uz
Feedback
Sheger Press️️

Sheger Press️️

Kanalga Telegram’da o‘tish

Official channel of sheger press Contact @Birukepromo

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Sheger Press️️ analitikasi

Sheger Press️️ (@sheger_press) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 36 089 obunachidan iborat bo'lib, Yangiliklar & Media toifasida 7 127-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 921-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 36 089 obunachiga ega bo‘ldi.

17 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -535 ga, so‘nggi 24 soatda esa -7 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 18.88% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 12.97% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 6 814 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 4 681 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 30 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Official channel of sheger press Contact @Birukepromo

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 18 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Yangiliklar & Media toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

36 089
Obunachilar
-724 soatlar
-667 kunlar
-53530 kunlar
Postlar arxiv
ከኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ የተላከ 63 ኪሎ ግራም ጫት ተያዘ የዩናይትድ ስቴትስ የጉምሩክ እና የድንበር ጥበቃ መኮንኖች ሐሙስ ጁን 4 ቀን በዋሽንግተን ዱለስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በስተርሊንግ የግብርና ስፔሻሊስቶች ወደ ሳክራሜንቶ ፣ ካሊፎርኒያ የሚጓዘውን የአየር ጭነት ከመረመሩ በኋላ ጫቱ መያዙን ባለሥልጣናቱ አስታወቁ። የጉዞው ዋጋ ወደ 17,000 ዶላር የሚገመት ጫት መሆኑን ገልፀዋል። ጭነቱ በተለያዩ ቅመማ ቅመሞች ውስጥ የተሸሸገ ሲሆን በ102 ሣጥኖች ውስጥ የተካተተ መሆኑን ኃላፊዎቹ ተናግረዋል። ጫት በተለምዶ በምስራቅ አፍሪካ እና በአረብ ባሕረ ገብ መሬት ይበቅላ። አንዳንድ ተጠቃሚዎች አበረታች ሻይ ለማዘጋጀት የደረቁ የጫት ቅጠሎችን ያፈላሉ። እፅዋቱ ካቲኖን እና ካቲን የተባሉ ሁለት የማዕከላዊ የነርቭ ሥርዓት አነቃቂዎች እንደያዘ አሜሪካ ማስታወቋን ዳጉ ጆርናል ዘግቧል። የፌደራል ባለስልጣናት እንዳሉት ጫት መነቃቃት ይፈጥራል፣ የምግብ ፍላጎት መቀነስ፣ የመተንፈስ ችግር፣ የደም ግፊት መጨመር እና የልብ ምት መጨመር ያስከትላል። የዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ ወደብ ዳይሬክተር የሆኑት ክሪስቲን ዋው "ጫት ወደ አሜሪካ እንዳይገባ ተከልክሏል ያሉ ሲሆን ምክንያቱም በውስጡ ያሉት የኬሚካል ንጥረነገሮች ቁጥጥር የሚደረግባቸው ንጥረ ነገሮች ናቸው" ብለዋል።

