en
Feedback
Sheger Press️️

Sheger Press️️

Open in Telegram

Official channel of sheger press Contact @Birukepromo

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Sheger Press️️

Channel Sheger Press️️ (@sheger_press) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 35 572 subscribers, ranking 7 115 in the News & Media category and 966 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 35 572 subscribers.

According to the latest data from 28 August, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -204 over the last 30 days and by -21 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 14.92%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.88% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 308 views. Within the first day, a publication typically gains 3 870 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 25.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Official channel of sheger press Contact @Birukepromo

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 29 August, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

35 572
Subscribers
-2124 hours
-587 days
-20430 days
Posts Archive
#ትኩረት ያሸዋል ተባለ "አዲስ አበባ ሜክሲኮ ደብረወርቅ ታወር ፊት ለፊት፣ ከቡናና ሻይ አጠገብ ባለው ዋና መንገድ ላይ የሚገኝ ይህ 'ፖል' የብዙዎችን ህይወት አደጋ ላይ ጥሏል ነው የተባለው ። 😱
#ትኩረት ያሸዋል ተባለ "አዲስ አበባ ሜክሲኮ ደብረወርቅ ታወር ፊት ለፊት፣ ከቡናና ሻይ አጠገብ ባለው ዋና መንገድ ላይ የሚገኝ ይህ 'ፖል' የብዙዎችን ህይወት አደጋ ላይ ጥሏል ነው የተባለው ። 😱 በተለይ በምሽት እይታው ስለሚቀንስ፣ አሽከርካሪዎችም ሆኑ እግረኞች ለማይፈለግ አደጋ እየተጋለጡ ይገኛሉ። ይህ ፖል ከመንገዱ ተነስቶ ሌላ ምቹ ቦታ ላይ ካልተተከለ የከፋ አደጋ ሊያደርስ ይችላል። የሚመለከተው አካል አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥ እና የአካባቢው ነዋሪዎችም ሆኑ አሽከርካሪዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እናሳስባለን። ⚠️⚠️ ይህ መረጃ ለሚመለከተው አካል እስኪደርስ ሼር በማድረግ ተባበሩ!"

እመብርሐን የከበደ ሸክማችንን ታቅልልልን፤በድካማችን ሁሉ ብርታት ትሁነን🙏 ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳይያስ በትንቢቱ ምእራፍ 7÷14 “እግዚአብሔር ምልክት ይሰጠናል ድንግል በድንግልና ጸንሳ በድንግልና ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች፡፡ ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው፡፡ እርሱም ድንቅ መካር ኃያል የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል።” አለን፡፡ በመሆኑም እመቤታችን የአምላክ እናት የእግዚአብሔር እናት ትባላለች። በ325 ዓ.ም በጉባኤ ኒቂያ በነበረው የሲኖዶስ ውይይት ላይ በአደባባይ ተከራክረው ከሐዲያንን ካሳፈሩ 318 ሊቃውንት አንዱ የቆጵሮሱ ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ የጌታችንን መለኮታዊ ባህርይ ለሚጠራጠሩ አርዮሳውያንና በተዋሕዶ ሰው ሆኖ መክበሩን ለሚክዱ የተዋሕዶን ምሥጢርና ቅድስት ድንግል ማርያም የመለኮት እናት ስለመሆኗ ሲያስተምር “ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውና አምላክ በተዋሕዶ የከበረ ነው አለ፡፡ በአምላክነቱ መለኮታዊ ባሕርይ ቢኖረውም እንደ ሰውነቱ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ያለ ወንድ ዘር ተፀንሶ በድንግልና ተወልዷል።ድንግል ማርያም ጌታን ከመፅነሷ በፊት በፀነሰች ጊዜ ከፀነሰችም በኋላ፤ እንዲሁም ከመውለዷ በፊት በወለደችም ጊዜ ከወለደችም በኋላ ድንግል ናት። ይህንንም እግዚአብሔር ስለገለጸለት ከአበይት ነቢያት መካከል አንዱ ቅዱስ ሕዝቅኤል በምዕራፍ 44÷1-4 “ወደ ምስራቅ ወደሚመለከተው በር አመጣኝ ይህ በርም ዝግ ነበር፣ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ለዘላለም ዝግ ሆኖ ይኖራል።” አለኝ ይላል፡፡ ምስራቅ ያላት ድንግል ማርያምን ነው ፀሐይ ከምስራቅ እንዲወጣ ጨለማውንም ዓለም ብርሃን እንዲያደርግ፤ ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስም ከአማናዊት ምስራቅ ከድንግል ማርያም ተልወዶ በኅጢያት ለጨለመው ዓለም የጽድቅ ብርሃን ሆኖ ተገልጧልና፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በገላትያ 4÷4 እንደጻፈው የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ያለ ወንድ ዘር ከቅድስት ድንግል ማርያም ከአምላክ እናት የተወለደውን አንድያ ልጁን ላከልን፣ እርሱም የእኛን ባህርይም ባህርይ አድርጎ ተወለደ። ልጆችም ስለሆንን እግዚአብሔር አባት ብለን የምንጠራበት የልጅነት መንፈስ ሰጠን፡፡ እመቤታችንም በሕቱም ድንግልና ይህን ጌታ ወለደችልን፡፡ ገዳማውያንም ይህችን እናት ዘወትር አማልጅን ይሏታል፡፡ ገዳማቸውን እደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡ ድጋፍ ለማድረግ፡- ቤተ ቅዱሳን ፈትለወርቅ ማርያም የእናቶች ገዳም፡- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000766349227 ወይም አቢሲንያ ባንክ  262281132 የገዳሙ ስልክ ቁጥር፡- 0944672222 ወይም 0916106921

