Sheger Press️️
Official channel of sheger press Contact @Birukepromo
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali Sheger Press️️ analitikasi
Sheger Press️️ (@sheger_press) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 35 916 obunachidan iborat bo'lib, Yangiliklar & Media toifasida 7 018-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 929-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 35 916 obunachiga ega bo‘ldi.
12 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -186 ga, so‘nggi 24 soatda esa 8 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 17.06% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 11.12% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 6 130 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 3 995 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 26 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“Official channel of sheger press
Contact @Birukepromo”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 13 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Yangiliklar & Media toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 13 Iyul | 0 | |||
| 12 Iyul | +8 | |||
| 11 Iyul | 0 | |||
| 10 Iyul | 0 | |||
| 09 Iyul | +10 | |||
| 08 Iyul | +5 | |||
| 07 Iyul | +13 | |||
| 06 Iyul | +3 | |||
| 05 Iyul | +1 | |||
| 04 Iyul | +7 | |||
| 03 Iyul | +6 | |||
| 02 Iyul | +2 | |||
| 01 Iyul | +5 |
| 2 | ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ🙏
ሚካኤል ማለት “ከመ እግዚአብሔር” እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው?” ማለት ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔርን ገናንነትና እሱን የሚመስል አምላክ እንደሌለ የሚያመለክት ነው፤ እንደ እግዚአብሔር ያለ ቅዱስ ንጹሕ ርህሩህ ኃይል ረቂቅ ማነው? መልሱ የለም ነው፡፡ በትህትናው ልዕልናን ያገኘው ቅዱስ ሚካኤል በእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠው ክብር ከማንኛውም መልአክ የበለጠ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ አስቀምጦታል፡፡ ቅዱስ ሚካኤል የስሙ ዘርፍ ሆነው የሚጨመሩ መጠሪያዎች አሉት እነዚህም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠውን የባለሟልነትና ክብር የሚገልጹ ናቸው፡፡ ይኸውም መልአከ ኃይል፣ መጋቤ ብሉይ፣ መልአከ ምክሩ ናቸው፡፡ መልአከ ኃይል የተባለው እግዚአብሔር በሱ አማካይነት ታላላቅ ሥራዎችን በመሥራት ኃይሉን ስለገለጸ፣ ዲያብሎስን ከነሠራዊቱ ስላሸነፈ ነው፡፡
መላእክትን ማክበርና መታዘዝ እንደሚገባ እግዚአብሔርም ነግሮናል፡፡ በዘጸ.23÷20-22 “በመንገድህ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ሥፍራ ያገባህ ዘንድ እነሆ እኔ መልአክን በፊትህ እሰዳለሁ፤ በፊቱ ተጠንቀቁ፤ ቃሉንም አድምጡ፤ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት፤ አንተ ግን ቃሉን ብትሰማ፣ ያልሁህንም ሁሉ ብታደርግ፣ ጠላቶችህን እጣላቸዋለሁ፣ የሚያስጨንቁህንም አስጨንቃቸዋለሁ፣ መልአኬ በፊትህ ይሄዳል” በማለት ለሙሴ ተናግሯል፡፡ ይህ ቃል ለሙሴና ለሕዝቡ ብቻ ተነግሮ ያበቃ ሳይሆን እስከዛሬና ወደፊትም የሚቀጥል ነው፡፡ መጋቤ ብሉይ የተባለበት ምክንያት በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከእግዚአብሔር እየተላከ ብዙ ታላላቅ ሥራዎችን የሠራ በመሆኑ ነው፡፡
መልአከ ምክር ወይም የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ የተባለበት ምክንያት፣ እግዚአብሔርን በምክሩ ይረዳዋል ለማለት ሳይሆን እግዚአብሔር የሚሠራውን ሥራ ለወዳጁ ለቅዱስ ሚካኤል ይገልጽለታል በሱም አማካኝነት ይሠራል ለማለት ነው፡፡ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ የሚለው በመላእክት ሁሉ ላይ በእግዚአብሔር የተሾመ ማለት ነው፡፡ መላእክት አለቆቻቸውን ያከብራሉ፤ ለእነሱም ይታዘዛሉ፡፡ ቅዱስ ሚካኤል የመላእክት ሁሉ አለቃ ስለሆነ ከትእዛዙ አይወጡም፤ ሠራዊተ መላእክት የሚያከብሩትንና የሚታዘዙለትን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን እኛም እንደ እነርሱ እናከብረዋለን እንታዘዘዋለን፡፡ ይህን ያመኑ ገዳማውያንም ሌሊትና ቀን ሚካኤል ሆይ አማልደን ይሉታል፡፡ ከጸሎታቸው በረከት እንድንካፈል ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 1 368 |
| 3 | Matn yo'q... | 1 255 |
| 4 | የባንኮች የማበደር ገደብ ተነሳ‼
የብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ (ቁጥር 7) ስብሰባ ዋና ዋና ውሳኔዎችና የኢኮኖሚ አፈጻጸም አጭር መግለጫ:-
፩. ዋና ዋና የፖሊሲ ውሳኔዎች
📌የብድር ገደብ መነሳት፦ በባንኮች ላይ ተጥሎ የነበረው የዓመታዊ የብድር ዕድገት ገደብ (Credit Cap) ሙሉ በሙሉ እንዲነሳ ተወስኗል።
📌 የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ ማሻሻያ፦ የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ (Policy Rate) በ1.0 በመቶ ነጥብ ከፍ በማለት ከ15 በመቶ ወደ 16 በመቶ እንዲያድግ ተደርጓል።
