Sheger Press️️
📈 Análisis del canal de Telegram Sheger Press️️
El canal Sheger Press️️ (@sheger_press) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 35 473 suscriptores, ocupando la posición 7 168 en la categoría Noticias y medios y el puesto 983 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 35 473 suscriptores.
Según los últimos datos del 02 septiembre, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -251, y en las últimas 24 horas de -22, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 14.76%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 11.02% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 239 visualizaciones. En el primer día suele acumular 3 912 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 23.
📝 Descripción y política de contenido
El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“Official channel of sheger press
Contact @Birukepromo”
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 03 septiembre, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Noticias y medios.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 03 septiembre | 0 | |||
| 02 septiembre | 0 | |||
| 01 septiembre | 0 |
| 2 | እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከክፉ ነገር ሁሉ ትከልለን፤ ምልጃዋ እና ረድኤቷም አይለየን🙏
በመጽሐፍ ቅዱስ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ያህል ትንቢት የተነገረላት ስለእርሷ የተጻፈላት ሴት የለችም። በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብዙ ምሳሌዎች ተጠቅሰዋል፤ የኖኅ መርከብ፣ ሰላማዊት ርግብ፣ የአብርሃም ድንኳን፣ ሙሴ በሲና ያያት ሐመልማል፣ ጽላተ ሙሴ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሐውልት፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ፣ የአሮን በትረ፣ የጌዴዎን ፀምር፣ የኖኅ የቃል ኪዳኑ ቀስተ ደመና፣ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ያያት መሰላል፣ የነቢዩ ኤልሳዕ ማሰሮና ሌሎች ምሳሌዎች በሰፊው የተነገሩላት የተጻፉላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ቤተ ክርስቲያን እርስዋን ለመጥራት የምትጠቀምባቸው ቅጽል ስሞቿና ውዳሴዎቿ ምንኛ ድንቅ ቢሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ገላጭነት በቅዱሳን የተነገሩ ምስጋናዎቿስ እጅግ ቢለዩ የክብሯን ያህል የሚገልጿት አይደሉም፡፡
እርሷ የሰው ሁሉ ረዳትና ርኅሩኅ እናት ናት፤ የብርሃን፣ የምሕረት፣ የድኅነትና የአማናዊው ወይን እናት ናት። ከንጉሡ በስተቀኝ የምትቆመው ንግሥት እርስዋ ናት፤ በመስቀል ስር የተቀበልናት የሁላችንም እናት እርሷ ናት፤ እርሷ ዘለዓለማዊ ድንግል ናት፤ እርሷ የእግዚአብሔር ጸጋ የሞላባት ንጽሕት ቅድስት ድንግል ናት፡፡ ከፍጥረት ሁሉ ተለይታ ወላዲተ አምላክ ለመሆን የተመረጠችበት አንዱ ምክንያት እመቤታችን እጅግ ትሑት፣ ፍጽምትና ንጽሕት ስለሆነች ነው። በሉቃስ 1÷48 እንደተጻፈው የአምላክ እናት እንደምትሆን ተነግሯት እንኳን ክብር ይግባትና ከመኩራትና ሌሎችን ከመናቅ ይልቅ ዘመዷ ኤልሳቤጥን ልትጠይቃት ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ወጣች፡፡ ከኤልሳቤጥ ፍጹም ምስጋናና በማሕጸን ያለው ዮሐንስ የሰላምታ ድምጿን ሰምቶ መዝለሉንከሰማች በኋላም “የባሪያይቱን መዋረድ ተመልክቷልና” በማለት በትሕትና ምስጋናዋን አቀረበች እንጂ የትዕቢት ቃል ከአፏ አልወጣም፡፡
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ “እርሷ በእግዚአብሔር ዓይን በታየ የቅድስና ውበት የተሞላች ነበረችና በእርሷ ንጹሕ ማሕፀን ሊያድር ወደደ፤ እንደ ድንግል ማርያም ራሱን ዝቅ ያደረገ ትሑት ማንም የለም” ይላል። ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም “በትሕትና የተናገርሽ ተራራ ሆይ…” ብሎ ያመሰገናት ይህች ድንግል ከተራሮች አናት ሁሉ ከፍ ያለች ስትሆን ራሷን ዝቅ አድርጋ “እንዲህ ያለ የምስጋና እጅ መንሻ እንደምን ይደረግልኛል” የሚል ምላሽ ለቅዱስ ገብርኤል ሰጠችው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ማርያም ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛው አምላክ ልጇ ነውና ማርልኝ ስትለው ምልጃዋ ፍጹም ነው፡፡ በእግዚአብሔር መመረጧ፣ ከሴቶች ሁሉ መለየቷ፣ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ መሆኗ ይህን ክብር አጎናጽፏታልና፡፡ ገዳማውያንም ይህን ልዩ እናትነቷንና ቅድስናዋን አምነው ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሯታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፡- ቤተ ቅዱሳን ፈትለወርቅ ማርያም የእናቶች ገዳም፡-