photo content

በንግድ እና አገልግሎት ዘርፍ የተሰማራቹ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ተጠንቀቁ ። በ3 የሻይ ሲኒ ደረሰኝ ምክንያት 300 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል። በአዲሱ የታክስ አስተዳደር አዋጅ መሰረት ደረሰኝ አ
+3
በንግድ እና አገልግሎት ዘርፍ የተሰማራቹ  ግለሰቦች እና ድርጅቶች ተጠንቀቁ ። በ3 የሻይ ሲኒ  ደረሰኝ  ምክንያት 300 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል። በአዲሱ የታክስ አስተዳደር አዋጅ መሰረት ደረሰኝ አለመስጠት ንብረትዎን ሊያሳጣዎት ይችላል! አንድ ሰራተኛዎ ቸልተኛ ሆና 100 ብር ለሚያወጣ 'ሻይ' ደረሰኝ ባትቆርጥ... ቅጣቱ 100 ብር ሳይሆን 100 ሺህ ብር ነው ተብሏል። ይባስ ብሎ ደግሞ... ሰራተኛዋ ለ3 ደንበኞች ደረሰኝ ካልሰጠች፣ ለድርጅቱ ባለቤት የ300 ሺህ ብር መብረቅ የመሰለ ቅጣት ይወርድበታል። ይህ ቅጣት ደግሞ በአዋጁ አንቀጽ 125 ንኡስ ቁጥር 2 መሰረት በባለስልጣኑ ሊነሳ ወይም 'ይቅር' ሊባል አይችልም! መፍትሄው መክፈል ብቻ ነው! ነጋዴዎች ተጠንቀቁ፣ ሰራተኞቻችሁን አስተምሩ።

በንግድ እና አገልግሎት ዘርፍ የተሰማራቹ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ተጠንቀቁ ። በ3 የሻይ ሲኒ ደረሰኝ ምክንያት 300 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል። በአዲሱ የታክስ አስተዳደር አዋጅ መሰረት ደረሰኝ አ
+3
በንግድ እና አገልግሎት ዘርፍ የተሰማራቹ  ግለሰቦች እና ድርጅቶች ተጠንቀቁ ። በ3 የሻይ ሲኒ  ደረሰኝ  ምክንያት 300 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል። በአዲሱ የታክስ አስተዳደር አዋጅ መሰረት ደረሰኝ አለመስጠት ንብረትዎን ሊያሳጣዎት ይችላል! አንድ ሰራተኛዎ ቸልተኛ ሆና 100 ብር ለሚያወጣ 'ሻይ' ደረሰኝ ባትቆርጥ... ቅጣቱ 100 ብር ሳይሆን 100 ሺህ ብር ነው ተብሏል። ይባስ ብሎ ደግሞ... ሰራተኛዋ ለ3 ደንበኞች ደረሰኝ ካልሰጠች፣ ለድርጅቱ ባለቤት የ300 ሺህ ብር መብረቅ የመሰለ ቅጣት ይወርድበታል። ይህ ቅጣት ደግሞ በአዋጁ አንቀጽ 125 ንኡስ ቁጥር 2 መሰረት በባለስልጣኑ ሊነሳ ወይም 'ይቅር' ሊባል አይችልም! መፍትሄው መክፈል ብቻ ነው! ነጋዴዎች ተጠንቀቁ፣ ሰራተኞቻችሁን አስተምሩ።

