Sheger Press️️
📈 Аналитический обзор Telegram-канала Sheger Press️️
Канал Sheger Press️️ (@sheger_press) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 35 461 подписчиков, занимая 7 165 место в категории Новости и СМИ и 986 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 35 461 подписчиков.
Согласно последним данным от 03 сентября, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -262, а за последние 24 часа — -13, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 14.75%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 10.96% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 5 231 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 3 886 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 23.
📝 Описание и контентная политика
Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
“Official channel of sheger press
Contact @Birukepromo”
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 04 сентября, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Новости и СМИ.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 04 сентября | 0 | |||
| 03 сентября | 0 | |||
| 02 сентября | 0 | |||
| 01 сентября | 0 |
| 2 | ቅዱስ ሚካኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ!!!
በጾርዓ ከተማ የሚኖር፣ ከዳን ወገን የሆነና ሚስቱም መካን የነበረች ማኑሄ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፡፡ የእግዚአብሔር መልአክም ለሴቲቱ ተገልጦ “እነሆ ትጸንሻለሽ፤ አሁንም ተጠንቀቂ፤ የወይን ጠጅን የሚያሰክርም ነገር አትጠጪ፥ ርኩስም ነገር አትብዪ፤ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፤ ልጁም ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ለእግዚአብሔር የተለየ ናዝራዊ ይሆናልና በራሱ ላይ ምላጭ አይድረስበት፤ እርሱም እስራኤልን ከፍልስጥኤማውያን እጅ ማዳን ይጀምራል” አላት። ሴቲቱም ለባልዋ የሆነውን ሁሉ ነገረችው፡፡ ማኑሄም የተላከው ሰው ዳግመኛ ወደኛ ይምጣ፤ ብሎ ወደ እግዚአብሔር ለመነ። እግዚአብሔርም የማኑሄን ድምፅ ሰማ፤ መልአኩም ሴቲቱ በእርሻ ውስጥ ተቀምጣ ሳለች እንደገና ተገለጠላት፤ ማኑሄ ግን አልነበረም።
ሴቲቱም ፈጥና ሮጠች፤ ባልዋንም ጠራችው። ማኑሄም “ከዚህች ሴት ጋር የተነጋገርህ አንተ ነህን? ቃልህ በደረሰ ጊዜ የልጁ ሥርዓት ምንድን ነው? አለው። መልአኩም ማኑሄን “ሴቲቱ ከነገርኋት ሁሉ ትጠንቀቅ፣ በማለት ለሴቲቱ የነገራትን ደገመለት፡፡ ማኑሔም “የፍየል ጠቦት እስክናዘጋጅልህ ድረስ፤ እባክህ ቆይ” አለው። መልአኩም የሚቃጠለውንም መሥዋዕት ማዘጋጀት ብትወድድ ለእግዚአብሔር አቅርበው” አለው። ማኑሄም “ነገርህ በደረሰ ጊዜ እንድናከብርህ ስምህ ማን ነው?” አለው፡፡ መልአኩ “ስሜ ድንቅ ነውና ለምን ትጠይቃለህ?” ብሎ መለሰለት። ማኑሄም የፍየሉን ጠቦትና የእህሉን ቍርባን ወስዶ በድንጋይ ላይ ለእግዚአብሔር አቀረበው።
መልአኩም በመሠዊያው ነበልባል ውስጥ ወደ ሰማይ ዐረገ፤ ማኑሄና ሚስቱም በግምባራቸው በምድር ተደፉ። ማኑሄም የእግዚአብሔር መልአክ መሆኑን አወቀ። ሶምሶን ከተወለደ በኋላም የእግዚአብሔርም መንፈስ በጾርዓና በኤሽታኦል መካከል ባለው በዳን ሰፈር ውስጥ ሊያነቃቃው ጀመረ። ይህ ሶምሶንና ወላጆቹን የረዳው ኃያሉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡
ታላቁ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ዛሬም ገዳማውያንን በተጋድሏቸው ሁሉ እየተራዳ አብሯቸው ይኖራል፡፡ ስለ ክርስቶስ ፍቅር ዓለምን ትተው ወጥተዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957 | 2 020 |
| 3 | Нет текста... | 1 816 |
| 4 | 🏠 ንብረት ሲገዙ እና ሲሸጡ የሚመለከቱዎት 2 ዋና ታክሶች
ንብረት ሲገዙ ወይም ሲሸጡ Property Tax እና Capital Gain Tax አንድ አይደሉም።
1. Property Tax 🏠
Property Tax ንብረት በባለቤትነት ስለያዙ የሚከፈል ዓመታዊ ታክስ ነው።
በተሰጠው ምሳሌ፦
* የንብረት የገበያ ዋጋ፦ 20,000,000 ብር
* 25% የግብር መሠረት፦ 5,000,000 ብር
* የProperty Tax ምጣኔ፦ 0.5% ቢሆን
* የዓመቱ ታክስ፦ 25,000 ብር
ስለዚህ ንብረት ሲገዙ የግዢ ዋጋውን ብቻ ሳይሆን የባለቤትነት ታክስንም ግምት ውስጥ ያስገቡ።
2. Capital Gain Tax 💰
Capital Gain Tax ደግሞ ንብረትዎን ሲሸጡ ከሚያገኙት የካፒታል ትርፍ ጋር የሚያያዝ ታክስ ነው።
ምሳሌ፦
* ንብረቱን 10 ሚሊዮን ብር ገዙ።
* በኋላ 15 ሚሊዮን ብር ሸጡት።
* የተገኘው ትርፍ፦ 5 ሚሊዮን ብር
* በ15% ከተተመነ፦ 750,000 ብር
ማለትም ንብረት ሲሸጥ የሚገኘውን ትርፍ በማስላት ላይ Capital Gain Tax ይመለከታል።
በአጭሩ
🏠 ንብረት መያዝ → Property Tax
💰 ንብረት ሸጦ ትርፍ ማግኘት → Capital Gain Tax
ንብረት ለመግዛት ዋጋውን ማወቅ ብቻ አይበቃም፤ በግዢ፣ በባለቤትነት እና በሽያጭ የሚመጡ የታክስ ጉዳዮችንም መረዳት ያስፈልጋል። | 3 324 |
| 5 | 295 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት አቅዷል‼
ኢትዮ ቴሌኮም “ቀጣዩ አድማስ ዲጂታል እና ከዚያም ባሻገር 2028” የተሰኘውን የሶስት ዓመት ስትራቴጂካዊ ፍኖተ ካርታውን ሁለተኛ ዓመት (የ2019 በጀት ዓመት) አጠቃላይ የቢዝነስ እቅድ ይፋ አድርጓል።
📌በእቅዱ የተካተቱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
💰 የገቢ እና የውጭ ምንዛሪ ግብ
አጠቃላይ ገቢ፦ የ36.7% (የ79.2 ቢሊዮን ብር) እድገት በማስመዝገብ 295 ቢሊዮን ብር ለማድረስ ታቅዷል።
የውጭ ምንዛሪ፦ 253.7 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል።
📌👥 የደንበኞች ቁጥር እድገት
አጠቃላይ ደንበኞች፦ በ6.7% በማሳደግ 96.2 ሚሊዮን ለማድረስ፤
የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች፦ የሞባይል ዳታ እና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎችን በ16.5% በማሳደግ 60.01 ሚሊዮን ለማድረስ ግብ ተይዟል።
📌📱 የቴሌብር እና የዲጂታል ፋይናንስ እድገት
የቴሌብር ደንበኞች፦ 67.69 ሚሊዮን ይደርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የግብይት መጠን፦ የንቁ ግብይቶች መጠን 7.4 ትሪሊዮን ብር (በብዛት 4.99 ቢሊዮን) ይደርሳል ተብሏል።
አነስተኛ ብድር፦ በቴሌብር የሚሰጠው የዲጂታል አነስተኛ ብድር ከ19.51 ቢሊዮን ብር ወደ 35.04 ቢሊዮን ብር ከፍ ይላል።
📌📡 የመሰረተ ልማት እና የኔትወርክ
የ4G ኔትወርክ፦ 5,417 አዳዲስ የ4ጂ ጣቢያዎችን በመገንባት ሽፋኑን ከ82.23% ወደ 95% ለማሳደግ ታቅዷል።
የ5G አገልግሎት፦ ተደራሽ የሚሆንባቸውን ከተሞች ቁጥር ከ33 ወደ 73 በማሳደግ የጣቢያዎቹን ቁጥር 648 ለማድረስ ዝግጅት ተጠናቋል።
📱 ስማርት ስልኮች እና የአገራዊ ልማት ድጋፍ
"ዘኔክሰስ" ስማርት ስልኮች፦ ዲጂታል አካታችነትን ለማረጋገጥ 1 ሚሊዮን ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸውን ስልኮች ለገበያ ያቀርባል።
የመንግስት ገቢ፦ 43.1 ቢሊዮን ብር የትርፍ ክፍፍል እና 83.8 ቢሊዮን ብር ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆነ ግብር ገቢ ለማድረግ ማቀዱን ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ፍሬህይወት ታምሩ ዛሬ በስካይላይት ሆቴል ለህዝብ ይፋ አድርገዋል። | 4 089 |
| 6 | ቅዱስ አማኑኤል ከክፉ ነገር ሁሉ ይከልለን፤ በሐጢዓት ፈተና ተጠልፎ ከመውደቅም ይጠብቀን🙏
አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው!!!
ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳይያስ “እነሆ ድንግል በድንግልና ትጸንሳለች፤ ወንድ ልጅንም ትወልዳለች፤ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች” በማለት ትንቢት እንደተናገረው የተስፋው ቃል ይፈጸም ዘንድ በዘመነ ሥጋዌ እግዚአብሔር ወልድ ከንጽሕተ ንጹሐን ከቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ተወለደ፡፡ በኢሳይያስ 7÷14፣ በማቴዎስ 1÷23 እንደተጻፈው መልአኩ የመውለዷን ነገር “እነሆ ትፀንሻለሽ፤ ስሙንም አማኑኤል ትይለዋለች፤ አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው።” ሲል አበሠራት፡፡ ሰዎች በሕይወት ዘመናችን ችግርና መከራ ሲጸናብንና ፈተናችን ሲበዛ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንደሆነ ማሰብ ያዳግተናል፤ እንዲያውም ጨርሶ እንደተወንም እናስባለን፡፡ ሆኖም ግን ፈጣሪያችን ሁሉን የሚያደርገው በምክንያት በመሆኑ ፈተናችን ለበጎ እንደሆነ በማሰብ ጸንተን መጓዝ ያስፈልጋል፡፡ እርሱ ሁሌም ከእኛ ጋር ነውና፡፡
አማኑኤል ‹አማነ› እና ‹ኤል› ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው፤ ትርጓሜውም የአምላክ ሰላም፣ የእግዚአብሔር እርቅ፣ የጌታ አንድነት ማለት ነው። አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ደግሞ ከሥጋችን ሥጋ ከነፍሳችን ነፍስ ነሥቶ የተዋሐደ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀር እንደኛ የሆነ ማለት ነው። አዳም ዕፀ በለስን በልቶ የሞት ፍርድ በተፈረደበት ጊዜ አምላኩ እግዚአብሔር እዲያድነው ስለተማጸነው በርኅራኄው ወደ ቀድሞ ቦታው እንደሚመልሰው በሰጠው ተስፋ ከልጅ ልጁ ተወለዶ አዳነው፡፡ በዚያችም በተከበረች ቀን ትንቢቱ ተፍጽሞ አምላካችን ከእኛ ጋር ሆነ፡፡ አምላክ ሰው የሆነለት የሰው ልጅ ኃጢአት ተፋቀ፡፡ ስለዚህ ከኃጢአት ርቀን በስሙ ተቀድስን እንድኖር እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ የሰው ልጅ ሕይወት ይቀደሳል ማለት ነው፡፡
አንድም “ዒማኑ” ማለት ምስሌነ ከእኛ ጋር ማለት ሲሆን፣ “ኤል” አምላክ የሚል ትርጓሜ አለው፡፡ በጥቅሉም “አምላክ ምስሌነ፣ ወይም ምስሌነ አምላክ፣” አምላክ ከኛ ጋራ ማለት መሆኑ በቅዱስ ማቴዎስ ወንጌልና በትንቢተ ኢሳይያስ መገለጹን ከላይ አይተናል፡፡ ሊቃውንት ግን “አምላክ ወሰብእ” “አምላክም ሰውም” ወይም ሰው የሆነ አምላክ፣ በመለኮቱ አምላክ፣ በለበሰው ስጋም ሰው ብለው በምስጢር አፈታት ይፈቱታል፡፡ አንድም ዐማኑኤል “ወዝስም ዘውእቱ ዐማኑኤል ዐቢይ ጥቀ ወኢደሉ ፈሊጦቱ ወውእቱ ዘበአማን ምስጢር ለጽንዐ ሃይማኖት” “ይህ ዐማኑኤል የተባለ ስም እጅግ ታላቅ ስም ነው፣ የማይለይ ተዋሕዶን የሚገልጽ የሃይማኖት መሠረት ነው” ይሉናል፡፡ ይህን ስም ተመክተው ነው ገዳማውያኑ ዓለምን ንቀው የመነኑት፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 3 842 |
| 7 | Нет текста... | 3 286 |
| 8 | እየተጠናከረ የመጣው ኤል ኒኖ ከባድ የአየር ሁኔታ ስጋት እያሳደረ እንደሆነ ተገለጸ
የዓለም ሜትሮሎጂ ድርጅት እንደገለጸው አሁን ላይ እየተስተዋለ የሚገኘው የኤል ኒኖ ክስተት በ70 ዓመታት ውስጥ ከታዩት በጣም ኃይለኛ ክስተቶች አንዱ ሊሆን እንደሚችል ያስታወቀ ሲሆን፥ ክስተቱም ቢያንስ እስከ የካቲት 2027 ሊቀጥል እንደሚችል ተገልጿል።
የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ዓለም ከፍተኛ የአየር ሁኔታ አደጋ ወደሚበዛበት ደረጃ እየገባች መሆኑን አንስተው፥ ኤል ኒኖ እየጠነከረ በመምጣቱ የድርቅ፣ የጎርፍ፣ የመሬት ናዳ እና የከፍተኛ ሙቀት አደጋዎች ሊባባሱ እንደሚችሉ ተናግረዋል።
በፓሲፊክ ውቅያኖስ ማዕከላዊና ምሥራቃዊ ክፍል የባሕር ሙቀት በቅርብ ወራት በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረ ሲሆን፥በተለይም የባሕር ወለል ሙቀት ከመደበኛው በ2 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል ።
የኤል ኒኖ ተጽዕኖ በሰው ልጅ ከሚመነጨው የረጅም ጊዜ የአየር ንብረት ሙቀት መጨመር ላይ ተደምሮ የከፋ የአየር ሁኔታ ሊያስከትል እንደሚችል ሳይንቲስቶች ገልጸዋል።
