uk
Feedback
Sheger Press️️

Sheger Press️️

Відкрити в Telegram

Official channel of sheger press Contact @Birukepromo

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Sheger Press️️

Канал Sheger Press️️ (@sheger_press) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 35 936 підписників, посідаючи 7 058 місце в категорії Новини і ЗМІ та 926 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 35 936 підписників.

За останніми даними від 08 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -246, а за останні 24 години на -10, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 17.03%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 11.65% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 6 121 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 4 188 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 27.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
Official channel of sheger press Contact @Birukepromo

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 09 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Новини і ЗМІ.

35 936
Підписники
-1024 години
-57 днів
-24630 день
Архів дописів
እናቱን ላጣው ተማሪ ካሊድ ቃሲም የመኖሪያ ቤት ሊገነባለት ነው ​በቅርቡ እናቱን በሞት ላጣው ተማሪ ካሊድ ቃሲም፣ በሸገር ከተማ ኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ የመኖሪያ ቤት ሊገነባለት መሆኑ ተነገረ። የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ቤቱን ሙሉ በሙሉ ገንብቶ ለማስረከብ ቃል የገባ ሲሆን፣ የኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ደግሞ ለቤት ግንባታው የሚሆን መሬት በይፋ አዘጋጅቶ አስረክቧል።

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ🙏 ሚካኤል ማለት “ከመ እግዚአብሔር” እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው?” ማለት ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔርን ገናንነትና እሱን የሚመስል አምላክ እንደሌለ የሚያመለክት ነው፤ እንደ እግዚአብሔር ያለ ቅዱስ ንጹሕ ርህሩህ ኃይል ረቂቅ ማነው? መልሱ የለም ነው፡፡ በትህትናው ልዕልናን ያገኘው ቅዱስ ሚካኤል በእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠው ክብር ከማንኛውም መልአክ የበለጠ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ አስቀምጦታል፡፡ ቅዱስ ሚካኤል የስሙ ዘርፍ ሆነው የሚጨመሩ መጠሪያዎች አሉት እነዚህም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠውን የባለሟልነትና ክብር የሚገልጹ ናቸው፡፡ ይኸውም መልአከ ኃይል፣ መጋቤ ብሉይ፣ መልአከ ምክሩ ናቸው፡፡ መልአከ ኃይል የተባለው እግዚአብሔር በሱ አማካይነት ታላላቅ ሥራዎችን በመሥራት ኃይሉን ስለገለጸ፣ ዲያብሎስን ከነሠራዊቱ ስላሸነፈ ነው፡፡ መላእክትን ማክበርና መታዘዝ እንደሚገባ እግዚአብሔርም ነግሮናል፡፡ በዘጸ.23÷20-22 “በመንገድህ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ሥፍራ ያገባህ ዘንድ እነሆ እኔ መልአክን በፊትህ እሰዳለሁ፤ በፊቱ ተጠንቀቁ፤ ቃሉንም አድምጡ፤ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት፤ አንተ ግን ቃሉን ብትሰማ፣ ያልሁህንም ሁሉ ብታደርግ፣ ጠላቶችህን እጣላቸዋለሁ፣ የሚያስጨንቁህንም አስጨንቃቸዋለሁ፣ መልአኬ በፊትህ ይሄዳል” በማለት ለሙሴ ተናግሯል፡፡ ይህ ቃል ለሙሴና ለሕዝቡ ብቻ ተነግሮ ያበቃ ሳይሆን እስከዛሬና ወደፊትም የሚቀጥል ነው፡፡ መጋቤ ብሉይ የተባለበት ምክንያት በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከእግዚአብሔር እየተላከ ብዙ ታላላቅ ሥራዎችን የሠራ በመሆኑ ነው፡፡ መልአከ ምክር ወይም የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ የተባለበት ምክንያት፣ እግዚአብሔርን በምክሩ ይረዳዋል ለማለት ሳይሆን እግዚአብሔር የሚሠራውን ሥራ ለወዳጁ ለቅዱስ ሚካኤል ይገልጽለታል በሱም አማካኝነት ይሠራል ለማለት ነው፡፡ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ የሚለው በመላእክት ሁሉ ላይ በእግዚአብሔር የተሾመ ማለት ነው፡፡ መላእክት አለቆቻቸውን ያከብራሉ፤ ለእነሱም ይታዘዛሉ፡፡ ቅዱስ ሚካኤል የመላእክት ሁሉ አለቃ ስለሆነ ከትእዛዙ አይወጡም፤ ሠራዊተ መላእክት የሚያከብሩትንና የሚታዘዙለትን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን እኛም እንደ እነርሱ እናከብረዋለን እንታዘዘዋለን፡፡ ይህን ያመኑ ገዳማውያንም ሌሊትና ቀን ሚካኤል ሆይ አማልደን ይሉታል፡፡ ከጸሎታቸው በረከት እንድንካፈል ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡ ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 1000442598391 ወይም አቢሲኒያ ባንክ 141029444 የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

photo content

አቶ ደሳለኝ ጫኔ ከቀጥተኛ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ራሳቸውን ማግለላቸውን አስታወቁ ​ባለፉት አምስት ዓመታት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የነበሩት ታዋቂው ተቃዋሚ ፖለቲከኛ አቶ ደሳለኝ ጫኔ፣ የፓርላማ ቆይታቸውን ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ከማንኛውም ቀጥተኛ የፖለቲካ እንቅስቃሴ መውጣታቸውን በይፋ ገለጹ። በትናንትናው ዕለት የምክር ቤቱ ዘመን ማክተሙን ተከትሎ ውሳኔያቸውን ያሳወቁት አቶ ደሳለኝ፣ ለጊዜው በማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ውስጥ በአባልነትም ሆነ በደጋፊነት እንደማይሳተፉ አስታውቀዋል። ​ቀደም ሲል በዩኒቨርሲቲ መምህርነት እና በሲቪክ ማኅበራት መሪነት ያገለገሉት ምሁር ፣ ባለፉት ስምንት ዓመታት በፖለቲካ አመራርነት እንዲሁም የባሕር ዳር ከተማ መራጮችን በመወከል በፓርላማ በንቁ ተቃዋሚነት አገልግለዋል። በዚህ ጉዟቸው ወቅትም ለ45 ቀናት መታሰራቸውን ጠቅሰዋል። ​   ከ10 ዓመታት የፖለቲካ ድካም መልስ ወደ ግሉ ዘርፍ  በመግባት በሙያቸው ሀገርን ለማገልገልና ለቤተሰባቸው ጊዜ ለመስጠት መወሰናቸውን አስታውቀዋል። ከተቃውሞ ፖለቲካው ቢወጡም፣ በሀገራዊ የሰላም እና የብሔራዊ ውይይት ጉዳዮች ላይ በሙያቸው አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል።

አቶ ደሳለኝ ጫኔ ከቀጥተኛ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ራሳቸውን ማግለላቸውን አስታወቁ ​ባለፉት አምስት ዓመታት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የነበሩት ታዋቂው ተቃዋሚ ፖለቲከኛ አቶ ደሳለኝ ጫኔ፣ የፓርላማ ቆይታቸውን ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ከማንኛውም ቀጥተኛ የፖለቲካ እንቅስቃሴ መውጣታቸውን በይፋ ገለጹ። በትናንትናው ዕለት የምክር ቤቱ ዘመን ማክተሙን ተከትሎ ውሳኔያቸውን ያሳወቁት አቶ ደሳለኝ፣ ለጊዜው በማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ውስጥ በአባልነትም ሆነ በደጋፊነት እንደማይሳተፉ አስታውቀዋል። ​ቀደም ሲል በዩኒቨርሲቲ መምህርነት እና በሲቪክ ማኅበራት መሪነት ያገለገሉት ምሁር ፣ ባለፉት ስምንት ዓመታት በፖለቲካ አመራርነት እንዲሁም የባሕር ዳር ከተማ መራጮችን በመወከል በፓርላማ በንቁ ተቃዋሚነት አገልግለዋል። በዚህ ጉዟቸው ወቅትም ለ45 ቀናት መታሰራቸውን ጠቅሰዋል። ​   ከ10 ዓመታት የፖለቲካ ድካም መልስ ወደ ግሉ ዘርፍ  በመግባት በሙያቸው ሀገርን ለማገልገልና ለቤተሰባቸው ጊዜ ለመስጠት መወሰናቸውን አስታውቀዋል። ከተቃውሞ ፖለቲካው ቢወጡም፣ በሀገራዊ የሰላም እና የብሔራዊ ውይይት ጉዳዮች ላይ በሙያቸው አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል።

እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከክፉ ነገር ሁሉ ትከልለን፤ ምልጃዋ እና ረድኤቷም አይለየን🙏 ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ በትንቢቱ  ኢሳ 7፡14 "ድንግል ትጸንሳለች፤ ወንድ ልጅም ትወልዳለች" ብሎ የተናገረላት ያቺ ድንግል በዚህች ዕለት ተወለደች፡፡ ይህች ቀን ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት በመዝ 44÷9 "የወርቅ ልብስ ተጎናጽፋ ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች"  ብሎ የተናገረላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተገኘችባት ናት፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም በራዕይ 12÷1 "ፀሐይን የተጎናጸፈች፣ ጨረቃን የተጫማች፣ አስራ ሁለት የክዋክብት አክሊል በራሷ ላይ ያላት" ብሎ የመሰከረላት የብርሃን እናቱ ድንግል ማርያም የተወለደችባት ቀን ናት፡፡ የእርስዋም ልደት እንደ እንግዳ ደራሽ  እንደ ውኃ ፈሳሽ ድንገት የተከሰተ ሳይሆን አስቀድሞ በትንቢት፣ በምሳሌና በራዕይ የሰውን ልጅ ድኅነት በጉጉት ሲጠባበቁ ለነበሩ ቅዱሳን ሲገለጽ የነበረ መሆኑን ቅዱስ መጽሐፍ እንዲህ ያስረዳናል፡፡ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግንቦት አንድ ቀን (የግንቦት ልደታ) የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት የሚከበርበት ዕለት ነው፡፡ ይህ ዕለት ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም ‹‹የመመኪያችን ዘውድ፣ የንጽሕናችንም መሰረት›› ያላት ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም የተወለደችበት ነው፡፡ ጠቢቡ ንጉስ ሰሎሞን በመኃልይ 4÷8 "ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ፡  ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ፡፡" ብሎ እንደተናገረ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት መሰረት የእመቤታችን የትውልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለው ተራራማ ሀገር ነው፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያም ግንቦት 1 ቀን በ15 ዓ.ዓ  ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በሊባኖስ ተራራ ተወልዳለች፡፡ ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ስለእመቤታችን ልደት "ማርያምሰ ተኀቱ እምትካት ውስተ ከርሱ ለአዳም ከመ ባሕርይ ጸዓዳ/ ማርያም ግን ከጥንት ጀምሮ በአዳም ባሕርይ ውስጥ እንደ ነጭ ዕንቁ ታበራለች፡፡  በማለት እርሷ በደፈረሰው ዓለም በንጽሕና፣ በቅድስናና በድንግልና ስታበራ እንደነበርና ኋላም የዓለም ብርሃን የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን መውለዷን አመስጥሮ ተናግሯል። ኢትዮጵያዊ ቄርሎስ የተባለው የነገረ ማርያም ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ሰሎሞን እመቤታችን በሊባኖስ እንደምትወለድ አስቀድሞ ሰሎሞን ስለእመቤታችን የተናገረውን ቃል መፈጸሙን ሲያመሰጠር "የአናብስት ልጅ አልኩሽ፡፡ ሙሽራዪት ሆይ ከሊባኖስ ተራራ ነዪ፤ ከአንበሶች ጒድጓድ ወጥተሽ ነዪ፤ ከምርጥ ነገድነት የተነሣ ከሚመካ ወገን የመወለድሽ ዜና እጅግ ግሩም ነው፡፡" ይላል፡፡ እመቤታችንም በሊባኖስ ተራራ እንድትወለድ ምክንያት የሆነው በማሕፀን ሳለች የአርሳባንን ልጅ ዓይን በማብራቷና ሳሚናስ የሚባለውን የጦሊቅን ልጅ ከሞት በማስነሳቷ አይሁድ በቅናት ተነሳስተውባቸው ስለነበር ሐናና ኢያቄም ወደ ሊባኖስ ተራራ እንዲሄዱ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለኢያቄም ተገልጾ ስለነገራቸው እንደሆነ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት ያስረዳሉ፡፡ ስለታላቅ መንፈሳዊ ተልዕኮ ሲባል ከሚያውቁት ቦታ መራቅን፣ ከለመዱት ቀዬ መሰደድን ከእመቤታችን የተረዱት ገዳማውያንም ዓለምን ንቀው ስሟን ስንቅ አድርገው ይመንናሉ። ገዳማቸውን ስንደግፍ ፣ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን። ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 1000442598391 ወይም አቢሲኒያ ባንክ 141029444 ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957

photo content

በአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% መደረጉ ተገለፀ‼️ የውል ምዝገባም ዛሬ ተጀምሯል ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቤት ኪራይ ገበያ ላይ የሚታየውን ያልተ
በአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% መደረጉ ተገለፀ‼️ የውል ምዝገባም ዛሬ ተጀምሯል ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቤት ኪራይ ገበያ ላይ የሚታየውን ያልተገባ አሰራር በዘላቂነት ለመግታትና የነዋሪዎችን የኑሮ ጫና ለማቃለል ያለመ አዲስ መመሪያ ይፋ አድርጓል። በዚህም መሠረት ለ2019 በጀት ዓመት የሚተገበረው ዓመታዊ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ብቻ ሆኖ እንዲገደብ መወሰኑን የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል። * ቀደም ሲል በወጣው የቤት ኪራይ ቁጥጥር አዋጅ መሠረት፣ የአከራይና ተከራይ አዲስ የውል እድሳት ምዝገባ ከዛሬ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም ክፍለ ከተሞች በሚገኙ የቤቶች አስተዳደር ፅሕፈት ቤቶች በይፋ መተግበር ጀምሯል። * ቢሮው እንዳመለከተው፤ ይህ የዋጋ ማስተካከያ የተደረገው በዘፈቀደ ሳይሆን፣ የሕዝቡን እውነተኛ የመክፈል አቅምና ወቅታዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ ያገናዘበ ሰፊ ሳይንሳዊ ጥናት ከተካሄደ በኋላ ነው። * አዲሱ አሰራር በአንድ በኩል አከራዮች ፍትሐዊና ተመጣጣኝ ገቢ እንዲያገኙ የሚያስችል ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ ተከራዮች ካልተገባ የዋጋ ጭማሪና ከማኅበራዊ ቀውስ ድነው የተረጋጋ ሕይወት እንዲመሩ ያግዛል። "የአከራይ-ተከራይ ግንኙነትን በሕግ ማዕቀፍ በመምራት የጋራ ተጠቃሚነትን እናረጋግጣለን!" ይህ ርምጃ በከተማዋ እየተስተዋለ ያለውን የኑሮ ውድነት ጫና በከፍተኛ ደረጃ የመቀነስ፣ የጎላ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ፋይዳዎች እንዳሉት ተገልጿል። የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት የጭማሪው ማሳያ ምሳሌዎች (በ11.5% ስሌት መሠረት)፦ አዲሱ አዋጅ በሚፈቅደው ከፍተኛው የ11.5% የኪራይ ጭማሪ ጣሪያ መሠረት የወደፊቱ ክፍያ በሚከተለው መልኩ ይተመናል፦ 1. በአሁኑ ወቅት የቤት ኪራይ  15,000 ብር ለሚከፍሉ ተከራዮች ፦ ህጋዊው የጭማሪ መጠን 1,725 ብር ብቻ ስለሚሆን አዲሱ ጠቅላላ የቤት ኪራይ 16,725 ብር ይሆናል ማለት ነው። 2. በአሁኑ ወቅት የቤት ኪራይ 10,000 ለሚከፍሉ ተከራዮች ህጋዊው የጭማሪ መጠን 1,150 ብር ብቻ ስለሚሆን አዲሱ ጠቅላላ የቤት ኪራይ 11,150 ብር ይሆናል ማለት ነው። 3. በአሁኑ ወቅት የቤት ኪራይ 20,000 ብር ለሚከፍሉ ተከራዮች ህጋዊው የጭማሪ መጠን 2,300 ብር ብቻ ስለሚሆን አዲሱ ጠቅላላ የቤት ኪራይ 22,300 ብር ይሆናል። 4. በአሁኑ ወቅት የቤት ኪራይ 5,000 ብር ለሚከፍሉ ተከራዮች ህጋዊው የጭማሪ መጠን 575 ብር ብቻ በመሆኑ፣ አዲሱ አጠቃላይ ክፍያቸው ከ 5,575 ብር ይሆናል::

