uz
Feedback
Dr. Eyob Mamo

Dr. Eyob Mamo

Kanalga Telegram’da o‘tish

Life skill development! You can contact me @DrEyobmamo

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Dr. Eyob Mamo analitikasi

Dr. Eyob Mamo (@dreyob) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 79 250 obunachidan iborat bo'lib, Taʼlim toifasida 1 942-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 407-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 79 250 obunachiga ega bo‘ldi.

26 Avgust, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -34 ga, so‘nggi 24 soatda esa -26 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 9.25% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 5.16% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 7 327 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 4 089 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 48 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Life skill development! You can contact me @DrEyobmamo

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 27 Avgust, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Taʼlim toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

79 250
Obunachilar
-2624 soatlar
-397 kunlar
-3430 kunlar
Postlar arxiv
ባለፈው ኃሙስ የጀመረው የአመራር እውነታዎች እና ልምምዶች” (Leadership Facts and Practices) የተሰኘው ስልጠኛ ዛሬ ሁለተኛ ክፍል ይቀጥላል፡፡ ያለፈው አምጧችሁ ከሆነና መሰልጠን ከ
ባለፈው ኃሙስ የጀመረው የአመራር እውነታዎች እና ልምምዶች” (Leadership Facts and Practices) የተሰኘው ስልጠኛ ዛሬ ሁለተኛ ክፍል ይቀጥላል፡፡ ያለፈው አምጧችሁ ከሆነና መሰልጠን ከፈለጋችሁ ዛሬ መቀላቀል ትችላላችሁ፡፡ ያለፈው ክፍለ ጊዜ voice recording and PDF note የ telegram ቡድኑን ስትቀላቀሉ ይገኛል፡፡ እሱን መከታተልና ለቀሩት ክፍለ-ጊዜዎች መዘጋጀት ይቻላል፡፡   የስልጠናው ርእስ፡- “የአመራር እውነታዎች እና ልምምዶች” (Leadership Facts and Practices) ስልጠናው የሚሰጠው፡- በዶ/ር ኢዮብ ማሞ ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በ online (telegram live) የስልጠናው ቀናት፡- ነሃሴ 14፣ ነሃሴ 21 እና ነሃሴ 28 (ሶስት የነሃሴ ወር ኃሙሶች) የስልጠናው ሰዓት፡- ለአራቱም ኃሙስ ምሽቶች ከ3፡00 እስከ 4፡30 (በኢትዮጲያ አቆጣጠር) ገለጻ:- 💡 ራስን መምራት (Leading Self) - ራሳችሁን የመምራት ጥበብ ካላዳበራችሁ ስሜታችሁ፣ ሁኔታዎች እና ሰዎች ይመሯችኋል፡፡ 💡 ሰዎችን መምራት (Leading Others) - ሰዎችን የመምራትን ብቃት ካላደበራችሁ ያላችሁ ተጽእኖ እየወረደ ይሄዳል፡፡ 💡 ስራን መምራት (Leading Work) - ስራችሁን የመምራት ክህሎት ካላዳበራችሁ ስኬታማነታችሁ እየደከመ ይሄዳል፡፡   በዚህ ስልጠና ለመሳተፍ፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡ Join now!!!

