ar
Feedback
አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

الذهاب إلى القناة على Telegram

አቡቀለምሲስ ማለት ረአየ ኅቡኣት አበ ራዕይ አበ ትንቢት ማለት ሲሆን የተሰወረውን የተደበቀውን የተከደነውን የሚገልጥ ማለት ነው። መሠራታዊ ዓለማው በሀገረ ስብከታችን ብሎም በመላ ቤተ ክርስቲያናችን የተሰወሩ ገዳማትን የተደበቁ ሊቃውንትን የተከደኑ ታሪኮችን የተሸሸጉ ቅርሶችን ማውጣት እና የተንሸዋረረ ታሪክ ማስተካከልና የጎበጠውን አዲሱን ትውልድ ማነጽ ነው መረጃ t.me/AbukelemsisSMSbot

إظهار المزيد
2 464
المشتركون
-324 ساعات
+27 أيام
+2430 أيام
أرشيف المشاركات
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የዕርገቷ በዓል በአንጎለላ ጽርሐ አርያም ቅድስት ኪዳነምሕረት ቤተ ክርስቲያን ተከበረ። ነሐሴ ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም አቡቀለምሲስ ሚዲያ(ደብረ ብርሃን) ++++++ +++++ ++++ +++++ +++ +++ ++++++ በየዓመቱ ነሐሴ ፲፮ የሚከበረው የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የዕርገቷ በዓል በአንጎለላ ጽርሐ አርያም ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ክቡር መጋቤ ሐዲስ ነቅዐ ጥበብ አባቡ የሰሜን ሽዋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በተገኙበት በከፍተኛ ድምቀት ተከብሮ ውሏል። በክብረ በዓሉ ላይ ክቡር መጋቤ ሐዲስ ነቅዐ ጥበብ "ቃልኪዳኔን እንዳላጎድል በራሴ ማልሑልሽ" በሚል ኃይለ ቃል መነሻነት ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል። ክቡር ሥራ አስኪያጁ በትምህርታቸው ቅዱስ ያሬድ "ቃልኪዳኔን እንዳላጎድል በራሴ ማልሑልሽ" በማለት ለእናቱ ድንግል ማርያም የገባላትን የምሕረት ቃልኪዳን የማይሻር የማይለወጥ ስለመሆኑ ከቅዱሳት መጻሕፍት ከቅዱሳኑ ቃል አስረጂ እያጣቀሱ በስፋት አብራርተዋል። ዛሬ የምናከብረው ከድንግል ማርያም ፴፫ቱ በዓላቶቿ መካከል አንዱ እና ታላቅ በዓሏን ነው በማለት የበዓሉን ምስጢር አስፍተው ገልጠዋል። ድንግል ማርያም ፷፬ ዓመት ሲሞላት ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ከዚህ ዓለም ወደማያልፈው ዓለም ጠራት በዚህ የከበረ ጥሪ ነፍሷ ከስጋዋ ተለየች፤ ሐዋርያት በአይሁድ ልማድ መሠረት አክብረው ገንዘው ሊቀብሯት ወደጌቴሴማኒ በሚሔዱ ጊዜም አይሁድ በምቀኝነት ተነሱ። ቀድሞ ልጇ ተነሣ ዐረገ እያሉ ቤተ አይሁድን ሲያውኩ ኖረዋል፣ አሁን ደግሞ እርሷን ተነሣች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን ነውና ኑ የማርያምን ሥጋ በድንጋይ ወግረን በእሳት አቃጠለን እናጥፋ በማለት