Sheger Press️️
📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Sheger Press️️
Канал Sheger Press️️ (@sheger_press) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 35 932 підписників, посідаючи 7 048 місце в категорії Новини і ЗМІ та 929 місце у регіоні Ефіопія.
📊 Показники аудиторії та динаміка
З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 35 932 підписників.
За останніми даними від 11 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -212, а за останні 24 години на -6, загальне охоплення залишається високим.
- Статус верифікації: Не верифікований
- Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 17.13%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 11.07% реакцій від загальної кількості підписників.
- Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 6 153 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 3 976 переглядів.
- Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 26.
📝 Опис та контентна політика
Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
“Official channel of sheger press
Contact @Birukepromo”
Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 12 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Новини і ЗМІ.
Триває завантаження даних...
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 12 липня | +8 | |||
| 11 липня | 0 | |||
| 10 липня | 0 | |||
| 09 липня | +10 | |||
| 08 липня | +5 | |||
| 07 липня | +13 | |||
| 06 липня | +3 | |||
| 05 липня | +1 | |||
| 04 липня | +7 | |||
| 03 липня | +6 | |||
| 02 липня | +2 | |||
| 01 липня | +5 |
| 2 | እንኳን ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን !!!
የአቡነ ገበረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት በረከታቸው በሁላችንም ላይ ይደርብን🙏🙏🙏❤️❤️❤️
ስጋቸው እስኪያልቅ ተዘቅዝቀው ጸልየዋል
ወላጆቻቸው ልጅ አጥተው ሠላሳ ዘመን ሲያዝኑ ኖረዋል፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ አንድ ቀን አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥዕለ ሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን “ሥልጣኑ ከሰማይ ከፍታ ከፍ የሚል፣ ንጽሕናው ከሚካኤል ከገብርኤል የሚተካከል፣ ክህነቱ እንደ መልከ ጼዴቅ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ እንደ ነቢዩ ኤልያስ የሆነ ልጅ እንቺ ተቀበይ” የሚል ድምጽ ሰማች፡፡ አቅሌስያም በመጋቢት 29 ቀን ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ቀን ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ ግብጽ ወስጥ ንሂሳ በምትባል ቦታ ወለደች፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ “የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን” አላት፡፡ ወዲያውም ሕፃኑ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገደ፡፡ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን” አለ፡፡
አባታችንም ከዚህ በኋላ እናታቸው አላቀፈቻችውም፤ ጡትም አልጠቡም፡፡ ሦስት ዓመት ሲሞላቸውም በእግዚአብሔር አምላክ ትዕዛዝ ብርሃናዊው መልአክ የራማው ልዑል ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ ሕፃኑን ከእናቱ ክንድ ወስዶ በክንፎቹ አቅፎና ስሞ እስከ ሰባቱ ሰማይ አውጥቶ በሥሉስ ቅዱስ ፊት አቅርቦት አስባረከው፡፡ እግዚአብሔርም መልአኩን “ወደ እናቴ ወደ ማርያም ውሰደውና ትባርከው” አለውና ወስዶት እመቤታችንም ባረከችው፡፡ ከአዳም ጀምሮ ያሉ ቅዱሳንም ሁሉ ባረኩት፡፡ አምላካችን እግዚአብሔርም አጸናው አበረታው፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ አባ ዘመደ ብርሃን ወዳለበት ገዳም አወረደውና ሕፃኑን ከበር ላይ አስቀምጦ ምግቡ የእግዚአብሔር ቃል እንደሆነ ነገረው፡፡ አባ ዘመደ ብርሃንም ሕፃኑን አስገብቶ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ እያስተማረ አሳደገው፡፡ ትምህርቱን በጨረሰ ጊዜ ዲቁና ተቀብሎ እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ሞገስን የተመላ ሥራው የተቃና ሆነ፡፡
አባ ዘመድ ብርሃንም እንደ ቅዱስ እንጦንስ አስኬማን ሰጠው፡፡ ከዚህም በኋላ ቅስናን ተቀበሉና በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ እንደ ሐዋርያትም የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸውና ድውያንን የሚፈውሱ፣ ሙታንን የሚያነሡ፣ አጋንንትን የሚያወጡ ሆኑ፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዳግመኛ ተገልጦላቸው ወደ ሰማይ አሳረጋቸው፡፡ እግዚአብሔርም ከባረካቸው በኋላም ከሰው ተለይተው ከአናብስትና ከአናብርት ጋር እንዲኖሩ፣ እንስሳቱም የእግራቸውን ትቢያ እየላሱ እንደሚኖሩ ነገራቸው፡፡ ሰውነታቸውም ሁሉ በጠጉር ተሸፈነ፡፡ በፍጹም ተጋድሎም ከኖሩ በኋላ በቀንና በሌሊት የክርስቶስን መከራ እያሰቡ ስለ ኃጥአንም ጥፋት እንባቸውን እያፈሰሱ ይጸልዩ ነበር፡፡ በጸሎታቸውም ብዙ እልፍ ነፍሳትን አስምረዋል፡፡
ሦስት መቶ ዓመት ከኖሩ በኋላም ከ60 አንበሶችና ከ60 ነብሮች ጋር ወደ ኢትዮጵያ መጡ፡፡ ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም በነፋስ ሠረገላ ጭኖ ምድረ ከብድ አደረሳቸው፡፡ ደብር ቅዱስ የሚባለው ዝቋላንም አሳያቸው፡፡ ሰው የገዛ ፊቱን በመሥታወት እንደሚያይ አባታችንም የኢትዮጵያን ሰዎች ኃጢአታቸውን በግልጽ በተመለከቱ ጊዜ ተወርውረው ወደ ባሕሩ በመግባት የኢትዮጵያን ሕዝብ ማርልኝ ብለው ለአንድ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ስጋቸው እስኪያልቅ ጸልየዋል፡፡ ጌታችንም መጥቶ ኢትዮጵያን ምሬልሀለሁ ውጣ አላቸው፡፡ ሲወጡም ሰውነታቸውን ዳሶ አደሳቸው፡፡ ታላቅ ቃል ኪዳንም ሰጣቸው፡፡ አባታችን በሀገራችን 262 ዓመታት በጸሎትና በትምህር እየቀዱሱዋት፣ አጋንንትን እያሳደዱ ኖረው በተወለዱ በ562 ዓመታቸው በዕለተ እሁድ አርፈዋል፡፡ በቅዱሳኑ ምልጃ ያመንን ገዳማውያንን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 2 536 |
| 3 | Немає тексту... | 2 304 |
| 4 | የአሜሪካው ሴናተር ሊንድሴ ግራሃም በ71 ዓመታቸው ‹‹በድንገተኛ ህመም›› ማለፋቸውን ቢሯቸዉ አስታወቀ
ከደቡብ ካሮላይና የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የሆኑት ግራሃም ከ2003 ጀምሮ በሴኔት ውስጥ አገልግለዋል
ቢሯቸዉ ባወጣው መግለጫ፤ ‹‹ቅዳሜ ምሽት የአሜሪካው ሴናተር ሊንድሴ ግራሃም በአጭር እና በድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል›› ብሏል።
ከደቡብ ካሮላይና ግዛት የመጡት የሪፐብሊካን ፓርቲ አባሉ ግራሃም፤ በ2002 ለሴኔት የተመረጡ ሲሆን በ2008፣ 2014 እና 2020 በድጋሚ ተመርጠዋል።
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቅርብ ወዳጅ የነበሩት ግራሃም፤ የሴኔት የበጀት ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆነው ያገለገሉ ሲሆን፤ በህዳር ወር ምርጫ ለአምስተኛ ጊዜ ለስድስት ዓመት የሴኔት የሥራ ዘመን ለመወዳደር በዝግጅት ላይ ነበሩ።
ግራሃም በቅርቡ ወደ ኪቭ ተጉዘው የተመለሱ ሲሆን፤ ባለፈው አርብ ከዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር ተገናኝተው ነበር።
እስከዳር ግርማ | 3 671 |
| 5 | እንኳን ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን !!!
