ ግልጽ ነው! በአሁኑ ሰዓት ጦርነቱ ሁሉም የጥፋት በትር ከድያብሎስ እንደራሴዎች ጋር ነው:: ይህን ያልነቃበት ካለ ተሳስቷል:: እኔንና መሰል አባቶችን ምናልባት የፈለጋችሁትን ቃል መሳደብ ትችላላችሁ:: እኔ ሁሌም የምጮኸው ትውልድ እንዲነቃ ነው:: ደግሞ ነቃፊዎቹ የእኛው አካላት መሆናቸው ልብን ይሰብራል! ለነገሩ ከአገዛዙ ጋር ሆነው ሀገርን እያፈረሱ ሃይማኖትን እያስደፈሩ ያሉት አንገታቸው ላይ መስቀል ያደረጉ አይደሉምን? እውነት እነርሱ ያደረጉት መስቀል ትክክለኛው ሳይሆን በጌታችን በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በግራ በኩል የተሰቀለውን የወንበደውን መስቀል ነው አንገታቸው ያሰሩት ብል ስህተት አይሆንብኝም!
ይህ አሁን የሚታየው ሀገራዊ ውድቀትና ግጭት ዋነኛ ምክንያት የኢትዮጵያ ህልውና መሰረት የሆነችውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን እና ታሪካዊ እሴቶቿን ከመጥላት የሚመነጭ እንደሆነ ግልጽ ነው:: ሀገሪቱ የተገነባችው በዚህች ጥንታዊት ቤተክርስቲያን መሰረትነት ላይ በመሆኑ የሀገሪቱን ታሪክ እና ባህል ለመቀየር የሚፈልጉ አካላት ቤተክርስቲያኗንና መዋቅሯን ማዳከም እንደ ዋና መንገድ ይወስዱታል፤ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል የሚካሄዱት ጦርነቶች እና በየቦታው የሚታዩት ውድመቶችም የፖለቲካ መልክ ይሰጣቸው እንጂ ከሀገሪቱ ማንነት መሸርሸር ጋር የተያያዙ ናቸው:: በታሪክ አጋጣሚ የውጭ ኃይሎች በቅኝ ግዛት ያላሳኩትን ዓላማ አሁን ከራሳችን ማህበረሰብ የበቀሉ አካላትንና የውስጥ ችግሮችን በመጠቀም የሀገሪቱን ህልውና የሚፈታተኑ ተግባራት እያከናወኑ ነው:: በሌላ በኩል በሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ውይይቶች ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እና የሀገሪቱን ታሪካዊ እሴቶች የሚወክሉ አካላት እውነተኛ ውክልና አልነበራቸውም የሚል ትችት ስናቀርብ እንደነበር አይዘነጋም። በወቅቱ ያነሳነው ተቃውሞ በጣም ትክክል የመሆናችን ማሳያው ይኸው እንደዚህ የጥፋት አጀንዳዎች ሲፈጸሙ ለጥፋት ተግባር በር ሲከፈት ከቤተክርስቲያን በኩል መከላከል አልተደረገም:: የቤተክርስቲያን ተወካይ ተብለው የቀረቡት የመንግሥት ካድሬዎች ነበሩ! በሂደቱ የተሳተፉት አካላት የቤተክርስቲያኗን እውነተኛ ድምፅ እና የህዝቡን ታሪካዊ ስጋት አያንጸባርቁም፤ ይልቁንም የሚወሰኑት ውሳኔዎች ሀገራዊ መግባባትን ከመፍጠር ይልቅ ቅድስት ኢትዮጵያንና ታሪካዊ ቅርሶቿን የሚጻረሩ ናቸው:: ህዝቡ በተለያዩ ግጭቶችና የኢኮኖሚ ፈተናዎች ተከቦ ባለበት ወቅት በድብቅ የሚከናወኑ የህግና የባህል ለውጦች የሀገሪቱን ዘላቂ ህልውና የባሰ ስለሚያናጉት ቀጣዩ የኢትዮጵያ መከራ ከባድ ነው የሚሆነው::
ውድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆችና ኢትዮጵያን የምትወዱ ሁላችሁም ኢትዮጵያውያን ሆይ እነዚህን ታሪካዊ ማንነታችንን መጠበቅ ማለት ሌሎችን መጥላት ወይም ሌላ ሃይማኖትንና ባህልን መናቅ አይደለም። ራስን ማክበር ሌላውን መጥላት አይደለም፤ ኢትዮጵያዊ ማንነታችንን ማስጠበቅ የሌሎችን መብት ማስከበርን አይከለክልም። የምንፈልገው አንድን ማንነት በሌላው ላይ ማስገደድ ሳይሆን የተለያዩ ማንነቶች በአንድ ሀገር ውስጥ በክብር የሚኖሩበትን የጋራ ሀገራዊ ማዕቀፍ መገንባት ነው። ብልጽግና ማለት የትናንትን ሁሉ መደምሰስ እንዲሁም ዘመናዊነት ማለት