ባለሙያዎች በበኩላቸው የኤል ኒኖ ተጽዕኖ በሰዎች ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ ቅድመ ማስጠንቀቂያ፣ የሕክምና ድጋፍና የአደጋ ዝግጅት ሥርዓቶችን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። | 3 892 |
| 9 | እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከክፉ ነገር ሁሉ ትከልለን፤ ምልጃዋ እና ረድኤቷም አይለየን🙏
በመጽሐፍ ቅዱስ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ያህል ትንቢት የተነገረላት ስለእርሷ የተጻፈላት ሴት የለችም። በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብዙ ምሳሌዎች ተጠቅሰዋል፤ የኖኅ መርከብ፣ ሰላማዊት ርግብ፣ የአብርሃም ድንኳን፣ ሙሴ በሲና ያያት ሐመልማል፣ ጽላተ ሙሴ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሐውልት፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ፣ የአሮን በትረ፣ የጌዴዎን ፀምር፣ የኖኅ የቃል ኪዳኑ ቀስተ ደመና፣ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ያያት መሰላል፣ የነቢዩ ኤልሳዕ ማሰሮና ሌሎች ምሳሌዎች በሰፊው የተነገሩላት የተጻፉላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ቤተ ክርስቲያን እርስዋን ለመጥራት የምትጠቀምባቸው ቅጽል ስሞቿና ውዳሴዎቿ ምንኛ ድንቅ ቢሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ገላጭነት በቅዱሳን የተነገሩ ምስጋናዎቿስ እጅግ ቢለዩ የክብሯን ያህል የሚገልጿት አይደሉም፡፡
እርሷ የሰው ሁሉ ረዳትና ርኅሩኅ እናት ናት፤ የብርሃን፣ የምሕረት፣ የድኅነትና የአማናዊው ወይን እናት ናት። ከንጉሡ በስተቀኝ የምትቆመው ንግሥት እርስዋ ናት፤ በመስቀል ስር የተቀበልናት የሁላችንም እናት እርሷ ናት፤ እርሷ ዘለዓለማዊ ድንግል ናት፤ እርሷ የእግዚአብሔር ጸጋ የሞላባት ንጽሕት ቅድስት ድንግል ናት፡፡ ከፍጥረት ሁሉ ተለይታ ወላዲተ አምላክ ለመሆን የተመረጠችበት አንዱ ምክንያት እመቤታችን እጅግ ትሑት፣ ፍጽምትና ንጽሕት ስለሆነች ነው። በሉቃስ 1÷48 እንደተጻፈው የአምላክ እናት እንደምትሆን ተነግሯት እንኳን ክብር ይግባትና ከመኩራትና ሌሎችን ከመናቅ ይልቅ ዘመዷ ኤልሳቤጥን ልትጠይቃት ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ወጣች፡፡ ከኤልሳቤጥ ፍጹም ምስጋናና በማሕጸን ያለው ዮሐንስ የሰላምታ ድምጿን ሰምቶ መዝለሉንከሰማች በኋላም “የባሪያይቱን መዋረድ ተመልክቷልና” በማለት በትሕትና ምስጋናዋን አቀረበች እንጂ የትዕቢት ቃል ከአፏ አልወጣም፡፡
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ “እርሷ በእግዚአብሔር ዓይን በታየ የቅድስና ውበት የተሞላች ነበረችና በእርሷ ንጹሕ ማሕፀን ሊያድር ወደደ፤ እንደ ድንግል ማርያም ራሱን ዝቅ ያደረገ ትሑት ማንም የለም” ይላል። ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም “በትሕትና የተናገርሽ ተራራ ሆይ…” ብሎ ያመሰገናት ይህች ድንግል ከተራሮች አናት ሁሉ ከፍ ያለች ስትሆን ራሷን ዝቅ አድርጋ “እንዲህ ያለ የምስጋና እጅ መንሻ እንደምን ይደረግልኛል” የሚል ምላሽ ለቅዱስ ገብርኤል ሰጠችው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ማርያም ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛው አምላክ ልጇ ነውና ማርልኝ ስትለው ምልጃዋ ፍጹም ነው፡፡ በእግዚአብሔር መመረጧ፣ ከሴቶች ሁሉ መለየቷ፣ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ መሆኗ ይህን ክብር አጎናጽፏታልና፡፡ ገዳማውያንም ይህን ልዩ እናትነቷንና ቅድስናዋን አምነው ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሯታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፡- ቤተ ቅዱሳን ፈትለወርቅ ማርያም የእናቶች ገዳም፡-
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000766349227
ወይም
አቢሲንያ ባንክ
262281132