📌 የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ግዴታ (FX Surrender)፦ ላኪዎችና የውጭ ምንዛሬ አስገኚዎች ለባንኮች ገቢ የሚያደርጉት የውጭ ምንዛሬ ግዴታ ከ50 በመቶ ወደ 30 በመቶ ዝቅ እንዲል ተወስኗል።
📌 የኮሚሽን ምጣኔ ቅነሳ፦ ባንኮች ከውጭ ምንዛሬ ግዢ ጋር ተያይዞ የሚያስከፍሉት የኮሚሽን ምጣኔ ከ2.5 በመቶ ወደ 1.5 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል።
፪. የኢኮኖሚ አፈጻጸም ማጠቃለያ
📌 የኢኮኖሚ ዕድገት፦ በ2017 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ዕድገት 9.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
📌የዋጋ ግሽበት፦ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በሰኔ ወር 2018 ዓ.ም. ወደ 13.4 በመቶ ዝቅ ብሏል።
📌 የበጀት ጉድለት፦ የአገሪቱ የበጀት ጉድለት ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) አንጻር ወደ 0.9 በመቶ ወርዷል።
📌 የውጭ ኢኮኖሚ ክምችት፦ አጠቃላይ የውጭ ክፍያ ሚዛን ትርፍ ያስመዘገበ ሲሆን፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ማሻሻያው ከመደረጉ በፊት ከነበረው አንጻር በ20 እጥፍ አድጓል።
| 2 275 |
| 5 | በሳውዲ እስር ላይ ለነበሩ 1,971 ኢትዮጵያውያን ምሕረት ተደረገላቸው‼
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፣ በሳዑዲ አረቢያ በሕግ ሂደትና አስገዳጅ እርምጃዎች ውስጥ የነበሩ 1,971 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ባለሥልጣናት የንጉሣዊ ምሕረት አዋጅ (Royal Amnesties) ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታወቀ።
በሪያድ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲና በጅዳ ከሚገኘው ቆንስላ ጄኔራል ጋር በመተባበር የተደረጉት ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አዎንታዊ ውጤት ማምጣታቸውን የገለጸው ሚኒስቴሩ፣ በምሕረቱ የተካተቱ ዜጎችን ወደ ሀገር ለመመለስ የሚያስችሉ ሥራዎች መጀመራቸውን ጠቁሟል።
የኢትዮጵያ መንግሥት በውጭ ሀገራት የሚገኙ ዜጎቹን ደኅንነትና መብት ለማስጠበቅ ከሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር የሚያደርገውን ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ንግግር አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጧል። | 3 282 |
| 6 | ቅድስት አርሴማ የልባችንን መልካም መሻት ትሙላልን፤ ረድኤቷ እና ምልጃዋ አይለየን🙏
ራሷን ለእርሱ በሙሽርነት አሳልፋ ሰጥታለች
ራሷን የክርስቶስ ሙሽራ አድርጋ የለየች የፊቷ መልክ እጅግ ልዩ፣ ደምግባቷ ያማረ ነበረች እናታችን ቅድስት አርሴማ። የዲዮቅልጥያኖስ ታዛዥ የሆነው ንጉሥ ድርጣድስ ከሮሜ ሸሽታ በሔደችባት አብረዋት ከነበሩ ገዳማውያን ደናግል ጋራ ካሠራቸው በኋላ እናታችን ቅድስት አርሴማን ሚስቱ እንድትሆን በብዙ ሊያታልላት ሞከረ። እርሷ ግን በመንፈሳዊ ሕይወቷ ፍጹም ራሷን አሳልፋ የሰጠች፣ ራሷንም ለቸሩ አምላካችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ሙሽራ ያደረገች ናትና ለሰማያዊ ሙሽርነቷ የታመነች ሆነች። በኋላም እመ ምኔቷን እንድታባብላት ላካት፤ እመ ምኔቷ ግን “አይዞሽ! እንዲህ ላለው ምድራዊ ኃላፊ ነገር እንዳትታለይ፤ ሰማያዊ ሙሽርነትሽንና ንጽሕናሽን አጽኚ” ብላ ይበልጥ አጸናቻት።
ንጉሡም በግድ ይዟት ሊሄድ ቢል ኃይለ መንፈስ ቅዱስ አድሮባት ነበርና ያንን በጦር የጎለመሰ ሰውነት ያለውን ብርቱ ጦረኛ ከመሬት ፈጠፈጠችው። ንጉሡም እጅግም ተቆጥቶ ቅድስት አርሴማን አሠራትና ደናግሉን በፊቷ አንድ በአንድ አንገታቸውን ቀላቸው። እርሷ ግን “አይዟችሁ!” እያለች ታጽናናቸው ነበር። ይልቁንም ትሳቀቃለች ብሎ ባደረገው ነገር ቅዱሳኑ ሰማያዊ አክሊልን ሲቀበሉ ትመለከት ነበር። እርሷንም ሁለቱን ጡቶቿን ቆረጠ፤ ቀጥሎም ሁለቱን ዐይኖቿን አወጣቸው፤ በብዙ መከራም እጅግ አሠቃያት። ንጽሕት ድንግል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልዩ የብርሃን ዐይኖችን ሰጠቻት።
በመጨረሻም እርሷን ማሠቃየት ሲሰለች ከቀሩት ከሰባ አምስት ወንዶችና ከሃያ ሰባት ደናግል ሴቶች ጋራ መስከረም ሃያ ዘጠኝ ቀን አንገቷን ሰየፋቸውና የሰማዕትነትን የድል አክሊል ተቀዳጁ። ቅድስት አርሴማ በሰማዕትነት ስታርፍ ጌታችን ነፍሷን በክብር ተቀበላት ራሷን ለእርሱ በሙሽርነት አሳልፋ ሰጥታለችና ብዙ ቃል ኪዳንም ሰጣት፡፡
ዓለምን የናቁ ገዳማውያን የሚያገኙት ምድራዊ ክብር አያጓጓቸውም፣ ስጋዊ ድሎትና ምቾት አይማርካቸውም ራሳቸውን ለጌታቸው አሳልፈው ሰጥተዋልና፡፡ እኛም ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና ከበረከታቸው እንሳተፋለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957 | 3 559 |
| 7 | Matn yo'q... | 3 047 |
| 8 | “ለሻዕቢያ ከምገረድ፣ ለብልጽግና ብንበረከክ እመርጣለሁ”‼️
የቀድሞዋ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም መጠይቅ፣ ከህወሓት ጋር ተድርጎ ለሻዕቢያ ከመገረድ በብልጽግና አንገት መድፋት ይሻለኛል ብለዋል፡፡ ኬሪያ ከፋና ቲቪ ጋር ባደረጉት ቃለ ትግራይን በበላይ የተቆጣጠሩትን እነ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልን የትግራይን ሕዝብ ለሻዕቢያ አሳልፈው በመስጠት ወንጅለዋል፡፡
ኬሪያ የቀድሞ ድርጅታቸው ህወሓት ትግራይን ለማጥፋት ይመኛል ላሉት ሻዕቢያ “ተላላኪ ሆኖ እየተገረደ” ነው ብለዋል፡፡ ህወሓት “የብልጽግና ተንበርካኪ መሆን የለብንም ነው የሚለን” ያሉት ኬሪያ፣ “ለሻዕቢያ ከምገረድ እዚህ ብንበረከክ ነው የምመርጠው” ብለዋል፡፡ | 4 250 |
| 9 | እንኳን ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን !!!