የአቡነ ገበረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት በረከታቸው በሁላችንም ላይ ይደርብን🙏🙏🙏❤️❤️❤️
ስጋቸው እስኪያልቅ ተዘቅዝቀው ጸልየዋል
ወላጆቻቸው ልጅ አጥተው ሠላሳ ዘመን ሲያዝኑ ኖረዋል፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ አንድ ቀን አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥዕለ ሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን “ሥልጣኑ ከሰማይ ከፍታ ከፍ የሚል፣ ንጽሕናው ከሚካኤል ከገብርኤል የሚተካከል፣ ክህነቱ እንደ መልከ ጼዴቅ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ እንደ ነቢዩ ኤልያስ የሆነ ልጅ እንቺ ተቀበይ” የሚል ድምጽ ሰማች፡፡ አቅሌስያም በመጋቢት 29 ቀን ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ቀን ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ ግብጽ ወስጥ ንሂሳ በምትባል ቦታ ወለደች፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ “የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን” አላት፡፡ ወዲያውም ሕፃኑ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገደ፡፡ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን” አለ፡፡
አባታችንም ከዚህ በኋላ እናታቸው አላቀፈቻችውም፤ ጡትም አልጠቡም፡፡ ሦስት ዓመት ሲሞላቸውም በእግዚአብሔር አምላክ ትዕዛዝ ብርሃናዊው መልአክ የራማው ልዑል ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ ሕፃኑን ከእናቱ ክንድ ወስዶ በክንፎቹ አቅፎና ስሞ እስከ ሰባቱ ሰማይ አውጥቶ በሥሉስ ቅዱስ ፊት አቅርቦት አስባረከው፡፡ እግዚአብሔርም መልአኩን “ወደ እናቴ ወደ ማርያም ውሰደውና ትባርከው” አለውና ወስዶት እመቤታችንም ባረከችው፡፡ ከአዳም ጀምሮ ያሉ ቅዱሳንም ሁሉ ባረኩት፡፡ አምላካችን እግዚአብሔርም አጸናው አበረታው፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ አባ ዘመደ ብርሃን ወዳለበት ገዳም አወረደውና ሕፃኑን ከበር ላይ አስቀምጦ ምግቡ የእግዚአብሔር ቃል እንደሆነ ነገረው፡፡ አባ ዘመደ ብርሃንም ሕፃኑን አስገብቶ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ እያስተማረ አሳደገው፡፡ ትምህርቱን በጨረሰ ጊዜ ዲቁና ተቀብሎ እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ሞገስን የተመላ ሥራው የተቃና ሆነ፡፡
አባ ዘመድ ብርሃንም እንደ ቅዱስ እንጦንስ አስኬማን ሰጠው፡፡ ከዚህም በኋላ ቅስናን ተቀበሉና በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ እንደ ሐዋርያትም የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸውና ድውያንን የሚፈውሱ፣ ሙታንን የሚያነሡ፣ አጋንንትን የሚያወጡ ሆኑ፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዳግመኛ ተገልጦላቸው ወደ ሰማይ አሳረጋቸው፡፡ እግዚአብሔርም ከባረካቸው በኋላም ከሰው ተለይተው ከአናብስትና ከአናብርት ጋር እንዲኖሩ፣ እንስሳቱም የእግራቸውን ትቢያ እየላሱ እንደሚኖሩ ነገራቸው፡፡ ሰውነታቸውም ሁሉ በጠጉር ተሸፈነ፡፡ በፍጹም ተጋድሎም ከኖሩ በኋላ በቀንና በሌሊት የክርስቶስን መከራ እያሰቡ ስለ ኃጥአንም ጥፋት እንባቸውን እያፈሰሱ ይጸልዩ ነበር፡፡ በጸሎታቸውም ብዙ እልፍ ነፍሳትን አስምረዋል፡፡
ሦስት መቶ ዓመት ከኖሩ በኋላም ከ60 አንበሶችና ከ60 ነብሮች ጋር ወደ ኢትዮጵያ መጡ፡፡ ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም በነፋስ ሠረገላ ጭኖ ምድረ ከብድ አደረሳቸው፡፡ ደብር ቅዱስ የሚባለው ዝቋላንም አሳያቸው፡፡ ሰው የገዛ ፊቱን በመሥታወት እንደሚያይ አባታችንም የኢትዮጵያን ሰዎች ኃጢአታቸውን በግልጽ በተመለከቱ ጊዜ ተወርውረው ወደ ባሕሩ በመግባት የኢትዮጵያን ሕዝብ ማርልኝ ብለው ለአንድ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ስጋቸው እስኪያልቅ ጸልየዋል፡፡ ጌታችንም መጥቶ ኢትዮጵያን ምሬልሀለሁ ውጣ አላቸው፡፡ ሲወጡም ሰውነታቸውን ዳሶ አደሳቸው፡፡ ታላቅ ቃል ኪዳንም ሰጣቸው፡፡ አባታችን በሀገራችን 262 ዓመታት በጸሎትና በትምህር እየቀዱሱዋት፣ አጋንንትን እያሳደዱ ኖረው በተወለዱ በ562 ዓመታቸው በዕለተ እሁድ አርፈዋል፡፡ በቅዱሳኑ ምልጃ ያመንን ገዳማውያንን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 3 502 |
| 6 | Немає тексту... | 3 082 |
| 7 | አሜሪካ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ለስድስት አገራት ዜጎች የተሰጠውን በአሜሪካ የመቆየትና የመሥራት ጊዜያዊ ሕጋዊ ከለላ ለተጨማሪ ቀናት አራዘመ።
በአሜሪካ የአገር ውስጥ ደሕንነት መሥሪያ ቤት ሥር የሚገኘው የዜግነትና የፍልሰት አገልግሎት በአገሪቱ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን የተሰጠው ከለላ በመጪው ሐምሌ 10 ቀን 2018 እንደሚያበቃ ትላንት አርብ አስታውቋል።
ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ለሶርያ፣ ሶማሊያ፣ የመን፣ ደቡብ ሱዳን እና ምያንማር ዜጎች የተሰጠው ጊዜያዊ ከለላ በተመሣሣይ ቀን ያበቃል።
ውሳኔው የሚመለከታቸው የሔቲ ዜጎች ከቀሪዎቹ አምስት አገራት አንድ ሳምንት ቀደም ብሎ በአሜሪካ ለመቆየትና ለመሥራት የሚፈቅድላቸውን ከለላ ያጣሉ።
ይህ ከለላ የተፈጥሮ አደጋ፣ የትጥቅ ግጭት ወይም ሌሎች ያልተለመዱ አስገዳጅ ሁኔታዎች ከገጠማቸው አገራት ወደ አሜሪካ የገቡ ሰዎች በአገሪቱ እንዲቆዩ እና በሕጋዊ መንገድ እንዲሠሩ የሚፈቅ ነው።
