Sheger Press️️
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Sheger Press️️
تُعد قناة Sheger Press️️ (@sheger_press) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 35 733 مشتركاً، محتلاً المرتبة 7 220 في فئة الأخبار والوسائط والمرتبة 948 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 35 733 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 01 أغسطس, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -194، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -8، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 16.42%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 11.59% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 870 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 4 144 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 26.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“Official channel of sheger press
Contact @Birukepromo”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 02 أغسطس, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الأخبار والوسائط.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 03 أغسطس | +4 | |||
| 02 أغسطس | +5 | |||
| 01 أغسطس | +1 |
| 2 | መድኃኔአለም በሐጢዓት ፈተና ተጠልፎ ከመውደቅ ይጠብቀን🙏
የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ቄርሎስ “ለቤተ ክርስቲያን ስትል በአደባባይ በጥፊ የተመታህ አቤቱ ይህን ማድረግህ እርስዋን በከበረ ደምህ ትቀድሳት ዘንድ ነው፡፡
ለእርስዋ ሲል ታሥሮ መጎተት የቻለ የበደለውም በደል ሳይኖር፣ ርኩስ ምራቅን ሲተፋበት የታገሠ መድኃኔ ዓለም በእንጨት መስቀል ላይ ተሰቀለ” በማለት ገለጸው፡፡ በመለኮቱ ሕያው ሲሆን በስጋው ግን ሞትን ቀመሰ፡፡ የአዳምን ሞት በሞቱ ሊሽር መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን በገዛ ፈቃዱ አሳልፎ ሰጠ፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር ሰው ሆኖ እንደሚያድነን በመጀመሪያ ለአዳም ቃል ገባለት፡፡ ከዚያም በነቢያት ትንቢት አስነገረ፡፡ በስጋ በተገለጠ ጊዜም የሰቀሉትና የገደሉት አይሁድ ሳይቀሩ እንዲናገሩ አፋቸውን አስከፈታቸው፡፡
ቅዱስ ጳውሎስም “ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን… አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን” ይላል፡፡ “ስለ ሕዝቡም ሁሉ አይደለም፣ ነገር ግን የተበተኑትን የእግዚአብሔርን ልጆች በአንድነት እንዲሰበስባቸው መጥቷል እንጂ።” ተብሎ ተጽፏልና፡፡ በድንቅ ተዋህዶ አምላክ ሰው፣ ሰውም አምላክ ሆኗልና ከኛ በነሳው ስጋም ወደ ሰማይ አረገ፡፡ ስለፍጹም የሰው ልጆች ፍቅር መድኃኔ ዓለም ተላልፎ ተሰጠ፡፡
በፊልጵ 2÷8 “በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፣ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ” ተብሎ እንደተጻፈው፡፡ በማዳኑ ስራ ውስጥ የቅድስት ድንግል ማርያም ድርሻ ታላቅ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በገላ 4÷4 “የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ልጁን ላከ፡፡” ሲል ጽፏል፡፡