እንኳን ለሊቀ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወርሃዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን🙏 ከአንገቱ የወጣው ደም እሳት ሆኖ አጥፍቷቸዋል በ277 ዓ.ም ጥር 20 ፍልስጤም ልዩ ስሟ “ልዳ” የተወለደው ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሁሉም ክርስቲያኖች ዘንድ ተቀባይነት ካላቸው ሰማዕታት ቀዳሚው ነው፡፡ የአባቱን ሞት ተከትሎ ከሌላ መኳንንት ጋር ያደገው ጊዮርጊስ የክርስትና ጠላት ከሆነው ዱዲያኖስና ከ70ው ነገስታት ጋር የተጋፈጠው የአባቱን ምስፍና እንዲሰጡት ሊጠይቅ በሔደበት ክርስቲያኖችና ክርስትና ሲገፉ በማየቱ ነው፡፡ ጊዮርጊስ ማለት “ብሩህ ኮከብ፣ ፀሐይ” ሲሆን ተጋድሎውን ሲጀምር የሃያ ዓመት ወጣት ነበር፡፡ በቤሩትም የሚመለክና ሴት ልጆቻቸውን የሚገብሩለትን ደራጎን ገድሎ ሕዝቡን ወደ ክርስትና አስገባቸው፡፡ በነገሥታቱ ፊትም የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ፡፡ ምንም እንኳን ንጉሡ ቅዱስ ጊዮርጊስ የመሣፍንት ወገን መሆኑን እንደ መግቢያ በመጠቀም ሊያባብለው ቢሞክርም “አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን አልክድም” ብሎ በእምነቱ ጸና፡፡ ዱድያኖስም ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን ያደርስበት ጀመር፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ያጸናው  ቍስሉንም ያድነው ነበር፡፡ ሦስት ጊዜ እንደሚሞት እርሱም እንደሚያስነሣው በአራተኛውም የሰማዕትነትን አክሊል እንደሚቀበል ነገረው፡፡ ቃል ኪዳንም ገባለት፤ ለሰባት ዓመትም በጽኑዕ መከራና በሥቃይም እንዲሁም በተጋድሎ እንደሚኖር በዚያም ስሙ በዓለሙ ሁሉ የተገለጠ እንደሚሆን መላእክትም እንደሚያገለግሉትም ነገረው፡፡ ንጉሥ ዱድያኖስም ቅዱስ ጊዮርጊስ ትእዛዙን ባለመቀበሉ ተቆጥቶ አትናስዮስ የሚባል ታላቅ መሠሪ አስጠርቶ በፍጥነት የሚገድል መርዝ ቀምሞ በጽዋ መልቶ አጠጣው፡፡  መርዙ ግን ምንም ጉዳት ሳይደርስበት ቀረ፡፡ ያ መሠርይም ይህን ድንቅ ሥራ ሲያይ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ በሰማዕትነት ሞተ፡፡ ቁጥራቸውም ሠላሳ ሺህ ሰባት መቶ የሚሆኑ ሌሎች ሰዎች ከእርሱ ጋር በሰማዕትነት ሞተው የሕይወትን አክሊል ተቀዳጁ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ለሰባት ዓመታት በቅድስና ሲጋደል ቆይቶ፣ ታላቅ የምህረት ቃል ኪዳን ተቀብሎ ሚያዝያ 23 ቀን በሰይፍ አንገቱን ተመቶ ሲሞት ከአንገቱ የወጣው ደም እሳት ሆኖ ሰባውን ነገስታት አጥፍቷቸዋል፡፡ ስለክርሳቶስ ፍቅር ዓለምን የናቁ ገዳማውያን ይህን አብነት አድርገው የዓለም ደስታቸውን ስለክርስቶስ ፍቅር ትተዋልና በረከታቸው ብዙ ነው፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና ከበረከታቸው እንሳተፋለን፡፡    ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 1000442598391 ወይም አቢሲኒያ ባንክ 141029444 የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

photo content

ለሕገ-ወጥ የሐዋላ ድርጅቶች ማስጠንቀቀያ ተሰጠ‼ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሕገ-ወጥ የሐዋላ መረቦችንና ፈቃድ የሌላቸውን የገንዘብ ማስተላለፊያ ተቋማት (MTAs) ከመጠቀም እንዲቆጠቡ ለሕዝቡና ለዲያስ
+1
ለሕገ-ወጥ የሐዋላ ድርጅቶች ማስጠንቀቀያ ተሰጠ‼ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሕገ-ወጥ የሐዋላ መረቦችንና ፈቃድ የሌላቸውን የገንዘብ ማስተላለፊያ ተቋማት (MTAs) ከመጠቀም እንዲቆጠቡ ለሕዝቡና ለዲያስፖራው ማኅበረሰብ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጠ። ባንኩ እንዳስታወቀው፣ ከሕግ ውጭ በሆኑ የሐዋላ ተቋማት መገልገል ለገንዘብ መበዝበዝ፣ ለክፍያ መዘግየት፣ ለባንክ ሒሳብ እገዳና ለሕጋዊ ተጠያቂነት ያጋልጣል። በምሳሌነት ከተጠቀሱት ፈቃድ የሌላቸው ድርጅቶች መካከል፦ 📌Adulis Money Transfer (ADZ), 📌Amal Express, 📌Amal USA, 📌Amana Express, 📌Avanti, 📌Awash Direct, 📌Bakaal Money Transfer, 📌Jubba Express, 📌Rasmy Pay, 📌Ramad Pay / Ramada Pay (Kaah), 📌Shgey Money Transfer, 📌Taaj Financial Service, 📌Tasa Pay, 📌Tawakal Money Services, 📌USwyre, 📌World Direct Link እና Zola ይገኙበታል። ባንኩ ደንበኞች ገንዘባቸውን ከመላካቸው በፊት በብሔራዊ ባንክ ፈቃድ የተሰጣቸውን ሕጋዊ ተቋማት ዝርዝር በኦፊሴላዊ ድረ-ገጹ (nbe.gov.et/mta/) ላይ ማረጋገጥ እንደሚችሉ ገልጿል።