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000766349227
ወይም
አቢሲንያ ባንክ
262281132
የገዳሙ ስልክ ቁጥር፡- 0944672222 ወይም 0916106921እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከክፉ ነገር ሁሉ ትከልለን፤ ምልጃዋ እና ረድኤቷም አይለየን🙏
በመጽሐፍ ቅዱስ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ያህል ትንቢት የተነገረላት ስለእርሷ የተጻፈላት ሴት የለችም። በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብዙ ምሳሌዎች ተጠቅሰዋል፤ የኖኅ መርከብ፣ ሰላማዊት ርግብ፣ የአብርሃም ድንኳን፣ ሙሴ በሲና ያያት ሐመልማል፣ ጽላተ ሙሴ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሐውልት፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ፣ የአሮን በትረ፣ የጌዴዎን ፀምር፣ የኖኅ የቃል ኪዳኑ ቀስተ ደመና፣ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ያያት መሰላል፣ የነቢዩ ኤልሳዕ ማሰሮና ሌሎች ምሳሌዎች በሰፊው የተነገሩላት የተጻፉላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ቤተ ክርስቲያን እርስዋን ለመጥራት የምትጠቀምባቸው ቅጽል ስሞቿና ውዳሴዎቿ ምንኛ ድንቅ ቢሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ገላጭነት በቅዱሳን የተነገሩ ምስጋናዎቿስ እጅግ ቢለዩ የክብሯን ያህል የሚገልጿት አይደሉም፡፡
እርሷ የሰው ሁሉ ረዳትና ርኅሩኅ እናት ናት፤ የብርሃን፣ የምሕረት፣ የድኅነትና የአማናዊው ወይን እናት ናት። ከንጉሡ በስተቀኝ የምትቆመው ንግሥት እርስዋ ናት፤ በመስቀል ስር የተቀበልናት የሁላችንም እናት እርሷ ናት፤ እርሷ ዘለዓለማዊ ድንግል ናት፤ እርሷ የእግዚአብሔር ጸጋ የሞላባት ንጽሕት ቅድስት ድንግል ናት፡፡ ከፍጥረት ሁሉ ተለይታ ወላዲተ አምላክ ለመሆን የተመረጠችበት አንዱ ምክንያት እመቤታችን እጅግ ትሑት፣ ፍጽምትና ንጽሕት ስለሆነች ነው። በሉቃስ 1÷48 እንደተጻፈው የአምላክ እናት እንደምትሆን ተነግሯት እንኳን ክብር ይግባትና ከመኩራትና ሌሎችን ከመናቅ ይልቅ ዘመዷ ኤልሳቤጥን ልትጠይቃት ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ወጣች፡፡ ከኤልሳቤጥ ፍጹም ምስጋናና በማሕጸን ያለው ዮሐንስ የሰላምታ ድምጿን ሰምቶ መዝለሉንከሰማች በኋላም “የባሪያይቱን መዋረድ ተመልክቷልና” በማለት በትሕትና ምስጋናዋን አቀረበች እንጂ የትዕቢት ቃል ከአፏ አልወጣም፡፡
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ “እርሷ በእግዚአብሔር ዓይን በታየ የቅድስና ውበት የተሞላች ነበረችና በእርሷ ንጹሕ ማሕፀን ሊያድር ወደደ፤ እንደ ድንግል ማርያም ራሱን ዝቅ ያደረገ ትሑት ማንም የለም” ይላል። ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም “በትሕትና የተናገርሽ ተራራ ሆይ…” ብሎ ያመሰገናት ይህች ድንግል ከተራሮች አናት ሁሉ ከፍ ያለች ስትሆን ራሷን ዝቅ አድርጋ “እንዲህ ያለ የምስጋና እጅ መንሻ እንደምን ይደረግልኛል” የሚል ምላሽ ለቅዱስ ገብርኤል ሰጠችው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ማርያም ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛው አምላክ ልጇ ነውና ማርልኝ ስትለው ምልጃዋ ፍጹም ነው፡፡ በእግዚአብሔር መመረጧ፣ ከሴቶች ሁሉ መለየቷ፣ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ መሆኗ ይህን ክብር አጎናጽፏታልና፡፡ ገዳማውያንም ይህን ልዩ እናትነቷንና ቅድስናዋን አምነው ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሯታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፡- ቤተ ቅዱሳን ፈትለወርቅ ማርያም የእናቶች ገዳም፡-
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000766349227
ወይም
አቢሲንያ ባንክ
262281132
የገዳሙ ስልክ ቁጥር፡- 0944672222 ወይም 0916106921 | 2 370 |
| 3 | Sin texto... | 2 192 |
| 4 | ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከሳምንታት በኋላ ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ ታዩ!