ክፋት መክረው መጡ፦ ታውፋንያ የተባለ ከመካከላቸው አንዱ የእመቤታችንን ስጋ ከሐዋርያት እጅ ለመንጠቅ የአልጋውን ሸንኮር ጨበጠ። ያን ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ የታውፋንያን እጆች በሰይፍ ቀጣቸው ያሉት ክቡር ሥራ አስኪያጁ ፦ እጆቹም በአልጋው ሸንኮር ላይ ተንጠልጥለው እንደቀሩ ገልጠው የምሕረት እናት ድንግል ማርያም በምልጃዋ እጆቹ እንደነበሩ እንዲሆኑለት እንዳደረገች አንስተዋል። ክቡር ሥራ አስኪናጁ አክለውም የእመቤታችን ስጋዋን መላእክት በገነት አኖሩት የምስጢር ሐዋርያ የተባለ ቅዱስ ዮሐንስ ይህን አየ፤ ሐዋርያት ቅዱስ ዮሐንስ ያየውን ምስጢር እነርሱም ያዩ ዘንድ ሽተው ከነሐሴ ፩ ጀምረው በጾምና በጸሎት ሱባኤ ያዙ በሁለተኛው ሱባኤ ማብቂያ ጌታችን የድንግል ማርያም ስጋዋን አምጥቶ ሰጣቸው። እነርሱም በጌቴሴማኒ መቃብር አክብረው ቀበሩት፦ ድንግል ማርያም ሞት ይዟት አልቀረም በ፫ኛው ቀን በልጇ ጥሪ በክብር ተነሳች እንደ ልጇ ትንሣኤ ተነሥታም ዐረገች እንጂ ብለዋል። ሐዋርያው ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለሰ በመንገድ የድንግል ዕርገቷን እንዳየ አንስተው ቀድሞ ከልጅሽ ትንሣኤ ተለየሁ ተጠራጣሪም ተባልሁ አንቺስ ከበረከተ ትንሣኤሽ ለምን ከለከልሽ ባላት ጊዜ አንተ ያየኸውን ያየ የለም ሒድ ወደ ሐዋርያት ትንሣኤና ዕርገቴን ንገራቸው አለችው ሰበኗንም ምስክር ይሆነው ዘንድ ሰጠችው ሲሉም ገልጠዋል። ሐዋርያው ቶማስ ወደ ሐዋርያቱ ሔዶ እንደጠየቃቸው ሰበኗንም እንዳሳያቸው በዓመቱ ሐዋርያት ቶማስ ያየውን የእመቤታችንን ዕርገት ለማየት ነሐሴ ፩ ቀን ሱባኤ እንደጀመሩ በ፲፮ኛው ቀን የሐዋርያትን ሱባኤ ልጇ እንደተቀበለ ቀድሶ እንዳቆረባቸው ገልጠዋል፤ በሐዋርያቱ ሱባኤ የተገለጠውን የእግዚአብሔርን ቸርነት አብራርተዋል። የእመቤታችን ትንሣኤ እና ዕርገት ሲነገር ግራ ሊገባን አይገባም ያሉት ክቡር መጋቤ ሐዲስ በእግዚአብሔር ፊት ያረጉ ሄኖክና ኤልያስን አውስተው በሰፊው አስረድተዋል። እኛም የሐዋርቱን ጾም ጾመን፦ ቅዱስ ዮሐንስ ያየውን ክብሯን፣ ቅዱስ ቶማስ ያየውን ትንሣኤዋን እንድናይ ናፍቀን በዚህ ቅዱስ ስፍራ ተሰብሰበናልና ከዚህ የቅድስና አምባ ያገኘነውን ሰላምና በረከት ተመልሰን ስንሔድ መጠበቅ ይገባናል ሲሉ አሳስበዋል። በክብረ በዓሉ ላይ የደብሩ ሊቃውንት እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤት ዘማርያን በዓሉን በገለጠ ወረብ አመስግነዋል። ላእከ ኄራን በቀለ ደመረ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ምክትል ሥራ አስኪያጅን ጨምሮ የሀገረ ስብከቱ ልኡካን፣ መልአከ አርያም ኃይለማርያም ማለደ የደብሩ ዋና አስተዳዳሪ ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በዓሉን ለማክበር ከተለያዩ ቦታዎች የመጡ ምእመናን በክብረ በዓሉ ላይ ተገኝተዋል። ፎቶ፦ ሚክያስ ዐቢይ