የሊቀ መላእክት  ቅዱስ ሚካኤል ረድኤቱ እና ምልጃው አይለየን !!! ድርሳነ ሩፋኤል ላይ ተጽፎ እደምናገኘው 7 ሊቃነ መላዕክት ሲኖሩ አለቃቸው ቅዱስ ሚካኤል ነው፤ የስሙ ትርጓሜም “እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው” ማለት ነው። ከእግዚአብሔር ዙፋን ስር ትዕዛዝ በወጣ ግዜ ኪሩቤል ተቀብለው ለሱራፌል ያስተላልፋሉ፤ ሱራፌልም ለሚካኤልና ለገብርኤል ለሩፋኤልም ያደርሳሉ፡፡ ሚካኤል ለፍጥረቱ በጎም ይሁን ክፉ ትዕዛዙን ይፈጽሙ ዘንድ መላዕክትን ያዛቸዋል፤ ኪሩቤልና ሱራፌል መላዕክቱም ሁሉ አቤቱ የእጅህን ስራ አታጥፋ እያሉ ቀንና ከማታ ይለምናሉ። የመላዕክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ከዲያቢሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ እግዚአብሔር ይገስፅህ አለው እንጂ የስድብን ቃል አልተናገረውም ሲባል ሰምተናል፡፡ ሊቀ ነብያት ሙሴ እጅግ ታዛዥና የዋህ ስለነበርና ከንዓንን ለማየት ወደ ናባው ተራራ ሲወጣ 2 መላዕክት በአረጋውያን ተመስለው መቃብር ሲቆፍሩ ቢያይ ላግዛቹ ብሎ መቆፈሪያውን ተቀበላቸው፡፡ በመጨረሻ “ሰውየው በአንተ ልክ ነውና እስቲ ገብተህ ለካልን” አሉት፡፡ እሱም በየዋህነቱ ጉድጓዱ ውስጥ ገብቶ እንደተኛ እንደ እንቅልፍ አሸልቦት በዚያው ዐረፈ፤ መላዕክቱም ቀበሩት። እስራኤላዊያን ሙሴን እጅግ ስለሚወዱት የሙሴን መቃብር እንደ ጣዖት እንዳያመልኩት እግዚአብሔር የሙሴን መቃብር ሰወረው፤ ነገር ግን ጠላት ዲያቢሎስ ሊያሳያቸው በመነሳቱ ቅዱስ ሚካኤል ተቃወመው፡፡ በመጨረሻም ቅዱስ ሚካኤል ዲያቢሎስን እግዚአብሔር ይገስጽህ ብሎ ከእርሱም ሰወረበት። በሐዋርያው ይሁዳ መልዕክት ቁጥር 8 የሚገኘው ቃል የቅዱስ ሚካኤልን ትዕግስት ያሳያል፡፡ ዳግመኛም አይሁድ ጌታን ሲሰቅሉት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በቁጣ ሰይፉን አወጣ፤ ቅዱስ ሚካኤል ግን በአይሁድ ስራ አዝኖ ፈጣሪን ፍጡራን ሰቀሉት እያለ በአርምሞና በትዕግስት አያቸው ይላል ድርሳኑ። ቅዱስ ሚካኤል ሰኔ 12 ቀን ዲያቢሎስን አሸንፎ በምትኩ ሊቀ መላዕክት ሆኖ የተሾመበትና አፎምያንም የረዳበት ቀን ስለሆነ በታላቅ ሥርዓት ይከበራል። ህዳር 12 ሕዝበ እስራኤልን በክንፎቹ ጥላ ከበረሃው ፀሐይ ከልሎ ከግብጽ ምድር እየመራና እየጠበቀ ከንዓን ያገባቸው እለት ነው። መላዕክቱ በክንፋቸው የእግዚአብሔር ስም ስለተፃፈበት ህዝቡን ይጠብቃሉ፤ የመላዕክቱን ስም የመጨረሻውን ፊደል ስናይ ኤል ብሎ ይጨርሳል፡፡ ሚካ-ኤል ገብር-ኤል ኡራ-ኤል፡፡ ይህም “ስሜ በሱ ላይ ነውና” እንደሚል የእግዚአብሔር የምህረት ስም ስለሆነና በክንፎቻቸው ስለተፃፉ መላዕክቱ ይጠብቁናል። “በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለአንተ ያዛቸዋል፤ እግርህም በድንጋይ እንዳይሰናከል በእጆቻቸው ያነሱሃል” ተብሎም በመዝሙር 90÷11 ተጽፋልና አህዛብን ጭምር ያለጊዜያቸው እንዳይሞቱ መላዕክት ይጠብቋቸዋል!!! ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 33÷7 “የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል” ይለናል፡፡ በትንቢተ ዳንኤል 10÷13 እና 10÷21 ደግሞ የስሙ ትርጉም እግዚአብሔር ዳኛዬ ነው የተባለው ነብዩ ቅዱስ ዳንኤልም ስለ ቅቅዱስ ሚካኤል እንዲህ ሲናገር ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፣ በተዘጋ ጉድጓድ ሲያጽናናው ደግሞ “ከሚካኤል በቀር የሚያጽናናኝ የለም” አለ፡፡ በዓለም ፍፃሜም ስለህዝቡ የሚቆመው ሚካኤል ይነሳል። በማለትረ በምዕራፍ 12÷1 ጽፎልናል፡፡ በራዕይ 8÷3 “የቅዱሳኑ ፀሎት ከዕጣኑ ጢስ ጋር ከመልአኩ እጅ ወደ እግዚአብሔር ፊት ወጣ” ተብሎ እንደተጻፈውም መላዕክት የቅዱሳኑን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ያሳርጋሉ፡፡ ገዳማውያን የሚያደርጉት ጸሎትና የሚያቀርቡት መስዋዕት በእርሱ ምልጃ ያርጋልና ገዳማቸውን እየረዳን በዓታቸውን እያጠናን የበረከታቸው ተካፋይ እንሁን፡፡ ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 1000442598391 ወይም አቢሲኒያ ባንክ 141029444 የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

photo content

የፋርማሲ ተማሪዎች ቅሬታ‼️ የፋርማሲ መውጫ ፈተና (Exit Exam) ተፈታኞች ፈተናው አስቀድሞ ተሰርቋል በማለት ቅሬታ አቀረቡ፤ የሚመለከተው አካል ማብራሪያ እንዲሰጥም ጠይቀዋል። ሰኔ 10 ቀን 20
+1
የፋርማሲ ተማሪዎች ቅሬታ‼️ የፋርማሲ መውጫ ፈተና (Exit Exam) ተፈታኞች ፈተናው አስቀድሞ ተሰርቋል በማለት ቅሬታ አቀረቡ፤ የሚመለከተው አካል ማብራሪያ እንዲሰጥም ጠይቀዋል። ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም የተሰጠው የፋርማሲ ትምህርት ክፍል ብሔራዊ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) አስቀድሞ ተሰርቆ ለተወሰኑ ተማሪዎች ተሰራጭቷል ሲሉ ተፈታኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። ቅሬታ አቅራቢዎቹ ተማሪዎች እንዳሉት፤ ለፈተናው በርካታ ልፋትና ዝግጅት ቢያደርጉም፣ ኃላፊነት በማይሰማቸው አካላት አማካኝነት ፈተናው ቀድሞ ወጥቶ መሰራጨቱን የሚያሳዩ መረጃዎች እንደደረሷቸው ገልጸዋል። ይህ መሆኑም በከፍተኛ ጥረትና በራሳቸው ልፋት የተፈተኑ ተማሪዎችን ስነ-ልቦና በእጅጉ የጎዳና ፍትሃዊነትን ያጓደለ ተግባር መሆኑን ጠቁመዋል። ተፈታኞቹ አያይዘውም፣ ጉዳዩ በሚመለከታቸው አካላት ትምህርት ሚኒስቴርና የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም በኢትዮጵያ ፋርማሲስቶች ማህበር (EPA) በኩል በአስቸኳይ ታይቶ፣ አስፈላጊው ማጣሪያ እንዲደረግና ተገቢው ምላሽ እንዲሰጣቸው በትህትና ጠይቀዋል።