ከለላው የተሰጣቸው በአሜሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ቢመለሱ “በግል ደሕንነታቸው ብርቱ ሥጋት አይገጥማቸውም” በሚል አመክንዮ በአገሪቱ የመቆየትና የመሥራት ዕድላቸው እንዲያበቃ የተወሰነው ባለፈው ታኅሳስ 2018 ነበር። | 4 480 |
| 8 | የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት እና ምልጃቸው አይለየን🙏
እናታቸው አላቀፈቻችውም፤ ጡትም አልጠቡም
ወላጆቻቸው ልጅ አጥተው ሠላሳ ዘመን ሲያዝኑ ኖረዋል፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ አንድ ቀን አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥዕለ ሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን ታላቅ ክብር ያለው ልጅ እንደምትወልድ የሚናገር ድምጽ ሰማች፡፡ በመጋቢት 29 ቀን ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ቀን ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ ግብጽ ንሂሳ በምትባል ቦታ ወለደች፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ “የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን” አላት፡፡ ሕፃኑ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገደ፡፡ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን” አለ፡፡ ከዚህ በኋላ እናታቸው አላቀፈቻችውም፤ ጡትም አልጠቡም፡፡
ሦስት ዓመት ሲሞላቸውም ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ ሕፃኑን ከእናቱ ክንድ ወስዶ እስከ ሰባቱ ሰማይ አውጥቶ በሥሉስ ቅዱስ ፊት አቅርቦት አስባረከው፡፡ እመቤታችን፣ ቅዱሳንም ሁሉ ባረኩት፡፡ አምላካችን እግዚአብሔርም አጸናው አበረታው፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ አባ ዘመደ ብርሃን ወዳለበት ገዳም አወረደው እርሱም አስተምሮ ካሳደገው በኋላ ዲቁና በኋላም ምንኩስናና ቅስና ሰጠው፡፡ ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸው፡፡ ከሰው ተለይተው ከአናብስትና ከአናብርት ጋር እንዲኖሩ፣ እንስሳቱም የእግራቸውን ትቢያ እየላሱ እንደሚኖሩ ነገራቸው፡፡
ሰውነታቸውም ሁሉ በጠጉር ተሸፈነ፡፡ በፍጹም ተጋድሎም ከኖሩ በኋላ በቀንና በሌሊት የክርስቶስን መከራ እያሰቡ ስለኃጥአንም ጥፋት እንባቸውን እያፈሰሱ ይጸልዩ ነበር፡፡ ሦስት መቶ ዓመት ሲሆናቸውም ቅዱስ ገብርኤል በነፋስ ሠረገላ ጭኖ ከ60 አንበሶችና ከ60 ነብሮች ጋር ወደ ኢትዮጵያ አምጥቶ ምድረ ከብድ አደረሳቸው፡፡ ደብር ቅዱስ ወደሚባለው ዝቋላም ሔደው የኢትዮጵያን ሕዝብ ማርልኝ ብለው ለአንድ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ስጋቸው እስኪያልቅ ጸልየዋል፡፡ ጌታችንም መጥቶ ኢትዮጵያን ምሬልሀለሁ ብሎ ታላቅ ቃል ኪዳን ሰጣቸው፡፡ አባታችን በሀገራችን 262 ዓመታት ኖረው በተወለዱ በ562 ዓመታቸው በዕለተ እሁድ አርፈዋል፡፡ በቅዱሳኑ ምልጃ ያመንን ገዳማውያንን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957 | 4 515 |
| 9 | Немає тексту... | 3 877 |
| 10 | የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC) ሳይኖራቸው ከ2010-2015 ዓ.ም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ የዲግሪ ተመራቂዎች የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ በያዙት የትምህርት ደረጃ የሚሰጥን ፈተና ማለፍን የሚያስገድደው ረቂቅ መመሪያ ለህዝብ አስተያየት ክፍት ተደረገ።
የኢፌዴሪ የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የከፍተኛ ትምህርት ማስረጃ አሰጣጥንና የደረጃ ግምገማ ሂደትን ለማሻሻል ያስችላል የተባለውን አዲስ ረቂቅ መመሪያ ለህዝብ አስተያየት ክፍት አድርጓል።
ባለስልጣኑ "የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ መመሪያ ቁጥር 990/2016" ላይ ማሻሻያ ለማድረግ በተዘጋጀው በዚህ ረቂቅ ላይ የትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት አስተያየት እንዲሰጡበት ጥሪ አቅርቧል።
ባለስልጣኑ እንዳስታወቀው፣ ይህ የማሻሻያ መመሪያ ያስፈለገው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ የትምህርት ማስረጃዎችን የማረጋገጥ ሂደት ፍትሃዊ፣ ቀልጣፋ እና ግልጽ ለማድረግ ነው።
በተለይም በደረጃ ግምገማ (Equivalency) እና በማስረጃ ማረጋገጫ (Authentication) ሂደት ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት ታልሞ የተዘጋጀ ነው።
ይህ መመሪያ በኢትዮጵያ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ የመንግስትም ሆነ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተምረው ከ2010 ዓ.ም እስከ 2015 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ለተመረቁ ተማሪዎች ተፈጻሚ ይሆናል።
ተፈጻሚነቱ:-
1.ለዲግሪ ትምህርት ከመግባታቸው በፊት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC) ፈተና ሳይወስዱ ዲግሪ የተማሩ እና የተመረቁ።
2. እንዲሁም የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC) የወሰዱት ለዲግሪ ትምህርት ከተመዘገቡ በኋላ የሆኑ ተማሪዎች ያጠቃልላል።
የመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ማስረጃ ለማረጋገጥ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ወይም በፌደራል ወይም በክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋም የተረጋገጠ ኦሪጅናል የስልጠና ማስረጃ ወይም ዲፕሎማ እና ትራንስክሪፕት ላላቸው ነገር ግን የደረጃ አራት የብቃት ማዕቀፍ (COC) ለሌላቸው በመጀመሪያ ዲግሪ ተምረው የተመረቁ ተመራቂዎች የትምህርት ማስረጃቸው እንዲረጋገጥላቸው ፦
👉 የመጀመሪያ፣ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ዲግሪ (ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2015 ዓ.ም) የያዙ ተማሪዎች ሚኒስትሩ በሚያዘጋጀው በያዙት የትምህርት ደረጃ የሚሰጥ ፈተና ላይ ተቀምጠው ማለፍ ይኖርባቸዋል።
👉 ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የተመረቁ ተማሪዎች የትምህርት ማስረጃቸው የሚረጋገጠው የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ወስደው ያለፉ መሆኑ ሲረጋገጥ ብቻ ነው።
👉 ይህ መመሪያ ተሻሽሎ በስራ ላይ ከዋለበት ጊዜ ጀምሮ ማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ያለበት ትምህርት ሚኒስቴር ወይም ማንኛውም የሚመለከተው አካል የሚያወጣውን የመግቢያ መስፈርት ብቻ ተከትሎ ይሆናል።
በመመሪያው ትርጋሜ መሰረት በያዙት የተምህርት ደረጃ ፈተና መስጠት“ ማለት የደረጃ አራት የብቃት ማረጋገጫ ሳይኖረው የመጀመረያ ዲግሪ ፣ ሁለተኛ ዲግሪ ወይም ሶስተኛ ዲግሪ ይዘው የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ አሁን የደረሱበት ወይም የያዙት ዲግሪን መሰረት ተደርጎ የሚሰጥ ፈተና ሆኖ ፈተናውን ሲያልፋ የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ ይሆናል።
ባለስልጣኑ ይህ ረቂቅ መመሪያ ከመጽደቁ በፊት በይፋ ለውይይት አቅርቦታል።
በዚህም መሰረት በረቂቁ ላይ የአስተያየት መስጫ ጊዜ ከሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይሆናል።
አስተያየት ለመስጠት ባለስልጣኑ ባዘጋጀው (https://forms.gle/ndRhodE2yoHSn2P5A) ሊንክ ወይም በኢሜል አድራሻ (info@eta.et) አስተያየት መስጠት ይቻላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሃምሌ 3 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 4 739 |
| 11 | ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ከክፉ ነገር ሁሉ ይከልለን፤ ምለሰጃው እና ረድኤቱም አይለየን🙏
የተወለደው በገሊላ አውራጀ በቤተ ሳይዳ ነው፣ አባቱ ዘብዴዎስ ይባላል ገና በወጣትነቱ ዘመን ከወንድሙ ከያዕቆብ ጋር ለሐዋርያነት ከተጠራበት ጊዜ ጀምሮ የጌታውን እግር ተከትሎ አድጓል ቅዱስ ዮሐንስ፡፡ ወልደ ዘብዴዎስ፣ ወልደ ነጎድጓድ፣ ነባቤ መለኮት /ታኦሎጎስ/፣ ቁጽረ ገጽ በመባል ይታወቃል። ወንጌላዊው ቅዱስ ዩሐንስ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን የመጀመሪያው ወጣት የመጨረሻው ሽማግሌ ሐዋርያ እሱ ነበር፡፡ የጌታ ደቀ መዝሙር ከመሆኑ በፊት የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ከነበሩት አንዱ ነው፡፡ ለጌታችን ባሳየው ልዩ ቀረቤታና ፍቅር ምክንያት “ፍቁረ እግዚእ” የሚል ስያሜ አግኝቷል፡፡ ፍቅሩንና ታማኝነቱንም ጌታ በተሰቀለ ጊዜ “እሱን ያገኘ ያገኘኛል” ብሎ ሳይፈራ ከመስቀሉ ስር በመዋል አስመስክሮአል፡፡
በዩሐንስ 19÷26 እንደተጻፈው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ በመጨረሻዋ ሰዓት ቅዱስ ዮሐንስን ሲያየው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን “እነኋት እናትህ ታጽናናህ” ብሎ ሰጥቶታል፡፡ እኛንም እመቤታችሁ እናታችሁ ቅድስት ድንግል ማርያም ናትና ታጽናናችሁ፣ ተስፋ አለኝታ ትሁናችሁ ማለቱ ነው፡፡ እርሷንም “እነሆ ልጅሽ፣ ይርዳሽ ያጽናናሽ” ብሎ ለእኛ ለክርስቲያኖችም በቅዱስ ዮሐንስ አማካኝነት ለእመቤታችን መስጠቱን እናያለን፡፡ እመቤታችን በቤተ ዮሐንስ እንደኖረች ሁሉ በልበ ምእመናንም አድራ በሃይማኖት የምታጸና፣ ምግባረ ሃይማኖትን፣ ሕገ ትሩፋትን የምታሰራ፣ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ክርስቶስ ድኀነተ ስጋንና ድኀነተ ነፍስን፣ በረከተ ስጋንና በረከተ ነፍስን የምታሰጠን መሆንዋን ነው፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ እንደ ጌታው ቃል እመቤታችንን ወደ ቤቱ ይዟት ሄደ ከእርሱ ጋርም አስራ አምስት ዓመት ተቀምጣለች፡፡ ሐዋርያው የጌታ ትንሣኤ በተነገረ ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስን ቀድሞ ከመቃብረ ክርስቶስ እንዲገኝ ያደረገው የፍቅሩ ጽናት ነበር፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ የድንግልና ሕይወትም ረቂቁን ምስጢረ መለኮት ለማየት አስችሎታል፡፡ ምስጢረ ሥጋዌን አስተካክሎ አደላድሎ በመጻፍ አምልቶ አስፍቶ አስተምሯል፡፡ የፍቅረ እግዚአብሔርንና የፍቅረ ቢጽን ጠቃሚነት በስፋት ጽፏል፡፡ ሰማያትን ሰንጥቆ የሚበር ንስር፣ ልዑለ ስብከት፣ ምሥጢራትን የሚያይ ወንጌላዊ ዮሐንስ፣ ነገሩ ሁሉ በምስጢረ መለኮት የተቀመመ ነው፡፡ ገዳማውያንም ቅዱሳንን አብነት አድርገው ስለ ክርስቶስ ፍቅር ዓለምን ንቀው ይመንናሉና ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጸና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444 | 4 306 |
| 12 | Немає тексту... | 3 891 |