የአቡነ ገበረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት በረከታቸው በሁላችንም ላይ ይደርብን🙏🙏🙏❤️❤️❤️
ስጋቸው እስኪያልቅ ተዘቅዝቀው ጸልየዋል
ወላጆቻቸው ልጅ አጥተው ሠላሳ ዘመን ሲያዝኑ ኖረዋል፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ አንድ ቀን አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥዕለ ሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን “ሥልጣኑ ከሰማይ ከፍታ ከፍ የሚል፣ ንጽሕናው ከሚካኤል ከገብርኤል የሚተካከል፣ ክህነቱ እንደ መልከ ጼዴቅ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ እንደ ነቢዩ ኤልያስ የሆነ ልጅ እንቺ ተቀበይ” የሚል ድምጽ ሰማች፡፡ አቅሌስያም በመጋቢት 29 ቀን ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ቀን ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ ግብጽ ወስጥ ንሂሳ በምትባል ቦታ ወለደች፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ “የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን” አላት፡፡ ወዲያውም ሕፃኑ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገደ፡፡ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን” አለ፡፡
አባታችንም ከዚህ በኋላ እናታቸው አላቀፈቻችውም፤ ጡትም አልጠቡም፡፡ ሦስት ዓመት ሲሞላቸውም በእግዚአብሔር አምላክ ትዕዛዝ ብርሃናዊው መልአክ የራማው ልዑል ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ ሕፃኑን ከእናቱ ክንድ ወስዶ በክንፎቹ አቅፎና ስሞ እስከ ሰባቱ ሰማይ አውጥቶ በሥሉስ ቅዱስ ፊት አቅርቦት አስባረከው፡፡ እግዚአብሔርም መልአኩን “ወደ እናቴ ወደ ማርያም ውሰደውና ትባርከው” አለውና ወስዶት እመቤታችንም ባረከችው፡፡ ከአዳም ጀምሮ ያሉ ቅዱሳንም ሁሉ ባረኩት፡፡ አምላካችን እግዚአብሔርም አጸናው አበረታው፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ አባ ዘመደ ብርሃን ወዳለበት ገዳም አወረደውና ሕፃኑን ከበር ላይ አስቀምጦ ምግቡ የእግዚአብሔር ቃል እንደሆነ ነገረው፡፡ አባ ዘመደ ብርሃንም ሕፃኑን አስገብቶ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ እያስተማረ አሳደገው፡፡ ትምህርቱን በጨረሰ ጊዜ ዲቁና ተቀብሎ እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ሞገስን የተመላ ሥራው የተቃና ሆነ፡፡
አባ ዘመድ ብርሃንም እንደ ቅዱስ እንጦንስ አስኬማን ሰጠው፡፡ ከዚህም በኋላ ቅስናን ተቀበሉና በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ እንደ ሐዋርያትም የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸውና ድውያንን የሚፈውሱ፣ ሙታንን የሚያነሡ፣ አጋንንትን የሚያወጡ ሆኑ፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዳግመኛ ተገልጦላቸው ወደ ሰማይ አሳረጋቸው፡፡ እግዚአብሔርም ከባረካቸው በኋላም ከሰው ተለይተው ከአናብስትና ከአናብርት ጋር እንዲኖሩ፣ እንስሳቱም የእግራቸውን ትቢያ እየላሱ እንደሚኖሩ ነገራቸው፡፡ ሰውነታቸውም ሁሉ በጠጉር ተሸፈነ፡፡ በፍጹም ተጋድሎም ከኖሩ በኋላ በቀንና በሌሊት የክርስቶስን መከራ እያሰቡ ስለ ኃጥአንም ጥፋት እንባቸውን እያፈሰሱ ይጸልዩ ነበር፡፡ በጸሎታቸውም ብዙ እልፍ ነፍሳትን አስምረዋል፡፡
ሦስት መቶ ዓመት ከኖሩ በኋላም ከ60 አንበሶችና ከ60 ነብሮች ጋር ወደ ኢትዮጵያ መጡ፡፡ ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም በነፋስ ሠረገላ ጭኖ ምድረ ከብድ አደረሳቸው፡፡ ደብር ቅዱስ የሚባለው ዝቋላንም አሳያቸው፡፡ ሰው የገዛ ፊቱን በመሥታወት እንደሚያይ አባታችንም የኢትዮጵያን ሰዎች ኃጢአታቸውን በግልጽ በተመለከቱ ጊዜ ተወርውረው ወደ ባሕሩ በመግባት የኢትዮጵያን ሕዝብ ማርልኝ ብለው ለአንድ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ስጋቸው እስኪያልቅ ጸልየዋል፡፡ ጌታችንም መጥቶ ኢትዮጵያን ምሬልሀለሁ ውጣ አላቸው፡፡ ሲወጡም ሰውነታቸውን ዳሶ አደሳቸው፡፡ ታላቅ ቃል ኪዳንም ሰጣቸው፡፡ አባታችን በሀገራችን 262 ዓመታት በጸሎትና በትምህር እየቀዱሱዋት፣ አጋንንትን እያሳደዱ ኖረው በተወለዱ በ562 ዓመታቸው በዕለተ እሁድ አርፈዋል፡፡ በቅዱሳኑ ምልጃ ያመንን ገዳማውያንን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 4 312 |
| 10 | Matn yo'q... | 3 894 |
| 11 | የአሜሪካው ሴናተር ሊንድሴ ግራሃም በ71 ዓመታቸው ‹‹በድንገተኛ ህመም›› ማለፋቸውን ቢሯቸዉ አስታወቀ