ዕለት ዕለት ፍቅሩን የከፈለልንን ዋጋ፣ ይህን መከራውንና ማዳኑን ዕለት ዕለት የሚያስቡ ገዳማውያን ሌሊትና ቀን በስግደትና በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቱን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጸና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 3 722 |
| 3 | لا يوجد نص... | 3 379 |
| 4 | በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ ዝግጅት ተጠናቀቀ
በመላው ሀገራችን በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል በተያዘው ታላቅ ሀገራዊ መርሐ ግብር መሠረት፤ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልም ለተከላው የሚጠየቀው ዝግጅት መጠናቀቁ ተገልጿል::
ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በሚካሄደው በዚህ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ዘመቻ ከ16 ሺህ 516 ሄክታር በላይ መሬት በልዩ ሁኔታ የተዘጋጀ ሲሆን፤ በተለያዩ አርሶ አደሮች ማሳ ላይ የሚተከሉ ችግኞችም በዕለቱ መርሐ ግብር ውስጥ ተካትተዋል | 4 482 |
| 5 | የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች።
በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች።
ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።
አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።
እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡
የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች።
ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 4 625 |
| 6 | لا يوجد نص... | 3 850 |
| 7 | “በብር ደመወዝ የሚከፈላቸው ሰዎች ገቢያቸው እጅግ ቀንሷል”ዳቪድ ማልፓስ
የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዳቪድ ማልፓስ የኢትዮጵያ ብር መዳከም እና የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያዎች ድህነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማባባሳቸውን በመግለጽ፤ በብር ደመወዝ የሚከፈላቸው ሰዎች «ገቢያቸው እጅግ ቀንሷል» ሲሉ ተናግረዋል።
በተቃራኒው ጥቂት ቡድኖች የውጭ ምንዛሬን እና የሀገር ውስጥ ብድርን በልዩ ሁኔታ ማግኘት በመቻላቸው ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ማልፓስ፤ ስታንሊ ፊሸር መታሰቢያ በተሰኘ መድረክ ላይ ባቀረቡት የፖሊሲ ጥናት ላይ ኢትዮጵያን በዋና ምሳሌነት የተጠቀሙ ሲሆን፥ ሀገሪቱ የእርሻ መሬት፣ የተፈጥሮ ሀብት፣ የውኃ፣ ተስማሚ የአየር ንብረት እና የሰው ኃይል አቅም ያላት በመሆኗ «ትልቅ የእድገት አቅም» ያላት ሀገር እንደሆነች ገልጸዋል።(AS) | 5 268 |
| 8 | የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
በነገሥታት ፊት የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ።
የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ገዳም ስትገባ የተቀደሰ ልጅ እንደምትወልድ ተነግሯት የተመለሰችው እናቱ ዮስቲና ትባላለች። ልጅም ሲወልዱ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔርም አንጸው አሳደጉት።
በቤተ ክርስቲያንም የሰማውን “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የምትል ጸሎት እጅጉን ቢወዳት ሌሊቱን ሙሉ በቤቱ እየጸለያት የሚጋደል ሆነ። አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ ጓደኞቹን “ዝናም ይዘንማልና ወደቤት እንግባ” አላቸው። ቃሉን ሊሰሙት ባይወዱ በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ኃይለኛ ዝናም ዘነመ። ገና በአዳጊነት እድሜውም ብዙ ተአምራት ያደርግ ነበር፡፡
በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል። እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ ጌታችን ተገለጠለት። አቡነ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡
ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ ስለማንበቡ፣ ስለተጋድሎው፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። ከሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትንና ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የብርሃን ሠረገላም ሰጠው፣ መታሰቢያውን የሚያደርጉትን እንደሚምርለትም፣ ቃል ኪዳን ገባለት። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው ስትለይም ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፤ ገዳማቸውን እንደግፍ ከበረከታቸውም እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 5 503 |
| 9 | لا يوجد نص... | 5 038 |
| 10 | ተራዝሟል‼️
በመዲናዋ የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት ጊዜ ተራዘመ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ተራዝሟል፡፡
ከተማ አስተዳደሩ እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲካሄድ አስታውቆት የነበረውን የቤት ኪራይ ውል እድሳት ነው እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ያራዘመው፡፡
የከተማ አስተዳደሩ የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ሕገ ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን በዘላቂነት ለመግታት የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11 ነጥብ 5 በመቶ እንዲሆን መወሰኑ ይታወቃል፡፡
ይህንን ተከትሎ በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ ተከራይ የውል እድሳት ምዝገባ ጊዜ እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የነበረው እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን ቢሮው አስታውቋል።
የውል እድሳት ጊዜው በሕብረተሰቡ ጥያቄ መሰረት የተራዘመ ሲሆን ÷ ይህም ነዋሪው ያለምንም መጨናነቅ እንዲዋዋል ያስችላል፡፡
ነዋሪው በሁሉም ክ/ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት ፤ በየወረዳው በተዘጋጁ የውል ቦታዎች እና በሁሉም ክ/ከተማ አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስፈላጊውን መረጃ በመያዝ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችል መገለጹን የቢሮው መረጃ አመልክቷል፡፡ | 6 493 |
| 11 | በአሜሪካ ጥገኝነት ጠያቂዎች ያለ ቃለ-መጠይቅ ወደ ፍርድ ቤት የሚላኩበት መመሪያ ጸደቀ።
የትራምፕ አስተዳደር በሀገሪቱ ጥገኝነት የጠየቁ ስደተኞችን የሚመለከት አዲስ መመሪያ አውጥቷል።
ይህን ተከትሎ በርካታ ጥገኝነት ጠያቂዎች ጉዳያቸው ሳይሰማ ቀጥታ ሊባረሩ የሚችሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
አዲሱ አሰራር ከ1.4 ሚሊዮን በላይ የተከማቹ የጥገኝነት ማመልከቻዎችን ለማቃለል የታሰበ ነው ተብሏል።
ቀደም ሲል የነበረው አሰራር አመልካቾች መጀመሪያ ጉዳያቸውን ለኢሚግሬሽን ኦፊሰር አቅርበው ጥያቄያቸው ውድቅ ከተደረገ ብቻ ወደ ፍርድ ቤት እንዲመሩ የሚያደርግ ነበር።
በአዲሱ መመሪያ በርካታ የጥገኝነት አመልካቾች ከኢሚግሬሽን ኦፊሰሮች ጋር የሚደረገውን የመጀመሪያ ደረጃ ቃለ-መጠይቅ ሳያደርጉ ጉዳያቸው በቀጥታ ወደ ፍርድ ቤት ሊመራ ይችላል።
444,724 ያህል መዝገቦችን ይነካል የተባለው ይህ ውሳኔ የሕግ ባለሙያዎችና የኢሚግሬሽን ተከራካሪዎች አሰራሩ የስደተኞችን የመሰማትና የፍትህ የማግኘት መብት የሚጎዳና ውሳኔዎችን በማፋጠን ሰዎችን በፍጥነት ለማባረር ያለመ ነው በማለት ተችተውታል።