ያቀደውን ባለማሳከቱ ስልጣኑን ለቀቀ‼️ የታቀደውን 10% ብቻ ስላሳካን ስልጣን ለቀናል !" የኢኳቶሪያል ጊኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ከነካቢኒያቸው በጋራ ውሳኔ ሥልጣን ለቀቀ። አስገራሚና ያልተጠበቀ ዜና ከ
ያቀደውን ባለማሳከቱ ስልጣኑን ለቀቀ‼️ የታቀደውን 10% ብቻ ስላሳካን ስልጣን ለቀናል !"  የኢኳቶሪያል ጊኒ  ጠቅላይ ሚኒስትር ከነካቢኒያቸው  በጋራ ውሳኔ ሥልጣን ለቀቀ። አስገራሚና ያልተጠበቀ ዜና ከኢኳቶሪያል ጊኒ! የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ማኑኤል ኦሳ ኑሱኤ ኑሱኤ፣ ከመላው የሚኒስትሮች ካቢኔ አባላት ጋር በመሆን፣ "የተቀመጠለትን ሀገራዊ ግብ ማሳካት አልቻልንም" በሚል በጋራ ውሳኔ የመልቀቂያ ደብዳቤያቸውን ለፕሬዝዳንቱ አቅርበዋል። ከጀርባው ስላለው አስገራሚ ምክንያት እና ስለ ሀገሪቱ የረጅም ዘመን አገዛዝ ማወቅ ያለባችሁ ዋና ዋና ነጥቦች፦ 📉 "10 በመቶ ብቻ!"፦ የፕሬዝዳንቱ ልጅ እና የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ቴዎዶሮ ንጉማ ኦቢያንግ ማንጌ እንዳስታወቁት፣ መንግሥት ሥልጣን የለቀቀው ካቢኔው እንዲያሳካ ከተቀመጡለት ሀገራዊ ግቦች ውስጥ እስካሁን ማሳካት የቻለው 10 በመቶውን ብቻ በመሆኑ ነው። 🏗️ የገዢው ፓርቲ ምላሽ፦ የሀገሪቱ ገዢ ፓርቲ (PDGE) በበኩሉ፣ ይህ የጅምላ መልቀቅ መንግሥታዊ መዋቅርን ለማሻሻልና አዳዲስ ቅድሚያ ለሚሰጣቸው የመሠረተ ልማት እና የኢኮኖሚ ልማት ሥራዎች ምላሽ ለመስጠት የተደረገ “ተቋማዊ መልሶ ማደራጀት” መሆኑን ገልጿል።

ቅዱስ ሚካኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ!!! መልአኩም በመሠዊያው ነበልባል ውስጥ ወደ ሰማይ ዐረገ በጾርዓ ከተማ የሚኖር፣ ከዳን ወገን የሆነና ሚስቱም መካን የነበረች ማኑሄ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፡፡ የእግዚአብሔር መልአክም ለሴቲቱ ተገልጦ “እነሆ ትጸንሻለሽ፤ አሁንም ተጠንቀቂ፤ የወይን ጠጅን የሚያሰክርም ነገር አትጠጪ፥ ርኩስም ነገር አትብዪ፤ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፤ ልጁም ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ለእግዚአብሔር የተለየ ናዝራዊ ይሆናልና በራሱ ላይ ምላጭ አይድረስበት፤ እርሱም እስራኤልን ከፍልስጥኤማውያን እጅ ማዳን ይጀምራል” አላት። ሴቲቱም ለባልዋ የሆነውን ሁሉ ነገረችው፡፡ ማኑሄም የተላከው ሰው ዳግመኛ ወደኛ ይምጣ፤ ብሎ ወደ እግዚአብሔር ለመነ። እግዚአብሔርም የማኑሄን ድምፅ ሰማ፤ መልአኩም ሴቲቱ በእርሻ ውስጥ ተቀምጣ ሳለች እንደገና ተገለጠላት፤ ማኑሄ ግን አልነበረም። ሴቲቱም ፈጥና ሮጠች፤ ባልዋንም ጠራችው። ማኑሄም “ከዚህች ሴት ጋር የተነጋገርህ አንተ ነህን? ቃልህ በደረሰ ጊዜ የልጁ ሥርዓት ምንድን ነው? አለው። መልአኩም ማኑሄን “ሴቲቱ ከነገርኋት ሁሉ ትጠንቀቅ፣ በማለት ለሴቲቱ የነገራትን ደገመለት፡፡ ማኑሔም “የፍየል ጠቦት እስክናዘጋጅልህ ድረስ፤ እባክህ ቆይ” አለው። መልአኩም የሚቃጠለውንም መሥዋዕት ማዘጋጀት ብትወድድ ለእግዚአብሔር አቅርበው” አለው። ማኑሄም “ነገርህ በደረሰ ጊዜ እንድናከብርህ ስምህ ማን ነው?” አለው፡፡ መልአኩ “ስሜ ድንቅ ነውና ለምን ትጠይቃለህ?” ብሎ መለሰለት። ማኑሄም የፍየሉን ጠቦትና የእህሉን ቍርባን ወስዶ በድንጋይ ላይ ለእግዚአብሔር አቀረበው። መልአኩም በመሠዊያው ነበልባል ውስጥ ወደ ሰማይ ዐረገ፤ ማኑሄና ሚስቱም በግምባራቸው በምድር ተደፉ። ማኑሄም የእግዚአብሔር መልአክ መሆኑን አወቀ። ሶምሶን ከተወለደ በኋላም የእግዚአብሔርም መንፈስ በጾርዓና በኤሽታኦል መካከል ባለው በዳን ሰፈር ውስጥ ሊያነቃቃው ጀመረ። ይህ ሶምሶንና ወላጆቹን የረዳው ኃያሉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ ታላቁ አለቃ ቅዱስ  ሚካኤል ዛሬም ገዳማውያንን በተጋድሏቸው ሁሉ እየተራዳ አብሯቸው ይኖራል፡፡ ስለ ክርስቶስ ፍቅር ዓለምን ትተው ወጥተዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡ ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 1000442598391 ወይም አቢሲኒያ ባንክ 141029444 ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957