በእስራኤል የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የመባረር ስጋት ተደቅኖባቸዋል ለሁለት አሥርት ዓመታት ያህል በእስራኤል ያለ ቋሚ ሕጋዊ ፈቃድ ሲኖሩ የቆዩ ኢትዮጵያውያን ጥገኝነት ጠያቂዎች፣ ሀገሪቱ በምትወስደው አዲስ የሕግ እርምጃ ምክንያት ከባድ የመባረር ስጋት ገጥሟቸዋል። እንደ አቶ እንዳልካቸው የማኔ እና ዮርዳኖስ ያሉ ስደተኞች ከባድ በደሎችን አልፈው እስራኤል ገብተው ሕይወት መስርተው ልጆቻችውን  እያስተማሩ ቢሆንም፣ ባለፈው ታኅሣሥ ወር የእስራኤል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የቡድን ከለላ ፈቃድ እንዲሰረዝ መወሰኑ ሕልማቸውን አደጋ ላይ ጥሎታል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መረጃ እንደሚያሳየው፣ እስራኤል የጥገኝነት ማጽደቅ ምጣኔዋ 0.1 በመቶ ብቻ መሆኑ ስጋቱን  አባብሶታል። ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት የወሰደው 'HIAS Israel' የተሰኘው ድርጅት፣ እስራኤል ዓለም አቀፍ የከለላ ስምምነቶችን አክብራ ስደተኞችን አደጋ ወደ ሚጠብቃቸው ሀገር እንዳትመልስ በቴል አቪቭ የዞን ፍርድ ቤት ክስ መመስረቱን ሃራምቤ ሬዲዮ ዘግቧል፡፡

ቅዱስ ጊዮርጊስ ከክፉ ነገር ሁሉ ይከልለን፤ ምልጃው እና ረድኤቱም አይለየን🙏 ይህን ከሃዲ እስካሳፍረው ድረስ ነፍሴን አትውሰዳት አባቱን ገና በልጅነቱ ቢሞትበትም ሌላ ክርስቲያናዊ መስፍን ወስዶ በጦር ኃይል አሰልጠኖ አሳድጎታል፡፡ የስሙ ትርጓሜ “ኮከብ ብሩህ፣ ፀሐይ” ማለት ነው፡፡ ፍልስጤም ውስጥ ልዩ ስሟ “ልዳ” በምትባል ቦታ በ277 ዓ.ም ጥር 20 ተወለደ ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ፡፡ ያሳደገው መስፍን ሲሞትም ኀዘኑን ጨርሶ ወደ ቤሩት ከተማ ሄደ፡፡ በዚያም የሚመለክና ሴት ልጆቻቸውን የሚገብሩለትን ደራጎን ገድሎ ሕዝቡን ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መለሳቸው፡፡ የአባቱን ሹመት ለማግኘት ወደ ፋርስም ሲሔድ ንጉሱ ዱድያኖስ ከሰባ ነገሥታት ጋር ጣዖታት ሲያመልኩ ቢያገኛቸው በፊታቸው የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ፡፡ ሰማዕቱ ከመኳንንት ወገን መሆኑን የተረዳው ዱዲያኖስ አጵሎንን ብታመልክ እሾምሃለው አለው፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም “አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን ላንተ ሹመት ስል አልክደውም” አለው፡፡ ዱድያኖስም እጅግ ተቆጥቶ ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን አደረሰበት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ግን ጌታችንን “ይህን ከሃዲ እስካሳፍረው ድረስ ነፍሴን አትውሰዳት” በማለት ለመነው፡፡ እግዚአብሔርም ጽናትን ሰጥቶታል፡፡ የደረሱበት እጅግ አሠቃቂ መከራዎች የሰው ኅሊና ሊያስባቸው እንኳን የማይችላቸው ናቸው፡፡ በእንጨት ላይ ሰቅለው ሥጋውን በመቃን አስፈተተው፣ ረጃጅም ችንካሮች ያሉበት የብረት ጫማ አጫምተው ሂድ አሉት፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ሚካኤልን ልኮለት ፈውሶታል፡፡ ሰውነቱን በመጋዝ አስተልትሎ ጨው ሲነሰንስበት ሥጋው መሬት ላይ ወደቀ፡፡  በሰባ ችንካሮች አስቸንክሮ፣ በእሳት አስተኩሶ፣ አናቱን በመዶሻ አስቀጥቅጦ፣ በሆዱ ላይ የደንጊያ ምሰሶ አሳስሮ እንዲያንከባልሉት አደረገ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈቀ ሌሊት በእጁ ዳስሶ ፈወሰው፤ ኃይልና ብርታትንም ሰጠው፡፡ በመከራው ብዛት ሦስት ጊዜ ሲሞት ጌታችን ሦስት ጊዜ ከሞት አስነሣው፡፡ ለሰባት ዓመታት ከተጋደለ በኋላም ሚያዝያ 23 በሰይፍ አንገቱን ተመቶ ሲሞት ሰባውን ነገስታት አጥፍቷቸዋል፡፡ ዓለምን የናቁ ገዳማውያን ይህን አብነት አድርገው ይጸናሉ በገድልም ይተጋሉ፡፡ እኛም ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡     ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 1000442598391 ወይም አቢሲኒያ ባንክ 141029444 የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