የመቅጃ ማሽኖች ልኬት ችግር በታየባቸው ማደያዎች ላይ ተገቢው የህግ እርምጃ ተወስዷል ተባለ በአዲስ አበባ ከተማ በነዳጅ ማደያዎች ላይ በተከናወነው የመቅጃ ልኬት ምርመራ፣ የመቅጃ ማሽኖች ልኬት ችግር በታየባቸው ማደያዎች ላይ ተገቢው የህግ እርምጃ ተወስዷል ሲል የአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ አሳወቀ ፡፡ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ወ/ሮ ሃላፊ ሀቢባ ሲራጅ እንደገለጹት፣ በሁለት ነዳጅ ማደያዎች የመቅጃ ማሽን የልኬት ችግር በመገኘቱ ከነዳጅ አቅርቦት ለሁለት ወራት እንዲታገዱ ተደርጓል። እርምጃ የተወሰደባቸው የነዳጅ ማደያዎች በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ጋርመንት አካባቢ የሚገኘው ኖክ ነዳጅ ማደያ እና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው አልፋ ነዳጅ ማደያ ናቸው ብለዋል። እንዲሁም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ተባረክ ነዳጅ ማደያ ከነዳጅ አቅርቦት ለአንድ ወር እንዲታገድ ተደርጓል የተባለ ሲሆን፣ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቱሉ ዲምቱ የሚገኘው የተባበሩት ነዳጅ ማደያ እና በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በካዛንቺስ ሱፐር ማርኬት አካባቢ የሚገኘው ኦላ ነዳጅ ማደያ የመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ አክለውም፣ ቢሮው በከተማው ውስጥ ልኬትን በማዛባት ፍትሃዊ የንግድ ውድድርን የሚያደናቅፉ ድርጊቶችን በሚፈጽሙ ነዳጅ ማደያዎች ላይ የጀመረውን የክትትልና የሕግ ማስከበር እርምጃ ይበልጥ በማጠናከር እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከክፉ ነገር ሁሉ ትከልለን፤ ምልጃዋ እና ረድኤቷም አይለየን🙏 በመጽሐፍ ቅዱስ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ያህል ትንቢት የተነገረላት ስለእርሷ የተጻፈላት ሴት የለችም። በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብዙ ምሳሌዎች ተጠቅሰዋል፤ የኖኅ መርከብ፣ ሰላማዊት ርግብ፣ የአብርሃም ድንኳን፣ ሙሴ በሲና ያያት ሐመልማል፣ ጽላተ ሙሴ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሐውልት፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ፣ የአሮን በትረ፣ የጌዴዎን ፀምር፣ የኖኅ የቃል ኪዳኑ ቀስተ ደመና፣ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ያያት መሰላል፣ የነቢዩ ኤልሳዕ ማሰሮና ሌሎች ምሳሌዎች በሰፊው የተነገሩላት የተጻፉላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ቤተ ክርስቲያን እርስዋን ለመጥራት የምትጠቀምባቸው ቅጽል ስሞቿና ውዳሴዎቿ ምንኛ ድንቅ ቢሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ገላጭነት በቅዱሳን የተነገሩ ምስጋናዎቿስ እጅግ ቢለዩ የክብሯን ያህል የሚገልጿት አይደሉም፡፡     እርሷ የሰው ሁሉ ረዳትና ርኅሩኅ እናት ናት፤ የብርሃን፣ የምሕረት፣ የድኅነትና የአማናዊው ወይን እናት ናት። ከንጉሡ በስተቀኝ የምትቆመው ንግሥት እርስዋ ናት፤ በመስቀል ስር የተቀበልናት የሁላችንም እናት እርሷ ናት፤ እርሷ ዘለዓለማዊ ድንግል ናት፤ እርሷ የእግዚአብሔር ጸጋ የሞላባት ንጽሕት ቅድስት ድንግል ናት፡፡ ከፍጥረት ሁሉ ተለይታ ወላዲተ አምላክ ለመሆን የተመረጠችበት አንዱ ምክንያት እመቤታችን እጅግ ትሑት፣ ፍጽምትና ንጽሕት ስለሆነች ነው። በሉቃስ 1÷48 እንደተጻፈው የአምላክ እናት እንደምትሆን ተነግሯት እንኳን ክብር ይግባትና ከመኩራትና ሌሎችን ከመናቅ ይልቅ ዘመዷ ኤልሳቤጥን ልትጠይቃት ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ወጣች፡፡ ከኤልሳቤጥ ፍጹም ምስጋናና በማሕጸን ያለው ዮሐንስ የሰላምታ ድምጿን ሰምቶ መዝለሉንከሰማች በኋላም “የባሪያይቱን መዋረድ ተመልክቷልና” በማለት በትሕትና ምስጋናዋን አቀረበች እንጂ የትዕቢት ቃል ከአፏ አልወጣም፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ “እርሷ በእግዚአብሔር ዓይን በታየ የቅድስና ውበት የተሞላች ነበረችና በእርሷ ንጹሕ ማሕፀን ሊያድር ወደደ፤ እንደ ድንግል ማርያም ራሱን ዝቅ ያደረገ ትሑት ማንም የለም” ይላል። ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም “በትሕትና የተናገርሽ ተራራ ሆይ…” ብሎ ያመሰገናት ይህች ድንግል ከተራሮች አናት ሁሉ ከፍ ያለች ስትሆን ራሷን ዝቅ አድርጋ “እንዲህ ያለ የምስጋና እጅ መንሻ እንደምን ይደረግልኛል” የሚል ምላሽ ለቅዱስ ገብርኤል ሰጠችው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ማርያም ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛው አምላክ ልጇ ነውና ማርልኝ ስትለው ምልጃዋ ፍጹም ነው፡፡ በእግዚአብሔር መመረጧ፣ ከሴቶች ሁሉ መለየቷ፣ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ መሆኗ ይህን ክብር አጎናጽፏታልና፡፡ ገዳማውያንም ይህን ልዩ እናትነቷንና ቅድስናዋን አምነው ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሯታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡ ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 1000442598391 ወይም አቢሲኒያ ባንክ 141029444 ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957