በሌላ በኩል ፥ የአሜሪካ መንግሥት በሀገሪቱ በሚማሩ የውጭ ሀገር ተማሪዎች ላይ እስከ 100,000 ዶላር የሚደርስ አዲስ ክፍያ ለመጣል ማቀዱ ተሰምቷል።
የታቀደው እርምጃ በተለይ ትምህርታቸውን አጠናቀው በአሜሪካ ለመቆየት ለሚፈልጉ ዓለም አቀፍ ተማሪዎች ፈተና ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል።
መንግሥት እርምጃው የቪዛ አጠቃቀምን ለማጥበቅና የሀገር ውስጥ የሥራ ገበያን ለመጠበቅ ያለመ መሆኑን ሲገልጽ፣ ተቃዋሚዎች ግን የውጭ ተማሪዎች ለአሜሪካ የትምህርትና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላቸውን አስተዋፅኦ ሊጎዳ ይችላል በማለት ስጋታቸውን ገልጸዋል።
የትራምፕ አስተዳደር ከስደተኞች ጋር በተያያዝ እጅግ ጠንካራ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑ ተደጋግሞ መገለጹ ይታወሳል። | 5 916 |
| 12 | እንኳን ለቅዱስ መርቆርዮስ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ፤አደረሰን🙏
የመጀመሪያ ስሙ ፒሉ-ፓዴር ሲሆን ቤተሰቦቹ አረማውያን ሲሆኑ ከአምልኮተ ጣኦት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር የተመለሱ ናቸው፡፡ ፊታቸው የውሻ የሆነ፣ የአውሬነት ጸባይ ያላቸው በእግዚአብሔር ኃይል የሚታዘዙት ሁለት አገልጋዮች የነበሩት አባቱ ወደ መርዶሳውያን ሀገር ተማርኮ ቢሔድም ጸጋ እግዚአብሔር በዝቶለት በዚያ ሹመት አጊቷል፡፡ ልጃቸው ቅዱስ መርቆርዮስን የወለዱት ግን በሮም ነው፡፡ ወላጆቹ ሲያርፉም የአባቱን ስልጣን ተረክቧል፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ በክርስቲያኖች ሁሉ ዘንድ እንደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ታሪካቸው ከሚነገርላቸው ሰማዕታት አንዱ ሲሆን በሀገራችን በኢትዮጵያም በአማላጅነቱ የሚታወቀው ታላቁ ሰማዕት ነው፡፡ መርቆሬዎስ ማለት የአብ ወዳጅ ማለት ነው። በሁለተኛ ትርጉሙ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው። በሀገራችን በኢትዮጵያም በበርካቶች ዘንድ በፈጣን ተራዲኢነቱ ይታወቃል፡፡
የዓለም ክብራቸውን ስለ ክርስቶስ ፍቅር ከጣሉና በተጋድሏቸው ከሚታወቁ ሰማዕታትም አንዱ ነው፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስ የአባቱን ስልጣን ወርሶ በንጉሱ ስር በመርዶሳውያን አገር ላይ ተሾመ፡፡ መርቆሬዎስ በመኰንንነት በተሾመም ጊዜ የውሻ ፊት ያላቸው የአባቱ አገልጋዮች አብረውት ነበሩ፤ ለመዋጋትም ሲወጣም እግዚአብሔር የአውሬነት ተፈጥሯቸውን ይመልስለት ስለነበር ማንም አይቋቋመውም ነበር፡፡ የድል አድራጊነት ኃይሉ ዜናም በሁሉም ሀገሮች ተሰማ፡፡ በሮሜ ሀገር ጣዖትን የሚያመልከው ዳኬዎስ የተባለውም ንጉሥ የበርበር ሰዎች ጋር ጦርነት ሊገጥም በወጣ ጊዜ እጅግ ሲበዙበት ፈራ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስ ግን በጦሩ መካከል የተሳለ ሰይፍ የያዘ የእግዚአብሔርን መልአክ ስላየ “እግዚአብሔር ያጠፋቸዋልና አትፍራ” አለው፤ ከዚያም ሰይፉን ለቅዱስ መርቆሬዎስ ሰጠውና “ጦርነቱን ድል ባደረግህ ጊዜ እግዚአብሔርን አስበው” አለው፡፡
ቅዱስ መርቆሬዎስ በድሉ ውስጥ ትልቅ ድርሻ በወሰደበት ውጊያም ጦርነቱ በንጉሱ ዳኪዮስ ወገን አሸናፊነት ተጠናቀቀ፡፡ መርቆሬዎስም ድል አድርጎ ሲጨርስም መልአኩ ድጋሚ ተገልጦለት “ለምን የፈጣሪህን ስም መጥራት ረሳህ” አለው፡፡ ንጉሡ ግን ከጦርነቱም በኋላ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረግ በዓልን አደረገ፡፡ በዚህ ያዘነው ቅዱስ መርቆሬዎስ ግን አልተገኘም፡፡ ንጉሡም መልእክተኞችን ልኮ አስመጣውና “ከእኔ ጋር ለምን አታጥንም?” አለው፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስ ትጥቁንና ልብሱን አውልቆ ከወረወረለት በኋላ “ክብር ይግባውና አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን ፈጽሞ አልክደውም፤ ለረከሱ ጣዖቶችህም አልሰግድም” አለው፡፡ ከዚህ በኋላ ሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ በክርስትናው ተፈተነ፤ ውለታው ተረስቶ ንጉሡ በልዩ ልዩ ሥቃዮችም እጅግ አሠቃየው፡፡ ይሁንና ስለ መርቆሬዎስ ብለው የሀገሩ ሰዎች እንዳይነሡበት ፈርቶ በብረት ችንካር ቸንክሮ የቀጵዶቅያና የእስያ ክፍል ወደ ሆነች ወደ ቂሳርያ ከደብዳቤ ጋር ላከው፡፡