ወይ ስምህን ወይም ደግሞ አመልህን ቀይር! ታዋቂው ታላቁ አሌክሳንደር (Alexander The Great) በዘመኑ በውን የሚታወቀውን አብዛኛውን የአለም አካባቢ በታላቅ ሰራዊቱ በቁጥጥር ስር እንዳዋለ የሚነገርለት ዝነኛ ሰው ነበር፡፡ አንድ ጊዜ ለጦር ዝግጅት በማድረግ ላይ እንዳሉ በሌሊት በሰራዊቱ መካከል ለመዘዋወር ሲወጣ ተረኛ የነበረ አንድ ጠባቂ አንቀላፍቶ አገኘው፡፡ በወቅቱ ተረኛ ሆኖ ያንቀላፋ ጠባቂ የሞት ፍርድ ይጠብቀዋል፡፡ ታላቁ አሌክሳንደር ወደወታደሩ ሲጠጋ ወታደሩ በመንቃት ላይ ነበረና የሆነውን ነገር ሲያውቅ ሕይወቱን እንደሚያስከፍለው ስላሰበ በጣም ፈራ፡፡ ታላቁ አሌክሳንደር ለወታደሩ፡- “የጥበቃ ተረኛ ሆኖ ማንቀላፋት በምን እንደሚያስቀጣ ታውቃለህ?” አለው፡፡ ወታደሩ ድምጹና ሰውነቱ በፍርሃት እየተንቀጠቀጡ፣ “አዎን አውቃለሁ” አለው፡፡ ታላቁ አሌክሳንደርም ለወታደሩ፡- “ስምህ ማን ነው?” አለው፡፡ ወታደሩ፡- “ስሜ አሌክሳንደር” ይባላል” አለው፡፡ ታላቁ አሌክሳንደር እንደገና ለወታደሩ:- “ስምህ ማን ነው?” አለው፡፡ ወታደሩ አሁንም “ስሜ አሌክሳንደር ይባላል” ብሎ ደግሞ መለሰ፡፡ ታላቁ አሌክሳንደር ለሶስተኛ ጊዜ ጮክ ብሎ ወታደሩን፣ “ስምህ ማን ነው?” ብሎ ጠየቀው፡፡ ወታደሩም ለሶስተኛ ጊዜ፣ “ስሜ አሌክሳንደር ይባላል” ብሎ መለሰ፡፡ ታላቁ አሌክሳንደር ወታደሩን ትኩር ብሎና አፍጥጦ እየተመለከተው፣ “ወይ ስምህን ቀይር ወይም ደግሞ አመልህን ቀይር” አለው ይባላል (ምንጭ፡- Snopes.com)፡፡ ራሱ በትጋቱና በዲሲፕሊኑ የሚታወቀው ታላቁ አሌክሳንደር በስም ሞክሼው የሆነው ወታደር የሱን ስም ይዞ በአመሉ ግን ቸልተኛና እንቅልፋም መሆኑ ስላበሳጨው ነው “ስምህና አመልህ ስለማይመሳሰል አንዱን ቀይር” የሚልን መልእክት ያስተላለፈለት፡፡ በዘመናችን ሁላችንንም የሚያታግለን ችግር በላያችን ላይ የለጠፍነው ስም ከአመላችንና ከተግባራችን ጋር አብሮ ያለመሄድ ችግር ነው፡፡ ወንድም፣ ፍቅረኛ፣ የሃገር ዜጋ፣ የሕዝብ አገልጋይ፣ ሕዝብ ጠባቂ፣ መሪ . . . የሚሰጡንና የምንሸከማቸው ስሞች አስገራሚ ናቸው፡፡ ሆኖም፣ ስማችንና አመላችን (ተግባራችን) አብሮ ካልሄደ አንዱን መቀየር የግድ ነው፡፡ ስምህ “ወንድም” ከሆነ ወይ የወንድም አመል ይኑርህ አለዚያ አንደኛህን ስምህን ቀይር! ስምህ “ፍቅረኛ” ከሆነ ወይ የፍቅረኛ አመልና ባህሪይ ይኑርህ አለዚያ አንደኛህን ስምህን ቀይር! ስምህ “የሐገር ዜጋ” ከሆነ ወይ እንደ ጨዋ የሐገር ዜጋ መልካም አመል ይኑርህ አለዚያ አንደኛህን ስምህን (ዜግነትህን) ቀይር! ስምህ “የሕዝብ አገልጋይ” ከሆነ ወይ ትሁት፣ ሕዝብ አክባሪና ጨዋ አመል ይኑርህ አለዚያ ስምህንና የስራ ዘርፍህን ቀይር! ስምህ “የሕዝብ ጠባቂ” ከሆነ ንቁ፣ በጥቅም የማይደለልና ለሕዝቡ ሲል ራሱን የሚሰዋ ጠባቂ ሁን አለዚያ ስምህንና የስራ ዘርፍህን ቀይር! ስምህ “መሪ” ከሆነ ወይ ራስን መርቶ ሌላውን በምሳሌ የሚመራ አመልና ዲሲፕሊን ይኑርህ አለዚያ አንደኛህን ስምህን ቀይር! ስምህ ማን ነው? ሹመትህ ምንድን ነው? ስልጣንህ ምንድን ነው? ስራህ ምንድን ነው? ከሰዎች ጋር ያለህ ግንኙነት ምንድን ነው? ወይ ያንን ኑር አለዚያ አንደኛህን ስምህን፣ ስራህን፣ ዘርፍህንና የግንኙነትህን መልክ ቀይር! ወይ ስምህን ወደ አመልህና ወደተግባርህ አምጣው፣ ወይም አመልህንና ተግባርህን ወደስምህ ውሰደውና አንድ አይነት ሁን! በአጭሩ፣ ሰው ሁን!!! https://t.me/Dreyob https://m.youtube.com/user/naeleyob623 https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/

ወይ ስምህን ወይም ደግሞ አመልህን ቀይር!
ወይ ስምህን ወይም ደግሞ አመልህን ቀይር!

