አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
አቡቀለምሲስ ማለት ረአየ ኅቡኣት አበ ራዕይ አበ ትንቢት ማለት ሲሆን የተሰወረውን የተደበቀውን የተከደነውን የሚገልጥ ማለት ነው። መሠራታዊ ዓለማው በሀገረ ስብከታችን ብሎም በመላ ቤተ ክርስቲያናችን የተሰወሩ ገዳማትን የተደበቁ ሊቃውንትን የተከደኑ ታሪኮችን የተሸሸጉ ቅርሶችን ማውጣት እና የተንሸዋረረ ታሪክ ማስተካከልና የጎበጠውን አዲሱን ትውልድ ማነጽ ነው
إظهار المزيد2 180
المشتركون
-224 ساعات
-47 أيام
+2430 أيام
أرشيف المشاركات
የደብረ ብርሃን ደብረ ፀሐይ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤት ተከበረ።
ግንቦት ፲፫ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም (አቡቀለምሲስ ሚዲያ ፤ ደብረ ብርሃን)
++++++++++ ++++++++++ ++++++++++
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ደብረ ብርሃን ከተማ የሚገኘው የጠባሴ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤት ተከብሯል።
በክብረ በዓሉ ላይ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ አባቡ "አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኲራት ሆኖ ከሙታን ተነስቷል" በሚል መነሻ ኃይለ ቃል ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል።
ክቡር ሥራ አስኪያጁ ወቅቱ ዘመነ ትንሣኤ እንደመሆኑ ስለ ጌታችን ትንሣኤ በሰፊው አስተምረዋል።
በትምህርታቸውም ሞት ሊይዘው መቃብር ወስኖ ሊያስቀረው ያልቻለው የትንሣኤው ንጉሥ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤያችን በኵር ሆኖ ከሙታን መካከል ተነስቷል።
በዚህም ትንሣኤውን ይናፍቁ የነበሩ ማርያም መግደላዊትን ጨምሩ የክርስቶስ ቤተሰቦች ሀዘናቸው በደስታ ተለውጦ ክርስቶስ ተነስቷል ብለው አመስግነዋል ትንሣኤውንም ሰብከዋል።
እኛም ዛሬ የጌታችንን ትንሣኤ ስናከብር ለሥጋችን ደስታ ብቻ ሳናስብ ለነፍሳችን የሚጠቅመውን በማድረግ ትንሣኤ ልቡና፣ ትንሣኤ ሕሊናን ገንዘብ አድርገን ሊሆን ይገባል። ክርስትናችን በተግባር ሊገለጥ፣ በንሥሐ ልብ ተመልሰን በቅዱስ ቁርባን ከብረን ክርስቶስን መስለን፣ ክርስቶስን ለብሰን ተዘጋጅተን ልንኖርም ያስፈልጋል በማለት አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል።
በክብረ በዓሉ ላይ በደብሩ ሊቃውንት እና በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ወረብ እና ዝማሬ ቀርቧል።
ዓመታዊው ክብረ በዓል መልአከ ብርሃን ይትባረክ ታጠቅ የደብረ ፀሐይ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ እና ምዕራፈ ቅዱሳን መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ አንድነት አብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪ፣ የሀገረስብከቱ የየክፍላት ሓላፊዎች፣ የወረዳ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጆች እና ሊቃነ ካህናት፣ የአድባራት እና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ የአብነት መምህራን እና ደቀመዛሙርት እንዲሁም ምእመናን በተገኙበት በቃልኪዳኑ ታቦት ባርኮት በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ውሏል።
Follow Us On
Youtube www.youtube.com/@AbukelemsisMedia
Telegram:- t.me/Abukelemsismedia
Instagram:- www.instagram.com/Abukelemsis.nsd
Twitter:- www.twitter.com/Abukelemsis01
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የመገለጥ በዓል እና የገዳሟ ቅዳሴ ቤት ክብረ በዓል ግንቦት ፳፩ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም በደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ገዳም።