photo content

ህወሃት ጦርነቱን የሚመራና ውሳኔ የሚሰጥ አስራ አንድ አባላት ያሉት ሴንትራል ኮማንድ ማቋቋሙ ተነገረ። ይህ ሴንትራል ኮማንድ አቶ ጌታቸው አሰፋን ጨምሮ ከሲቪል አስተዳደር አምስት ከወታደራዊ አመራሮች ደግሞ ስድስት አባላት እንዳሉት የተነገረ ሲሆን የሚመጣውን ጦርነት አመራር ሰጪ ነው ተብሏል። በተያያዘ የአማራ ሀይሎችም ለቀጣዩ ጦርነት የአደረጃጀት ለውጥ ማድረጋቸው የተዘገበ ሲሆን ይሄም በሌላ የጦርነት ግንባር ቢሆንም ከጥምር ጦሩ ጋር እንደአንድ ሰራዊት ሆነው በጋራ እንቅስቃሴ የሚያደርጉበት አደረጃጀት ነው ተብሏል። ከህወሓት 1) ዶ/ር ደብረፅየን ገ/ሚካኤል 2) ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/ሄር (ሞንጀሪኖ) 3) አቶ አማኑኤል አሰፋ 4) ዶ/ር አብርሃም ተኸስተ 5) አቶ ጌታቸው አሰፋ ሲሆኑ ከወታደራዊ አዛዦች ደግሞ 1) ሌፍተናል ጀነራል ፍስሃ ኪዳኑ(ፍስሃ ማንጁስ) 2) ብርጋዴር ጀነራል ሃ/ስላሴ ግርማይ (ወዲ እምበይተይ) 3) ሜጀር ጀነራል የውሃንስ ወ/ጅወርግስ (ጆን መዲድ) 4) ብርጋዴር ጀነራል ምግበይ ሃይለ(መርዘን) ራሴ ያወጣሁለት ቅፅል ስም ወይም ሳጓ ነው) 5) ሜጀር ጀነራል ብርሃነ ነጋሽ ( ወዲ መድህን) 6) ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ናቸው። ]