በዚያም እጅግ ካሠቃዩት በኋላ በንጉሥ ዳኬዎስ ትዕዛዝ ኅዳር 25 ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆረጡትና የሰማዕትነት ተጋድሎውን ፈጸመ፤ በየወሩ በ25ኛው ቀንም መታሰቢያው ነው፡፡ የሕይወትንም አክሊል ተቀዳጀ፤ በዓለሙ ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት ታነጹለት፡፡ ዛሬም የገዳማውያንን ጸሎት ይሰማል፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957 | 5 706 |
| 13 | لا يوجد نص... | 5 159 |
| 14 | ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ ታሰረ።
የ"እግረኛው ሚዲያ" መስራችና ባለቤት የሆነው ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰምቷል።
ጋዜጠኛው በቁጥጥር ስር የዋለው በትናንትናው ዕለት ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሆነ የታወቀ ሲሆን፤ ለእስሩ ምክንያት ከመከላከያ ሰራዊት አልባሳት (ዩኒፎርም) ጋር ተያይዞ ከቀረበው ዘገባ ጋር ሳይያያዝ እንዳልቀረ ምንጮቹ ጠቁመዋል። | 6 349 |
| 15 | የአባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ረድኤት እና ምልጃ አይለየን🙏
በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት ሥላሴን አመስግነዋል፡፡
አባታቸው ጸጋ ዘአብና እናታቸው እግዚእ ኃረያ ፍሥሐ ጽዮን ብለው ሰየሟቸው፡፡ በአንድ ወቅት ታዳጊው ፍሥሐ ጽዮን ወደ ጫካ ለአደን በሔዱበት ጌታችን ተገልጦ ጸጋ መንፈስ ቅዱን አሳደረባቸው፡፡ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ለስብከተ ወንጌል እንደሚልካቸውም አስረዳቸው፡፡ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው መዓርገ ዲቊናን፣ በ22 ዓመታቸው ደግሞ መዓርገ ቅስናን ከግብጻዊው ጳጳስ አባ ቄርሎስ ተቀብለዋል፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ስማቸውም ተክለ ሃይማኖት እንደሚባል፣ ትርጓሜውም ተክለ አብ፣ ተክለ ወልድ፣ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት እንደሆነ አበሠራቸው፡፡
ወላጆቻቸው ካረፉ በኋላም ንብረታቸውን ሁሉ ለቤተ ክርስቲያንና ለነዳያን ሰጥተው ቤታቸውን ትተው ወንጌልን ለማስተማር ወጡ፡፡ በደብረ ዳሞ ገዳም ለ12 ዓመታት ተቀምጠው ሲወርዱ ገመዱ ቢበጠስ ስድስት ክንፍ አውጥተው በረዋል፡፡ በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ወንጌልን በመስበክና ተአምራትን በማድረግ በርካታ አሕዛብን አጥምቀዋል፤ አብያተ ክርስቲያናትንም አሳንጸዋል፡፡ በደብረ ሊባኖስ ገዳም አስቦ ዋሻ በዙሪያቸው ስምንት ጦሮች ተክለው እጆቻቸውን በትእምርተ መስቀል በመዘርጋት የክርስቶስን ሕማምና ሞት በማሰብ ሌሊትና ቀን ያለ ማቋረጥ በጾምና በጸሎት ሲጋደሉ፤ ከመቆም ብዛት አንድ እግራቸው ተሰብራል፡፡
ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ በኋላም ለሰባት ዓመታት በአንድ እግራቸው ቆመው ለሰው ዘር ሁሉ ድኅነትን ለምነዋል፡፡ ከዚህ ዓለም ድካም በሚያርፉበት ቀንም ጌታችን ከእናቱ ከቅዱሳን መላእክት፣ ከወዳጆቹ ጋር መጥቶ የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡
የጻድቁን ቃል ኪዳን ያመኑ ገዳማውያን እንደሳቸው ሁሉ ዓለምን ንቀው በተጋድሎ ይኖራሉና ከበረከታቸው እንድንሳተፍ ገዳማቸውን እየደገፍን በዓታቸውን እያጸናን ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 6 363 |
| 16 | لا يوجد نص... | 5 705 |
| 17 | ወርቅነህ ገበየሁ ሱዳን ምን እግር ጣላቸው‼
ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ሱዳን ካርቱም ገብተዋል!