የመስከረም ወር Book Reading Challenge with Dr. Eyob ለመስከረም ወር reading challenge የተመረጠው መጽሐፍ፣ “ትኩረት” የተሰኘው ነው፡፡ ትኩረት ሁለት ገጽታዎች አሉት፦
የመስከረም ወር Book Reading Challenge with Dr. Eyob ለመስከረም ወር reading challenge የተመረጠው መጽሐፍ፣ “ትኩረት” የተሰኘው ነው፡፡ ትኩረት ሁለት ገጽታዎች አሉት፦ 1.     በየእለት ተግባራችን  - ይህ የትኩረት ሁኔታ በየቀኑ ባለን ኑሮ ከአላማችን አንጻር መገንባትንና በየእለቱ በሚከሰቱ ሁኔታዎች ሃሳባችን እንዳይበታተን የመጠበቃችንን ሁኔታ ያመለክታል፡፡ 2.    አጠቃላይ የሕይወት ዘይቤ - ይህ የትኩረት ሁኔታ ለአጠቃላይ የሕይወታችን እድገትና ለስኬታማነታችን ከማይጠቅሙ የሕይወት ዘይቤዎችና ልምምዶች ላይ ትኩረታችንን በማንሳት ወደ ዋናውና ወደ አስፈላጊው ዓላማችን ማዞርን ያመለክታል፡፡   መጽሐፉን ለማንበብ ከአሁኑ በመመዝገብ ራሳችሁን አዘጋጁ፡፡ የንባብ ወር - መስከረም / 2019 ለንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “ትኩረት” ንባቡ የሚጀመርበት ቀን - መስከረም 1 / 2019 ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - መስከረም 30 / 2019 ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡ Join now!!!

ውቅያኖሱ ጨዋማ መሆኑን ለማወቅ . . . “ውቅያኖሱ ጨዋማ መሆኑን ለማወቅ ሙሉውን ውቅያኖስ መጠጣት አያስፈልግም፤ አንድ ጉንጭ ብቻ ቀምሰህ እወቀውና መንገድህን ቀጥል”፣ ይባላል፡፡ ይህ አባባል ከሰዎች ጋር ግንኑነትን ስንመሰርት ምልክቶችን ማየትን፣ ከልምድ መማርን እና መቼ በግንኙነቱ መቀጠል እንዳለብን እና መቼ መራቅ እንደሚገባን የሚገልጽ አባባል ነው። አንድ ሰው ሆን ብሎ ከከዳችሁ፣ አስቦበት ካታለላችሁ፣ ደጋግሞ ከዋሻችሁ፣ በተንኮል ከተጠቀመባችሁ፣ እና ካለማቋረጥ የሚቆጣጠራችሁ ከሆነ ይህንን ችግር ለማረጋገጥ ተመሳሳይ ነገር እስከ 10 ጊዜ ደጋግሞ እስኪያደርግባችሁ መጠበቅ አያስፈልጋችሁም:: አንዳንድ ጊዜ አንድ ክስተት የሰዎችን የማይለወጥ ባህሪይ የማወቂያ ምልክት ይሆናል፤ ያው ነገር ደጋግሞ መከሰቱ ደግሞ ንድፍ (pattern) ሊታይና ጥንቃቄ ሊደረግበት ይገባል፡፡ የሰዎችን ቃላት ብቻ ሳይሆን ተግባራቸውንም ተመልከቱ፡፡ የሚነግሯችሁ ሌላ፣ የሚተገብሩት ሌላ ሲሆን ያንኑ የክህደት ተግባራቸውን እየተጎነጫችሁ መኖር የለባችሁም፡፡ አንድ ሰው “እወድሃ/ሻለሁ” የሚለው ቃል በድርጊቱ ካልተደገፈ፤ “እመነ/ኚኝ” የሚለው ንግግሩ በክህደት ተግባሩ ካፈረሰው ቃሉ ብቻ በቂ አይደለም ማለት ነው። በይቅርታ የምታልፉን የአንድ ጊዜ ስህተትና በሰዎቹ ላይ የምታዩትን የባህሪይ ሁኔታና ድግግሞሾች ለዩ፡፡ አንዳንድ ጊዜ እውነቱን አውቀን እንኳን መቀበል ስለማንፈልግ ተጨማሪ ማስረጃ እንፈልጋለን። “ምናልባት ይለወጣል።” “ምናልባት ይህ የመጨረሻው ጊዜ ነው።” “ምናልባት እኔ ተሳስቻለሁ።” “ምናልባት ብወደው ይለወጣል።” ነገር ግን የአንድን ሰው እውነተኛ ባህሪ በተስፋው ሳይሆን በተደጋጋሚ በሚያሳየው ድርጊት መለየት ይኖርባችኋል። ስለዚህ ምን እናድርግ? 1.      ይቅርታ ማድረግን እና ድንበር (የቀይ መስመር) ማበጀትን አታምታቱ ለሰዎች ይቅርታ አድርጉ፣ የሚጣስ ክልላችሁን ግን በሚገባ አስምሩ፡፡ ይቅርታ ማለት ድንበር የሌለውና ሰው መጫወቻ መሆን አይደለም። 2.     ትእግሥትን ራስን ለጉዳት ከማጋለጥ ጋር አታምታቱ ሰዎችን ታገሱ፣ ነገር ግን የማይቀለበስ ጉዳት እስከሚደርስባችሁ ድረስ አትጠብቁ፡፡ ትእግስት ማለት ራስን ለጥፋት ማጋለጥ ማለት አይደለም፡፡ 3.     ከሰው መራቅን እና ጥላቻን አታምታቱ ሰዎችን አትጥሉ፣ ነገር ለህልውናችሁ አደጋ ከሚሆን ሁኔታ ራሳችሁን ጠብቁ፡፡ ከጎጂ ሰው ርቀታችንን መጠበቅ ማለት በጥላቻ መሞላት ማለት አይደለም፡፡ አንዴ ባያችሁት ባህሪይ ወይም ተግባር ምክንያት ሰዎችን አትፈርጇቸው፡፡ ሆኖም፣ የምታዩትን የባህሪይ ድግግሞሽ በሚገባ በማጥናትና በመመርመር ተገቢውን ውሳኔ ውሰዱ። https://t.me/Dreyob https://m.youtube.com/user/naeleyob623 https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/