ከደቡብ ካሮላይና የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የሆኑት ግራሃም ከ2003 ጀምሮ በሴኔት ውስጥ አገልግለዋል
ቢሯቸዉ ባወጣው መግለጫ፤ ‹‹ቅዳሜ ምሽት የአሜሪካው ሴናተር ሊንድሴ ግራሃም በአጭር እና በድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል›› ብሏል።
ከደቡብ ካሮላይና ግዛት የመጡት የሪፐብሊካን ፓርቲ አባሉ ግራሃም፤ በ2002 ለሴኔት የተመረጡ ሲሆን በ2008፣ 2014 እና 2020 በድጋሚ ተመርጠዋል።
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቅርብ ወዳጅ የነበሩት ግራሃም፤ የሴኔት የበጀት ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆነው ያገለገሉ ሲሆን፤ በህዳር ወር ምርጫ ለአምስተኛ ጊዜ ለስድስት ዓመት የሴኔት የሥራ ዘመን ለመወዳደር በዝግጅት ላይ ነበሩ።
ግራሃም በቅርቡ ወደ ኪቭ ተጉዘው የተመለሱ ሲሆን፤ ባለፈው አርብ ከዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር ተገናኝተው ነበር።
እስከዳር ግርማ | 4 607 |
| 12 | እንኳን ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን !!!
የአቡነ ገበረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት በረከታቸው በሁላችንም ላይ ይደርብን🙏🙏🙏❤️❤️❤️
ስጋቸው እስኪያልቅ ተዘቅዝቀው ጸልየዋል
ወላጆቻቸው ልጅ አጥተው ሠላሳ ዘመን ሲያዝኑ ኖረዋል፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ አንድ ቀን አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥዕለ ሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን “ሥልጣኑ ከሰማይ ከፍታ ከፍ የሚል፣ ንጽሕናው ከሚካኤል ከገብርኤል የሚተካከል፣ ክህነቱ እንደ መልከ ጼዴቅ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ እንደ ነቢዩ ኤልያስ የሆነ ልጅ እንቺ ተቀበይ” የሚል ድምጽ ሰማች፡፡ አቅሌስያም በመጋቢት 29 ቀን ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ቀን ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ ግብጽ ወስጥ ንሂሳ በምትባል ቦታ ወለደች፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ “የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን” አላት፡፡ ወዲያውም ሕፃኑ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገደ፡፡ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን” አለ፡፡
አባታችንም ከዚህ በኋላ እናታቸው አላቀፈቻችውም፤ ጡትም አልጠቡም፡፡ ሦስት ዓመት ሲሞላቸውም በእግዚአብሔር አምላክ ትዕዛዝ ብርሃናዊው መልአክ የራማው ልዑል ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ ሕፃኑን ከእናቱ ክንድ ወስዶ በክንፎቹ አቅፎና ስሞ እስከ ሰባቱ ሰማይ አውጥቶ በሥሉስ ቅዱስ ፊት አቅርቦት አስባረከው፡፡ እግዚአብሔርም መልአኩን “ወደ እናቴ ወደ ማርያም ውሰደውና ትባርከው” አለውና ወስዶት እመቤታችንም ባረከችው፡፡ ከአዳም ጀምሮ ያሉ ቅዱሳንም ሁሉ ባረኩት፡፡ አምላካችን እግዚአብሔርም አጸናው አበረታው፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ አባ ዘመደ ብርሃን ወዳለበት ገዳም አወረደውና ሕፃኑን ከበር ላይ አስቀምጦ ምግቡ የእግዚአብሔር ቃል እንደሆነ ነገረው፡፡ አባ ዘመደ ብርሃንም ሕፃኑን አስገብቶ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ እያስተማረ አሳደገው፡፡ ትምህርቱን በጨረሰ ጊዜ ዲቁና ተቀብሎ እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ሞገስን የተመላ ሥራው የተቃና ሆነ፡፡
አባ ዘመድ ብርሃንም እንደ ቅዱስ እንጦንስ አስኬማን ሰጠው፡፡ ከዚህም በኋላ ቅስናን ተቀበሉና በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ እንደ ሐዋርያትም የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸውና ድውያንን የሚፈውሱ፣ ሙታንን የሚያነሡ፣ አጋንንትን የሚያወጡ ሆኑ፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዳግመኛ ተገልጦላቸው ወደ ሰማይ አሳረጋቸው፡፡ እግዚአብሔርም ከባረካቸው በኋላም ከሰው ተለይተው ከአናብስትና ከአናብርት ጋር እንዲኖሩ፣ እንስሳቱም የእግራቸውን ትቢያ እየላሱ እንደሚኖሩ ነገራቸው፡፡ ሰውነታቸውም ሁሉ በጠጉር ተሸፈነ፡፡ በፍጹም ተጋድሎም ከኖሩ በኋላ በቀንና በሌሊት የክርስቶስን መከራ እያሰቡ ስለ ኃጥአንም ጥፋት እንባቸውን እያፈሰሱ ይጸልዩ ነበር፡፡ በጸሎታቸውም ብዙ እልፍ ነፍሳትን አስምረዋል፡፡