| 13 | በአዲስ አበባ ከተማ በሆቴሎች እና ተመሳሳይ ተቋማት የመኝታ አገልግሎት ላይ የ5 በመቶ ማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ ተጣለ።
⚫️ በአዲሱ ደንብ ድንጋጌ መሰረት ማንኛውም የመኝታ አገልግሎት ሰጪ ተቋም የመኝታ ክፍሎቹን ብዛትና የእያንዳንዱን ክፍል የቀን የዋጋ ዝርዝር በገቢዎች ቢሮ በአካል ቀርቦ በልዩ ቅጽ መሙላትና ማሳወቅ ይኖርበታል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሆቴሎች፣ በሪዞርቶች፣ በሞቴሎች እና በሌሎች መሰል የመኝታ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ አዲስ የማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ የሚጥል ደንብ አወጣ።
"የሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የመኝታ አገልግሎት ማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ ደንብ ቁጥር 204/2018" በሚል የወጣው ይህ ደንብ፣ የከተማዋን የገቢ አቅም ለማሳደግና መሰረተ ልማቶችን ለማስፋፋት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በደንቡ አንቀጽ 6 መሠረት፣ ማንኛውም የመኝታ አገልግሎት ተጠቃሚ ለክፍል አገልግሎት ከሚከፍለው ዋጋ ላይ 5 በመቶ (5%) የማዘጋጃ ቤታዊ ታክስ እንዲከፍል ይደረጋል።
ይህ የታክስ ተመን የሚሰላው የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ሳይታከልበት ባለው መደበኛ የክፍል ዋጋ ላይ ተመስርቶ መሆኑ ተደንግጓል።
ይህ አዲስ የታክስ ሕግ በከተማዋ አስተዳደር ወሰን ውስጥ የሚገኙ ሁሉንም የመኝታ አገልግሎት ሰጪዎችን የሚያካትት ሲሆን፣ እነዚህም፦
• ከ1 እስከ 7 ኮከብ ደረጃ ያላቸው ሆቴሎች እና ኮከብ የሌላቸው ሆቴሎች፣
• ሪዞርቶች፣ ሎጆች እና ሞቴሎች፣
• የእንግዳ ማረፊያ ቤቶች (Guest Houses) እና ፔንሲዮኖችን ያጠቃልላል።
አገልግሎት ሰጪ ተቋማቱ በየወሩ ወይም በየሦስት ወሩ (እንደ ግብር ከፋይ ደረጃቸው) የሰበሰቡትን ታክስ ለከተማው ገቢዎች ቢሮ ሪፖርት የማድረግና ገቢ የማድረግ ግዴታ ተጥሎባቸዋል።
ደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች በየወሩ ሪፖርት አድርገው ገቢ የሚያደርጉ ሲሆን ደረጃ "ለ" ግብር ከፋዮች ደግሞ በየሦስት ወሩ ሪፖርት አድርገው ገቢ ያደርጋሉ።
ደንቡን በማይተገብሩ፣ ሪፖርት በሚያዘገዩ ወይም የገቢ መረጃ በሚደብቁ ተቋማት ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና ቅጣት እንደሚጣል ተመልክቷል።
ለማሳያም ሪፖርት ያዘገየ ተቋም ካለበት ዕዳ ላይ እስከ 50 በመቶ የሚደርስ ቅጣት ሊጣልበት እንደሚችልና የታክስ መረጃ መደበቅ ደግሞ በወንጀል እንደሚያስጠይቅ ተደንግጓል።
እንደ ደንቡ ድንጋጌ፣ ማንኛውም የመኝታ አገልግሎት ሰጪ ተቋም በገቢዎች ቢሮ በአካል ቀርቦ የመመዝገብ ግዴታ ያለበት ሲሆን፣ በሚመዘገብበት ወቅትም የተቋሙን የክፍሎች ብዛትና የእያንዳንዱን ክፍል የቀን የዋጋ ዝርዝር በልዩ ቅጽ መሙላትና ማሳወቅ ይኖርበታል።
ይህ የታክስ አከፋፈል ሂደት ከተቋማቱ የንግድ ፈቃድ እድሳት ጋርም በቀጥታ የተያያዘ ነው።
የከተማዋ የቱሪዝም ኮሚሽን የሆቴሎችን የሙያ ብቃት ፈቃድ የሚያድሰው ተቋማቱ ታክሱን በአግባቡ መክፈላቸውን የሚገልጽ ማረጋገጫ ደብዳቤ ከገቢዎች ቢሮ ሲያቀርቡ ብቻ መሆኑ በደንቡ ላይ በግልጽ ተቀምጧል።
የታክስ አሰባሰቡን ግልጽነት ለማረጋገጥም፣ ተቋማቱ በሚሰጡት የሽያጭ ደረሰኝ ላይ "የማዘጋጃ ቤታዊ መኝታ አገልግሎት ታክስ" የሚለው ሐረግ በግልጽ እንዲሰፍር ታዟል።
የሒሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ የሌለባቸው ግብር የሚከፍሉ ተቋማት ደግሞ ከሚሰጡት አገልግሎት 70 በመቶው ላይ የ5 በመቶ ታክስ ታስቦ እንዲከፍሉ ይደረጋል።
በተጨማሪም ተቋማቱ የሰበሰቡትን የታክስ ገቢ በየወሩ ጠቅልለው ሪፖርት ከማድረጋቸው ባለፈ፣ ሰብስበው ባጠናቀቁ በ30 ቀናት ውስጥ ለዚሁ ተብሎ ወደተከፈተ የባንክ ሒሳብ ገቢ የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል።
አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም በታክስ አሰባሰብና በአሠራር ሂደት ላይ ቅሬታ ካላቸው በየደረጃው ለሚገኝ የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ የማቅረብ መብት አላቸው።
ኮሚቴው ቅሬታውን ተቀብሎ በ15 የሥራ ቀናት ውስጥ ውሳኔ መስጠት ያለበት ሲሆን፣ በውሳኔው ቅር የተሰኘ ወገን ውሳኔው በደረሰው በ30 ቀናት ውስጥ ለከተማ አስተዳደሩ የታክስ ይግባኝ ኮሚሽን አቤቱታውን ማቅረብ ይችላል።
ማንኛውም የሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋም ከመኝታ አገልግሎት የተገኘን ገቢ ወቅቱን ጠብቆ ሪፖርት አለማሳወቅ ለዘገየበት በየወሩ 5 ከመቶ ከክፍያው ከ50 ከመቶ ያልበለጠ ቅጣት እንዲከፍል ይደረጋል።
በተጨማሪም የታክስ ገቢውን በወቅቱ ገቢ ያላደረገ ተቋም በወቅታዊ የባንክ ብድር ወለድ ተመን መሠረት ወለድና በወለዱ ላይ ተጨማሪ 15 በመቶ ቅጣት እንዲከፍል ይደረጋል።
አዲስ አበባ የቱሪስት መዳረሻነቷ እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ፣ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለከተማዋ የልማት ስራዎች ለማዋል ታስቦ የወጣ መሆኑን የመግቢያው ክፍል ያስረዳል።
ይህም የከተማዋን የገቢ መሠረት በማስፋት የንግድ እንቅስቃሴው ለከተማዋ እድገት የሚኖረውን ድርሻ ከፍ ያደርጋል ተብሏል።
ይህ ደንብ በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተፈርሞ የወጣ ሲሆን፣ ከሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የጸና ሆኗል። | 4 630 |
| 14 | ቅዱስ ሚካኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ!!!