ውቅያኖሱ ጨዋማ መሆኑን ለማወቅ . . .
ውቅያኖሱ ጨዋማ መሆኑን ለማወቅ . . .

photo content

የትኩረት ሽሚያ! ባለንበት ዘመን ትኩረታችንን የሚሻሙ እና አንድን ነገር እንዳንገነባ የሚያደርጉን ተጽእኖዎች አሉብን፡፡ ትኩረት ማጣት በአንድ ጎኑ አንድን ነገር እንዳንጀምር ሲያደርገን፣ በሌላ ጎኑ
የትኩረት ሽሚያ! ባለንበት ዘመን ትኩረታችንን የሚሻሙ እና አንድን ነገር እንዳንገነባ የሚያደርጉን ተጽእኖዎች አሉብን፡፡ ትኩረት ማጣት በአንድ ጎኑ አንድን ነገር እንዳንጀምር ሲያደርገን፣ በሌላ ጎኑ ደግሞ የጀመርነውን ነገር እንዳንቀጥል ጫና ያሳድርብናል፡፡ አንዳን መንስኤዎች . . . 1. ከመጠን በላይ መረጃ መቀበል 2. የዲጂታል ልማድና ሱስ 3. ስኬት እንዳያመልጠን ብዙ ነገሮችን በአንድ ጊዜ ለመሥራት መሞከር 4. የአእምሮና የስሜት ጫና የሚስከትለው ጭንቀት፣ ፍርሃት እና የመሳሰሉት ሁኔታዎች 5. ማስቀደም ለምንፈልጋቸው ነገሮች ግልጽ የሆነ ቅደም-ተከተል አለመኖር ለመስከረም ወር የተዘጋጀላችሁ የንባብ መጽሐፍ ይህንን አስፈላጊ ልምምድ እንድታዳብሩ የሚረዳችሁ መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፉን ለማንበብ ከአሁኑ በመመዝገብ ራሳችሁን አዘጋጁ፡፡ የንባብ ወር - መስከረም / 2019 ለንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “ትኩረት” ንባቡ የሚጀመርበት ቀን - መስከረም 1 / 2019 ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - መስከረም 30 / 2019 ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡ Join now!!!