እንኳን ለቅዱስ ዑራኤል ወርሃዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ፤አደረሰን🙏 ቅዱስ ዑራኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ🙏 የስሙን ትርጓሜ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ሲያስቀምጡም “ዑራ” ማለት ብርሃን ማለት ሲሆን “ኤል” አምላክ ማለት ነው፡፡ በዚህም ዑራኤል ማለት የአምላክ ብርሃን፣ ወይም የብርሃን ጌታ ማለት ነው ይላሉ፡፡ መልአከ ብርሃናት፣ ለሚጠሩት ፈጥኖ የሚደርስ መሆኑን የቤተ ክርስቲያናችን መጻሕፍት በስፋት ይገልጹታል፡፡ ከሰባቱ ሊቃነ መላዕክት አንዱ ሲሆን በየዓመቱ ጥር 22 በዓለ ሲመቱ ይከበራል፡፡ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ዑራኤል፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር በመባርቅትና በነጎድጓድ ላይ የተሾመው ታላቅ መልአክም ነው ቅዱስ ዑራኤል፡፡ በመጽሐፈ ሔኖክ 6÷2 መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ይሰማራል። ምሥጢረ ሰማይና እውቀትንም ሁሉ ለሄኖክ የገለጸለትም የፀሐይን፣ የጨረቃን፣ የከዋክብትንና የሰማይ ሠራዊትን ብርሃንን የሚመራ እርሱ መሆኑን ለነቢዩ ሄኖክ ነግሮታል። እውቀት ተሠውሮበት ለነበረው ኢትዮጵያዊው ሊቅ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫም በእመቤታችን በድንግል ማርያም ትእዛዝ ፅዋዐ ጥበብን አጠጥቶ ሠማያዊውን ጥበብ የገለጸለት ቅዱስ ዑራኤል ነው። "ዑራኤል የተባለ መልአክ ሊረዳኝ መጣ" ይላልና፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር የሕይወትና የይቅርታ ዝናብ በምድራችን ላይ ያዘንብ ዘንድ እንዲሁም የእርሻችንን አዝመራ በዝናብ አብቅሎ በፀሐይ አብስሎ ለምግብነት እንዲበቃ ከፈጣሪ ዘንድ ምህረትን የሚለምን ነው ቅዱስ ዑራኤል። ምሥጢር ማናገር የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ቢሆንም የተሠወረውን መግለጥ፣ በአዲስ ቋንቋ ማናገር ለመላእክት የተሰጠ ጸጋቸው መሆኑም ግልጽ ነው።  በዕዝራ ሱቱኤል 13÷38 ተጽፎ እንደምናገኘው መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል “አፍህን ክፈት፤ እኔም የማጠጣህን ጠጣ” ብሎ አእምሮ ለብዎውን ወይም ማስተዋልን ገልጦለታል። የተወደደ ሥራ ለሚሠሩና እንዲያውቁ ለተፈቀደላቸው ሁሉ ቅዱስ ዑራኤል ምሥጢር ይገልጣል፤ ለዕዝራ ሱቱዔል የሆነለትም እንዲሁ ነውና። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከልጇ ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ግብጽ ስትሰደድ መንገድ የመራ፣ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ በተሰቀለ ጊዜ ክቡር ደሙን በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃነ መነሳንስ በዓለም ላይ የረጨ እርሱ ነው፡፡ ሊቀ መልአኩ የጌታችንን ደም የረጨበት ጽዋ በሀገራችን በኢትዮጵያ እመጓ ቅዱስ ኡራኤል እንደሚገኝ ስፍረዋን የጎበኙ ጸሐፍትና የስፍራው አገልጋዮች ይገልጻሉ፡፡ በርካታ ቅዱሳን አባቶች ምስጢር እንዲገለጥላቸው የረዳቸው ቅዱስ ዑራኤል መሆኑ በበርካታ የቤተ ክርስቲያናችን መጻሕፍት ሰፍሮ ይገኛል፡፡ አፋቸውን ከፍተው የምስጋና ቃል እንዲናገሩ፣ የሚጽፉበት ብዕር በመንፈስ ቅዱስ የተቃኘ ለሕይወት ድህነት የሚሆን መልዕክት እንዲያስተላልፍ ቅዱስ ዑራኤል አግዟቸዋል፡፡ ይህም ምሥጢር ማናገር የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ቢሆንም የተሠወረውን መግለጥ፣ በአዲስ ቋንቋ ማናገር ለመላእክት የተሰጠ ጸጋቸው መሆኑም ያሳየናል፡፡ ዛሬም በየገዳማቱ ያሉ ቅዱሳን አባቶችና እናቶች ዓለምን ንቀው፣ ድንጋይ ተንተርሰው፣ ጤዛ ልሰው፤ ግርማ ሌሊቱን፣ ድምጸ አራዊቱን፣ ጸብአ አጋንንቱን ተቋቁመው በጾምና በጸሎት ሲተጉ ይህ ቅዱስ መልአክ ዑራኤል ፈጽሞ ይራዳቸዋል፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ በራዕይ 8÷4 “የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ።” እንዲል ስለ ሀገራችን ሰላም፣ ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ደህንነት እግዚአብሔርን በሚለምኑት በገዳማውያኑ መካከል ተገኝቶ ጸሎታቸውን ያሳርጋል፤ ልመናቸውን በአምላክ ፊት ያቀርባል፡፡ ቅዱሳን መካናትን ስናግዝ፣ ገዳማትን ስንረዳ፣ በዓታቸውን ስናጸና የገዳማውያኑ ጸሎትና በረከት ይደርሰናል፡፡     ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 1000442598391 ወይም አቢሲኒያ ባንክ 141029444 የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

photo content

የምሽቱ ትልቁን ፍልሚያ ጆኒ አሸነፈ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በታላቅ ድምቀት ሲካሄድ የሰነበተው የኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ኮከቦች ምሽት በጉጉት በተጠበቀውና በዋናው የዋንጫ ፍልሚያ (Main Event) በይፋ ፍጻሜ አግኝቷል! በሚድል ዌይት (Middleweight MMA Bout) ዘርፍ በጆኒ እና በሴዶ መካከል የተደረገው ይህ አስደናቂና አቃጣጣኝ ፍልሚያ የመላው ተመልካች ቀልብ የሳበ ነበር። በከፍተኛ የኤምኤምኤ (MMA) ቴክኒክ፣ የላቀ ብቃትና ፍጹም የድል ወኔ ተጋጣሚውን ሴዶን ያሸነፈው ጆኒ፡ የምሽቱን ትልቅ ድል በመቀዳጀት አዲሱ የ ETFC 2 ቻምፒዮን (Champion) በመሆን ዘውዱን ደፍቷል!