በጾርዓ ከተማ የሚኖር፣ ከዳን ወገን የሆነና ሚስቱም መካን የነበረች ማኑሄ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፡፡ የእግዚአብሔር መልአክም ለሴቲቱ ተገልጦ “እነሆ ትጸንሻለሽ፤ አሁንም ተጠንቀቂ፤ የወይን ጠጅን የሚያሰክርም ነገር አትጠጪ፥ ርኩስም ነገር አትብዪ፤ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፤ ልጁም ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ለእግዚአብሔር የተለየ ናዝራዊ ይሆናልና በራሱ ላይ ምላጭ አይድረስበት፤ እርሱም እስራኤልን ከፍልስጥኤማውያን እጅ ማዳን ይጀምራል” አላት። ሴቲቱም ለባልዋ የሆነውን ሁሉ ነገረችው፡፡ ማኑሄም የተላከው ሰው ዳግመኛ ወደኛ ይምጣ፤ ብሎ ወደ እግዚአብሔር ለመነ። እግዚአብሔርም የማኑሄን ድምፅ ሰማ፤ መልአኩም ሴቲቱ በእርሻ ውስጥ ተቀምጣ ሳለች እንደገና ተገለጠላት፤ ማኑሄ ግን አልነበረም።
ሴቲቱም ፈጥና ሮጠች፤ ባልዋንም ጠራችው። ማኑሄም “ከዚህች ሴት ጋር የተነጋገርህ አንተ ነህን? ቃልህ በደረሰ ጊዜ የልጁ ሥርዓት ምንድን ነው? አለው። መልአኩም ማኑሄን “ሴቲቱ ከነገርኋት ሁሉ ትጠንቀቅ፣ በማለት ለሴቲቱ የነገራትን ደገመለት፡፡ ማኑሔም “የፍየል ጠቦት እስክናዘጋጅልህ ድረስ፤ እባክህ ቆይ” አለው። መልአኩም የሚቃጠለውንም መሥዋዕት ማዘጋጀት ብትወድድ ለእግዚአብሔር አቅርበው” አለው። ማኑሄም “ነገርህ በደረሰ ጊዜ እንድናከብርህ ስምህ ማን ነው?” አለው፡፡ መልአኩ “ስሜ ድንቅ ነውና ለምን ትጠይቃለህ?” ብሎ መለሰለት። ማኑሄም የፍየሉን ጠቦትና የእህሉን ቍርባን ወስዶ በድንጋይ ላይ ለእግዚአብሔር አቀረበው።
መልአኩም በመሠዊያው ነበልባል ውስጥ ወደ ሰማይ ዐረገ፤ ማኑሄና ሚስቱም በግምባራቸው በምድር ተደፉ። ማኑሄም የእግዚአብሔር መልአክ መሆኑን አወቀ። ሶምሶን ከተወለደ በኋላም የእግዚአብሔርም መንፈስ በጾርዓና በኤሽታኦል መካከል ባለው በዳን ሰፈር ውስጥ ሊያነቃቃው ጀመረ። ይህ ሶምሶንና ወላጆቹን የረዳው ኃያሉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡
ታላቁ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ዛሬም ገዳማውያንን በተጋድሏቸው ሁሉ እየተራዳ አብሯቸው ይኖራል፡፡ ስለ ክርስቶስ ፍቅር ዓለምን ትተው ወጥተዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957 | 4 494 |
| 15 | Немає тексту... | 4 253 |
| 16 | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንበኞቹን በተለያዩ የታሪፍ መደብ ይከፋፍላቸዋል፡፡ እርስዎ ከየትኛው ምድብ ነዎት?
👉 የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚ ደንበኛ፣
👉 ለንግድ፣ ለቢሮ እና ለሃይማኖት ተቋማት የሚያጠቃልለው የጠቅላላ አገልግሎት ተጠቃሚ፣
👉 የዝቅተኛ ቮልቴጅ ኢንደስትሪ ተጠቃሚ ወይስ፣
👉 የመካከለኛ ቮልቴጅ ኢንደስትሪ ተጠቃሚ ደንበኛ?
➡️ የኢነርጂ ቢል የሚይዘው የክፍያ ዝርዝሮችንስ ምን ያህል ያውቃሉ?