የገዳሙ ስልክ ቁጥር፡- 0944672222 ወይም 0916106921እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከክፉ ነገር ሁሉ ትከልለን፤ ምልጃዋ እና ረድኤቷም አይለየን🙏
በመጽሐፍ ቅዱስ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ያህል ትንቢት የተነገረላት ስለእርሷ የተጻፈላት ሴት የለችም። በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብዙ ምሳሌዎች ተጠቅሰዋል፤ የኖኅ መርከብ፣ ሰላማዊት ርግብ፣ የአብርሃም ድንኳን፣ ሙሴ በሲና ያያት ሐመልማል፣ ጽላተ ሙሴ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሐውልት፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ፣ የአሮን በትረ፣ የጌዴዎን ፀምር፣ የኖኅ የቃል ኪዳኑ ቀስተ ደመና፣ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ያያት መሰላል፣ የነቢዩ ኤልሳዕ ማሰሮና ሌሎች ምሳሌዎች በሰፊው የተነገሩላት የተጻፉላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ቤተ ክርስቲያን እርስዋን ለመጥራት የምትጠቀምባቸው ቅጽል ስሞቿና ውዳሴዎቿ ምንኛ ድንቅ ቢሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ገላጭነት በቅዱሳን የተነገሩ ምስጋናዎቿስ እጅግ ቢለዩ የክብሯን ያህል የሚገልጿት አይደሉም፡፡
እርሷ የሰው ሁሉ ረዳትና ርኅሩኅ እናት ናት፤ የብርሃን፣ የምሕረት፣ የድኅነትና የአማናዊው ወይን እናት ናት። ከንጉሡ በስተቀኝ የምትቆመው ንግሥት እርስዋ ናት፤ በመስቀል ስር የተቀበልናት የሁላችንም እናት እርሷ ናት፤ እርሷ ዘለዓለማዊ ድንግል ናት፤ እርሷ የእግዚአብሔር ጸጋ የሞላባት ንጽሕት ቅድስት ድንግል ናት፡፡ ከፍጥረት ሁሉ ተለይታ ወላዲተ አምላክ ለመሆን የተመረጠችበት አንዱ ምክንያት እመቤታችን እጅግ ትሑት፣ ፍጽምትና ንጽሕት ስለሆነች ነው። በሉቃስ 1÷48 እንደተጻፈው የአምላክ እናት እንደምትሆን ተነግሯት እንኳን ክብር ይግባትና ከመኩራትና ሌሎችን ከመናቅ ይልቅ ዘመዷ ኤልሳቤጥን ልትጠይቃት ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ወጣች፡፡ ከኤልሳቤጥ ፍጹም ምስጋናና በማሕጸን ያለው ዮሐንስ የሰላምታ ድምጿን ሰምቶ መዝለሉንከሰማች በኋላም “የባሪያይቱን መዋረድ ተመልክቷልና” በማለት በትሕትና ምስጋናዋን አቀረበች እንጂ የትዕቢት ቃል ከአፏ አልወጣም፡፡
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ “እርሷ በእግዚአብሔር ዓይን በታየ የቅድስና ውበት የተሞላች ነበረችና በእርሷ ንጹሕ ማሕፀን ሊያድር ወደደ፤ እንደ ድንግል ማርያም ራሱን ዝቅ ያደረገ ትሑት ማንም የለም” ይላል። ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም “በትሕትና የተናገርሽ ተራራ ሆይ…” ብሎ ያመሰገናት ይህች ድንግል ከተራሮች አናት ሁሉ ከፍ ያለች ስትሆን ራሷን ዝቅ አድርጋ “እንዲህ ያለ የምስጋና እጅ መንሻ እንደምን ይደረግልኛል” የሚል ምላሽ ለቅዱስ ገብርኤል ሰጠችው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ማርያም ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛው አምላክ ልጇ ነውና ማርልኝ ስትለው ምልጃዋ ፍጹም ነው፡፡ በእግዚአብሔር መመረጧ፣ ከሴቶች ሁሉ መለየቷ፣ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ መሆኗ ይህን ክብር አጎናጽፏታልና፡፡ ገዳማውያንም ይህን ልዩ እናትነቷንና ቅድስናዋን አምነው ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሯታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፡- ቤተ ቅዱሳን ፈትለወርቅ ማርያም የእናቶች ገዳም፡-
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000766349227
ወይም
አቢሲንያ ባንክ
262281132
የገዳሙ ስልክ ቁጥር፡- 0944672222 ወይም 0916106921 | 4 115 |
| 10 | Нет текста... | 3 745 |
| 11 | ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከሳምንታት በኋላ ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ ታዩ!