ጠቅላዩ በማኅበራዊ ገፃቸው ላይ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ስምምነት ዛሬ ማከናወናቸውን ገልጸዋል። | 2 826 |
| 5 | ቅዱስ አማኑኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ🙏
አማኑኤል ‹አማነ› እና ‹ኤል› ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው፤ ትርጓሜውም የአምላክ ሰላም፣ የእግዚአብሔር እርቅ፣ የጌታ አንድነት ማለት ነው። አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው።
እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ደግሞ ከሥጋችን ሥጋ ከነፍሳችን ነፍስ ነሥቶ የተዋሐደ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀር እንደኛ የሆነ ማለት ነው። አዳም ዕፀ በለስን በልቶ የሞት ፍርድ በተፈረደበት ጊዜ አምላኩ እግዚአብሔር እዲያድነው ስለተማጸነው በርኅራኄው ወደ ቀድሞ ቦታው እንደሚመልሰው በሰጠው ተስፋ ከልጅ ልጁ ተወለዶ አዳነው፡፡ በዚያችም በተከበረች ቀን ትንቢቱ ተፍጽሞ አምላካችን ከእኛ ጋር ሆነ፡፡
አንድም “ይህ ዐማኑኤል የተባለ ስም እጅግ ታላቅ ስም ነው፣ የማይለይ ተዋሕዶን የሚገልጽ የሃይማኖት መሠረት ነው” ይሉናል፡፡ “ዒማኑ” ማለት ምስሌነ ከእኛ ጋር ማለት ሲሆን፣ “ኤል” አምላክ በተገናኘ፣ አምላክ ምስሌነ ወይም ምስሌነ አምላክ፣ አምላክ ከኛ ጋራ ማለት እንደሆነ በኢሳይያስ 7÷14፣ በማቴዎስ 1÷23 ተጽፏል፡፡ ሊቃውንት ግን “አምላክና ሰው” ወይም ሰው የሆነ አምላክ፣ በመለኮቱ አምላክ፣ በለበሰው ስጋም ሰው ብለው በምስጢር ይፈቱታል፡፡ አምላክ ሰው የሆነለት የሰው ልጅ ኃጢአት ተፋቀ፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስ “እነሆ ድንግል በድንግልና ትጸንሳለች፤ ወንድ ልጅንም ትወልዳለች፤ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች” ብሎ እንደተናገረው እግዚአብሔር ወልድ ከንጽሕተ ንጹሐን ከቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ተወለደ፡፡ ገዳማውያን እናቶችና አባቶች ይህን ስም መመኪያ አድርገው ነው ዓለምን ንቀው የመነኑት፡፡
እርሱ ከኛ ጋር ከሆነ እኛ ከዓለም ጋር ምን ሕብረት አለን ብለው የምንኩስናን ጎዳና መረጡ ገዳማቸውን ስንደግፍ አዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 3 212 |
| 6 | Sin texto... | 2 934 |
| 7 | ለጊዜው ከስራ ታገዱ‼️
2ቱ የትራፊክ የቁጥጥር ባለሙያዎች ለጊዜው ከስራ እንዲታገዱ መደረጉ ተገለፀ::
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በከተማዋ የመንገድ ተጠቃሚዎችን ደህንነት ለማስጠበቅና የትራፊክ እንቅስቃሴን ለማስፈጸም በሚያከናውናቸው የመስክ ቁጥጥር ስራዎች ወቅት ከመንገድ ተጠቃሚዎች ጋር አለመግባባቶች እንደሚከሰቱ ገልጿል።
በዛሬው ዕለት (ነሀሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም) በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ሲሰራጭ የዋለውን ምስል አስመልክቶ ተቋሙ ባወጣው መረጃ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አብራርቷል፦
• የቁጥጥር ባለሙያዎች ደንብ የተላለፈን አሽከርካሪ የመንጃ ፈቃድ በሚጠይቁበት ወቅት "አልሰጥም" በማለት ስራ ማስተጓጎል፣ ስድብ፣ ዛቻ ወይም ሃይል መጠቀም በህግ የሚያስጠይቅ ተግባር መሆኑ ተመልክቷል።