❇️ የኢነርጂ ፍጆታ ሂሳብ
❇️ የአገልግሎት ሂሳብ
❇️ ተጨማሪ እሴት ታክስ (15%)፣
❇️ የተቆጣጣሪ ባለሥልጣን (0.5%)
❇️ የቴሌቪዥን ግብር (10 ብር) ይካተታል።
➡️ በዚህም መሠረት የመኖሪያ ቤት መደብ በሚጠቀሙት ወርሀዊ የኢነርጂ መጠን በ7 እርከን ይከፈላሉ👇
✅ ከ1-50፤
✅ ከ51-100፤
✅ ከ101-200፤
✅ ከ201-300፤
✅ ከ301-400 እና
✅ ከ401-500
✅ ከ501 በላይ
☑️ ይህም በወር ውስጥ በሚጠቀሙት ኪሎ ዋት ሰዓት፤ ደንበኛው አጠቃላይ ተጠቅመዉ ያረፉበት እርከን መሰረት የፍጆታ ሂሳቡ ይሰላል፡፡
🛑 የኢነርጂ አጠቃቀማቸው በወር 200 ኪሎ ዋት ሰዓት በታች የሚጠቀሙ ደንበኞች የተጨማሪ አሴት ታክስ አይመለከታቸውም፡፡
🛑 እንዲሁም የገቢ ሁኔታቸውን እንዳይጎዳ የፍጆታ መጠን ክፍያቸው ላይ የድጎማ ተጠቃሚ ናቸው።
👉 ለንግድ፣ ለቢሮ እና ለሃይማኖት ተቋማት የሚያጠቃልለው የጠቅላላ አገልግሎት ታሪፍ መደብ ደንበኞች፣ ከመኖሪያ ቤት ተጠቃሚዎች የሚለይና በወር ውስጥ ለተጠቀሙት ኢነርጂ በወጥ ታሪፍ የሚከፍሉ ናቸው።
ወርሃዊ ወጪን ለመቀነስ👇
⚡️ኃይል ቆጣቢና ኢነርጂ የመቆጠብ ብቃት ያላቸው የኤሌክትሪክ ዕቃዎችን መጠቀም
⚡️ የኢነርጂ ፍጆታ ንባብን በወቅቱ መነበቡን ማረጋገጥ
⚡️ ወርሀዊ የፍጆታ ክፍያን በጊዜ መርሀ ግብሩ መሰረት በወቅቱ መፈፀም
⚡️ በየትኛው የታሪፍ እርከን ወይም መደብ እንደሚከፍሉ ማወቅ።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት | 4 875 |
| 17 | እንኳን ለበዓታ ለማርያም አደረሳችሁ፤ አደረሰን!!!
ወደ ቤተ መቅደስ ገባች🙏🙏🙏
በመካንነት የነበሩት ወላጆቿ ኢያቄምና ሐና በንጽህና በቅድስና ቢኖሩም በወቅቱ የነበሩት ካሕናተ ኦሪት ልጅ ስላልወለዱ መስዋዕታቸውን እንኳን ሊቀበሏቸው ፈቃደኛ አልነበሩም፡፡
ወላጆቿ ወደ እግዚአብሔር ጸልየው፣ ልጅ ከሰጣቸው ለቤተ እግዚአብሔር ሊሰጡ ስዕለት ገብተው ቅድስት ድንግል ማርያምን ወለዱ፡፡ እመቤታችን ገና በቅድስት ሐና ማሕጸን ከነበረችበት ወቅት ጀምሮ ተአምራት ታደርግ ነበር፡፡ ቤርሳቤህ የተባለች ሴት የሀናን መጽነስ ስትሰማ በደስታ ልትጎበኛት መጣች፡፡ አንድ አይኗን አጥታ የነበረችው ይህች ሴት ቅድስት ሐናን እንኳን ደስ አለሽ ብላ ሆዷን ከዳሰሰቻት በኋላ በዚያው እጇ ዓይኗን ብትነካው ዐይኗ በርቶላታል፡፡
ይህን ምሳሌ አደርገው ድውያን እየመጡ ሆዷን ዳሰው ይፈወሱ ነበር፡፡ በቅድስት ድንግል ማርያም መወለድ ወላጆቿ ቅዱስ ኢያቄምና ቅድስት ሀና ፍሬ አጊኝተዋል፡፡ ዓለም ደግሞ የመድኃኒቱን እናት አጊኝቷል፡፡
እናታችን ቅድስት ሐና እመቤታችን ጸንሳ ሳለች ሳሚናስ የሚባል የአጓቷ ልጅ ይሞታል፡፡ ቅድስት ሐናም እጅግ ትወደው የአልጋውን ሸንኮር እየዞረች ስታለቅስ ከሞተበት ተነስቶ “የሰማይና የምድር ፈጣሪ አያት ሆይ ላንቺ ክብር ይገባሻል!!!” ብሎ መስክሮ አርፏል፡፡ አይሁድም “ቀድሞ የእነዚህ ዘር የነበሩ ዳዊትና ሰሎሞን አርባ፣ አርባ ዘመን ገዙን አሁን ከዚህች የሚወለድ ምን ሊያደርገን ነው?” ብለው በድንጋይ ሊወግሯት ተነሱ፡፡ የራማው ልዑል ቅዱሰ ገብርኤል እየመራ ወደ ሊባኖስ ተራራ ወሰዳቸው፡፡ በእዚያም ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች፡፡ ሰማያት ብርሃን ሰጡ፣ ቅዱሳን መላእክት አዲስ ምስጋና ተቀኙላቸው፣ የሊባኖስ ተራራም በብርሃን ደመቀ፡፡ በጨለማውስጥ የነበረው ዓለም ብርሃን የሚያይባት፣ የእውነተኛው ጸሐይ እናቱ ተወለደች፡፡ አባቷ ንጉስ ሰሎሞን “ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ” እንዳለ በሊባኖስ ተራራ ተወለደች፡፡
ኢያቄምና ሐና የተሳሉትን ስእለታቸው አስታውሰው በሦት ዓመቷ ወስደው ለቤተ እግዚአብሔር ሲሰጧትም ካህኑ ዘካርያስ ስለምግቧ ስለተጨነቀ፤ ሕዝቡን ሰብስቦ ሳለ መልአኩ ፋኑኤል ኅብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ይዞ ከሰማይ ወረደ፤ ዘካርያስ ለእርሱ የመጣ ሀብት መስሎት ሊቀበል ሲቀርብ ወደ ላይ ራቀበት፡፡ ከእርሱ በታች ካለው ስምዖን ጀምሮ በዚያ የተሰበሰቡት ሰዎችም በየተራ ቢሞክሩ በተመሳሳይ መልኩ ወደ ላይ ራቀባቸው፡፡ ምን አልባት ለእንግዶች የመጣ ሀብት እንደሆነ ብለው ሐናና ኢያቄም እንዲቀርቡ አደረጓቸው፤ ነገር ግን ለእነርሱም ራቀባቸው፤ ዘካርያስም ሐናን “እግዚአብሔር የሚያደርገውን የሚያውቅ የለምና ልጅቷን ትተሸ ወደዚህ ነይ” አላት፤ በዚያም ጊዜ ቅድስት ማርያም እናቷን ስትከተል መልአኩ ፋኑኤል ፈጥኖ ወርዶ አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክንፉን ጋርዶ መግቧት፤ በክብር ዐረገ፡፡