ጠቅላዩ በማኅበራዊ ገፃቸው ላይ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ስምምነት ዛሬ ማከናወናቸውን ገልጸዋል። | 4 137 |
| 12 | ቅዱስ አማኑኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ🙏
አማኑኤል ‹አማነ› እና ‹ኤል› ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው፤ ትርጓሜውም የአምላክ ሰላም፣ የእግዚአብሔር እርቅ፣ የጌታ አንድነት ማለት ነው። አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው።
እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ደግሞ ከሥጋችን ሥጋ ከነፍሳችን ነፍስ ነሥቶ የተዋሐደ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀር እንደኛ የሆነ ማለት ነው። አዳም ዕፀ በለስን በልቶ የሞት ፍርድ በተፈረደበት ጊዜ አምላኩ እግዚአብሔር እዲያድነው ስለተማጸነው በርኅራኄው ወደ ቀድሞ ቦታው እንደሚመልሰው በሰጠው ተስፋ ከልጅ ልጁ ተወለዶ አዳነው፡፡ በዚያችም በተከበረች ቀን ትንቢቱ ተፍጽሞ አምላካችን ከእኛ ጋር ሆነ፡፡
አንድም “ይህ ዐማኑኤል የተባለ ስም እጅግ ታላቅ ስም ነው፣ የማይለይ ተዋሕዶን የሚገልጽ የሃይማኖት መሠረት ነው” ይሉናል፡፡ “ዒማኑ” ማለት ምስሌነ ከእኛ ጋር ማለት ሲሆን፣ “ኤል” አምላክ በተገናኘ፣ አምላክ ምስሌነ ወይም ምስሌነ አምላክ፣ አምላክ ከኛ ጋራ ማለት እንደሆነ በኢሳይያስ 7÷14፣ በማቴዎስ 1÷23 ተጽፏል፡፡ ሊቃውንት ግን “አምላክና ሰው” ወይም ሰው የሆነ አምላክ፣ በመለኮቱ አምላክ፣ በለበሰው ስጋም ሰው ብለው በምስጢር ይፈቱታል፡፡ አምላክ ሰው የሆነለት የሰው ልጅ ኃጢአት ተፋቀ፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስ “እነሆ ድንግል በድንግልና ትጸንሳለች፤ ወንድ ልጅንም ትወልዳለች፤ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች” ብሎ እንደተናገረው እግዚአብሔር ወልድ ከንጽሕተ ንጹሐን ከቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ተወለደ፡፡ ገዳማውያን እናቶችና አባቶች ይህን ስም መመኪያ አድርገው ነው ዓለምን ንቀው የመነኑት፡፡
እርሱ ከኛ ጋር ከሆነ እኛ ከዓለም ጋር ምን ሕብረት አለን ብለው የምንኩስናን ጎዳና መረጡ ገዳማቸውን ስንደግፍ አዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 4 303 |
| 13 | Нет текста... | 4 049 |
| 14 | ለጊዜው ከስራ ታገዱ‼️
2ቱ የትራፊክ የቁጥጥር ባለሙያዎች ለጊዜው ከስራ እንዲታገዱ መደረጉ ተገለፀ::
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በከተማዋ የመንገድ ተጠቃሚዎችን ደህንነት ለማስጠበቅና የትራፊክ እንቅስቃሴን ለማስፈጸም በሚያከናውናቸው የመስክ ቁጥጥር ስራዎች ወቅት ከመንገድ ተጠቃሚዎች ጋር አለመግባባቶች እንደሚከሰቱ ገልጿል።
በዛሬው ዕለት (ነሀሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም) በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ሲሰራጭ የዋለውን ምስል አስመልክቶ ተቋሙ ባወጣው መረጃ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አብራርቷል፦
• የቁጥጥር ባለሙያዎች ደንብ የተላለፈን አሽከርካሪ የመንጃ ፈቃድ በሚጠይቁበት ወቅት "አልሰጥም" በማለት ስራ ማስተጓጎል፣ ስድብ፣ ዛቻ ወይም ሃይል መጠቀም በህግ የሚያስጠይቅ ተግባር መሆኑ ተመልክቷል።
• ተቋሙ በምስሉ ላይ የታየውን አለመግባባት ግራና ቀኝ ያለውን አካል ሚዛናዊ በሆነ መንገድ በማጣራት ላይ እንደሚገኝና እስከዚያው ድረስ በክስተቱ ላይ የተሳተፉት ሁለቱ የቁጥጥር ባለሙያዎች ለጊዜው ከስራ እንዲታገዱ ማድረጉን አስታውቋል።