በሕይወታችን ያሉ ጥሩ ሰዎችን በቀላሉ ለማጣት ከፈለግን . . . 1. መልካምነታቸውን መልመድ ሰዎች የሚያደርጉልን በጎ ነገር፣ ፍቅር፣ ድጋፍና ታማኝነት ስንለምደው እና ምስጋና ማቅረብ ስንተው ሰዎቹን
በሕይወታችን ያሉ ጥሩ ሰዎችን በቀላሉ ለማጣት ከፈለግን . . . 1. መልካምነታቸውን መልመድ ሰዎች የሚያደርጉልን በጎ ነገር፣ ፍቅር፣ ድጋፍና ታማኝነት ስንለምደው እና ምስጋና ማቅረብ ስንተው ሰዎቹን ቀስ በቀስ እናጣቸዋለን። 2. ለጥቅማችን ብቻ መፈለግ እነሱን ከእኛ ጋር ስላላቸው ወዳጅነት ሳይሆን ጥቅም በምንፈልግበት ጊዜ ስንፈልጋቸው ሰዎቹን ቀስ በቀስ እናጣቸዋለን። 3. ደጋግመን መጉዳት እና አለመለወጥ ስናጠፋቸው “ይቅርታ” እያልን ተመሳሳይ ነገር ደግመን በማድረግ ትዕግስታቸውን ስንፈታተነው ሰዎቹን ቀስ በቀስ እናጣቸዋለን። 4. እነሱን አለመስማት የራሳችንን ሃሳብም ሆነ ስሜት እየገለጽን የእነሱን ስሜት ችላ የማለት፣ ንግግራቸውን የማቋረጥ ወይም ሁልጊዜ የራሳችንን ነገር ብቻ የማውራት ልማድ ካለብን ሰዎቹን ቀስ በቀስ እናጣቸዋለን። 5. ከጀርባቸው ስለ እነሱ ማውራት ስለ እነሱ ሁኔታም ሆነ ተግባር ያለንን ሃሳብምና አመለካከት ከእነሱ ጋር መወያየት ሲገባን ከሌላ ሰው ጋር ስለ እነሱ ስናወራ፣ ምንም እንኳን ለጊዜው ቢታገሱንም ሰዎቹን ቀስ በቀስ እናጣቸዋለን። በዚህ ምድር ላይ ሁል ጊዜ እንደሚገኝልንና እንደሚታገሰን ሰው አቅልለን የምናየው ነገር የለም፡፡ እነደዚህ አይነት ሰው ደግሞ የሚጠቅመንና የሚበጀን፣ አንዴ ካጣነው ደግሞ ደግመን ለማግኘት የሚያስቸግረን ነገር የለም፡፡ የሰዎች መልካምነትና ሁል ጊዜ መገኘት አይቅለልባችሁ! https://t.me/Dreyob https://m.youtube.com/user/naeleyob623 https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/

የመስከረም ወር Book Reading Challenge with Dr. Eyob ለመስከረም ወር reading challenge የተመረጠው መጽሐፍ፣ “ትኩረት” የተሰኘው ነው፡፡ ትኩረት ሁለት ገጽታዎች አሉት፦
የመስከረም ወር Book Reading Challenge with Dr. Eyob ለመስከረም ወር reading challenge የተመረጠው መጽሐፍ፣ “ትኩረት” የተሰኘው ነው፡፡ ትኩረት ሁለት ገጽታዎች አሉት፦ 1.     በየእለት ተግባራችን  - ይህ የትኩረት ሁኔታ በየቀኑ ባለን ኑሮ ከአላማችን አንጻር መገንባትንና በየእለቱ በሚከሰቱ ሁኔታዎች ሃሳባችን እንዳይበታተን የመጠበቃችንን ሁኔታ ያመለክታል፡፡ 2.    አጠቃላይ የሕይወት ዘይቤ - ይህ የትኩረት ሁኔታ ለአጠቃላይ የሕይወታችን እድገትና ለስኬታማነታችን ከማይጠቅሙ የሕይወት ዘይቤዎችና ልምምዶች ላይ ትኩረታችንን በማንሳት ወደ ዋናውና ወደ አስፈላጊው ዓላማችን ማዞርን ያመለክታል፡፡   መጽሐፉን ለማንበብ ከአሁኑ በመመዝገብ ራሳችሁን አዘጋጁ፡፡ የንባብ ወር - መስከረም / 2019 ለንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “ትኩረት” ንባቡ የሚጀመርበት ቀን - መስከረም 1 / 2019 ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - መስከረም 30 / 2019 ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡ Join now!!!