የኢጋድ ሊቀመንበሩ ጉዞ የሱዳኑን አስከፊ ጦርነት በድርደር "ለመቋጨት" ያለመ እንደሆነ ተዘግቧል፡፡
ባሁኑ ወቅት የሱዳን ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እየተለጠጠ እና በኢትዮጵያ ካለው የአገር ውስጥ ግጭት ጋር ተያይዞ እየተነሳ መሆኑ ይታወቃል፡፡
| 6 217 |
| 18 | የአባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ረድኤት እና ምልጃ አይለየን🙏
ታኅሣሥ 24 ቀን 1212 ዓ.ም ከካህኑ አባታቸው ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኃረያ በእግዚአብሔር መልካም ፈቃድና በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ብሥራት ተወለዱ፡፡
ወላጆቻቸውም ፍሥሐ ጽዮን ብለው ሰየሟቸው፡፡ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት ሥላሴን አመስግነዋል፡፡ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው መዓርገ ዲቊናን፣ በ22 ዓመታቸው ደግሞ መዓርገ ቅስናን ከግብጻዊው ጳጳስ አባ ቄርሎስ ተቀብለዋል፡፡ በአንድ ወቅት ሕፃኑ ፍሥሐ ጽዮን ወደ ጫካ ለአደን በሔዱበት ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጦ ጸጋ መንፈስ ቅዱን አሳደረባቸው፡፡ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወንጌል ወዳልተዳረሰበት ቦታ እንደሚልካቸውም አስረዳቸው፡፡
ቅዱስ ሚካኤልም ከአዳኝነት ሰውን ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመመለስ እንደተመረጡ፣ ስማቸውም ተክለ ሃይማኖት እንደሚባል፣ ትርጓሜውም ተክለ አብ፣ ተክለ ወልድ፣ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት እንደሆነ አበሠራቸው፡፡ ከዚህ በኋላ ያላቸውን ንብረት ዅሉ ለቤተ ክርስቲያንና ለነዳያን ሰጥተው “አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! የመንግሥተ ሰማያትን በር ትከፍትልኝ ዘንድ እነሆ ቤቴን እንደ ተከፈተ ተውኹልህ” በማለት ቤታቸውን ትተው ወንጌልን ለማስተማር ፈጥነው ወጡ፡፡ በደብረ ዳሞ ገዳምም ለ12 ዓመታት ተቀምጠው ከዚያ ሲወርዱ ገመዱ ገመዱ ሲበጠስ ስድስት ክንፍ አውጥተው በረዋል፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምረው በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ወንጌልን በመስበክና ተአምራትን በማድረግ በርካታ አሕዛብን ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር፤ ከገቢረ ኀጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ መልሰዋል፡፡ አብያተ ክርስቲያናትንም አሳንጸዋል፡፡
ከዚህ በኋላ በደብረ ሊባኖስ ገዳመ አስቦ ዋሻ በመግባትም በዙሪያቸው ስምንት ጦሮችን ተክለው እጆቻቸውን በትእምርተ መስቀል በመዘርጋት የክርስቶስን ሕማም፣ ሞትና ነገረ መስቀል በማሰብ በተመስጦ ለ22 ሌሊትና ቀን ያለ ማቋረጥ በጾምና በጸሎት ተወስነው ሲጋደሉ፤ ከመቆም ብዛት የአንድ እግራቸው አገዳ ተሰብራል፡፡ ደቀ መዛሙርቱም የመንፈሳዊ አባታቸውን የዐፅም ስባሪ አክብረው አኑረውታል፡፡ እግራቸው ከተሰበረ በኋላም ለሰባት ዓመታት በአንድ እግራቸው ቆመው ሌሊትና ቀን ጸንተው ለሰው ዘር ሁሉ ድኅነትን ሲለምኑ ጥቂት ውኃ እንኳ የቀመሱት በአራተኛው ዓመት ብቻ እንደ ነበረ መጽሐፈ ገድላቸው ይናገራል፡፡ ጻድቁ አባታችን ምድራዊ ሕይወታቸውን በተጋድሎና በሐዋርያዊ አገልግሎት ከፈጸሙ በኋላ ከዚህ ዓለም ድካም የሚያርፉበት ቀን ሲቃረበ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከቅዱሳን መላእክት፣ ከወዳጆቹ ጋር መጣ፡፡