photo content

ያልታከመ የማህፀን ኢንፌክሽን መካንነትን ሊያስከትል ይችላል ተባለ   በባክቴሪያ ፣በፈንገስ እና በቫይረስ አማካኝነት የሚከሰት የሴቶች የመራቢያ አካል ወይንም የማህፀን ኢንፌክሽን ህክምና ካላገኘ እና በተደጋጋሚ የሚከሰት ከሆነ መካንነትን ሊያስከትል እንደሚችል ከብስራት ሬዲዮ ጋር ቆይታ ያደረጉት የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ታዘባቸዉ ዉዴ ገልፀዋል።   የማህፀን ወይንም ብልት አካባቢ የሚከሰት ኢንፌክሽን በርካታ ሰዎችን ከሚያጠቁ የኢንፌክሽን አይነቶች መካከል ዋነኛዉ መሆኑ ተገልጿል ።ለማህፀን ኢንፌክሽን አጋላጭ የሚሆኑ በርካታ ምክንያቶች መኖራቸዉን የሚገልፁት ዶክተር ታዘባቸዉ በግብረ ስጋ ግንኙነት የሚተላለፉ እንደ ክላሚዲያ እና ጎኖሪያ ያሉ ባክቴሪያዎች ዋነኞቹ መሆናቸዉን አስገንዝበዋል ።   በአብዛኛዉ መካንነትን ሊያስከትሉ የሚችሉትም በባክቴሪያ አማካኝነት የሚከሰቱ ኢንፌክሽኖች ናቸዉ። የማህፀን ኢንፌክሽን ከመከሰቱ አስቀድሞ መከላከል ዋነኛዉ መፍትሄ መሆኑን ዶክተር ታዘባቸዉ  ገልፀው ብልት አካባቢ የማሳከክ ፣የመቁሰል ፣የሆድ ህመም እና ሽንት በሚሸናበት ወቅት የማቃጠል ስሜት ሲኖር ወደ ጤና ተቋም በመሄድ ምርመራ ማድረግ እና ህክምና ማግኘት ተገቢ ነዉ ብለዋል ።

በሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች ከ65% በላይ መጠናቀቃቸው ተገለጠ!ሰኔ 30/2018 ዓ.ም | አዲስ አበባ ​በታሪካዊውና በታላቁ ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የተጀመሩ ግዙፍ የልማትና የህንጻ ግንባታ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም አሁን ላይ ከ65% በላይ መድረሱ ዛሬ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በተሰጠ ይፋዊ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተነገረ። ​በዚሁ የሃይማኖት አባቶችና ጥሪ የተደረገላቸው የሚዲያ ማህበረሰቦች  በተገኙበት መግለጫ ላይ፤ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ፣ የገዳሙ አባቶችና ጥሪ የተደረገላቸው ክቡራን እንግዶች ተገኝተዋል። በመግለጫውም ገዳሙ ከዚህ ቀደም የነበሩበትን ፈታኝ ችግሮች እንዴት በጽናት እንዳለፈና አሁን ላይ ወደ ምን የመንፈሳዊና ገዳማዊ ከፍታ ላይ እንደደረሰ ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል። ​ገዳሙ በሌሎች እጅ ሳይወድቅ ራሱን በራሱ ለመቻልና ዘላቂ ገቢ ለማስገኘት በወሰደው ቁርጠኛ አቋም ​በሐሙሲት እና በአዲስ አበባ ከተሞች ደረጃቸውን የጠበቁ የንግድ ሱቆችን በመክፈት ወደ ሥራ መግባቱ ተገልጧል። ​"ገዳማዊ ልማት ለቤተ ክርስቲያን ትሩፋት " ነው በሚለው ታላቅ መርህ መሰረት፥ ገዳሙ የሰው ኃይልን በሃይማኖት፥ በእውቀት፥ በምግባርና በግልጽነት ለመገንባት በቁርጠኝነት ተነስቷል። ​የነገውን ትውልድ በጥበብና በዕውቀት ለማነጽ ይረዱ ዘንድ በአሁኑ ሰዓት በገዳሙ ውስጥ ​ደረጃውን የጠበቀና ጥራት ያለው የአብነት ትምሕርት ቤት፥ ​ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ መሰናዶ ድረስ ማስተማር የሚችል ዘመናዊ ትምሕርት ቤት ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል። ​የገዳማውያኑንና የአባቶችን የመኖሪያ (በዓት) ችግር ከመቅረፍ ጀምሮ በመንፈሳዊ አገልግሎቱ ረገድ ትልቅ ስኬት እየተመዘገበም ይገኛል። ከዚህ ቀደም የእናቶች ገዳማውያን በዓት መጠናቀቁ የሚታወስ ሲሆን፣ አሁን ደግሞ የአባቶች ገዳማውያን በዓት ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል። ​ የገዳሙ ዋና ህንጻ ቤተ ክርስቲያን፥ ቤተልሔም፥ እንዲሁም የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ማረፊያ ህንጻ ግንባታዎች በአሁኑ ሠዓት በሥራ ላይ ይገኛሉ። ​ይህ የተጀመሩ ፕሮጀክቶች የ65% ማጠናቀቂያ ምዕራፍ የገዳሙን የነገ ብሩህ ተስፋ የሚያሳይ ሲሆን፣ ከዚህ በኋላም በገዳሙ ውስጥ የሚሰሩና እውን የሚሆኑ በርካታ ታላላቅ የልማት ሥራዎች እንደሚኖሩ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ በሰፊው ተመልክቷል። ​ በመርሐግብሩ ላይም የተገኙ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ "ሙት አንሳ እየለማ ነው ፥ በዓለም ያላችሁ መላው ኦርቶዶክሳዊያን እንኳን ደስ ያላችሁ፥ ያየነውን እንመሰክራለን የተጀመሩትንም ጨርሱ " ሲሉም በመርሐግብሩ ላይ ተናግረዋል።

photo content
+3

“ሻዕቢያ እና ወያኔ፣ ከሱዳን ጋር ተባብረው” መንግስትን የመጣል “ምኞት” እንዳላቸው ጠ/ሚ አብይ ተናግረዋል በትግራይ ክልል ዳግም ጦርነት እንዲቀሰቀስ “ሰፊ ፍላጎት” እንዳለ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ
“ሻዕቢያ እና ወያኔ፣ ከሱዳን ጋር ተባብረው” መንግስትን የመጣል “ምኞት” እንዳላቸው ጠ/ሚ አብይ ተናግረዋል በትግራይ ክልል ዳግም ጦርነት እንዲቀሰቀስ “ሰፊ ፍላጎት” እንዳለ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። በደርግ ዘመነ መንግስት “ሻዕቢያ እና ወያኔ፣ ከሱዳን ጋር ተባብረው” የወቅቱን አገዛዝ መጣላቸውን እና አሁንም ተመሳሳይ “ምኞት” እንዳለ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እነዚህ ወገኖች ብቻ ሳይሆኑ “ሌላም ቢጨመር በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ቅንጣት ታክል ስጋት የለም” ሲሉ ተደምጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ይህን ያሉት ተሰናባቾቹ የፓርላማ አባላት ላቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ እና ማብራሪያ ነው። ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 30፤ 2018 በተካሄደው የተወካዮች ምክር ቤት የመጨረሻ መደበኛ ስብሰባ ላይ 18 የፓርላማ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄ አቅርበዋል። የትግራይ ክልልን ወቅታዊ ሁኔታ በዛሬው ስብሰባ ያነሱት ገነት ቤተ የተባሉ የፓርላማ አባል፤ የፕሪቶሪያ ስምምነትን፣ “አክራሪ” ሲሉ የጠሩትን የህወሓት ቡድን ሰሞነኛ ድርጊቶችን፣ ያታጠቁ ኃይሎች እንቅስቃሴን እና የግጭት ቅስቀሳዎችን ጠቅሰዋል። በክልሉ “ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ” መንግስት በአሁኑ ወቅት እየወሰዳቸው ያሉ “ተጨባጭ እርምጃዎች እና የወደፊት እቅዶች” ምን እንደሆነ ጠይቀዋል። ለጥያቄው ምላሽ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ፤ በማብራሪያቸው በቅድሚያ ያነሱት በፌዴራል መንግሥት እና በሕወሓት መካከል በጥቅምት 2015 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ከተማ የተፈረመውን የግጭት ማቆም ስምምነት ነው። ስምምነቱ “እንደ ድርድር ብቻ መታየት ያለበት ጉዳይ ብቻ አይመስለኝም” ያሉት አብይ፤ “ብዙ ውጤት ያስገኘ” እንደሆነ ገልጸዋል። Via ኢትዮጵያ ኢንሳይደር