የተስፋ እስር ቤት “ሰው ከምግብ ውጪ አርባ ቀን መኖር ይችላል፤ ከውኃ ውጪ ሶስት ቀን ሊኖር ይችላል፤ ከአየር ውጪ ስምንት ደቂቃዎች መኖር ይችላል፤ ከተስፋ ውጪ ግን ከአንዲት ደቂቃ በላይ መኖር አይችልም” – Hal Lindsey በአሁን ሰአት ያለህበትን ወዳጅነት፣ የፍቅር ግንኙነትት፣ ስራ፣ ንግድም ሆነ ማንኛውንም በየእለቱ ጠዋት መንጋቱን የምትጠብቅበትን ነገር ተመልከተው፣ በዚያ ነገር ውስጥ ያለህ ተስፋ ነው እንደዚያ የሚደርግህ፡፡ በአንድ ነገር ላይ ተስፋ እንደሌለህ እንዳሰብክ ወዲያውኑ አቅም የማጣት ስሜት፣ እንቅልፍ መጣትና አንዳንዴም መኖር ያለመፈለግ ስሜት ይጫጫንሃል፡፡ ተስፋ ማለት የነገ መሄጃ ነውና ተስፋ ከሌለ ወደየት ይኬዳል? ተስፋ የጉልበት ምንጭ ነው፡፡ ተስፋ ዛሬ ካለህበት ሁኔታ ወጥተህ ነገ እንዲሆን ከምታስበው ነገር ጋር አጣብቆ የሚያቆይህ ወሳኝ ሂደት ነው፡፡ ሆኖም ተስፋ ለአንዳንድ ሰዎች የሕመም ምክንያት ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ የሚሆንበት ምክንያት የማይሞላን ተስፋ ከሰዎች በመጠበቅ ከአመት እስከ አመት ሲኖሩ ነው፡፡ ሰዎች በተለያየ ጊዜ በተስፋ እንድንጠብቃቸው ቃል በመግባት ያስጠብቁናል፡፡ የምንወዳቸውንና የምናምናቸው ሰዎች በተስፋ መጠበቅ የጨዋዎች ምልክት ነው፡፡ ነገር ግን የተገባው ተስፋ ከመጠን ያለፈ ፈተና ውስጥ በሚጨምረን ጊዜና ዝም ብለን የምንጠብቅ ከሆነ፣ የተስፋ እስር ቤት ውስጥ እንዳለን ማወቅ አለብን፡፡ ወይ በተስፋው ምክንያት በጉጉት አንኖር፣ ወይም ደግሞ አንደኛችንን የራሳችንን መንገድ አንከተል፣ እንዲሁ ተስፋውን በመጠበቅ እንደ እስረኛ እንከርማለን፡፡ ሰዎች በማይሞላ ተስፋ ውስጥ አንጠልጥለውን እየኖርን እንደሆነ ከተሰማን ሰዎቹን እውነተኛነት ለመመዘን የሚከተሉት ጥያቄዎች መጠየቅ እንችላለን፡- 1. ተስፋ የሰጡን ሰዎች ጉዳዩን የሚያስታውሱት እኛ ስናነሳላቸው ብቻ ሲሆን 2. ተስፋውን የመጠበቃችን ሁኔታ አመታቶቻችንንና እድሜያችንን የሚበላ ሲሆንና ስጋት ውስጥ ስንገባ 3. ሰዎቹ የሚያደርጉት ነገር ከምንጠብቀው ተስፋ አንጻር ተቃራኒ ሲሆን 4. ስለተሰጠን ተስፋ ለመወያየት ስንፈልግ (ልክ እንደተጠራጠርናቸው በማሳየት) በእኛ ላይ የቁጣና የንዴት ስሜት የሚያሳዩ ከሆነ ከላይ የተጠቀሱትንና መሰል ሁኔታዎች ከተመለከትን መስጠት ከምንችላቸው ምላሾች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል . . . 1. ግልጽ ውይይት የማድረግ ጉዳይ አጽንቶ በመጠየቅ የሚቻለውን ያህል መታገስ 2. ሁኔታዎች ግልጽ ባለመሆን ከቀጠሉ የጊዜ ገደብ በማስቀመጥ አቋምን ግልጽ ማድረግ 3. ልብን ከስብራት ለመጠበቅ መዘጋጀትና ከተገባልን ተስፋ ውጪ መኖር እንደምንችል ራስን ማሳመን 4. የተገባውን ተስፋ በማይጣረስ መልኩ የግል ሕይወትን እቅድ በማውጣት ራስን የመቻል ሂደት መጀመር በማይሞላ ተስፋ ድባብ ውስጥ ለአመታት መኖር አደገኛ የሆነ “የተስፋ እስር ቤት” ነውና ዛሬውኑ ተነሱና ከዚህ እስር ቤት ውጡ! https://t.me/Dreyob https://m.youtube.com/user/naeleyob623 https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/ https://t.me/Dreyob