እመብርሐን የከበደ ሸክማችንን ታቅልልልን፤በድካማችን ሁሉ ብርታት ትሁነን🙏 በ325 ዓ.ም በጉባኤ ኒቂያ በነበረው የሲኖዶስ ውይይት ላይ በአደባባይ ተከራክረው ከሐዲያንን ካሳፈሩ 318 ሊቃውንት አንዱ የቆጵሮሱ ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ነበረ። የጌታችንን የመድኅኒታችንን መለኮታዊ ባህርይ ለሚጠራጠሩ እና በተዋሕዶ ሰው ሆኖ መክበሩን ለሚክዱ፣ ቅዱስ ኤጲፋኒዮስ ስለ ተዋሕዶ ምሥጢርና ቅድስት ድንግል ማርያም የመለኮት እናት ስለመሆኗ ሲያስተምር “ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውና አምላክ በተዋሕዶ የከበረ ነው፡፡ በአምላክነቱ መለኮታዊ ባሕርይ ቢኖረውም እንደ ሰውነቱ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ያለ ወንድ ዘር ተፀንሶ በድንግልና ተወልዷል። ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳይያስ በትንቢቱ 7፣14 እንደጻፈው “እግዚአብሔር ምልክት ይሰጠናል ድንግል በድንግልና ጸንሳ በድንግልና ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች፡፡ ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው፡፡ እርሱም ድንቅ መካር ኃያል የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል።” በመሆኑም እመቤታችን የአምላክ እናት የእግዚአብሔር እናት ትባላለች። በሉቃስ ወንጌል ላይ ማርያም ነገርን ሁሉ በልቧ ትጠብቀው ስለነበር ከቅዱሳን የከበረች ከመላዕክትም የበለጠች እንደነበር አያውቅም ነበር። በሌላው ጌታን በፀነሰች ጊዜ ገጽዋ ይለዋወጥ ነበር ይህንንም ሲያይ ዮሴፍ ጻድቅም ስለነበር ሳይገልጣት ተዋት። አበው እንዳስተማሩን እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ከፈጠረበት ጥበቡ ይልቅ፣ በተዋሕዶ ሰው ሆኖ ዓለምን ያዳነበት ጥበቡ ይበልጣልና። ድንግል ማርያም ጌታን ከመፅነሷ በፊት በፀነሰች ጊዜ ከፀነሰችም በኋላ ድንግል ናት። እንዲሁም ከመውለዷ በፊት በወለደችም ጊዜ ከወለደችም በኋላ ድንግል ናት። ይህንንም እግዚአብሔር ስለገለጸለት ከአበይት ነቢያት መካከል አንዱ ቅዱስ ሕዝቅኤል በምዕራፍ 44÷1-4 “ወደ ምስራቅ ወደሚመለከተው በር አመጣኝ ይህ በርም ዝግ ነበር፣ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ለዘላለም ዝግ ሆኖ ይኖራል።” አለኝ ይላል፡፡ ምስራቅ ያላት ድንግል ማርያምን ነው፡፡ ፀሐይ ከምስራቅ እንዲወጣ ጨለማውንም ዓለም ብርሃን እንዲያደርግ፤ ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስም ከአማናዊት ምስራቅ ከድንግል ማርያም ተልወዶ በኅጢያት ለጨለመው ዓለም የጽድቅ ብርሃን ሆኖ ተገልጧልና፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞንም በመኃልዬ መኃልይ 4÷12 "እህቴ ሙሽራዬ ሆይ የተዘጋ ገነት የታተመ ፈሳሽ ነሽ" በማለት ስለዘላለማዊ ድንግልናዋ ጽፏል። በቅዱስ ጳውሎስም በገላትያ 4÷4 እንደጻፈው የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ያለ ዘርአ ብእሲ ወይም ያለ ወንድ ዘር ከቅድስት ድንግል ማርያም ከአምላክ እናት የተወለደውን አንድያ ልጁን ላከልን፣ እርሱም የእኛን ባህርይም ባህርይ አድርጎ ተወለደ። ልጆችም ስለሆንን እግዚአብሔር አባ አባት ብለን የምንጠራበት የልጅነት መንፈስ ሰጠን፡፡ እመቤታችንም በሕቱም ድንግልና ይህን ጌታ ወለደችልን፡፡ ገዳማውያንም ይህችን እናት ዘወትር አማልጅን ይሏታል፡፡ ገዳማቸውን እደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡ ከበረከቱ እንካፈል። ድጋፍ ለማድረግ፡- ቤተ ቅዱሳን ፈትለወርቅ ማርያም የእናቶች ገዳም፡- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000766349227 ወይም አቢሲንያ ባንክ  262281132 የገዳሙ ስልክ ቁጥር፡- 0944672222 ወይም 0916106921

photo content

የምሽቱ ትልቁን ፍልሚያ ጆኒ አሸነፈ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በታላቅ ድምቀት ሲካሄድ የሰነበተው የኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ኮከቦች ምሽት በጉጉት በተጠበቀውና በዋናው የዋንጫ ፍልሚያ (Main
የምሽቱ ትልቁን ፍልሚያ ጆኒ አሸነፈ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በታላቅ ድምቀት ሲካሄድ የሰነበተው የኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ኮከቦች ምሽት በጉጉት በተጠበቀውና በዋናው የዋንጫ ፍልሚያ (Main Event) በይፋ ፍጻሜ አግኝቷል! በሚድል ዌይት (Middleweight MMA Bout) ዘርፍ በጆኒ እና በሴዶ መካከል የተደረገው ይህ አስደናቂና አቃጣጣኝ ፍልሚያ የመላው ተመልካች ቀልብ የሳበ ነበር። በከፍተኛ የኤምኤምኤ (MMA) ቴክኒክ፣ የላቀ ብቃትና ፍጹም የድል ወኔ ተጋጣሚውን ሴዶን ያሸነፈው ጆኒ፡ የምሽቱን ትልቅ ድል በመቀዳጀት አዲሱ የ ETFC 2 ቻምፒዮን (Champion) በመሆን ዘውዱን ደፍቷል!

በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በቴሌ ብር መተግበሪያ የ4 ነጥብ 19 ትሪሊየን ብር የዲጅታል ግብይት መፈጸሙን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስታወቀ። ኢንቨስትመንት ሆልዲንግሱ ይሄንን ያለው በስሩ የሚገኙ ተቋማት አመታዊ አፈጻጸም ግምገማ ለ3ኛ ቀን መቀጠሉን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ላይ ነው። የቴሌ ብር ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ60 ሚሊዮን በላይ መድረሱን ያነሳው ተቋሙ ቴሌ ብር በ2018 በጀት ዓመት 7 ነጥብ 83 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱንም ገልጿል። በተጨማሪም በበጀት አመቱ የኢትዮ ቴሌኮም ገቢ በ33 ነጥብ 2 በመቶ ማደጉም ነው የተጠቀሰው።

ቅዱስ ዑራኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ🙏 በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ🙏 መልአከ ብርሃናት፣ ለሚጠሩት ፈጥኖ የሚደርስ መሆኑን የቤተ ክርስቲያናችን መጻሕፍት በስፋት ይገልጹታል፡፡ ከሰባቱ ሊቃነ መላዕክት አንዱ ሲሆን በየዓመቱ ጥር 22 በዓለ ሲመቱ ይከበራል፡፡ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ዑራኤል፡፡ የስሙን ትርጓሜ ሊቃውተ ቤተክርስቲያን ሲያስቀምጡም “ዑራ” ማለት ብርሃን ማለት ሲሆን “ኤል” አምላክ ማለት ነው፡፡ በዚህም ዑራኤል ማለት የአምላክ ብርሃን፣ ወይም የብርሃን ጌታ ማለት ነው፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር በመባርቅትና በነጎድጓድ ላይ የተሾመው ታላቅ መልአክም ነው ቅዱስ ዑራኤል፡፡ በመጽሐፈ ሔኖክ 6÷2 መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ይሰማራል። ምሥጢረ ሰማይና እውቀትንም ሁሉ ለሄኖክ የገለጸለትም የፀሐይን፣ የጨረቃን፣ የከዋክብትንና የሰማይ ሠራዊትን ብርሃንን የሚመራ እርሱ መሆኑን ለነቢዩ ሄኖክ ነግሮታል። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከልጇ ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ግብጽ ስትሰደድ መንገድ የመራ፣ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ በተሰቀለ ጊዜ ክቡር ደሙን በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃነ መነሳንስ በዓለም ላይ የረጨ እርሱ ነው፡፡ ሊቀ መልአኩ የጌታችንን ደም የረጨበት ጽዋ በሀገራችን በኢትዮጵያ እመጓ ቅዱስ ኡራኤል እንደሚገኝ ስፍረዋን የጎበኙ ጸሐፍትና የስፍራው አገልጋዮች ይገልጻሉ፡፡ ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ጥበብን ያጠጣ፣ ኢትዮጵያዊውን ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በርካታ ቅዱሳት መጻሕፍትን አንዲደርሱ ያገዘ፣ የረዳና የዕውቀት ጽዋን ያጠጣ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ በርካታ ቅዱሳን አባቶች ምስጢር እንዲገለጥላቸው የረዳቸው ቅዱስ ዑራኤል መሆኑ በበርካታ የቤተ ክርስቲያናችን መጻሕፍት ሰፍሮ ይገኛል፡፡ አፋቸውን ከፍተው የምስጋና ቃል እንዲናገሩ፣ የሚጽፉበት ብዕር በመንፈስ ቅዱስ የተቃኘ ለሕይወት ድህነት የሚሆን መልዕክት እንዲያስተላልፍ ቅዱስ ዑራኤል አግዟቸዋል፡፡ ይህም ምሥጢር ማናገር የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ቢሆንም የተሠወረውን መግለጥ፣ በአዲስ ቋንቋ ማናገር ለመላእክት የተሰጠ ጸጋቸው መሆኑም ያሳየናል፡፡ ዛሬም በየገዳማቱ ያሉ ቅዱሳን አባቶችና እናቶች ዓለምን ንቀው፣ ድንጋይ ተንተርሰው፣ ጤዛ ልሰው፤ ግርማ ሌሊቱን፣ ድምጸ አራዊቱን፣ ጸብአ አጋንንቱን ተቋቁመው በጾምና በጸሎት ሲተጉ ይህ ቅዱስ መልአክ ዑራኤል ፈጽሞ ይራዳቸዋል፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ በራዕይ 8÷4 “የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ።” እንዲል በገዳማውያኑ መካከል ተገኝቶ ጸሎታቸውን ያሳርጋል፤ ልመናቸውን በአምላክ ፊት ያቀርባል፡፡ ቅዱሳን መካናትን ስናግዝ፣ ገዳማትን ስንረዳ፣ በዓታቸውን ስናጸና የገዳማውያኑ ጸሎትና በረከት ይደርሰናል፡፡     ድጋፍ ለማድረግ:-ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 1000442598391 ወይም አቢሲኒያ ባንክ 141029444 የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444