ህብረተሰቡ የችግሩን የማጣራት ሂደት በስክነት እንዲከታተልና ትክክለኛ ካልሆኑ መረጃዎች እንዲቆጠብ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጥሪ አቅርቧል። | 5 187 |
| 15 | የአርቲስት ፊሊሞን ገብረህይወት መሰወር እንዳሳሰበው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ገለፀ፡፡ የሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆነው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ዛሬ ባወጣው መግለጫ የ33 አመቱ የሰብአዊ መብት ተከራካሪ እንዲሁም የፎቶግራፍና ቪዲዮ ባለሙያ አርቲስት ፊሊሞን ከተሰወረ አንድ አመት እንደሆነው አውስቷል፡፡ የጠፋ እለት ቤተሰቦቹ በአካባቢው ለሚገኝ ፖሊስ ያመለከቱ ቢሆንም እስካሁን ድረስ የት እንዳለ እንደማይታወቅም አስታውቋል፡፡
በአርቲስቱ መጥፋት ዙሪያ የተጀመሩ ወይንም እየተካሄዱ ስላሉ ምርመራዎች ከመንግስት ባለስልጣናት የተሰማ ነገር እንደሌለም አስረድቷል፡፡ ፊሊሞን በትግራይ ክልል መቀሌ ከሚሰራበት ቦታ ወጥቶ በባጃጅ ወደቤቱ እየሄደ እያለ መጥፋቱ ተገልጿል፡፡ በባጃጅ ከመሳፈሩ በፊት ለባለቤቱ ደውሎ አሳውቋት የነበረ ሲሆን ለረጅም ሰአት ቤቱ ባለመመለሱ መልሳ ስትደውልለት ስልኩን አላነሳም፡፡
ከዚያን እለት ጀምሮ አርቲስቱ የት እንዳለ እንደማይታወቅ የጠቀሰው አምነስቲ ፊሊሞን የሁለት ልጆች አባት መሆኑንም አስታውቋል፡፡ የሚመለከታቸው ባለስልጣናት በአርቲስቱ አፈና ላይ ገለልተኛ፣ ጥልቅና ግልፅ ምርመራ በማካሄድ የት እንዳለና ምን እንደሆነ እንዲያሳውቁ አምነስቲ ጨምሮ ጥሪውን አቅርቧል፡፡ | 5 573 |
| 16 | መድኃኔአለም በሐጢዓት ፈተና ተጠልፎ ከመውደቅ ይጠብቀን🙏
እግዚአብሔር እስራኤልን ከደመና መና አውርዶ፣ ከአለት ውሀ አፍልቆ መገባቸው፡፡
እነርሱ ግን እዚህ ደጋ ላይ ቢሆንለት የውርጭ ሰደቃ እያበጀ፣ ውሀውን እያረጋ፣ መና መገብኳችሁ ይላል እንጅ ቆላ ቢሆነማ ባልተቻለውም ነበር ብለዋል። የርሱን ከሃሊነት፣ የእነርሱንም ሀሰት ሊገልጥ ቢወድ፣ ሙሴን የውሃ ምንጭ የሌለበት በረሐ ይዘሀቸው ሂድ ብሎት በዚያም መናው ወርዶላቸዋል፣ ውሀውም ፈልቆላቸዋል። ነገር ግን ነዘር የሚባል እባብ እየነከሰ ይፈጃቸው ጀመር። በዚህ ጊዜ ከሙሴ ዘንድ ሂደው ከጌታ ምህረት ቸርነት ከእኛ ኃጢአት አይታጣም በእግዚአብሔርና በአንተ ላይ ተናግረን በድለናል እባቦችን እንዲያርቅልን ወደ እግዚአብሔር አመልክትልን አሉት።
ሙሴም ወደ እግዚአብሔር ቢጸልይ ከንጹህ ነሐስ የእባብ ምስል ሠርተህ ከሚገናኙበት አደባባይ ከእንጨት ላይ ስቀልላቸው አለው። እንደተባለው ቢያደርግ እባብም የነደፈችው ሰው ሁሉ የነሐሱን እባብ ባየ ጊዜ ዳነ። “ሙሴ እባብን በምድረ በዳ እንደሰቀለው የሰው ልጅ ክርስቶስ ይሰቀል ዘንድ አለው” ተብሎ በዮሐንስ 3÷14 እንደተነገረ፡፡ አባቶቻችንም በትርጓሜ ወንጌል የበረሐው እባብ የዲያብሎስ፤ የብረቱ እባብ የጌታ ምሳሌ ነው። በእባብ መርዝ እንዳለበት በዲያብሎስም ፍዳ ኃጢአት አለበት።
በነሐሱ እባብ መርዝ እንደሌለበት በጌታም ፍዳ ኃጢአት የለበትም። የነሐሱ እባብ በእባብ አምሳል መሰቀሉ ጌታ እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ለመሰቀሉ ምሳሌ ነው። ክርስቶስ ኢየሱስ በመስቀል በተሰቀለ ጊዜ፤ የተሰቀለው የክብር ባለቤት ሰማይን የፈጠረ ነውና ፀሐይ ጨልማለች፣ ጨረቃ ደም ሆኗል፣ ከዋክብት ረግፈዋል።
ገዳማውያኑም በመስቀል የተደረገልንን ማዳን እያሰቡ ዓለምን ንቀው፣ ስጋቸውን ጎድተው ይከተሉታል፡፡ የጽድቃቸው አክሊል እርሱ መድኃኔ ዓለም የሚወደኝ መስቀሌን ተሸክሞ ይከተለኝ እንዳለ፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 5 446 |
| 17 | Нет текста... | 4 685 |
| 18 | ሚኒስትሯ ተራ ታካሚ መስለው የወሰዱት እርምጃ‼️
የኡጋንዳዋ የጤና ሚኒስትር ሌቦችን ለመያዝ የሄዱበት ርቀት ውጤት አምጥቶለታል።