የተስፋ እስር ቤት
የተስፋ እስር ቤት

ስራን በስኬታማነት መምራት “መሪ ማለት ሰዎችን ማደራጀት፣ ሀብትና ኃይልን ማስተባበር፣ ቡድኑም ዓላማውን እንዲያሳካ መርዳት ነው” - Unknown Source ራሱን በትክክለኛው መርህ መምራት የቻለ እ
ስራን በስኬታማነት መምራት “መሪ ማለት ሰዎችን ማደራጀት፣ ሀብትና ኃይልን ማስተባበር፣ ቡድኑም ዓላማውን እንዲያሳካ መርዳት ነው” - Unknown Source ራሱን በትክክለኛው መርህ መምራት የቻለ እና ከዚያ ተነስቶ በሰዎች ላይ መልካም ተጽእኖ ማምጣት የቻለ ሰው ይህ ብቃቱ ለስራ መነሳሳትን ይሰጠዋል፣ አልፎም የሚሰራውን ማንኛውም ስራ ስኬታማ በሆነ መልኩ የመስራት አቋም ደረጃ ያደርሰዋል፡፡ ስለሆነም፣ ዓላማን የመያዝ፣ አቅጣጫን የማስቀመጥ፣ የስራ ሂደትን የማደራጀት፣ ስልት የመዘርጋት እና ስራን በስኬታማነት ወደ ፊት የማስኬድ ብቃት ወደመለማመድ እያደገ ይሄዳል፡፡ ይህ ብቃቱ ደግሞ የአመራር ተጽእኖውን ሙሉ ያደርገዋል፡፡ ባለፈው ኃሙስ ምሽት የተጀመረውና ለሁለት ተጨማሪ ኃሙስ ምሽቶች የሚቀጥለው ስልጠና ከሚያብራራቸው እውነታዎች አንዱ ይህ ራስን የመምራት ዘርፍ ነው፡፡ ስልጠናውን ለመቀላቀል ከፈለጋችሁ ያመለጣችሁን ክፍል በድምጽ እና በጽሑፍ ግሩፑ ውስጥ ታገኛላችሁ፡፡   የስልጠናው ርእስ፡- “የአመራር እውነታዎች እና ልምምዶች” (Leadership Facts and Practices) ስልጠናው የሚሰጠው፡- በዶ/ር ኢዮብ ማሞ ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በ online (telegram live) የስልጠናው ቀናት፡- ነሃሴ 14፣ ነሃሴ 21 እና ነሃሴ 28 (ሶስት የነሃሴ ወር ኃሙሶች) የስልጠናው ሰዓት፡- ለአራቱም ኃሙስ ምሽቶች ከ3፡00 እስከ 4፡30 (በኢትዮጲያ አቆጣጠር) በዚህ ስልጠና ለመሳተፍ፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡ Join now!!!

ሰዎችን በተጽእኖ መምራት “ሌሎችን በተጽእኖ ለመምራት ዋነኛውና ብቸኛው ነገር ምሳሌ መሆን ነው” - Albert Schweitzer አንድ ሰው ራሱን በትክክለኛው መልኩ መምራት እና የራስ-በራስ ተጽእኖ
ሰዎችን በተጽእኖ መምራት “ሌሎችን በተጽእኖ ለመምራት ዋነኛውና ብቸኛው ነገር ምሳሌ መሆን ነው” - Albert Schweitzer አንድ ሰው ራሱን በትክክለኛው መልኩ መምራት እና የራስ-በራስ ተጽእኖ ማሳደር ከቻለ፣ ሌሎችን ሰዎች የመምራት አቋም እና ብርታት ላይ ራሱን ያገኘዋል፡፡ ይህ የሚሆንበት ዋነኛ ምክንያት ራሱን በመምራት ሂደት እያደገ ሲሄድ በመደበኛም ሆነ መደበኛ ባልሆነ መልኩ በአካባቢው በሚገኙ ሰዎች ላይ መልካም ተጽእኖ ማምጣት ስለሚችል ነው፡፡ ይህ አውነታ፣ “አመራር ማለት ተጽእኖ ማምጣት ማለት ነው” ከሚለው ብዙዎች ከሚስማሙበት የአመራር ትርጉም ጋር ይስማማል፡፡ ባለፈው ኃሙስ ምሽት የተጀመረውና ለሁለት ተጨማሪ ኃሙስ ምሽቶች የሚቀጥለው ስልጠና ከሚያብራራቸው እውነታዎች አንዱ ይህ ራስን የመምራት ዘርፍ ነው፡፡ ስልጠናውን ለመቀላቀል ከፈለጋችሁ ያመለጣችሁን ክፍል በድምጽ እና በጽሑፍ ግሩፑ ውስጥ ታገኛላችሁ፡፡   የስልጠናው ርእስ፡- “የአመራር እውነታዎች እና ልምምዶች” (Leadership Facts and Practices) ስልጠናው የሚሰጠው፡- በዶ/ር ኢዮብ ማሞ ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በ online (telegram live) የስልጠናው ቀናት፡- ነሃሴ 14፣ ነሃሴ 21 እና ነሃሴ 28 (ሶስት የነሃሴ ወር ኃሙሶች) የስልጠናው ሰዓት፡- ለአራቱም ኃሙስ ምሽቶች ከ3፡00 እስከ 4፡30 (በኢትዮጲያ አቆጣጠር) በዚህ ስልጠና ለመሳተፍ፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡ Join now!!!