በገዳሙ ውስጥ የሚገኘው እና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የሚፈጸምበት በቅዱስ ሚካኤል ስም የተሰየመው ህንጻ ቤተ ክርስቲያን “ቤተ መቅደስ” ፣ እጅግ ጠባብ እና ከጥቂት ጊዜያት በኃላ የመፍረስ አደጋ የተጋረጠበት መሆኑ ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን በመረዳት፣የጥንታዊውን  የቤተ ክርስቲያን ቅርጽ ባልተወ መልኩ ፣ወደ ፊት የመነኮሳት እና ምዕመናን ቁጥር እንደሚጨምር በማሰብ ካለበት ስፋት በመጨመር እና ፣ መሰረታዊ የግንባታ ንድፍ በማውጣት፣ የሰርቬ ስራ በማከናወን ግንባታው ተጀምሮ የግንባታ ስራው ከ25 በመቶ በላይ ተከናውኗል፡፡ የግብጽ ቤተ ክርስቲያን በሁለት ታሪካዊ ክሥተቶች ተፈትና በነበረችበት ወቅት፣ ዳግም ሕዳሴዋን ያስገኙላት ሦስት ዐበይት ጉዳዮች ነበሩ። እነርሱም፦ የሥነ መለኮት ኮሌጅ መከፈት ፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች እንቅስቃሴ እና የበጎ አድራጊ ምዕመናን መገኘት ናቸው። ከዚህ የለውጥ ፋና ጀርባ የነበረውም ሊቀ ዲያቆናት ማር ሀቢብ ጊዮርጊስ ፣ ለትምህርት ሥርዓት ትኩረት በመስጠቱ ዛሬ ያሉ ግብጻውያን ከሀገራቸው አልፈው በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ፣ ቤተ ክርስቲያንን በማስፋፋት ፣ የተማረ እና ለቤተ ክርስቲያን ፍቅር የጸናበት ትውልድ በማፍራት ጠንካራ ሥርዓትን መዘርጋት ችለዋል። ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም መንፈሳዊ አገልጋዮችን ለማፍራት እና የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማስተላለፍ እንዲሁም የዕውቀት ማዕከል ለመሆን፣ ከመንግሥት ግዥ በፈጸምነው የሊዝ መሬት ላይ G+3 የአብነት ትምህርት ቤት ስራን እያከናወነ ሲሆን የግንባታ ስራውንም ከ70 በመቶ በላይ ማሳካት ተችሏል፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዘመናት ያጋጠሟትን ችግሮች ያለፈችው በዓለማዊውም በመንፈሳዊውም ዕውቀት በበቁ ልጆቿ ነውና፣ በሁለት እንደተሳለ ሰይፍ ፍጹም በተሰማሩበት ሁሉ ስኬትን የሚጎናጸፉ አገልጋዮችን ለማፍራት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ 12ኛ ክፍል የአስኳላ ትምህርት ቤት እየተሰራ ሲሆን ግንባታው የፊኒሽንግ ስራ ላይ የደረሰ እና ለትምህርት ቤቱ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን  በማሟላት ላይ ይገኛል፡፡እንዲሁም የትምህርት ቤቱ ካሪኩለም ስራ በመሰራት ላይ ይገኛል የጸበልተኞች እና የሱባኤ ማረፊያ ቤት ግንባታ ለማከናወን አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡ የውሃ እና የመብራት አገልግሎት እንዲያገኙ የማድረግ ሥራ፤ ማለትም የከርሰ ምድር ውሃ የማውጣት እና 8 ኪሎ ሜትር የሚረዝም የመብራት ዝርጋታ ስራ የሚከናወን ይሆናል፡፡ ከፍተኛ ደረጃ ክሊኒክ፣የንጽህና መጠበቂያ ውጤቶች ማምረቻ መጋዘን፣የምግብ ማቀነባበሪያ እየተሰሩ ካሉ እና በቀጣይ ከሚሰሩ ስራዎች መካከል ናቸው፡፡ በገዳሙ የተከናወነው የልማት ስራ አበረታች የሚባል ቢሆንም በተሻለ ፍጥነት ሥራዎች እንዳይከናወኑ ያደረጉ ተግዳሮቶችም ማጋጠማቸው አልቀረም። ከነዚሀም መካከል ፦ በግንባታ ዕቃዎች ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚስተዋል እጅግ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሬ። በገበያ ላይ የእቃዎች አቅርቦት እጥረት። ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ዛሬም ድረስ የራሳቸውን አሉታዊ ተጽዕኖ መፍጠራቸው። የነዳጅ እና የትራንስፖርት ዋጋ በእጅጉ መጨመር። በሶሻል ሚዲያ በተለይም ቲክቶክ ላይ ትክክለኛ ያልሆኑ፣ተጨባጭ ማስረጃ ሳይያዝ፣ የገዳሙ አባቶችንም ሆነ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ያሉ የሚመለከታቸውን አካላት ምንም አይነት መረጃ ሳይጠይቁ ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎችን ማሰራጨት ዛሬም እያጋጠመ ያለ ችግር ነው፡፡ እነዚህን ከላይ የተጠቀሱት በገዳሙ ላይ ሊሰሩ የታስቡ ፕሮጀክቶች በሁለት ዓመት ሰርተን የምናጠናቅቅ ሲሆን በገዳሙ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ከፍፃሜ አድርሶ ገዳማውያኑም ካሉባቸው ተደራራቢ ችግሮች እራሳቸውን እንዲችሉ እና ከልመና እንዲወጡ ለማድረግ በቀጣይ ለሚስሩት የልማት ሥራዎች ማከናወኛ 210,000,000 ብር (ሁለት መቶ አስር ሚሊዮን ብር) የሚያስፈልግ ሲሆን ይህን የማሰባሰብ ሥራም የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተፈፃሚ እስኪሆኑ ድረስ ተጠናክሮ ይቀጥላል። “እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ ፥ በጽድቄም ቀኝ እጅ እደግፍሃለሁ፤ (ኢሳይያስ 41:10)።” እንዲል ቃሉ፤ የሚያጋጥሙ ፈተናዎች ሁሉ በሃያሉ በልዑል እግዚአብሄር ቸርነት ፣ በእናታችን በቅድስት ድንግል ማርያም እና  በቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት  እየታለፉ ገዳማዊያኑን ካለባቸው የዓለም ፈተና ለመታደግ አሁንም ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ድንቅ ስራም እየተሰራ ይገኛል፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞንም “ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሄር ያበድራል ፣ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል” ይላል፡፡ ቅዱሳን አባቶች ጀምረው ሳይፈጽሙት የተውት ስራ የለምና እኛም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የአሥራት እና የቃል ኪዳን ልጆች በዚህ በእኛ ዘመን ፣ ለዓለሙ ሰላም፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ድኅነት ዘወትር የሚማጸኑት እነዚህ ገዳማዊያን፣ያሉባቸው ችግሮች ተፈተውላቸው፣ ዓለሙን ትተው የሄዱበትን የምንኩስና ህይወት ፈጣሪን መማጸን ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ፣ ሁሉም ምዕመን ባለው ጸጋ በዕውቀቱ፣ በጉልበቱ እና በገንዘቡ ድጋፍ እንዲያደርግ በልዑል እግዚአብሄር ስም ጥሪ እናቀርባለን።     የገዳማውያኑ ጸሎት እና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን !   ወስብሐት ለእግዚአብሔር ሰኔ ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል፣ አዲስ አበባ