ማንነትን መተው ዲሞክራሲ ማለት ታሪክን ማጥፋት አይደለም። በዚህ ዘመን ትልቁ አደጋ ሕዝቡ በየቀኑ በሚመጡ አዳዲስ ዜናዎች በጦርነትና በማኅበራዊ ሚዲያ ክርክር ተጠምዶ ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ ሀገራዊ ጉዳዮችን እንዳይ መሆኑ ነው። ዛሬ አንድ አጀንዳ ይመጣል፤ ነገ ሌላ አጀንዳ ይመጣል፤ እኛም በየአጀንዳው «ሆ» እያልን እንከተላለን። ነገር ግን በዚህ መካከል በስውር የሀገር ምንነት እየጠፋ ነው:: ሁሉን በእኛ ማንቀላፋት ልክ አንመዝን ጠላት ተግቶ እየሰራ ነውና:: ስለዚህ እንንቃ! ንቃት ማለት ጥላቻ ወይም ጦርነት መፈለግ ብቻ አይደለም፤ ንቃት ማለት ጥያቄ መጠየቅ፣ ማስረጃ መፈለግ፣ የመንግሥትን ውሳኔ መመርመር፣ የውጭ ተጽዕኖ ካለ መጠየቅ እና የራሳችንንም ስህተትና አካሄድ መመርመር ነው። አስፈላጊ በሆነ ጊዜ ደግሞ እንደ አባቶቻችን ክንዳችንንም ማበርታት ነው፤ ምን ለማለት እንዳሰብኩ ግልጽ ይሆንላችኋል ብዬ አምናለሁ:: አባቶች ጠብቀው ያቆዩዋትን ሀገር፣ ባህል፣ ታሪክ እና ሃይማኖታዊ እሴቶች ከፍጹም ውድቀት ለማዳን ትውልዱ ከእንቅልፉ ሊነቃ ይገባል። የቀድሞ ትውልዶች ያስረከቡንን ሀገር እኛ በተገቢው መልኩ ተጠቅመን ለሚቀጥለው ትውልድ የማስረከብ ኃላፊነት አለብን። ኢትዮጵያን ለማዳን የምንፈልገው በሕግ፣ በሰላም፣ በእውነት፣ በተጠያቂነትና በዜጎች ንቁ ተሳትፎ ነው። አምባገነናዊነትን መቃወም ማለት ህዝብን በህዝብ ላይ ለጥላቻ አመፅን መጥራት አይደለም፤ ሕጋዊና፣ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ መንገዶችን በመጠቀም ሥልጣን ከሕዝብ በላይ እንዳይሆን መጠየቅ ነው። በፍትሃዊነት የአምባገንኖችን ተግባር በሚመጣጠን መልኩ እንከላከላለን! በዚህ ጊዜ የሚደረገው ትግል ሁሉ ፍትሃዊ ሲሆን ከፈጣሪ ዘንድም የማያስጠይቀን ነው:: ‹‹እግዚአብሔር የእውነት ዳኛ ነው፤ ኃይለኛም ታጋሽም ነው፡፡›› መዝ.፯፥፲፩ እንዲል! ብልጽግና ስልጣኑን ሀገርን ለማፍረስ እየተጠቀመበት እንደሆነ ሁሉም ስለሚያውቀው | 2 404 |
| 18 | Matn yo'q... | 2 162 |
| 19 | #ጥቅስ
እንደ ሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ የሥጋን ነገር ያስባሉና፥ እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ።
ስለ ሥጋ ማሰብ ሞት ነውና፥ ስለ መንፈስ ማሰብ ግን ሕይወትና ሰላም ነው።
ሮሜ 8:5-6
#አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ ጌታ ሆይ ማራቸው
ከፍ ከፍ አድርጋቸው/2/
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ግሩኙን ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedoo
#ለሃሳብ አስተያየት
@Orthodox_tewahedo_Bot | 2 073 |
| 20 | #ብሂለ አበው
"በዕብራይስጥ ማርይም የተባልሽ የተመረጥሽ እመቤቴ ድንግል ማርይም ሆይ ፍጡራንን ሁሉ ከሚጎዳ ደዌና መከራ እድኝኝ"
♦️አባ ጊዮርጊስ
#አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ ጌታ ሆይ ማራቸው
ከፍ ከፍ አድርጋቸው/2/
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ግሩኙን ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedoo
#ለሃሳብ አስተያየት
@Orthodox_tewahedo_Bot | 2 087 |
