አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
አቡቀለምሲስ ማለት ረአየ ኅቡኣት አበ ራዕይ አበ ትንቢት ማለት ሲሆን የተሰወረውን የተደበቀውን የተከደነውን የሚገልጥ ማለት ነው። መሠራታዊ ዓለማው በሀገረ ስብከታችን ብሎም በመላ ቤተ ክርስቲያናችን የተሰወሩ ገዳማትን የተደበቁ ሊቃውንትን የተከደኑ ታሪኮችን የተሸሸጉ ቅርሶችን ማውጣት እና የተንሸዋረረ ታሪክ ማስተካከልና የጎበጠውን አዲሱን ትውልድ ማነጽ ነው
إظهار المزيد2 176
المشتركون
-124 ساعات
+97 أيام
+3030 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
ልዩ የትንሣኤ በዓል ዝግጅት ቅዳሜ በEOTC TV ይጠብቁን
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶሰ በትህትና ዝቅ ብሎ የደቀ መዛሙርቱን እግር ያጠበበት ጸሎተ ሐሙስ መታሰቢያ በዓል በደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ተከበረ።
በዓሉ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ተከብሯል።
በበዓሉ ላይ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ አባቡን ጨምሮ የሀገረ ስብከቱ የክፍላት ሓላፊዎች ፣ የደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃናት ቆሞስ አባ ይትባረክ መኮንን ተገኝተዋል።
በተመሳሳይ በርካታ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እና ሕዝበ ክርስቲያን በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል።
ፎቶ፦ሚኪያስ ዐቢይ
፦ቴዎድሮስ አየለ
የሰሙነ ሕማማት እለተ ረቡዕ የጸሎት እና የስግደት ሥርዓት በደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን በፎቶ:-
እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻእር ወድካም አመ ከመዮም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም!!!