ሦስት መቶ ዓመት ከኖሩ በኋላም ከ60 አንበሶችና ከ60 ነብሮች ጋር ወደ ኢትዮጵያ መጡ፡፡ ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም በነፋስ ሠረገላ ጭኖ ምድረ ከብድ አደረሳቸው፡፡ ደብር ቅዱስ የሚባለው ዝቋላንም አሳያቸው፡፡ ሰው የገዛ ፊቱን በመሥታወት እንደሚያይ አባታችንም የኢትዮጵያን ሰዎች ኃጢአታቸውን በግልጽ በተመለከቱ ጊዜ ተወርውረው ወደ ባሕሩ በመግባት የኢትዮጵያን ሕዝብ ማርልኝ ብለው ለአንድ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ስጋቸው እስኪያልቅ ጸልየዋል፡፡ ጌታችንም መጥቶ ኢትዮጵያን ምሬልሀለሁ ውጣ አላቸው፡፡ ሲወጡም ሰውነታቸውን ዳሶ አደሳቸው፡፡ ታላቅ ቃል ኪዳንም ሰጣቸው፡፡ አባታችን በሀገራችን 262 ዓመታት በጸሎትና በትምህር እየቀዱሱዋት፣ አጋንንትን እያሳደዱ ኖረው በተወለዱ በ562 ዓመታቸው በዕለተ እሁድ አርፈዋል፡፡ በቅዱሳኑ ምልጃ ያመንን ገዳማውያንን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 4 466 |
| 13 | Matn yo'q... | 3 984 |
| 14 | አሜሪካ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ለስድስት አገራት ዜጎች የተሰጠውን በአሜሪካ የመቆየትና የመሥራት ጊዜያዊ ሕጋዊ ከለላ ለተጨማሪ ቀናት አራዘመ።
በአሜሪካ የአገር ውስጥ ደሕንነት መሥሪያ ቤት ሥር የሚገኘው የዜግነትና የፍልሰት አገልግሎት በአገሪቱ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን የተሰጠው ከለላ በመጪው ሐምሌ 10 ቀን 2018 እንደሚያበቃ ትላንት አርብ አስታውቋል።
ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ለሶርያ፣ ሶማሊያ፣ የመን፣ ደቡብ ሱዳን እና ምያንማር ዜጎች የተሰጠው ጊዜያዊ ከለላ በተመሣሣይ ቀን ያበቃል።
ውሳኔው የሚመለከታቸው የሔቲ ዜጎች ከቀሪዎቹ አምስት አገራት አንድ ሳምንት ቀደም ብሎ በአሜሪካ ለመቆየትና ለመሥራት የሚፈቅድላቸውን ከለላ ያጣሉ።
ይህ ከለላ የተፈጥሮ አደጋ፣ የትጥቅ ግጭት ወይም ሌሎች ያልተለመዱ አስገዳጅ ሁኔታዎች ከገጠማቸው አገራት ወደ አሜሪካ የገቡ ሰዎች በአገሪቱ እንዲቆዩ እና በሕጋዊ መንገድ እንዲሠሩ የሚፈቅ ነው።
ከለላው የተሰጣቸው በአሜሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ቢመለሱ “በግል ደሕንነታቸው ብርቱ ሥጋት አይገጥማቸውም” በሚል አመክንዮ በአገሪቱ የመቆየትና የመሥራት ዕድላቸው እንዲያበቃ የተወሰነው ባለፈው ታኅሳስ 2018 ነበር። | 5 110 |
| 15 | የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት እና ምልጃቸው አይለየን🙏
እናታቸው አላቀፈቻችውም፤ ጡትም አልጠቡም
ወላጆቻቸው ልጅ አጥተው ሠላሳ ዘመን ሲያዝኑ ኖረዋል፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ አንድ ቀን አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥዕለ ሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን ታላቅ ክብር ያለው ልጅ እንደምትወልድ የሚናገር ድምጽ ሰማች፡፡ በመጋቢት 29 ቀን ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ቀን ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ ግብጽ ንሂሳ በምትባል ቦታ ወለደች፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ “የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን” አላት፡፡ ሕፃኑ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገደ፡፡ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን” አለ፡፡ ከዚህ በኋላ እናታቸው አላቀፈቻችውም፤ ጡትም አልጠቡም፡፡
ሦስት ዓመት ሲሞላቸውም ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ ሕፃኑን ከእናቱ ክንድ ወስዶ እስከ ሰባቱ ሰማይ አውጥቶ በሥሉስ ቅዱስ ፊት አቅርቦት አስባረከው፡፡ እመቤታችን፣ ቅዱሳንም ሁሉ ባረኩት፡፡ አምላካችን እግዚአብሔርም አጸናው አበረታው፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ አባ ዘመደ ብርሃን ወዳለበት ገዳም አወረደው እርሱም አስተምሮ ካሳደገው በኋላ ዲቁና በኋላም ምንኩስናና ቅስና ሰጠው፡፡ ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸው፡፡ ከሰው ተለይተው ከአናብስትና ከአናብርት ጋር እንዲኖሩ፣ እንስሳቱም የእግራቸውን ትቢያ እየላሱ እንደሚኖሩ ነገራቸው፡፡