• ተቋሙ በምስሉ ላይ የታየውን አለመግባባት ግራና ቀኝ ያለውን አካል ሚዛናዊ በሆነ መንገድ በማጣራት ላይ እንደሚገኝና እስከዚያው ድረስ በክስተቱ ላይ የተሳተፉት ሁለቱ የቁጥጥር ባለሙያዎች ለጊዜው ከስራ እንዲታገዱ ማድረጉን አስታውቋል።
ህብረተሰቡ የችግሩን የማጣራት ሂደት በስክነት እንዲከታተልና ትክክለኛ ካልሆኑ መረጃዎች እንዲቆጠብ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጥሪ አቅርቧል። | 4 465 |
| 8 | የአርቲስት ፊሊሞን ገብረህይወት መሰወር እንዳሳሰበው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ገለፀ፡፡ የሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆነው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ዛሬ ባወጣው መግለጫ የ33 አመቱ የሰብአዊ መብት ተከራካሪ እንዲሁም የፎቶግራፍና ቪዲዮ ባለሙያ አርቲስት ፊሊሞን ከተሰወረ አንድ አመት እንደሆነው አውስቷል፡፡ የጠፋ እለት ቤተሰቦቹ በአካባቢው ለሚገኝ ፖሊስ ያመለከቱ ቢሆንም እስካሁን ድረስ የት እንዳለ እንደማይታወቅም አስታውቋል፡፡
በአርቲስቱ መጥፋት ዙሪያ የተጀመሩ ወይንም እየተካሄዱ ስላሉ ምርመራዎች ከመንግስት ባለስልጣናት የተሰማ ነገር እንደሌለም አስረድቷል፡፡ ፊሊሞን በትግራይ ክልል መቀሌ ከሚሰራበት ቦታ ወጥቶ በባጃጅ ወደቤቱ እየሄደ እያለ መጥፋቱ ተገልጿል፡፡ በባጃጅ ከመሳፈሩ በፊት ለባለቤቱ ደውሎ አሳውቋት የነበረ ሲሆን ለረጅም ሰአት ቤቱ ባለመመለሱ መልሳ ስትደውልለት ስልኩን አላነሳም፡፡
ከዚያን እለት ጀምሮ አርቲስቱ የት እንዳለ እንደማይታወቅ የጠቀሰው አምነስቲ ፊሊሞን የሁለት ልጆች አባት መሆኑንም አስታውቋል፡፡ የሚመለከታቸው ባለስልጣናት በአርቲስቱ አፈና ላይ ገለልተኛ፣ ጥልቅና ግልፅ ምርመራ በማካሄድ የት እንዳለና ምን እንደሆነ እንዲያሳውቁ አምነስቲ ጨምሮ ጥሪውን አቅርቧል፡፡ | 5 222 |
| 9 | መድኃኔአለም በሐጢዓት ፈተና ተጠልፎ ከመውደቅ ይጠብቀን🙏
እግዚአብሔር እስራኤልን ከደመና መና አውርዶ፣ ከአለት ውሀ አፍልቆ መገባቸው፡፡
እነርሱ ግን እዚህ ደጋ ላይ ቢሆንለት የውርጭ ሰደቃ እያበጀ፣ ውሀውን እያረጋ፣ መና መገብኳችሁ ይላል እንጅ ቆላ ቢሆነማ ባልተቻለውም ነበር ብለዋል። የርሱን ከሃሊነት፣ የእነርሱንም ሀሰት ሊገልጥ ቢወድ፣ ሙሴን የውሃ ምንጭ የሌለበት በረሐ ይዘሀቸው ሂድ ብሎት በዚያም መናው ወርዶላቸዋል፣ ውሀውም ፈልቆላቸዋል። ነገር ግን ነዘር የሚባል እባብ እየነከሰ ይፈጃቸው ጀመር። በዚህ ጊዜ ከሙሴ ዘንድ ሂደው ከጌታ ምህረት ቸርነት ከእኛ ኃጢአት አይታጣም በእግዚአብሔርና በአንተ ላይ ተናግረን በድለናል እባቦችን እንዲያርቅልን ወደ እግዚአብሔር አመልክትልን አሉት።
ሙሴም ወደ እግዚአብሔር ቢጸልይ ከንጹህ ነሐስ የእባብ ምስል ሠርተህ ከሚገናኙበት አደባባይ ከእንጨት ላይ ስቀልላቸው አለው። እንደተባለው ቢያደርግ እባብም የነደፈችው ሰው ሁሉ የነሐሱን እባብ ባየ ጊዜ ዳነ። “ሙሴ እባብን በምድረ በዳ እንደሰቀለው የሰው ልጅ ክርስቶስ ይሰቀል ዘንድ አለው” ተብሎ በዮሐንስ 3÷14 እንደተነገረ፡፡ አባቶቻችንም በትርጓሜ ወንጌል የበረሐው እባብ የዲያብሎስ፤ የብረቱ እባብ የጌታ ምሳሌ ነው። በእባብ መርዝ እንዳለበት በዲያብሎስም ፍዳ ኃጢአት አለበት።