በስማቸው መታሰቢያ ለሚያደርጉ፣ ለነዳያን ለሚመጸዉቱ ቤተ ክርስቲያን ለሚያሠሩ የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጥቷቸው፣ ስለ ተጋድሏቸው ጽናትም “በሰው እጅ የማይለካውን ይህንን የመንግሥት አዳራሽ ውሰድ” በማለት የጸጋ ልብስ አልብሷቸው፤ በመስቀል ምልክት ያጌጡ ሰባት የሕይወት አክሊላትንም አቀዳጅቷቸው በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም የመንፈስ ልጆቻቸውን ጠርተው ጌታችን የነገራቸውን ዅሉ አስረድተው አባታዊ ምክርና ተግሣፅ ከሰጧቸው በኋላ ነሐሴ 24 ቀን በዘጠና ዘጠኝ ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል፡፡ የመንፈስ ልጆቻቸውም በማኅሌት፣ በዝማሬና በምስጋና ቀብረዋቸዋል፡፡ጌታችንም ነፍሳቸውንም በክብር ተቀብሏታል፡፡ የጻድቁን ቃል ኪዳን ያመኑ ገዳማውያን እንደሳቸው ዓለምን ንቀው በተጋድሎ ይኖራሉ፡፡ ገዳማቸውን እየደገፍን በዓታቸውን እያጸናን ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
| 6 573 |
| 19 | لا يوجد نص... | 5 214 |
| 20 | በሀዋሳ ከተማ በረዶ ቀላቅሎ በጣለ ከባድ ዝናብ የአንድ ሰው ህይወት አለፈ
👉አደጋው በ1ሰው ላይ ከባድ እና በ8 ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት ኡድርሷል
በሀዋሳ ከተማ ትናንት ምሽት በተከሰተው ያልተለመደ ኃይለኛ ንፋስ እና በረዶ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ ምክንያት የአንድ ሰው ህይወቱ ማለፉን የከተማዋ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል።በአደጋው አንድ ሰው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ሲደርስ በ8 ሰዎች ደግሞ ቀላል ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገልጿል።
የሀዋሳ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የመምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ቶርባ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት በአደጋው በርካታ ቤቶች ጣሪያዎች በኃይለኛው ንፋስ ተነስተው በመውደቃቸው በሰዎችና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል።በተጨማሪም የኮንክሪት የኤሌክትሪክና የቴሌ ፖሎች በመውደቃቸው በከተማዋ በባህል አዳራሽ ምሥራቅ እና መሀል ክፍለ ከተማዎች አካባቢ የኃይል መቋረጥ መከሰቱን ገልጸዋል።
በአደጋው ሁለት መኪኖችና አንድ ባጃጅ ላይ የዛፍ ቅርንጫፎች በመውደቃቸው የመስታወት መሰበር ጉዳት ቢደርስም ከባድ ጉዳት እንዳልደረሰባቸው ተጠቁሟል። በባጃጁ ውስጥ የነበሩ ሰዎች ከአደጋው በፊት ወጥተው በመጠለላቸው ከጉዳት መትረፋቸው ተገልጿል።በከተማዋ የተሰሩት የኮሪደር ልማት ላይ የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ ለአቶ ወንድሙ ብስራት ሬዲዮ ጥያቄ ያነሳ ሲሆን አዳዲስ የተሰሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች እና ቦዮች ወይም ካናሎች ጎርፍ በቀላሉ እንዲፈስ ስለረዱ ከጎርፍ ጋር ተያይዞ የሚመጣውን አደጋ በከፍተኛ ሁኔታ ቀናንሰውታል በኮሪደር ልማቱ ላይ የደረሰ የጎርፍ ጉዳት የለም ሲሉ ተናግረዋል።
የከተማ አስተዳደሩና የተለያዩ አካላት በማድረግ ባሉት የመስክ ምልከታ መሠረት አስቸኳይ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ድጋፍ ለማድረግ ሥራዎች እየተጀመሩ መሆኑ ተገልጿል።አደጋው ለ8 ደቂቃ ያህል አጭር ጊዜ ቢቆይም የንፋሱና የበረዶው መጠን ከፍተኛ እንደነበር ተጠቁሟል። ህብረተሰቡም የቅድመ ማስጠንቀቂያ መረጃዎችን በመከታተል ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል። | 6 138 |