photo content

የአክሱም ዩኒቨርስቲ ሆስፒታል በአምስት ቀናት ውስጥ የማህፀን መውጣት ላጋጠማቸው 50 እናቶች ነፃ ህክምና እንደሚሰጥ አስታወቀ   የማህፀን መውረድ ወይም የማህፀን ወደ ውጪ መውጣት የሚከሰትባቸው በርካታ ምክንያቶች ቢኖሩም እናቶች ደጋግመዉ ልጆችን መውለዳቸው፣ የአመጋገብ ሁኔታቸው ዝቅተኛ መሆን እና በቤት ውስጥ እንደ ሸክም ያሉ ከባድ ስራዎችን መስራታቸው ለዚህ ተጋላጭ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል።የእናቶች እድሜ መጨመርን ተከትሎ  የሆርሞን መቀነስ ስለሚፈጠር ማህፀን አካባቢ ያሉ ጡንቻዎች መላላት ስለሚያጋጥማቸው  ማህፀን ወደ ውጪ ይወጣል።   ይህንን ሁኔታ በቀዶ ህክምና ማስተካከል እንደሚቻል  የአክሱም ዩኒቨርስቲ የማህፀን እና ፅንስ እስፔሻሊስት እንዲሁም በዩኒቨርስቲዉ የማህፀን እና ፅንስ ትምህርት ክፍል ኃላፊ ዶክተር ሙሉ ዳኜ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸዉ ቆይታ ተናግረዋል፡፡የአክሱም ዩኒቨርስቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝ ሆስፒታል ከዊንግስ ኦፍ ሂሊንግስ ከሚባል ድርጅት ጋር  በመተባበር  የማህፀን ወደ ውጪ የመውጣት ችግር ላጋጠማቸው 50 እናቶች ነፃ ህክምና እየሰጠ ይገኛል።   የነፃ ህክምና አገልግሎቱ እስከ ሰኔ 12 ቀን ድረስ እንደሚቆይ የገለፁት ዶክተር ሙሉ ለቀዶ ህክምና የሚያስፈልጉ መሳሪያዎችን ዊንግስ ኦፍ ሂሊንግስ መለገሱን አክለዋል።በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ለ50 እናቶች የህክምና አገልግሎትን ለመስጠት ቢታቀድም በትራንስፖርት እጥረት ሳቢያ  የታካሚዎች ቁጥር  በሚፈለገው ልክ አለመሆኑን  ዶክተር ሙሉ ከጣቢያችን ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀዋል።

ሊቀ መልእክት ቅዱስ ሚካኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ🙏 የስሙ ትርጓሜም “እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው” ማለት ሲሆን የ7 ሊቃነ መላዕክት አለቃቸው ነው ቅዱ ሚካኤል። ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 33÷7 “የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል” ይለናል፡፡ ከእግዚአብሔር ዙፋን ስር ትዕዛዝ በወጣ ግዜ ኪሩቤል ተቀብለው ለሱራፌል ያስተላልፋሉ፤ ሱራፌልም ለሚካኤልና ለገብርኤል ለሩፋኤልም ያደርሳሉ፡፡ ሚካኤል ለፍጥረቱ በጎም ይሁን ክፉ ትዕዛዙን ይፈጽሙ ዘንድ መላዕክትን ያዛቸዋል፤ መላዕክቱም ሁሉ አቤቱ የእጅህን ስራ አታጥፋ እያሉ ቀንና ከማታ ይለምናሉ። በዓለም ፍፃሜም ስለህዝቡ የሚቆመው ሚካኤል ይነሳል። በማለት በምዕራፍ 12÷1 ጽፎልናል፡፡ በራዕይ 8÷3 “የቅዱሳኑ ፀሎት ከዕጣኑ ጢስ ጋር ከመልአኩ እጅ ወደ እግዚአብሔር ፊት ወጣ” ተብሎ እንደተጻፈውም መላዕክት የቅዱሳኑን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ያሳርጋሉ፡፡ አይሁድ ጌታን ሲሰቅሉት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በአይሁድ ስራ አዝኖ በቁጣ ሰይፉን አወጣ፤ ቅዱስ ሚካኤል ግን በእግዚአብሔር ትዕግስት ተገርሞ፣ ፈጣሪን ፍጡራን ሰቀሉት እያለ በአርምሞና በትዕግስት አያቸው ይላል ድርሳኑ። ቅዱስ ሚካኤል ሰኔ 12 ቀን ዲያቢሎስን አሸንፎ በምትኩ ሊቀ መላዕክት ሆኖ የተሾመበትና አፎምያንም የረዳበት ቀን ስለሆነ በታላቅ ሥርዓት ይከበራል። ህዳር 12 ሕዝበ እስራኤልን በክንፎቹ ጥላ ከበረሃው ፀሐይ ከልሎ ከግብጽ ምድር እየመራና እየጠበቀ ከንዓን ያገባበት ዕለት ነው። መላዕክቱ በክንፋቸው የእግዚአብሔር ስም ስለተፃፈበት ህዝቡን ይጠብቃሉ፤ የመላዕክቱን ስም የመጨረሻውን ፊደል ስናይ ኤል ብሎ ይጨርሳል፡፡ ሚካ-ኤል ገብር-ኤል ኡራ-ኤል፡፡ ይህም “ስሜ በሱ ላይ ነውና” እንደሚል የእግዚአብሔር የምህረት ስም ስለሆነና በክንፎቻቸው ስለተፃፉ መላዕክቱ ይጠብቁናል። “በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለአንተ ያዛቸዋል፤ እግርህም በድንጋይ እንዳይሰናከል በእጆቻቸው ያነሱሃል” ተብሎም በመዝሙር 90÷11 ተጽፋልና አህዛብን ጭምር ያለጊዜያቸው እንዳይሞቱ መላዕክት ይጠብቋቸዋል፡፡ በትንቢተ ዳንኤል 10÷13 እና 10÷21 ደግሞ የስሙ ትርጉም እግዚአብሔር ዳኛዬ ነው የተባለው ነብዩ ቅዱስ ዳንኤልም ስለ ቅዱስ ሚካኤል እንዲህ ሲናገር ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፣ በተዘጋ ጉድጓድ ሲያጽናናው ደግሞ “ከሚካኤል በቀር የሚያጽናናኝ የለም” አለ፡፡ ገዳማውያን የሚያደርጉት ጸሎትና የሚያቀርቡት መስዋዕት በእርሱ ምልጃ ያርጋልና ገዳማቸውን እየረዳን በዓታቸውን እያጠናን የበረከታቸው ተካፋይ እንሁን፡፡ ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 1000442598391 ወይም አቢሲኒያ ባንክ 141029444 የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