በነሐሱ እባብ መርዝ እንደሌለበት በጌታም ፍዳ ኃጢአት የለበትም። የነሐሱ እባብ በእባብ አምሳል መሰቀሉ ጌታ እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ለመሰቀሉ ምሳሌ ነው። ክርስቶስ ኢየሱስ በመስቀል በተሰቀለ ጊዜ፤ የተሰቀለው የክብር ባለቤት ሰማይን የፈጠረ ነውና ፀሐይ ጨልማለች፣ ጨረቃ ደም ሆኗል፣ ከዋክብት ረግፈዋል።
ገዳማውያኑም በመስቀል የተደረገልንን ማዳን እያሰቡ ዓለምን ንቀው፣ ስጋቸውን ጎድተው ይከተሉታል፡፡ የጽድቃቸው አክሊል እርሱ መድኃኔ ዓለም የሚወደኝ መስቀሌን ተሸክሞ ይከተለኝ እንዳለ፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 5 082 |
| 10 | Sin texto... | 4 328 |
| 11 | ሚኒስትሯ ተራ ታካሚ መስለው የወሰዱት እርምጃ‼️
የኡጋንዳዋ የጤና ሚኒስትር ሌቦችን ለመያዝ የሄዱበት ርቀት ውጤት አምጥቶለታል።
በኡጋንዳ የመንግሥት ሆስፒታሎች ውስጥ በሕመምተኞች ላይ የሚፈጸመውን ሕገ ወጥ የገንዘብ ብዝበዛና የእንግልት ጥቆማ የተከታተሉት የሃገሪቱ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳራ አቺየንግ ነገሩ ስር የሰደደ ነው ብለዋል።
ድርጊቱን እጅ ከፍንጅ ለመያዝ ራሳቸውን ተሸፋፍነው ተራ ታካሚ መስለው ባደረጉት አስደናቂ እንቅስቃሴ አዎንታዊ ውጤት ማስመዝገባቸው ተገለጸ።
ሚኒስትሯ በካምፓላ በሚገኘው ናጉሩ ሆስፒታል በድብቅ ባደረጉት ምልከታ የሕዝቡ የምሬት ምንጭ የሆኑ አንዳንድ የጤና ባለሙያዎች በመንግሥት ተቋማት ውስጥ ከፍተኛ ችግር እየፈጠሩ መሆናቸውን በገሃድ አረጋግጠዋል።
በነጻ ሊሰጡ የሚገባቸው የሕክምና አገልግሎቶች ላይ ክፍያ ሲጠየቅባቸው የቆዩት ዜጎች ምሬት ትክክለኛነት ያረጋገጡት ሚኒስትሯ ተራ ታካሚ ሆነው በቀረቡበት ወቅት በርካታ ችግሮች መኖራቸውን ነው የገለፁት።
ሚኒስትሯ በካፓላ ናጉሩ ሆስፒታል በነፃ የሚሰጡ ምርመራዎች ላይ ባለሙያዎች ከ150 ሺሊንግ በላይ አእያስከፈሉ እጅ ከፍንጅ ይዘዋል።
ሕገ ወጥ ክፍያውን ፈጽመው ከተቀበሉ በኋላ ወዲያውኑ ማንነታቸውን ይፋ ያደረጉት ሚኒስትሯ በሥፍራው ፖሊስ በመጥራት ጥፋተኞቹን በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ አድርገዋል።
ይህ የኡጋንዳዋ የጤና ሚኒስትር የሄዱበት ርቀትና የወሰዱት ቁርጠኛ እርምጃ በመልካም አስተዳደርና በተቋማት ተጠያቂነት ዙሪያ ለሌሎች አመራሮችም ትልቅ ማሳያና ትምህርት ሰጪ ልምድ መሆኑን ነው የተገለጸው።
ይህንን ተሞክሮ ወደ ሀገራችን ወስደን ብንሞክረው። | 4 894 |
| 12 | መንግስት የሚሊሻ ሰላም አስጠባቂ የሚባለዉን አካል አደብ ሊያስገዛ ይገባል ፡፡ | 4 723 |
| 13 | በበዓል ሰሞን የሚታየውን ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር ጥብቅ ክትትል እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ
የአዲስ አበባ ከተማ የንግድ ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ እንደገለፁት የበዓል ገበያን ተገን በማድረግ የሚከናወኑ ህገ-ወጥ ተግባራትን ለመከላከል በመላው ከተማዋ ጥብቅ የቁጥጥር ስራ መጀመሩን አስታውቋል።
ቢሮው በተለይም የኢንዱስትሪ ምርቶች በሚሸሸጉባቸው መጋዘኖች ላይ ድንገተኛ ፍተሻዎችን እያከናወነ ሲሆን፣ ምርት በመደበቅና ሰው ሰራሽ እጥረት በመፍጠር ዋጋ በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።
የቁጥጥር ስራው የምርት ጥራትንና ደረጃን ማረጋገጥን የሚያካትት ሲሆን፣ ጊዜያቸው ያለፈባቸውና ለጤና ጎጂ የሆኑ ምርቶች ለገበያ እንዳይቀርቡ በየደረጃው ያሉ ተቆጣጣሪዎች ስምሪት ተሰጥቷቸዋል።