በኡጋንዳ የመንግሥት ሆስፒታሎች ውስጥ በሕመምተኞች ላይ የሚፈጸመውን ሕገ ወጥ የገንዘብ ብዝበዛና የእንግልት ጥቆማ የተከታተሉት የሃገሪቱ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳራ አቺየንግ ነገሩ ስር የሰደደ ነው ብለዋል።
ድርጊቱን እጅ ከፍንጅ ለመያዝ ራሳቸውን ተሸፋፍነው ተራ ታካሚ መስለው ባደረጉት አስደናቂ እንቅስቃሴ አዎንታዊ ውጤት ማስመዝገባቸው ተገለጸ።
ሚኒስትሯ በካምፓላ በሚገኘው ናጉሩ ሆስፒታል በድብቅ ባደረጉት ምልከታ የሕዝቡ የምሬት ምንጭ የሆኑ አንዳንድ የጤና ባለሙያዎች በመንግሥት ተቋማት ውስጥ ከፍተኛ ችግር እየፈጠሩ መሆናቸውን በገሃድ አረጋግጠዋል።
በነጻ ሊሰጡ የሚገባቸው የሕክምና አገልግሎቶች ላይ ክፍያ ሲጠየቅባቸው የቆዩት ዜጎች ምሬት ትክክለኛነት ያረጋገጡት ሚኒስትሯ ተራ ታካሚ ሆነው በቀረቡበት ወቅት በርካታ ችግሮች መኖራቸውን ነው የገለፁት።
ሚኒስትሯ በካፓላ ናጉሩ ሆስፒታል በነፃ የሚሰጡ ምርመራዎች ላይ ባለሙያዎች ከ150 ሺሊንግ በላይ አእያስከፈሉ እጅ ከፍንጅ ይዘዋል።
ሕገ ወጥ ክፍያውን ፈጽመው ከተቀበሉ በኋላ ወዲያውኑ ማንነታቸውን ይፋ ያደረጉት ሚኒስትሯ በሥፍራው ፖሊስ በመጥራት ጥፋተኞቹን በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ አድርገዋል።
ይህ የኡጋንዳዋ የጤና ሚኒስትር የሄዱበት ርቀትና የወሰዱት ቁርጠኛ እርምጃ በመልካም አስተዳደርና በተቋማት ተጠያቂነት ዙሪያ ለሌሎች አመራሮችም ትልቅ ማሳያና ትምህርት ሰጪ ልምድ መሆኑን ነው የተገለጸው።
ይህንን ተሞክሮ ወደ ሀገራችን ወስደን ብንሞክረው። | 5 326 |
| 19 | መንግስት የሚሊሻ ሰላም አስጠባቂ የሚባለዉን አካል አደብ ሊያስገዛ ይገባል ፡፡ | 5 034 |
| 20 | በበዓል ሰሞን የሚታየውን ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር ጥብቅ ክትትል እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ
የአዲስ አበባ ከተማ የንግድ ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ እንደገለፁት የበዓል ገበያን ተገን በማድረግ የሚከናወኑ ህገ-ወጥ ተግባራትን ለመከላከል በመላው ከተማዋ ጥብቅ የቁጥጥር ስራ መጀመሩን አስታውቋል።
ቢሮው በተለይም የኢንዱስትሪ ምርቶች በሚሸሸጉባቸው መጋዘኖች ላይ ድንገተኛ ፍተሻዎችን እያከናወነ ሲሆን፣ ምርት በመደበቅና ሰው ሰራሽ እጥረት በመፍጠር ዋጋ በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።
የቁጥጥር ስራው የምርት ጥራትንና ደረጃን ማረጋገጥን የሚያካትት ሲሆን፣ ጊዜያቸው ያለፈባቸውና ለጤና ጎጂ የሆኑ ምርቶች ለገበያ እንዳይቀርቡ በየደረጃው ያሉ ተቆጣጣሪዎች ስምሪት ተሰጥቷቸዋል።
በተለይም በስጋ ቤቶች፣ በዱቄትና በዳቦ መሸጫዎች ላይ የሚታዩ የምርት መጠን ማነስ ችግሮችን ለመከላከል ክትትል እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
ህገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ዝውውርን ለመቆጣጠርም ከጸጥታ ግብረ-ኃይሉ ጋር በመቀናጀት በመግቢያ በሮችና በዋና ዋና የንግድ ማዕከላት ላይ ጥበቃና ፍተሻው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተደርጓል።
የቁጥጥር ሰራተኞቹ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እንዲቻል ልዩ መለያ (ባጅ) እና ባርኮድ ያለው መታወቂያ እንዲይዙ የተደረገ ሲሆን፣ ይህም ደንበኞችን ከሐሰተኛ ተቆጣጣሪዎች ለመጠበቅ ይረዳል ተብሏል።
ህብረተሰቡ በገበያ ውስጥ የሚታዩ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪዎችን፣ የምርት ጥራት ጉድለቶችንና ሌሎች ህገ-ወጥ ተግባራትን ሲመለከት በነጻ ስልክ መስመር 8588 ጥቆማ እንዲሰጥ ተጠይቋል።
| 5 262 |