photo content

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቺ ከአሜሪካ ጋር የሰላም ስምምነት ላይ ለመድረስ እስራኤል ጦሯን ከሊባኖስ ማስወጣት እንደሚኖርባት ዳግም አሳሰቡ   የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት፣ እስራኤል በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት በዘላቂነት ለማቆም የሚደረገውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ልታደናቅፍ ትችላለች የሚል ስጋት እየጨመረ በመጣበት ወቅት ነው። ዶናልድ ትራምፕ ሳይቀሩ፣ የጦርነት አጋራቸው የሆነችውን እስራኤልን “ኃላፊነት የጎደለው እርምጃ እየወሰደች ነው” በማለት ተችተዋታል።   የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቺ በሰጡት መግለጫ፣ “የእስራኤል ጦር በዚህ ጦርነት ወቅት ከተቆጣጠራቸው ግዛቶች ሳይወጣ፣ ጦርነቱ ሙሉ በሙሉ አብቅቷል ሊባል አይችልም” ብለዋል። የሂዝቦላህ የሚዲያ ግንኙነት ኃላፊም እንደገለጹት፣ ኢራን ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው ቀጣይ የውይይት ምዕራፍ ላይ የእስራኤል ጦር ከሊባኖስ እንዲወጣ ጥያቄ እንደምታቀርብ ለቡድኑ ማረጋገጫ ሰጥታለች።   እነዚህ አስተያየቶች የተሰሙት ዶናልድ ትራምፕ በፈረንሳይ ኤቪያን በተካሄደው የቡድን 7  መሪዎች ጉባኤ ላይ የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁን በጠንካራ ቃላት በወቀሱበት ወቅት ነው። ትራምፕ ኔታንያሁ “በሊባኖስ ረገድ የበለጠ ኃላፊነት በተሞላበት መንገድ መንቀሳቀስ አለባቸው” ያሉ ሲሆን፣ በቅርቡ እስራኤል በቤሩት ላይ የፈጸመችውን የቦምብ ጥቃት “አረመኔያዊ” ሲሉ ጠርተውታል።   ትራምፕ አክለውም፣ “እስራኤል ከሂዝቦላህ ጋር ለረዥም ጊዜ ስትዋጋ ቆይታለች፣ በዚህም ምክንያት በጣም ብዙ ሰዎች እየተገደሉ ነው” ብለዋል። “አንድን የምትፈልጉትን ሰው ለማደን ስትሉ የመኖሪያ ህንፃን ማፍረስ የለባችሁም፤ ምክንያቱም በእነዚያ ህንፃዎች ውስጥ ብዙ ሰዎች አሉ። ሁሉም ደግሞ የሂዝቦላህ አባላት አይደሉም፣ ይህንን በእርግጠኝነት ልነግራችሁ እችላለሁ” ሲሉ ተናግረዋል።   የሶሪያ መንግስት ከሂዝቦላህ ጋር “በመገናኘት” ረገድ የተሻለ ስራ ሊሰራ እንደሚችልም ጠቁመዋል። ደማስቆ በሶሪያ የእርስ በርስ ጦርነት ወቅት ከሂዝቦላህ ጋር የተዋጉ የቀድሞ አማፂያን የሚመሩት ቢሆንም፣ አሁን ያለው መንግስት ግን መረጋጋትን ይፈልጋል።   ትራምፕ ከኔታንያሁ ጋር “ለማመን የሚያስቸግር የግል ግንኙነት” እንዳላቸው ቢገልጹም፣ አሁን ያለውን ውጊያ ግን ከኢራን ጋር ከተደረገው ስምምነት አንፃር ሲመዘን “እንደ ጥቃቅን ነገር” ነው የቆጠሩት። የትራምፕ አስተያየት እንደሚያሳየው እስራኤል የተኩስ አቁም ስምምነትን ለመቀበል ፍቃደኛ አለመሆኗ እና ከኢራን ጋር ለተደራደሩት የ60 ቀናት የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እየደገነችው ያለው አደጋ ትዕግስታቸውን እየተፈታተነው  ይመስላል።   “ያለ አሜሪካ፣ ያለ እኔ፣ እስራኤል አትኖርም ነበር፤ ምክንያቱም እኔ ያደረግኩትን ለማድረግ የተዘጋጀ ሌላ ፕሬዝዳንት የለም” ብለዋል።  የእስራኤል እርምጃ በሰላም እቅዱ ላይ የደገነው ስጋት የአውሮፓ መሪዎችን ስለ ስምምነቱ ዘላቂነት ያላቸውን ስጋትት አጠናክሮታል።  