ሊቀ ካህናቱና ሕዝቡም “የምግቧ ነገር ከተያዘልን በቤት እግዚአብሔር ትኑር” ብለው ታህሣስ 3 ቀን ወደ ቤተ መቅደስ አስገቧት፡፡ ለ12 ዓመታትም ሰማያዊ ኅብስትና መጠጥ እየተመገበች በቤተ መቅደስ ኖረች፡፡ በ15 ዓመቷም ለአቅመ ሔዋን በመድረሷ ከቤተ መቅደስ ትውጣልን በማለት አይሁድ በጠላትነት ተነሡባት፡፡ ካህኑ ዘካርያስም በጸለየ ጊዜ እግዚአብሔር አረጋዊው ዮሴፍ እንዲጠብቃት ምልክትን ሰጣቸው፡፡ ርግብም መጥታ በራሱ ላይ ዐረፈች፤ ስለሆነም ዮሴፍ እንዲጠብቃት ተወሰነ፡፡ ቤተ መቅደስም እየተመላለሰች ታገለግል ነበር፡፡
በመልአኩ ብስራትም የዓለሙ መድኅን ጌታን ጸንሳለች፡፡ ይህችን ብርሃን፣ የብርሃን እናት ገዳማውያን አባቶችና እናቶች ዘወትር በጸሎታቸው ያስቧታል፡፡ ገዳማቸውን እናግዝ፣ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957 | 4 734 |
| 18 | Немає тексту... | 4 255 |
| 19 | አያቶላህ ዓሊ ኻምኔይ ተቀበሩ‼
ባለፈው የካቲት ወር በአሜሪካና እስራኤል ጥቃት የተገደሉት የኢራን የፖለቲካና የሃይማኖት መሪ አያቶላህ ዓሊ ኻምኔይ፣ ዛሬ በትውልድ ስፍራቸው ማሽሃድ ውስጥ ተቀብረዋል።
በቀብር ሥርዓቱ ላይ በመቶ ሺህ የሚቆጠር የኢራን ሕዝብ የብቀላ ጥሪ ምልክት የሆነውን ቀይ አርማ እያወለበለበ የተገኘ ሲሆን፣ አሜሪካ ከቀብሩ ጥቂት ሰዓታት በፊት የቴህራን-ማሽሃድ የባቡር መስመርን ጨምሮ የተለያዩ የሀገሪቱን መሠረተ-ልማቶች ማውደሟ ተገልጿል።
የአባታቸውን ሥልጣን የተረከቡት አዲሱ ላዕላይ መሪ ሞጅታባ ኻምኔይ፣ እስካሁን ለሕዝብ እይታ ያልቀረቡ ሲሆን በዛሬው የቀብር ሥርዓት ላይም አልተገኙም። | 5 400 |
| 20 | እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከክፉ ነገር ሁሉ ትከልለን፤ ምልጃዋ እና ረድኤቷም አይለየን🙏
መልአኩ ፋኑኤል ፈጥኖ ወርዶ አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክንፉን ጋርዶ መገባት🙏
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ገና በቅድስት ሐና ማሕጸን ከነበረችበት ወቅት ጀምሮ ተአምራት ታደርግ ነበር፡፡ አንድ አይኗን ያጣች ቤርሳቤህ የተባለች ሴት የሀናን መጽነስ ስትሰማ በደስታ ልትጎበኛት መጣች፡፡ ቅድስት ሐናን እንኳን ደስ አለሽ ብላ ሆዷን ከዳሰሰቻት በኋላ በዚያው እጇ ዓይኗን ብትነካው ዐይኗ በርቶላታል፡፡ ይህን ምሳሌ አደርገው ድውያን እየመጡ ሆዷን ዳሰው ይፈወሱ ነበር፡፡ በመካንነት የነበሩት ወላጆቿ ልጅ ከሰጣቸው ለቤተ እግዚአብሔር ሊሰጡ ስዕለት ገብተው በቅድስት ድንግል ማርያም መወለድ ፍሬ ሲያገኙ ዓለም ደግሞ የመድኃኒቱን እናት አጊኝቷል፡፡ እናታችን ቅድስት ሐና ጸንሳ ሳለች የአጓቷ ልጅ አርፎ እጅግ የአልጋውን ሸንኮር እየዞረች ስታለቅስ ከሞተበት ተነስቶ “የሰማይና የምድር ፈጣሪ አያት ሆይ ላንቺ ክብር ይገባሻል” ብሎ መስክሮ ተመልሶ አርፏል፡፡
አይሁድም “ቀድሞ የእነዚህ ዘር የነበሩ ዳዊትና ሰሎሞን አርባ፣ አርባ ዘመን ገዙን አሁን ከዚህች የሚወለድ ምን ሊያደርገን ነው?” ብለው በድንጋይ ሊወግሯት ተነሱ፡፡ የራማው ልዑል ቅዱሰ ገብርኤል ወደ ሊባኖስ ተራራ ወሰዳቸው፤ በእዚያም በጨለማ ውስጥ የነበረው ዓለም ብርሃን የሚያይባት፣ የእውነተኛው ጸሐይ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች፡፡ ኢያቄምና ሐና የተሳሉትን ስእለታቸው አስታውሰው በሦስት ዓመቷ ወስደው ለቤተ እግዚአብሔር ሲሰጧትም ካህኑ ዘካርያስ ስለምግቧ ተጨንቆ፤ ሕዝቡን ሰብስቦ ሳለ መልአኩ ፋኑኤል ኅብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ይዞ ከሰማይ ወረደ፤ ዘካርያስ ለእርሱ የመጣ ሀብት መስሎት ሊቀበል ሲቀርብ ወደ ላይ ራቀበት፡፡ በዚያ በተሰበሰቡትም ቢሞክሩ አልሆነም፡፡
ዘካርያስም ሐናን “እግዚአብሔር የሚያደርገውን የሚያውቅ የለምና ልጅቷን ትተሸ ወደዚህ ነይ” አላት፤ በዚያም ጊዜ ቅድስት ማርያም እናቷን ስትከተል መልአኩ ፋኑኤል ፈጥኖ ወርዶ አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክንፉን ጋርዶ መግቧት፤ በክብር ዐረገ፡፡ ሊቀ ካህናቱና ሕዝቡም “የምግቧ ነገር ከተያዘልን በቤት እግዚአብሔር ትኑር” ብለው ታህሣስ 3 ቀን ወደ ቤተ መቅደስ አስገቧት፡፡ ለ12 ዓመታትም ሰማያዊ ኅብስትና መጠጥ እየተመገበች በቤተ መቅደስ ኖረች፡፡ ይህችን ብርሃን፣ የብርሃን እናት ገዳማውያን አባቶችና እናቶች ዘወትር በጸሎታቸው ያስቧታል፡፡ ገዳማቸውን እናግዝ፣ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957 | 5 229 |