ሰውነታቸውም ሁሉ በጠጉር ተሸፈነ፡፡ በፍጹም ተጋድሎም ከኖሩ በኋላ በቀንና በሌሊት የክርስቶስን መከራ እያሰቡ ስለኃጥአንም ጥፋት እንባቸውን እያፈሰሱ ይጸልዩ ነበር፡፡ ሦስት መቶ ዓመት ሲሆናቸውም ቅዱስ ገብርኤል በነፋስ ሠረገላ ጭኖ ከ60 አንበሶችና ከ60 ነብሮች ጋር ወደ ኢትዮጵያ አምጥቶ ምድረ ከብድ አደረሳቸው፡፡ ደብር ቅዱስ ወደሚባለው ዝቋላም ሔደው የኢትዮጵያን ሕዝብ ማርልኝ ብለው ለአንድ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ስጋቸው እስኪያልቅ ጸልየዋል፡፡ ጌታችንም መጥቶ ኢትዮጵያን ምሬልሀለሁ ብሎ ታላቅ ቃል ኪዳን ሰጣቸው፡፡ አባታችን በሀገራችን 262 ዓመታት ኖረው በተወለዱ በ562 ዓመታቸው በዕለተ እሁድ አርፈዋል፡፡ በቅዱሳኑ ምልጃ ያመንን ገዳማውያንን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957 | 5 053 |
| 16 | Matn yo'q... | 4 432 |
| 17 | የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC) ሳይኖራቸው ከ2010-2015 ዓ.ም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ የዲግሪ ተመራቂዎች የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ በያዙት የትምህርት ደረጃ የሚሰጥን ፈተና ማለፍን የሚያስገድደው ረቂቅ መመሪያ ለህዝብ አስተያየት ክፍት ተደረገ።
የኢፌዴሪ የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የከፍተኛ ትምህርት ማስረጃ አሰጣጥንና የደረጃ ግምገማ ሂደትን ለማሻሻል ያስችላል የተባለውን አዲስ ረቂቅ መመሪያ ለህዝብ አስተያየት ክፍት አድርጓል።
ባለስልጣኑ "የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ መመሪያ ቁጥር 990/2016" ላይ ማሻሻያ ለማድረግ በተዘጋጀው በዚህ ረቂቅ ላይ የትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት አስተያየት እንዲሰጡበት ጥሪ አቅርቧል።
ባለስልጣኑ እንዳስታወቀው፣ ይህ የማሻሻያ መመሪያ ያስፈለገው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ የትምህርት ማስረጃዎችን የማረጋገጥ ሂደት ፍትሃዊ፣ ቀልጣፋ እና ግልጽ ለማድረግ ነው።
በተለይም በደረጃ ግምገማ (Equivalency) እና በማስረጃ ማረጋገጫ (Authentication) ሂደት ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት ታልሞ የተዘጋጀ ነው።
ይህ መመሪያ በኢትዮጵያ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ የመንግስትም ሆነ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተምረው ከ2010 ዓ.ም እስከ 2015 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ለተመረቁ ተማሪዎች ተፈጻሚ ይሆናል።
ተፈጻሚነቱ:-
1.ለዲግሪ ትምህርት ከመግባታቸው በፊት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC) ፈተና ሳይወስዱ ዲግሪ የተማሩ እና የተመረቁ።
2. እንዲሁም የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC) የወሰዱት ለዲግሪ ትምህርት ከተመዘገቡ በኋላ የሆኑ ተማሪዎች ያጠቃልላል።
የመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ማስረጃ ለማረጋገጥ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ወይም በፌደራል ወይም በክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋም የተረጋገጠ ኦሪጅናል የስልጠና ማስረጃ ወይም ዲፕሎማ እና ትራንስክሪፕት ላላቸው ነገር ግን የደረጃ አራት የብቃት ማዕቀፍ (COC) ለሌላቸው በመጀመሪያ ዲግሪ ተምረው የተመረቁ ተመራቂዎች የትምህርት ማስረጃቸው እንዲረጋገጥላቸው ፦
👉 የመጀመሪያ፣ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ዲግሪ (ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2015 ዓ.ም) የያዙ ተማሪዎች ሚኒስትሩ በሚያዘጋጀው በያዙት የትምህርት ደረጃ የሚሰጥ ፈተና ላይ ተቀምጠው ማለፍ ይኖርባቸዋል።
👉 ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የተመረቁ ተማሪዎች የትምህርት ማስረጃቸው የሚረጋገጠው የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ወስደው ያለፉ መሆኑ ሲረጋገጥ ብቻ ነው።
👉 ይህ መመሪያ ተሻሽሎ በስራ ላይ ከዋለበት ጊዜ ጀምሮ ማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ያለበት ትምህርት ሚኒስቴር ወይም ማንኛውም የሚመለከተው አካል የሚያወጣውን የመግቢያ መስፈርት ብቻ ተከትሎ ይሆናል።
በመመሪያው ትርጋሜ መሰረት በያዙት የተምህርት ደረጃ ፈተና መስጠት“ ማለት የደረጃ አራት የብቃት ማረጋገጫ ሳይኖረው የመጀመረያ ዲግሪ ፣ ሁለተኛ ዲግሪ ወይም ሶስተኛ ዲግሪ ይዘው የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ አሁን የደረሱበት ወይም የያዙት ዲግሪን መሰረት ተደርጎ የሚሰጥ ፈተና ሆኖ ፈተናውን ሲያልፋ የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ ይሆናል።