ለገዳማውያኑ እንቅስቃሴ የማይመች እና አዳጋች የነበረው መንገድ 179 ሜትር ተራራ ተቦርቡሮ በአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል። የእናቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ተከናውኖ ሙሉ ቁሳቁስ ተሟልቶለት እየተገለገሉበት ይገኛል። ገዳማት መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ኃላፊነት የሚወጡበት ፣ በተፈጥሮ እና ሰው - ሰራሽ አደጋዎች የተጎዱ ማኅበረሰቦችን የሚረዱበት እና ሕገ ወንጌልን የሚፈጽሙበት አቅምን ለማግኘት ፣ የኢኮኖሚ ነጻነት አስፈላጊ ነው። ቅዱስ አትናቴዎስ “ገዳማዊ ሕይወት ጠንካራ ከሆነ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ እንዲሁ ጠንካራ ትሆናለች ፤ ነገር ግን ገዳማዊ ሕይወት መዳከም ከጀመረ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ትደክማለች።” በማለት የገዳማት መጠንከርን አጽንዖት ሰጥቶ ይናገራል። በዚህም መሰረት ገዳማዊያኑ በተደጋጋሚ የሚያጋጥማቸውን የምግብ አቅርቦት ችግር እና የአቅም ውስንነት በዘላቂነት ለመቅረፍ፣ ገዳማውያኑ እየሰሩ ቀጣይነት ያለው ገቢ እንዲያመነጩ ለማድረግ በማሰብ በሃሙሲት ከተማ የሸቀጣ ሸቀጥ እና የንዋያተ ቅዱሳት መሸጫ ሱቅ ተከፍቶ እየሰሩበት ይገኛሉ እንዲሁም አዲስ አበባ ላይ ደረጃውን የጠበቀ ሱቅ ተከፍቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ የእርሻ መሬት በመከራየት የእህል እና የጥጥ ምርቶችን በስፋ እያመረቱ ይገኛሉ፡፡ ገዳሙ በሃሙሲት ከተማ ላይ የእህል መጋዘን በመከራየት ያመረታቸው ምርቶች እንዲሁም ከገበሬ በመረከብ ለአከባቢው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በስፋት እያቀረበ ይገኛል፡፡ ግሸን እና ላሊበላ እንዲሁም የተለያዩ አብያተክርስቲያናት እና ገዳማት ላይ ገዳሙ ያመረታቸው ምርቶች ለሽያጭ እያቀረበ ይገኛል፡፡ ምንኩስና በምድር ላይ እየኖሩ ከምድራውያን ተለይቶ ከሰማያውያን ቅዱሳን መላእክት ጋር ኅብረት የሚፈጥሩበት እና የሚገናኙበት መንገድ ነው።ሥራ ደግሞ የቅድስና መድረሻ የዲያብሎስ ውጊያን ማምለጫ መንገድ ነው። እንደ ሃገራችን አባባል “ሥራ የፈታ መነኩሴ ቆቡን ቀዶ ይሰፋል።” እንዲል ፣ ያለ ሥራ መቀመጥ በገዛ ፍቃድ አዕምሮን ለሰይጣን ቤተ ሙከራነት ማስረከብ ነውና ፣ ሁሌ ትጥቃቸውን ይዘው ከእግሩ በታች በመሆን የሚተጉ ንቁዓን ወታደሮች ፤ ሀብት ንብረታቸውን ትተው ለዓለሙ ሙት የሆኑ መነኮሳት በተሰበሰቡበት ገዳም፦ እርሻ ፣ የእጅ ሥራ እንዲሁም ሌሎች ተግባራትን የሚያከናውኑበት ቦታ ሊኖራቸው ግድ ነው። ነገር ግን በሙት አንሣ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ያለው መልክአ ምድራዊ አቀማመጥ እና በረሃማነት ፣ ለእርሻ ሥራ ምቹ ባይሆንም ሴት መነኮሳዪያት የሚሠሩበት የተግባር ቤት ግንባታ ተጠናቆ ፣ የእደ ጥበብ ማምረቻ ማሽኖች ገብተው ገዳሙ ገቢ የሚያገኝበት እና ፣ መነኮሳዪታት የሰይጣንን ፈተና ድል የሚነሱበት ምቹ የሥራ ቦታ ተፈጥሯል። ከ20 ላላነሱ መነኮሳዪያት ሙያዊ ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች ቦታ ድረስ በማቅረብ ለረጅም ወራት ሥልጠና ተሰጥቷቸው ወደ ስራ ገብተዋል። የሻማ እና የጧፍ መስሪያ ማሽኖች ግዢ ተፈጽሞ ወደ ምርት ተገብቷል፣ በስፋት ለሽያጭ እየቀረበም ይገኛል፡፡ ገዳማት ከተፈጥሮ ጋር ባላቸው ትስስር ገዳማውያን ለሱባኤ የሚመርጡት ከከተማ የወጡ ፣ ዙርያቸውን በዕፀዋት የተሸፈኑ ገዳማትን ነው። ቤተክርስቲያን የነፍስን ቁስል ስታክም የተፈጥሮ መንፈስን ታድሳለች። ይህን ተመጋጋቢ ሂደት መነጠል የማይቻል ሲሆን ፣ በሙት አንሣ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ምድረበዳነት ይህን ሂደት አስቀርቶ ለዓመታት ቢቆይም ፣ በተሰሩ የአካባቢ ጥበቃ እና የአረንጓዴ ልማት ስራዎች ገዳሙ በእጽዋት እንዲሸፈን ከማድረጉም ባሻገር የአካባቢ የአየር ንብረት ጥበቃ ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ማለት ይቻላል። ወደ ገዳሙ የሚያደርስ 8 (ስምንት) ኪሜ ደረጃ አንድ የጠጠር መንገድ ተሰርቶ ለአካባቢው ማህበረሰብ ጭምር አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል። ለእናቶች መነኮሳይት ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ ሻወር እና መጸዳጃ ቤት ተገንብቶ እናቶች እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡ ለግንባታ አገልግሎት የሚውሉ የሲሚንቶ ማቡኪያ ማሽን፣የብረታ ብረትና የእንጨት መስሪያ ማሽን ፣ ዊንች ማሽን ፣ ኮንክሪት ቫይብሬተር፣ኮምፓክተር እንዲሁም ዘመናዊ የብሎኬት ማምረቻ ማሽን  ግዥ ተፈጽሞ የፕሮጀክቱን ግንባታ ሙሉ ለሙሉ በራስ አቅም እየተሰራ ይገኛል፡፡ ከመንግሥት ተቋማት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶችን በማድረግ የገዳሙ ህጋዊ ይዞታውን የመከለል፣የማስፋፋት እና ህጋዊ የማድረግ ሥራ ተከናውኗል። ለአብነት ት/ቤት ፣ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ት|ቤት ፣ ከፍተኛ ደረጃ ክሊኒክ እና ሌሎች አስፈላጊ የልማት ስራዎች የሚሰሩበት ህንጻ ግንባታ የሚገነባበት 30,000 (ሰላሳ ሺህ) ካሬ ሜትር ቦታ በሀሙሲት ከተማ ላይ እንዲሁም 717 (ሰባት መቶ አስራ ሰባት) ካሬ ሜትር ለገበያ ማዕከል ግንባታ የሚውል ቦታ ከመንግስት በሊዝ ግዥ ተከናውኗል፡፡ ገዳሙን ከማስተዋወቅ እና ግንዛቤ ከመፍጠር አኳያ በቤተክርስቲያን አገልግሎት ላይ የሚገኙ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የሚመለከታቸው የወረዳ ቤተ ክህነት፣ የሃገረ ስብከት እና የጠቅላይ ቤተ ክህነት አመራሮች ፣መምህራነ ወንጌል እና ዘማሪዎች ቦታው ድረስ ተገኝተው ገዳሙ ያለበትን ሁኔታ እና እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እንዲመለከቱ ተደርጓል። የቅዱስ ሚካኤልን በረከቱን ፣ ምልጃውን ፣ ተዓምሩን የሚገልጽ እና ገዳሙንም ለማስተዋወቅ በዘማሪ ዲያቆን አቤል መክበብ "ማር ሚካኤል" የተሰኘ ዝማሬ ተሰርቶ እና ቀረጻው በገዳሙ ላይ ተከናውኖ በማኅቶት ቲዩብ አማካኝነት ለህዝብ እንዲደርስ ተደርጓል፤ አሁንም በእይታ ላይ ይገኛል። ከገዳሙ ወደ ጸበል ቦታ እና ከጸበልተኞች ማደሪያ ወደ ጸበል ቦታ የሚወስደው አስቸጋሪ የተራራ መንገድ የነበረ ሲሆን፣ተራራው እየተቆረጠ የአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት ፤ 260 ሜትር የሚሆን መንገድ ስራው ተጠናቆ ለአቅመ ደካሞች እና በህመም ላይ ሆነው ፈውስን ለሚጠብቁ ጭምር ለእንቅስቃሴ ምቹ ሆኖ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡ የአባቶች እና የሊቃውንት በዓት የግንባታ ሥራ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡ ለአባቶች መነኮሳት ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ ሻወር እና መጸዳጃ ቤት ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ የአባቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ሥራ ተጠናቆ አስፈላጊው ቁሳቁስ ተሟቶለት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ መነኮሳቱ ጉባኤዎችን፣ውይይቶችን ለማድረግ፣መንፈሳዊ ትምህርትን ለመስጠት የሚገለገሉበት ደረጃውን የጠበቀ የመሰብሰቢያ አዳራሽም ግንባታው ተጠናቆ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡ ዓይነ ስውራን እና የማየት እክል ያለባቸው ምዕመናን መጽሐፍ ቅዱስ፣ የጸሎት መጻሕፍት እና ሌሎች መንፈሳዊ መጻሕፍትን በራሳቸው እንዲያነቡ፣በአምልኮ ሕይወት በእኩልነት እንዲሳተፉ እና ሁሉም ምዕመናን የመንፈሳዊ ትምህርት ተደራሽነት እንዲያገኙ ለማስቻል የብሬል መጽሐፍ ቅዱስ ፣ውዳሴ ማርያም እና መዝሙረ ዳዊት ግዢ ተፈጽሟል፡፡   ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ/ም በሚኒሊየም አዳራሽ ተጋባዥ እንግዶች እና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ገዳሙን ለማስተዋወቅ እንዲሁም ያለበትን ደረጃ ለማሳየት መርሃ ግብር ተዘጋጅቶ ግንዛቤ ለመፍጠር ጥረት ተደርጓል፡፡ “መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት፤ ተስፋን ሳንቆርጥ በጊዜው እናጭዳለንና፤ እንዲል (ገላትያ 6፥9) ።” ጅምራቸው መልካም፣ግንባታቸውም በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ የሚገኙ ስራዎችም ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ሰዓት “ገዳማዊ ልማት ለቤተክርስቲያን ትሩፋት” በሚል ንቅናቄ እየተሠሩ ካሉ ሥራዎች መካከል፡-