መድኃኔአለም በሐጢዓት ፈተና ተጠልፎ ከመውደቅ ይጠብቀን🙏 እግዚአብሔር እስራኤልን ከደመና መና አውርዶ፣ ከአለት ውሀ አፍልቆ መገባቸው፡፡ እነርሱ ግን እዚህ ደጋ ላይ ቢሆንለት የውርጭ ሰደቃ እያበጀ፣ ውሀውን እያረጋ፣ መና መገብኳችሁ ይላል እንጅ ቆላ ቢሆነማ ባልተቻለውም ነበር ብለዋል። የርሱን ከሃሊነት፣ የእነርሱንም ሀሰት ሊገልጥ ቢወድ፣ ሙሴን የውሃ ምንጭ የሌለበት በረሐ ይዘሀቸው ሂድ ብሎት በዚያም መናው ወርዶላቸዋል፣ ውሀውም ፈልቆላቸዋል። ነገር ግን ነዘር የሚባል እባብ እየነከሰ ይፈጃቸው ጀመር። በዚህ ጊዜ ከሙሴ ዘንድ ሂደው ከጌታ ምህረት ቸርነት ከእኛ ኃጢአት አይታጣም በእግዚአብሔርና በአንተ ላይ ተናግረን በድለናል እባቦችን እንዲያርቅልን ወደ እግዚአብሔር አመልክትልን አሉት። ሙሴም ወደ እግዚአብሔር ቢጸልይ ከንጹህ ነሐስ የእባብ ምስል ሠርተህ ከሚገናኙበት አደባባይ ከእንጨት ላይ ስቀልላቸው አለው። እንደተባለው ቢያደርግ እባብም የነደፈችው ሰው ሁሉ የነሐሱን እባብ ባየ ጊዜ ዳነ። “ሙሴ እባብን በምድረ በዳ እንደሰቀለው የሰው ልጅ ክርስቶስ ይሰቀል ዘንድ አለው” ተብሎ በዮሐንስ 3÷14 እንደተነገረ፡፡ አባቶቻችንም በትርጓሜ ወንጌል የበረሐው እባብ የዲያብሎስ፤ የብረቱ እባብ የጌታ ምሳሌ ነው። በእባብ መርዝ እንዳለበት በዲያብሎስም ፍዳ ኃጢአት አለበት። በነሐሱ እባብ መርዝ እንደሌለበት በጌታም ፍዳ ኃጢአት የለበትም። የነሐሱ እባብ በእባብ አምሳል መሰቀሉ ጌታ እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ለመሰቀሉ ምሳሌ ነው።  ክርስቶስ ኢየሱስ በመስቀል በተሰቀለ ጊዜ፤ የተሰቀለው የክብር ባለቤት ሰማይን የፈጠረ ነውና ፀሐይ ጨልማለች፣ ጨረቃ ደም ሆኗል፣ ከዋክብት ረግፈዋል። ገዳማውያኑም በመስቀል የተደረገልንን ማዳን እያሰቡ ዓለምን ንቀው፣ ስጋቸውን ጎድተው ይከተሉታል፡፡ የጽድቃቸው አክሊል እርሱ መድኃኔ ዓለም የሚወደኝ መስቀሌን ተሸክሞ ይከተለኝ እንዳለ፡፡ ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 1000442598391 ወይም አቢሲኒያ ባንክ 141029444 የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

photo content

የአርቲስት ሰማኸኝ በለው ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ አንጋፋው የባሕል ሙዚቃ አቀንቃኝ አርቲስት ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ሥርዓተ ቀብር በዛሬው ዕለት ተፈጽሟል፡፡ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በትናንትናው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡

ሊቀ መልእክት ቅዱስ ሚካኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ🙏 የስሙ ትርጓሜም “እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው” ማለት ሲሆን የ7 ሊቃነ መላዕክት አለቃቸው ነው ቅዱ ሚካኤል። ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 33÷7 “የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል” ይለናል፡፡ ከእግዚአብሔር ዙፋን ስር ትዕዛዝ በወጣ ግዜ ኪሩቤል ተቀብለው ለሱራፌል ያስተላልፋሉ፤ ሱራፌልም ለሚካኤልና ለገብርኤል ለሩፋኤልም ያደርሳሉ፡፡ ሚካኤል ለፍጥረቱ በጎም ይሁን ክፉ ትዕዛዙን ይፈጽሙ ዘንድ መላዕክትን ያዛቸዋል፤ መላዕክቱም ሁሉ አቤቱ የእጅህን ስራ አታጥፋ እያሉ ቀንና ከማታ ይለምናሉ። በዓለም ፍፃሜም ስለህዝቡ የሚቆመው ሚካኤል ይነሳል። በማለት በምዕራፍ 12÷1 ጽፎልናል፡፡ በራዕይ 8÷3 “የቅዱሳኑ ፀሎት ከዕጣኑ ጢስ ጋር ከመልአኩ እጅ ወደ እግዚአብሔር ፊት ወጣ” ተብሎ እንደተጻፈውም መላዕክት የቅዱሳኑን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ያሳርጋሉ፡፡ አይሁድ ጌታን ሲሰቅሉት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በአይሁድ ስራ አዝኖ በቁጣ ሰይፉን አወጣ፤ ቅዱስ ሚካኤል ግን በእግዚአብሔር ትዕግስት ተገርሞ፣ ፈጣሪን ፍጡራን ሰቀሉት እያለ በአርምሞና በትዕግስት አያቸው ይላል ድርሳኑ። ቅዱስ ሚካኤል ሰኔ 12 ቀን ዲያቢሎስን አሸንፎ በምትኩ ሊቀ መላዕክት ሆኖ የተሾመበትና አፎምያንም የረዳበት ቀን ስለሆነ በታላቅ ሥርዓት ይከበራል። ህዳር 12 ሕዝበ እስራኤልን በክንፎቹ ጥላ ከበረሃው ፀሐይ ከልሎ ከግብጽ ምድር እየመራና እየጠበቀ ከንዓን ያገባበት ዕለት ነው። መላዕክቱ በክንፋቸው የእግዚአብሔር ስም ስለተፃፈበት ህዝቡን ይጠብቃሉ፤ የመላዕክቱን ስም የመጨረሻውን ፊደል ስናይ ኤል ብሎ ይጨርሳል፡፡ ሚካ-ኤል ገብር-ኤል ኡራ-ኤል፡፡ ይህም “ስሜ በሱ ላይ ነውና” እንደሚል የእግዚአብሔር የምህረት ስም ስለሆነና በክንፎቻቸው ስለተፃፉ መላዕክቱ ይጠብቁናል። “በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለአንተ ያዛቸዋል፤ እግርህም በድንጋይ እንዳይሰናከል በእጆቻቸው ያነሱሃል” ተብሎም በመዝሙር 90÷11 ተጽፋልና አህዛብን ጭምር ያለጊዜያቸው እንዳይሞቱ መላዕክት ይጠብቋቸዋል፡፡ በትንቢተ ዳንኤል 10÷13 እና 10÷21 ደግሞ የስሙ ትርጉም እግዚአብሔር ዳኛዬ ነው የተባለው ነብዩ ቅዱስ ዳንኤልም ስለ ቅዱስ ሚካኤል እንዲህ ሲናገር ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፣ በተዘጋ ጉድጓድ ሲያጽናናው ደግሞ “ከሚካኤል በቀር የሚያጽናናኝ የለም” አለ፡፡ ገዳማውያን የሚያደርጉት ጸሎትና የሚያቀርቡት መስዋዕት በእርሱ ምልጃ ያርጋልና ገዳማቸውን እየረዳን በዓታቸውን እያጠናን የበረከታቸው ተካፋይ እንሁን፡፡ ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 1000442598391 ወይም አቢሲኒያ ባንክ 141029444 የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

photo content

ባለስልጣናቱ “ህወሓት በፌዴራል መንግሥቱ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ወስኗል” ሲሉ፣ ህወሓትም በተመሳሳይ ትግራይ ላይ ጦርነት ሊከፈት ነው ሲል ተናገረ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የፌደራል መንግስት ገዢ ፓርቲ ብልፅግና፣ የሚያራምደው ሥርዓት በትግራይ ሕዝብ ላይ ድጋሚ ጦርነት ለመክፈት የሚያደርገውን ዝግጅት “በማታለልና በማጭበርበር ለመደበቅ እየሞከረ ነው” በማለት ኮንኖታል። ህወሓት በትናንትላው ዕለት ባወጣው መግለጫ ገዥው ፓርቲ ልዩነቶችን በኃይል ለመፍታት በማመን ቀደም ሲል በትግራይ ህዝብ ላይ ፈጽሞታል ያለውን “የጅምላ ግድያ” በሁለተኛ ዙር ለመፈፀም አሁንም የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ ይገኛል ብሏል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን በኃይል የተቆጣጠረው፣ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድም ህጋዊ ሰውነቱ የተሰረዘው ህወሓት፣ ገዥው ፓርቲን በጦርነት ዝግጅት እና በሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ከስሷል፤ በመግለጫው፡፡ ከጥቂት ቀናት በፊት፣ በህወሓት ላይ ሰፊ ትችቶችን በመሰንዘር የጋራ ጽሁፋቸውን ያስነበቡት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ አማካሪ ሚኒስትር እና የቀድሞው የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር የነበሩት ጌታቸው ረዳ እና የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተሩ ሬድዋን ሁሴን “ህወሓት በፌዴራል መንግሥቱ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ወስኗል” ሲሉ መክሰሳቸው ይታወሳል። አክለዉም በትግራይ ክልል የፕሪቶሪያውን የዘላቂ ግጭት ማቆም ስምምነት የሚቃወመው የህወሓት ስብስብ፣ ስምምነቱን በይፋ በመሻር ከፌዴራል መንግሥቱ ጋር ለቀጥታ ወታደራዊ ግጭት እየተዘጋጀ መሆኑን አጽዕኖት ሰጥተው ነበር፡፡ ከዚህ በተቸማሪም “ጽምዶ” የተሰኘው ጥምረት በአስመራ፣ በመቀሌ እንዲሁም በሱዳን ተደጋጋሚ ስብሰባ እያደረጉ መሆኑን በመጥቀስ ህወሓት በፌዴራል መንግሥቱ ላይ ጥቃት ለመክፈት ዝግጅት እያደረገ መሆኑ መገለጹ አይዘነጋም፡፡