ባለስልጣኑ ይህ ረቂቅ መመሪያ ከመጽደቁ በፊት በይፋ ለውይይት አቅርቦታል።
በዚህም መሰረት በረቂቁ ላይ የአስተያየት መስጫ ጊዜ ከሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይሆናል።
አስተያየት ለመስጠት ባለስልጣኑ ባዘጋጀው (https://forms.gle/ndRhodE2yoHSn2P5A) ሊንክ ወይም በኢሜል አድራሻ (info@eta.et) አስተያየት መስጠት ይቻላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሃምሌ 3 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 5 107 |
| 18 | ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ከክፉ ነገር ሁሉ ይከልለን፤ ምለሰጃው እና ረድኤቱም አይለየን🙏
የተወለደው በገሊላ አውራጀ በቤተ ሳይዳ ነው፣ አባቱ ዘብዴዎስ ይባላል ገና በወጣትነቱ ዘመን ከወንድሙ ከያዕቆብ ጋር ለሐዋርያነት ከተጠራበት ጊዜ ጀምሮ የጌታውን እግር ተከትሎ አድጓል ቅዱስ ዮሐንስ፡፡ ወልደ ዘብዴዎስ፣ ወልደ ነጎድጓድ፣ ነባቤ መለኮት /ታኦሎጎስ/፣ ቁጽረ ገጽ በመባል ይታወቃል። ወንጌላዊው ቅዱስ ዩሐንስ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን የመጀመሪያው ወጣት የመጨረሻው ሽማግሌ ሐዋርያ እሱ ነበር፡፡ የጌታ ደቀ መዝሙር ከመሆኑ በፊት የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ከነበሩት አንዱ ነው፡፡ ለጌታችን ባሳየው ልዩ ቀረቤታና ፍቅር ምክንያት “ፍቁረ እግዚእ” የሚል ስያሜ አግኝቷል፡፡ ፍቅሩንና ታማኝነቱንም ጌታ በተሰቀለ ጊዜ “እሱን ያገኘ ያገኘኛል” ብሎ ሳይፈራ ከመስቀሉ ስር በመዋል አስመስክሮአል፡፡
በዩሐንስ 19÷26 እንደተጻፈው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ በመጨረሻዋ ሰዓት ቅዱስ ዮሐንስን ሲያየው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን “እነኋት እናትህ ታጽናናህ” ብሎ ሰጥቶታል፡፡ እኛንም እመቤታችሁ እናታችሁ ቅድስት ድንግል ማርያም ናትና ታጽናናችሁ፣ ተስፋ አለኝታ ትሁናችሁ ማለቱ ነው፡፡ እርሷንም “እነሆ ልጅሽ፣ ይርዳሽ ያጽናናሽ” ብሎ ለእኛ ለክርስቲያኖችም በቅዱስ ዮሐንስ አማካኝነት ለእመቤታችን መስጠቱን እናያለን፡፡ እመቤታችን በቤተ ዮሐንስ እንደኖረች ሁሉ በልበ ምእመናንም አድራ በሃይማኖት የምታጸና፣ ምግባረ ሃይማኖትን፣ ሕገ ትሩፋትን የምታሰራ፣ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ክርስቶስ ድኀነተ ስጋንና ድኀነተ ነፍስን፣ በረከተ ስጋንና በረከተ ነፍስን የምታሰጠን መሆንዋን ነው፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ እንደ ጌታው ቃል እመቤታችንን ወደ ቤቱ ይዟት ሄደ ከእርሱ ጋርም አስራ አምስት ዓመት ተቀምጣለች፡፡ ሐዋርያው የጌታ ትንሣኤ በተነገረ ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስን ቀድሞ ከመቃብረ ክርስቶስ እንዲገኝ ያደረገው የፍቅሩ ጽናት ነበር፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ የድንግልና ሕይወትም ረቂቁን ምስጢረ መለኮት ለማየት አስችሎታል፡፡ ምስጢረ ሥጋዌን አስተካክሎ አደላድሎ በመጻፍ አምልቶ አስፍቶ አስተምሯል፡፡ የፍቅረ እግዚአብሔርንና የፍቅረ ቢጽን ጠቃሚነት በስፋት ጽፏል፡፡ ሰማያትን ሰንጥቆ የሚበር ንስር፣ ልዑለ ስብከት፣ ምሥጢራትን የሚያይ ወንጌላዊ ዮሐንስ፣ ነገሩ ሁሉ በምስጢረ መለኮት የተቀመመ ነው፡፡ ገዳማውያንም ቅዱሳንን አብነት አድርገው ስለ ክርስቶስ ፍቅር ዓለምን ንቀው ይመንናሉና ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጸና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 4 676 |
| 19 | Matn yo'q... | 4 269 |
| 20 | በአዲስ አበባ ከተማ በሆቴሎች እና ተመሳሳይ ተቋማት የመኝታ አገልግሎት ላይ የ5 በመቶ ማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ ተጣለ።
⚫️ በአዲሱ ደንብ ድንጋጌ መሰረት ማንኛውም የመኝታ አገልግሎት ሰጪ ተቋም የመኝታ ክፍሎቹን ብዛትና የእያንዳንዱን ክፍል የቀን የዋጋ ዝርዝር በገቢዎች ቢሮ በአካል ቀርቦ በልዩ ቅጽ መሙላትና ማሳወቅ ይኖርበታል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሆቴሎች፣ በሪዞርቶች፣ በሞቴሎች እና በሌሎች መሰል የመኝታ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ አዲስ የማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ የሚጥል ደንብ አወጣ።
"የሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የመኝታ አገልግሎት ማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ ደንብ ቁጥር 204/2018" በሚል የወጣው ይህ ደንብ፣ የከተማዋን የገቢ አቅም ለማሳደግና መሰረተ ልማቶችን ለማስፋፋት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በደንቡ አንቀጽ 6 መሠረት፣ ማንኛውም የመኝታ አገልግሎት ተጠቃሚ ለክፍል አገልግሎት ከሚከፍለው ዋጋ ላይ 5 በመቶ (5%) የማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ እንዲከፍል ይደረጋል።
ይህ የታክስ ተመን የሚሰላው የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ሳይታከልበት ባለው መደበኛ የክፍል ዋጋ ላይ ተመስርቶ መሆኑ ተደንግጓል።
ይህ አዲስ የታክስ ሕግ በከተማዋ አስተዳደር ወሰን ውስጥ የሚገኙ ሁሉንም የመኝታ አገልግሎት ሰጪዎችን የሚያካትት ሲሆን፣ እነዚህም፦
• ከ1 እስከ 7 ኮከብ ደረጃ ያላቸው ሆቴሎች እና ኮከብ የሌላቸው ሆቴሎች፣
• ሪዞርቶች፣ ሎጆች እና ሞቴሎች፣
• የእንግዳ ማረፊያ ቤቶች (Guest Houses) እና ፔንሲዮኖችን ያጠቃልላል።
አገልግሎት ሰጪ ተቋማቱ በየወሩ ወይም በየሦስት ወሩ (እንደ ግብር ከፋይ ደረጃቸው) የሰበሰቡትን ታክስ ለከተማው ገቢዎች ቢሮ ሪፖርት የማድረግና ገቢ የማድረግ ግዴታ ተጥሎባቸዋል።
ደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች በየወሩ ሪፖርት አድርገው ገቢ የሚያደርጉ ሲሆን ደረጃ "ለ" ግብር ከፋዮች ደግሞ በየሦስት ወሩ ሪፖርት አድርገው ገቢ ያደርጋሉ።
ደንቡን በማይተገብሩ፣ ሪፖርት በሚያዘገዩ ወይም የገቢ መረጃ በሚደብቁ ተቋማት ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና ቅጣት እንደሚጣል ተመልክቷል።
ለማሳያም ሪፖርት ያዘገየ ተቋም ካለበት ዕዳ ላይ እስከ 50 በመቶ የሚደርስ ቅጣት ሊጣልበት እንደሚችልና የታክስ መረጃ መደበቅ ደግሞ በወንጀል እንደሚያስጠይቅ ተደንግጓል።
እንደ ደንቡ ድንጋጌ፣ ማንኛውም የመኝታ አገልግሎት ሰጪ ተቋም በገቢዎች ቢሮ በአካል ቀርቦ የመመዝገብ ግዴታ ያለበት ሲሆን፣ በሚመዘገብበት ወቅትም የተቋሙን የክፍሎች ብዛትና የእያንዳንዱን ክፍል የቀን የዋጋ ዝርዝር በልዩ ቅጽ መሙላትና ማሳወቅ ይኖርበታል።
ይህ የታክስ አከፋፈል ሂደት ከተቋማቱ የንግድ ፈቃድ እድሳት ጋርም በቀጥታ የተያያዘ ነው።
የከተማዋ የቱሪዝም ኮሚሽን የሆቴሎችን የሙያ ብቃት ፈቃድ የሚያድሰው ተቋማቱ ታክሱን በአግባቡ መክፈላቸውን የሚገልጽ ማረጋገጫ ደብዳቤ ከገቢዎች ቢሮ ሲያቀርቡ ብቻ መሆኑ በደንቡ ላይ በግልጽ ተቀምጧል።
የታክስ አሰባሰቡን ግልጽነት ለማረጋገጥም፣ ተቋማቱ በሚሰጡት የሽያጭ ደረሰኝ ላይ "የማዘጋጃ ቤታዊ መኝታ አገልግሎት ታክስ" የሚለው ሐረግ በግልጽ እንዲሰፍር ታዟል።
የሒሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ የሌለባቸው ግብር የሚከፍሉ ተቋማት ደግሞ ከሚሰጡት አገልግሎት 70 በመቶው ላይ የ5 በመቶ ታክስ ታስቦ እንዲከፍሉ ይደረጋል።
በተጨማሪም ተቋማቱ የሰበሰቡትን የታክስ ገቢ በየወሩ ጠቅልለው ሪፖርት ከማድረጋቸው ባለፈ፣ ሰብስበው ባጠናቀቁ በ30 ቀናት ውስጥ ለዚሁ ተብሎ ወደተከፈተ የባንክ ሒሳብ ገቢ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል።
አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም በታክስ አሰባሰብና በአሠራር ሂደት ላይ ቅሬታ ካላቸው በየደረጃው ለሚገኝ የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ የማቅረብ መብት አላቸው።
ኮሚቴው ቅሬታውን ተቀብሎ በ15 የሥራ ቀናት ውስጥ ውሳኔ መስጠት ያለበት ሲሆን፣ በውሳኔው ቅር የተሰኘ ወገን ውሳኔው በደረሰው በ30 ቀናት ውስጥ ለከተማ አስተዳደሩ የታክስ ይግባኝ ኮሚሽን አቤቱታውን ማቅረብ ይችላል።
ማንኛውም የሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋም ከመኝታ አገልግሎት የተገኘን ገቢ ወቅቱን ጠብቆ ሪፖርት አለማሳወቅ ለዘገየበት በየወሩ 5 ከመቶ ከክፍያው ከ50 ከመቶ ያልበለጠ ቅጣት እንዲከፍል ይደረጋል።
በተጨማሪም የታክስ ገቢውን በወቅቱ ገቢ ያላደረገ ተቋም በወቅታዊ የባንክ ብድር ወለድ ተመን መሠረት ወለድና በወለዱ ላይ ተጨማሪ 15 በመቶ ቅጣት እንዲከፍል ይደረጋል።
አዲስ አበባ የቱሪስት መዳረሻነቷ እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ፣ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለከተማዋ የልማት ስራዎች ለማዋል ታስቦ የወጣ መሆኑን የመግቢያው ክፍል ያስረዳል።
ይህም የከተማዋን የገቢ መሠረት በማስፋት የንግድ እንቅስቃሴው ለከተማዋ እድገት የሚኖረውን ድርሻ ከፍ ያደርጋል ተብሏል።
ይህ ደንብ በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተፈርሞ የወጣ ሲሆን፣ ከሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የጸና ሆኗል። | 4 972 |