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን   ብጹዕ አባታችን አቡነ  መርቆሪዮስ ፣ የካናዳ ሐገረ ስብከት ሊቀጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል መንፈሳዊ ተልዕኮ ተቀብላችሁ ልዑል እግዚአብሔር በሰጣችሁ ጸጋ በተለያየ ስፍራ የምታገለግሉ ሊቃውንተ ቤተ-ክርስቲያን ጥሪ የተደረገላችሁ ተጋባዥ እንግዳዎች ፣ የመንግስት እና የግል ሚዲያ ተቋማት ፣ ጥሪያችንን አክብራችሁ ስለተገኛችሁ በልዑል እግዚአብሔር ስም ልባዊ ምስጋናችንን ለማቅረብ እንወዳለን።   "ጾም የነፍስ ምግብ ነው፤ ለፈተናም መቋቋሚያ ጥንካሬን ይሰጣል።" እንዲል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ።" እኛ ኦርቶዶክሳዊያን የሐዋሪያት ጾም ላይ እንገኛለን፡፡ የሰኔ ጾም (ጾመ ሐዋርያት) ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰባቱ አዋጅ አጽዋማት አንዱ ሲሆን፣ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉና ለስብከተ ወንጌል ከመሰማራታቸው በፊት የጾሙት ጾም ነው።ይህ ጾም እንደ እምነቱ አስተምህሮ ለሁሉም ክርስቲያን የተሰጠ የበረከት ጾም ነው። ይህን ጾም እንድንካፈል ለፈቀደልን ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ይግባው፤ለጾሙ ፍችም በሰላም ያድርሰን እያልኩ፣መግለጫው የተዘጋጀው በጽሁፍ ስለሆነ በተዘጋጀበት አግባብ ይቀርባል፡፡ በወልድ ውሉድ ፣ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባለ ሁሉ ፣ አምላኩን በንጽሐ ነፍስ ፣ በንጽሐ ሥጋ የሚያገለግልበት እና ፣ ከራሱ ከፈጣሪው መድሐኒዓለም ክርስቶስ ዘንድ የተሰጠው የጸጋ አገልግሎት፣ነገር ግን ጥቂቶች ብቻ የሚያገኙት ፤ መጨከንን ፣ ጥብዓትን ፣ ትሕርምትን እና ትዕግሥትን የሚጠይቅ ሕይወት ፣ የምንኩስና ሕይወት እና ሥርዓት ነው።የምንኩስና ሕይወት እና የገዳማዊ ሥርዓት በቅዱሳን አባቶች አባ እንጦንስ እና አባ መቃርስ የተጀመረ ሲሆን ፣ ሕይወቱም ሥርዓቱም በቀኖና ቤተክርስቲያን የተደነገገ እና የጸደቀ ሕግ ነው። በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ፣ ገዳም የእኔ የግሌ የሚሉት ንብረት የሌለበት፣ ሁሉ በማኅበር በአንድነት በጸሎት በስራ እየተጉ ፍጹም የዓለምን ኃላፊነት ተረድተው ፣ የማታልፍ የእግዚአብሔር መንግስት እንዳለች በመገንዘብ ዘወትር በቀኖና ተወስነው የሚኖሩበት የቅዱሳን መኖሪያና ጸጋ እግዚአብሔር የማይለይበት የዲያቢሎስ ፈተና የሚበዛበት ስፍራ ነው።   ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ በመሆኑ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ አርአያ ሆኖን ፣ በገዳመ ቆሮንጦስ ከዲያቢሎስ ይፈተን ዘንድ ተቀመጠ (ማቴ. 4፡ 1-11) ፈታኝ ዲያቢሎስንም ድል አደረገው ፣ ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ ሆኖ የመሰረተልን አምላካችን አርአያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ዛሬም እርሱን በመከተል ገዳማዊ ሕይወት ለትሩፋት መስሪያ ፣ ለንስሃ ሕይወት ማቆያ ፣ ለበረከት ለረድኤት የአምላካችንን አርአያነት ተከትለው አባቶች እናቶች በገዳም ተወስነው ይገኛሉ።   በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ “ገዳማዊ ህይወት” ራስን ለእግዚአብሔር በማስገዛት ትህትናን ገንዘብ አድርጎ እያንዳንዷን ሰዓት አንደበትን ፣ ጉልበትን እና ሃሳብን ለእግዚአብሔር በመስጠት የዓለም ዝና ሃብት ንብረት አላፊ የሆነውን ንግሥና ውበትን በመናቅ ቤተሰብ እና ዘመድን ተለይቶ በመውጣት በገዳም ውስጥ በስርዓተ አበው ተወስኖ መስቀሉን ተሸክሞ መኖር መሆኑን ትናገራለች።   ገዳማት የቤተ-ክርስቲያናችን ስውር ጓዳዎችና የሚስጢር መዝገቦች ፣ የመማጸኛ ቅዱስ ስፍራዎች ፣ የቤ-ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎት መሰረት ፣ የተግባራዊ ክርስትና ምሳሌዎች እና የታላላቅ የቤተ-ክርስቲያን ሊቃውንት መፍለቂያዎች ናቸው።   እነዚህ አብያተ-ክርስቲያናት እና ገዳማት መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን እየሰጡ ፣ ትውልድንም በክርስቲያናዊ ስነ-ምግባር እያነጹ ይቀጥሉ ዘንድ ገቢ ያስፈልጋቸዋል። ይህንን ገቢያቸውን ከሚያገኙባቸው መንገዶች መካከል በራሳቸው አቅም ገቢ የሚያመነጩ ስራዎችን ማከናወን እንዲሁም ምዕመኑ በሚሰጡት መባ እና አስራት በኩራት ይጠቀሳሉ።   ይሁንና አንዳንዴ ተፈጥሮ ፊቷን ስታዞር እና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ሲበረቱ ሰው ሰራሽ ችግሮችም ሲጨመሩ፣ገዳማት የገቢ ምንጫቸውና ህልውናቸው ሙሉ በሙሉ ህዝበ ክርስቲያኑ በሚያደርገው ድጋፍ ላይ የተንጠለጠለ የሚሆንበት አጋጣሚ ይፈጠራል ፤  ከ160 በላይ ገዳማዊያን የሚገኙበት ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የገጠመው ችግርም በዚህ ደረጃ የሚገለጽ ነው።   በዚህ ገዳም የሚገኙ ገዳማውያን ከፀሃይ ፣ ከብርድ ፣ ከዝናብ የሚከላከል መጠለያ አጥተው በከፍተኛ ችግር እየተፈተኑ የሚገኙ በመሆኑ ፣ ገዳማውያኑ ከነዚህ ችግሮች እንዲወጡ እና በቀጣይም ገዳሙ ራሱን እንዲችል ለማድረግ ፣ በጠቅላይ ቤተ-ክህነት እውቅና እና በሐገረ ስብከቱ ፍቃድ ገዳሙ ብቻ የሚጠቀመው በገዳሙ ስም የተከፈቱ የባንክ አካውንቶች ይፋ ተደርገው ፣ በሕዝበ ክርስቲያኑ በሚደረገው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን ፣ ገዳሙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በወረዳ ቤተ-ክህነት ፣ በሐገረ ስብከት እና በጠቅላይ ቤተ-ክህነት ጸድቆ በሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና የቅርብ ክትትል እየተደረገበት ከምዕመናን በሚገኘው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል።   “ከእግዚአብሔር ዐይን የተሰወረ ምንም ፍጥረት የለም፤ ስለ ራሳችን መልስ መስጠት በሚገባን በርሱ ፊት ሁሉም ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው” (ዕብራውያን 4:13) እንዲል ቃሉ፣እኛም አጠቃላይ ፕሮጀክቱን በተመለከተ የተሰሩ ስራዎችን፣የተደረገውን ድጋፍ፣ በቀጣይ ስለሚከናወኑ ስራዎች እና ተያያዥ ጉዳዮችን በተለያዩ ጊዜያት ለምዕመኑ ይፋ እያደረግን፣እያሳወቅን ዛሬ ላይ ደርሰናል፡፡ዛሬ ስለ ፕሮጀክቱ እና የደረሰበትን ደረጃ በሚመለከት የምንሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለ4ኛ ጊዜ ሲሆን ይህም ምዕመኑ ፕሮጀክቱ የደረሰበትን ወቅታዊ የስራ ደረጃን እንዲገነዘብ ለማድረግ በማሰብ ነው፡፡       በገዳሙ የተያዙ የልማት ስራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ገቢ የማሰባሰብ ሂደት ዕቅዶችን በመንደፍ እና በመቅረጽ ተግባራዊ ለማድረግ ስንቀሳቀስ ቆይተናል፣አሁንም በመንቀሳቀስ ላይ እንገኛለን። ለአብነትም ገዳሙ ያለበትን አሁናዊ እና ተጨባጭ ሁኔታ የሚገልፁ እና የሚያሳዩ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማ ቀኖና እንዲሁም ትውፊት በጠበቀ መልኩ   በቴሌቪዥን ጥራታቸውን የጠበቁና ገላጭ የሆኑ ዶክመንተሪዎችን በማስተላለፍ ህብረተሰቡ መረጃው ኖሮት ድጋፍ እንዲያደርግ ጥረት ተደርጓል። ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ለታቀዱት የልማት ስራዎች የሚያስፈልገውን ገቢ ለማሰባሰብ ጥረት ተደርጓል፤እየተደረገም ይገኛል። በዚህም እስከ አሁን 52,640,000 ብር ( ሃምሳ ሁለት ሚሊዮን ስድስት መቶ አርባ ሽህ ብር)የገንዘብ ድጋፍ እና 11,320,000 ብር ( አስራ አንድ ሚሊዮን ሶስት መቶ ሃያ ሽህ ብር) የሚገመት የአይነት ድጋፍ ማሰባሰብ ተችሏል። በሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የተጀመረው ፕሮጀክት 2 ዓመት ከ 6 ወር ያስቆጠረ ሲሆን በእነዚህ ጊዜያት በመጀመሪያው እና በሁለተኛው ምዕራፍ የፕሮጀክቱን 65 % በላይ ማሳካት ተችሏል። ከእነዚህም መካከል፦   የእናቶች በዓት እና የእንግዳ ማረፊያ በጥሩ ሁኔታ ተገንብቶ እናቶች እየተገለገሉበት ይገኛል።