እናታችን ቅድስት  ኪዳነ ምህረት ከክፉ ነገር ሁሉ  ትከልለን፤ ምልጃዋ እና ረድኤቷም አይለየን🙏 ማልሁልሽ ቃል ኪዳንም ገባሁልሽ አላት!!! የእግዚአብሔር የምሕረት ቃል ኪዳን ለቅዱሳኑ ከሃይማኖታቸው ጽናት ከፍጹምነታቸውና ከሥራቸው ትሩፋት የተነሳ በቅድስና ክብር አክብሮ ለገድላቸው እንዲሁም በተጋድሎ ላሳለፉበት ቦታ ለረገጡት አፈር ሁሉ በረከታቸው ተርፎ ዛሬ እኛ ምእመናን በየመካናቱ እምነቱን በመተሻሸት በመጠጣት ከቅዱሳኑ በረከት እንሳተፋለንል፡፡ በዘጸአት 20÷2-6 እግዚአብሔር አምላክ ለሚወዱትም ትእዛዙን ለሚጠብቁ እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ምሕረትን እንደሚያደርግ ተጽፏል፡፡ በዘዳግም 7÷12 ደግሞ “እንዲህም ይሆናል፤ ይህችን ፍርድ ሰምተህ ብትጠብቃት ብታደርጋትም፥ አምላክህ እግዚአብሔር ለአባቶችህ የማለውን ቃል ኪዳንና ምሕረት ለአንተ ይጠብቅልሃል” ይላል፡፡ ኪዳነ ምህረት፣ የምህረት ቃል ኪዳን ማለት ነው፡፡ ይህም ፍጹም ከከበሩ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ የማይጠፋ የዘላለም ኪዳን የሰጠበት ዕለት መታሰቢያ ነው፡፡ ታላቁ የነገረ ማርያም መጽሐፍ እንደሚያስረዳን ጌታችን ካረገ በኋላ እመቤታችን ጌታ ወደ ተቀበረበት ጎልጎታ እየሄደች ትጸልይ ነበር፡፡ በየካቲት 16 ቀንም ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ “ልጄ ወዳጄ ሆይ ከሥጋዬ ሥጋ ከነፍሴ ነፍስ ነሥተህ ሰው በመሆንህ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በቻለችህ ማኅፀኔ ከአንተ ጋር ሀገር ለሀገር ስለመሰደዴ መጥተህ ልመናዬን ትሰማኝ ዘንድ እለምንሃለሁ” እያለች ጸለየች፡፡ ጌታችንም መጥቶ ምን እንዲያደርግላት እንደምትፈልግ ጠየቀችው፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያም በስሟ ለሚማጸኑ መታሰቢያዋን ለሚያደርጉ፣ ለችግረኛ ለሚራሩ፣ በስሟ ቤተ ክርስቲያን ለሚያንጹ፣ ዕጣን ዘይትና መብአ ለቤተ ክርስቲያን ለሚሰጡ ምሕረትን እንዲያደርግላቸው ጠየቀችው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በአባቴ፣ በራሴና በመንፈስ ቅዱስ ማልሁልሽ ቃል ኪዳንም ገባሁልሽ አላት፡፡ ይህን የማያልፍ የምህረት ቃል ኪዳን ስለገባላትም ዕለቱ ኪዳነ ምሕረት የምሕረት የይቅርታ መሐላ፣ ውል፣ ስምምነት፣ ተብሎ በዝማሬ፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡ ምዕመናንም ዘወትር በረከትን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ይቀበላሉ፡፡ ገዳማውያንም ይህን ቃል ኪዳኗን አስበው ዘወትር ምህረትን አማልጂ ይሏታልና ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡ ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 1000442598391 ወይም አቢሲኒያ ባንክ 141029444 የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

photo content

የአማራ ወጣቶች እንዲታገሉ አቶ አረጋ ከበደ ጥሪ አቀረቡ‼️ የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት አረጋ ከበደ ለአማራ ወጣቶች የትግል ጥሪ አቀረቡ፡፡ ‹‹አመራሮቹን ሄዳችሁ ታገሏቸው›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ አረጋ
የአማራ ወጣቶች እንዲታገሉ አቶ አረጋ ከበደ ጥሪ አቀረቡ‼️ የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት አረጋ ከበደ ለአማራ ወጣቶች የትግል ጥሪ አቀረቡ፡፡ ‹‹አመራሮቹን ሄዳችሁ ታገሏቸው›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ አረጋ ይህን ያሉት “ባህር ዳርን ወደ ላቀ ከፍታ ለመውሰድ የወጣቶች ሚና የማይተካ ነው” በሚሉ መሪ ቃላት  ከባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ጋር በተወያዩበት ወቅት ነው። ከተማን ለነዋሪዎቿ ምቾት አልባ የሚያደርገው የአስተዳደር ብልሽት መሆኑን የጠቀሱት ርዕሰ መስተዳደሩ፣ አመራሩ በቀላሉ የሚገኝ፣ ቀላልና ውሳኔ መስጠት የሚችል መሆን እንዳለበት አጽንኦት የሰጡ ሲሆን በተለይም በሕዝብና በሀገር ላይ የሚፈጸሙ የሌብነት ድርጊቶችን ወጣቱ በግንባር ቀደምትነት ሊታገላቸው ይገባል ብለዋል። “ሌብነት ውስጥ የመሬት ስርቆት፣ የግብር ስርቆት፣ የኮንትራት ስርቆት ውስጥ የሚገባ፣ ግን መስረቅ ሳያንስ የሚመራውን ደሃ ሕዝብ የጎሪጥ የሚያይ አመራር ላይ በጽናት መታገል ያስፈልጋል።” ሲሉ የባህር ዳር ወጣቶች በተሰበሰቡበት መልዕክት አስተላልፈዋል