በተለይም በስጋ ቤቶች፣ በዱቄትና በዳቦ መሸጫዎች ላይ የሚታዩ የምርት መጠን ማነስ ችግሮችን ለመከላከል ክትትል እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
ህገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ዝውውርን ለመቆጣጠርም ከጸጥታ ግብረ-ኃይሉ ጋር በመቀናጀት በመግቢያ በሮችና በዋና ዋና የንግድ ማዕከላት ላይ ጥበቃና ፍተሻው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተደርጓል።
የቁጥጥር ሰራተኞቹ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እንዲቻል ልዩ መለያ (ባጅ) እና ባርኮድ ያለው መታወቂያ እንዲይዙ የተደረገ ሲሆን፣ ይህም ደንበኞችን ከሐሰተኛ ተቆጣጣሪዎች ለመጠበቅ ይረዳል ተብሏል።
ህብረተሰቡ በገበያ ውስጥ የሚታዩ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪዎችን፣ የምርት ጥራት ጉድለቶችንና ሌሎች ህገ-ወጥ ተግባራትን ሲመለከት በነጻ ስልክ መስመር 8588 ጥቆማ እንዲሰጥ ተጠይቋል።
| 4 953 |
| 14 | የእናታችን ቅድስት ኪዳነ ምህረት ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳኗ ዘወትር ይታሰባል
ኪዳን የሚለው ቃል ተካየደ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተማማለ፣ ተስማማ፣ ውል ገባ ማለት ነው፡፡ ኪዳነ ምሕረት ማለትም ደግሞ የምሕረት ቃል ኪዳን ማለት ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ስለሰው ልጆች ይቅርታ የገባላት ኪዳን ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለሚፈሩት፣ ለሚያከብሩት፣ ለሚወዱትና ለሚወዳቸው ሁሉ በተለያዩ ጊዜያት ብዙ ኪዳናትን ሰጥቷል፡፡ የኪዳነ ምሕረት ሥዕል በመባል የሚታወቀው ሥዕል በቤተ ክርሰቲያናችን በስፋት ከሚሳሉት የወላዲተ አምላክ ሥዕል ጭብጦች ውስጥ አንዱ ሲሆን። ከጌታችን ኢየሱስ ቃልኪዳን ስትቀበል በጎሎጎታ የሚያሳየው ሥዕል ትክክለኛው ገላጭ ሥዕል ሲሆን፤ ይህ ሥዕል እንደ ቤተ ክርስቲያኑ ስፋት የሚጨመረው ጭብጥ ሊለያይ ይችላል፡፡
ለምሳሌ በዚህ ሥዕል ዘይቤ ላይ የሚታዩት መላእክት ቁጥራቸው ሊበዛ አሊያም ሊያንስ ይችላል፡፡ በዚህ ሥዕል እመቤታችንና ጌታችን ቆመው አሊያም ተቀምጠው ጌታችን በቅዱሳን እጆቹ የእናቱን ቅዱሳን እጆች በመያዝ ቃል ኪዳን ሲገባላት አሊያም በቅዱሳት እጁ ቃል ሲገባላት የሚያሳይ ዓይነት ሥዕል ነው፡፡ በዚህ መልኩ እመቤታችን ከተሳለችባቸው አብያተክርስቲያናት መካከል ጎርጎራ ደብረ ሲና (17ኛው መ.ክ.ዘ)፣ አብርሐወ አጽብሐ (19ኛው መ.ክ.ዘ)፣ መቐለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (20ኛው መ.ክ.ዘ)፤ ከጥንታውያን ብራና መጻሕፍት ከተመለከትን በአክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን ግምጃ ቤት የሚገኘው የ17ኛው መ.ክ.ዘ ተአምረ ማርያም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ገዳማውያንም ዘወትር በሥዕሏ ፊት ቆመው ይለምኗታል፡፡ እርሷም ልመናና ጸሎታቸውን ታሳርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸውመ እንካፈል፡፡
ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተሰጠው ኪዳን፣ ቀድመው ለነበሩ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖህ፣ ኪዳነ መልከ ጸዴቅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ሙሴና ኪዳነ ዳዊት መደምደሚያ ነው፡፡ ዘለዓለማዊ ስለ ሆነው የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳን እየታሰበም ዕለቱ በመዝሙር፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን ለምንባል ለእኛ ለሐዲስ ኪዳን የቤተ ክርስቲያን ልጆችም ይህ አዲስ ውል የተደረገልን ለነፍሳችን ድኅነት በመሆኑ በስሟ እየተማጸንን እንዲሁም መታሰቢያዋን እያደረግን ለተራቡት ማብላት፣ ለተጠሙት ማጠጣትና የተቸገሩትን መርዳት ይገባናል፡፡ ገዳማውያን በበቃል ኪዳኗ ታምነው፣ ዘወትር በሥዕሏ ፊት በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፡- ቤተ ቅዱሳን ፈትለወርቅ ማርያም የእናቶች ገዳም፡-
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000766349227
ወይም
አቢሲንያ ባንክ
262281132
የገዳሙ ስልክ ቁጥር፡- 0944672222 ወይም 0916106921 | 4 853 |
| 15 | Sin texto... | 3 943 |
| 16 | አስደንጋጭ የኢትዮጵያውያን ግድያ በሳውዲ አረቢያ‼
"በሳውዲ አረቢያ ድንበር ላይ በኢትዮጵያውያን መካከል የተፈፀመው አስደንጋጭ ግድያ አዲስ መረጃ ወጥቷል።
• ግድያውን የፈፀመው ግለሰብና 5 ግብረ አበሮቹ ተይዘዋል።
• በሶሻል ሚዲያ ጉዳዩን በማራገብ ተጠርጣሪ የሆኑ ከ100 በላይ ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
• የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከሳውዲ የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን ወንጀለኞችን የማደን ስራውን አጠናክሯል።
የኢትዮጵያዊነትን ባህል ያረከሰው ይሄ ድርጊት የህግ የበላይነት ሊረጋገጥበት ይገባል።
ድምፅ ለሆናችሁና መረጃ ለሰጣችሁ ሁሉ ኤምባሲው ምስጋና አቅርቧል። | 4 328 |
| 17 | መድኃኔአለም በሐጢዓት ፈተና ተጠልፎ ከመውደቅ ይጠብቀን🙏
የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ቄርሎስ “ለቤተ ክርስቲያን ስትል በአደባባይ በጥፊ የተመታህ አቤቱ ይህን ማድረግህ እርስዋን በከበረ ደምህ ትቀድሳት ዘንድ ነው፡፡
ለእርስዋ ሲል ታሥሮ መጎተት የቻለ የበደለውም በደል ሳይኖር፣ ርኩስ ምራቅን ሲተፋበት የታገሠ መድኃኔ ዓለም በእንጨት መስቀል ላይ ተሰቀለ” በማለት ገለጸው፡፡ በመለኮቱ ሕያው ሲሆን በስጋው ግን ሞትን ቀመሰ፡፡ የአዳምን ሞት በሞቱ ሊሽር መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን በገዛ ፈቃዱ አሳልፎ ሰጠ፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር ሰው ሆኖ እንደሚያድነን በመጀመሪያ ለአዳም ቃል ገባለት፡፡ ከዚያም በነቢያት ትንቢት አስነገረ፡፡ በስጋ በተገለጠ ጊዜም የሰቀሉትና የገደሉት አይሁድ ሳይቀሩ እንዲናገሩ አፋቸውን አስከፈታቸው፡፡
ቅዱስ ጳውሎስም “ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን… አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን” ይላል፡፡ “ስለ ሕዝቡም ሁሉ አይደለም፣ ነገር ግን የተበተኑትን የእግዚአብሔርን ልጆች በአንድነት እንዲሰበስባቸው መጥቷል እንጂ።” ተብሎ ተጽፏልና፡፡ በድንቅ ተዋህዶ አምላክ ሰው፣ ሰውም አምላክ ሆኗልና ከኛ በነሳው ስጋም ወደ ሰማይ አረገ፡፡ ስለፍጹም የሰው ልጆች ፍቅር መድኃኔ ዓለም ተላልፎ ተሰጠ፡፡