photo content
+3

"ኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ሥራ ቢኖርም ሰራተኛ ማግኘት በጣም ከባድ ሆኗል" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ሥራ ቢኖርም ሰራተኛ ማግኘ
"ኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ሥራ ቢኖርም ሰራተኛ ማግኘት በጣም ከባድ ሆኗል" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ሥራ ቢኖርም ሰራተኛ ማግኘት በጣም ከባድ ሆኗል አሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፥ ወላጆች ከከተማ ውጪ የሚሰሩ ሥራዎችን ወጣቶች እንዲሞክሯቸው ማበረታታት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡ ለአብነትም ‎በግንባታ ላይ በሚገኘው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቂ የሰው ኃይል ማግኘት አዳጋች መሆኑን ነው ያስረዱት፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የቤት ሰራተኝነት ሥራን የሚሰሩ ሰዎች ቁጥር እጅግ ጥቂት መሆኑን ጠቁመው፥ ለተመሳሳይ ሥራ ከሀገር የሚወጡ ዜጎች ቁጥር ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡ ‎ከሀገር የወጡ ወጣቶች በቀን ለ16 ሰዓታት ያህል ሰርተው ራሳቸውን ሲለውጡ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ወጣቶች ግን ጊዜን በአግባቡ የመጠቀም ክፍተት እንዳለባቸው ነው የገለጹት፡፡ ‎ ‎በሁለት እና ሶስት የሥራ ፈረቃዎች በመስራት አቅምን ማሳደግና መተጋገዝ ካልተቻለ የኑሮ ውድነት ከዚህ በላይ ሊሆን አንደሚችል አመልክተዋል፡፡