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ እርገት በደብረ ብርሃን ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ አባታው ቡራኬ ተከቀረ!! ነሐሴ ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም(አቡቀለምሲስ:ደብረ ብርሃን) ⛪️⛪️⛪️ ⛪️ ⛪️⛪️ ⛪️⛪️ ⛪️⛪️ ⛪️⛪️⛪️ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ዕርገት በደብረ ብርሃን ከተማ ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ እና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ አባታዊ ቡራኬ በድምቀት ተከብሯል!! በክብረ በዓሉ ላይ መራኄ ሊቃውንት ያዕቆብ ተክለ አረጋዊ የጠባሴ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የአራቱ ጉባኤያት መምህር «ከሚያልፈው ወደማያልፈው ፈለሰች” የሚለውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ኃይለ ቃል መነሻ በማድረግ ሰፊ ትምህረተ ወንጌል ሰጥተዋል።

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ዕርገት በደብረ ብርሃን ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ አባታው ቡራኬ ተከበረ። ነሐሴ ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም(አቡቀለምሲስ:ደብረ ብርሃን) ⛪️⛪️⛪️ ⛪️ ⛪️⛪️ ⛪️⛪️ ⛪️⛪️ ⛪️⛪️⛪️ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ዕርገት በደብረ ብርሃን ከተማ ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ እና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ አባታዊ ቡራኬ በድምቀት ተከብሯል!! በክብረ በዓሉ ላይ መራሔ ሊቃውንት ያዕቆብ ተክለ አረጋዊ የጠባሴ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የአራቱ ጉባኤያት መምህር «ከሚያልፈው ወደማያልፈው ፈለሰች” የሚል ኃይለ ቃል መነሻ በማድረግ ሰፊ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል።

"በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች" መዝ.፵፬÷፱ እንኳን ለእመቤታችን የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ++++++++++++++ በነገረ ማርያም ላይ ተጽፎ እንደምናገኘው እመቤታችን ፷፬ ዓመት በሞላት ጊዜ ልጇ ወዳጇ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከኃላፊው ዓለም ወደማያልፈው ሰማያዊውና ዘለዓለማዊው ዓለም እንደሚወስዳት ነገራት፤ በጥር ፳፩ ቀንም በልጇ ፈቃድ በይባቤ መላእክት ነፍሷ ከሥጋዋ ተለየች። ሊቁ ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ "የሕይወት ደም ግባት የአምላክ እናት ከሊባኖስ ውጪ፤ ፍቅርሽ የቀና ነው፤ ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ፤ የመለኮት ማደሪያ ሰላምታ ላንቺ ይገባል፤ የአምላክ እናት ማርያም ሆይ ልጅሽ ወደ ዘላለማዊ ሕይወትና ወደ ክብር መንግሥት ይጠራሻል" በማለት ስለ ዕረፍቷ በምሥጢር ይናገራል። ቅዱሳን ሐዋርያትም በአምላክ እናት ሥጋ ፊት ምስጋናን እያሰሙ እየዘመሩ በክብር ገንዘው በጌቴሴማኔ በመቃብር ሥፍራ ቅዱስ ሥጋዋን አሳርፈዋል። ጌታችንም ቅዱስ ሥጋዋን ከዮሐንስ ጋር በደመና ነጥቆ በገነት በሕይወት ዛፍ ሥር አኑሯታል። ቅዱስ ዮሐንም ለቅዱሳን ሐዋርያቱ በዕፀ ሕይወት ሥር ማረፏን በነገራቸው ጊዜ እኛ ይህን ምሥጢር ሳናይ ብለው በነሐሴ ፩ ሱባኤ እንደጀመሩ በ፲፬ኛው ቀንም ጌታችን የእናቱን ሥጋ አምጥቶ ሰጥቷቸው በጌቴሴማኔ እንደቀበሯት መጽሐፍት ይነግሩናል። ኋላም በልጇ ሥልጣን የቅድስት ድንግል ማርያም ነፍሷና ሥጋዋ ተዋሕደው በተወደደች እለት ነሐሴ 16 ከሞት ተነስታለች በክብር አርጋለች። ነሐሴ ፲፮ ቀን አስደናቂውን የእመቤታችንን የዕርገቷን በዓል ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን በማኅሌት፣ በቅዳሴ አንዲሁም በዝማሬ በታላቅ ድምቀት ታከብረዋለች። ከእናቷ ማሕፀን ጀምራ በመንፈስ ቅዱስ የተጠበቀች አዳማዊ ኀጢአት ያላገኛት፤ ኀጢአት አልባ የኾነች እንዲያውም አዳምና ሔዋን ይኽነን መርገም ከመስማታቸው በፊት ከነበራቸው ንጽሕና የበለጠ ንጽሕናን ገንዘብ ያደረገች ናትና በመቃብር አልቀረችም ልጇ ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሣ የመቅደሱ ታቦት ቅድስት ድንግልም በልጇ ሥልጣን ከሞት ተነሥታ በሰማይ አለች፡፡ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃ በረከት የእናትነት ፍቅሯ ከሁላችን አይለየን ከትንሣኤዋ ከዕርገቷ በረከት ታሳትፈን!!! መልካም በዓል!