በፊልጵ 2÷8 “በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፣ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ” ተብሎ እንደተጻፈው፡፡ በማዳኑ ስራ ውስጥ የቅድስት ድንግል ማርያም ድርሻ ታላቅ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በገላ 4÷4 “የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ልጁን ላከ፡፡” ሲል ጽፏል፡፡
ዕለት ዕለት ፍቅሩን የከፈለልንን ዋጋ፣ ይህን መከራውንና ማዳኑን ዕለት ዕለት የሚያስቡ ገዳማውያን ሌሊትና ቀን በስግደትና በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቱን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጸና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 4 532 |
| 18 | Sin texto... | 4 576 |
| 19 | Sin texto... | 5 226 |
| 20 | በአውሮፕላን ውስጥ “እውነትን የመስማት ግዴታ አለባቸው” በሚል ስብከት ያቀረበችው ፕሮቴስታንት ወንጌላዊት በአየር መንገዱ በረራ እንዳታደርግ ታገደች
ታዋቂዋ አሜሪካዊት ወንጌላዊት እና የሶሻል ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ ዊትኒ ሊን (Whitney Lynn)፣ በትላንትናው ዕለት ከኦርላንዶ ወደ ሳንዲያጎ በሚጓዝ የአላስካ አየር መንገድ (Alaska Airlines) በረራ ላይ....
የአውሮፕላኑን መተላለፊያ መስመር በመያዝ ስብከት በማቅረቧ እና የበረራ ሰራተኞችን መመሪያ ባለማክበሯ ከአውሮፕላን እንድትወርድ ተደርጋለች።
አየር መንገዱ ለደህንነት አስጊ የሆኑ ባህሪያትን በፍፁም እንደማይታገስ በመግለጽ፣ የ40 ዓመቷን ወንጌላዊት ከአላስካ አየር መንገድ፣ ከሃዋይያን አየር መንገድ እና ከሆራይዘን ኤር በረራዎች ላይ በጊዜያዊነት ማገዱን አስታውቋል።
ወንጌላዊቷ በረራው ከመነሳቱ በፊት በነበረው የሰዓት መዘግየት ወቅት በአውሮፕላኑ መተላለፊያ ላይ በመቆም መስበክ የጀመረች ሲሆን፣ ተጓዦች...
በአውሮፕላን ውስጥ ተዘግቶባቸው ስላሉ “እውነትን ከመስማት ውጪ ሌላ ምርጫ የላቸውም” የሚል እምነት እንዳላት በግልፅ ተናግራለች።
የበረራ ሰራተኞቹ ደጋግመው እንድትቀመጥ እና ንግግሯን እንድታቆም ቢጠይቋትም፣ እርሷ ግን ጥያቄውን ውድቅ በማድረጓ የደህንነት ሰራተኞች ተጠርተው ከአውሮፕላን እንዲያስወጧት ተደርጓል።
ከአውሮፕላን ከተባረረች በኋላ ባስተላለፈችው መልዕክት፣ በአየር መንገዱ የተወሰደውን እርምጃ “መንፈሳዊ ውጊያ” ስትል የጠራችው ሲሆን፣ እራሷንም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስደት ከደረሰባቸው ታላላቅ ሰዎች ጋር አነጻጽራለች።
አላስካ አየር መንገድ በሰጠው መግለጫ፣ ማዕቀቡ የተጣለው የበረራ ሰራተኞችን የስራ ደህንነት ለማስከበር እና የደንበኞችን ምቾት ለመጠበቅ ሲባል መሆኑን አስታውቋል።
ይህ ክስተት በሶሻል ሚዲያ ላይ ከፍተኛ ክርክር ያስነሳ ሲሆን፣ ብዙዎች “በአውሮፕላን ውስጥ ሰዎችን አስገድዶ ማሰማት የሌሎችን መብት መጣስ ነው” ሲሉ፣ ጥቂቶች ደግሞ “የሃይማኖት ነፃነት ሊከበርላት ይገባል” በሚል እየተከራከሩ ይገኛሉ።
በሀገራችን ኢትዮጵያ መሰል የፕሮቴስታንት አማኞች በየመንገዱና በየገበያው ማዕከል በብዛት ያከናውናሉ ። እንዲሁ ማድረጋቸው ትክክል ነው ? አይደለም ? በጨዋነት ሀሳብ አስተያየታችሁን አካፍሉን እስኪ ?
| 5 286 |