ራስን በጥበብ መምራት “ሌሎችን በብቃት መምራት ከመቻልህ በፊት ራስህን መምራትን መማር አለብህ” — John C. Maxwell ማንኛውም ሰው ሌላን ሰውም ሆነ ስራውን ከመምራቱ በፊት መጀመሪያ ራሱን መ
ራስን በጥበብ መምራት “ሌሎችን በብቃት መምራት ከመቻልህ በፊት ራስህን መምራትን መማር አለብህ” — John C. Maxwell ማንኛውም ሰው ሌላን ሰውም ሆነ ስራውን ከመምራቱ በፊት መጀመሪያ ራሱን መምራት እንዳለበት ግልጽ ነው፡፡ ስለሆነም፣ አመራር የሚጀምረው ራስን ከመምራት ነው፡፡ ይህ እውነታ አመራር የኃይል ወይም የስልጣን ቦታ መያዝ ሳይሆን፣ ተጽእኖ ማሳደርና ሌሎችን ሰዎችም ሆነ ስራን ወደ ትክክለኛ አቅጣጫ መምራት መሆኑን አመልካች ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ አንድ ሰው በማንም ሰውና በምንም ነገር ላይ መልካም ተጽእኖ ከማምጣቱ በፊት በራሱ ላይ ተጽእኖ በማድረግ መምራት አለበት፡፡ ባለፈው ኃሙስ ምሽት የተጀመረውና ለሁለት ተጨማሪ ኃሙስ ምሽቶች የሚቀጥለው ስልጠና ከሚያብራራቸው እውነታዎች አንዱ ይህ ራስን የመምራት ዘርፍ ነው፡፡ ስልጠናውን ለመቀላቀል ከፈለጋችሁ ያመለጣችሁን ክፍል በድምጽ እና በጽሑፍ ግሩፑ ውስጥ ታገኛላችሁ፡፡   የስልጠናው ርእስ፡- “የአመራር እውነታዎች እና ልምምዶች” (Leadership Facts and Practices) ስልጠናው የሚሰጠው፡- በዶ/ር ኢዮብ ማሞ ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በ online (telegram live) የስልጠናው ቀናት፡- ነሃሴ 14፣ ነሃሴ 21 እና ነሃሴ 28 (ሶስት የነሃሴ ወር ኃሙሶች) የስልጠናው ሰዓት፡- ለአራቱም ኃሙስ ምሽቶች ከ3፡00 እስከ 4፡30 (በኢትዮጲያ አቆጣጠር) በዚህ ስልጠና ለመሳተፍ፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡ Join now!!!

ከሚከፈለን በላይ መስራት! “ከሚከፈለው በላይ የሚሠራ ሰው፣ ብዙም ሳይቆይ ከሚሠራው በላይ ይከፈለዋል”፣ ይባላል! የተጠበቀብንን ያህል ብቻ እየሰራን ያልተጠበቀ ውጤትና እድገት መጠበቅ አንችልም፡፡ ከ
ከሚከፈለን በላይ መስራት! “ከሚከፈለው በላይ የሚሠራ ሰው፣ ብዙም ሳይቆይ ከሚሠራው በላይ ይከፈለዋል”፣ ይባላል! የተጠበቀብንን ያህል ብቻ እየሰራን ያልተጠበቀ ውጤትና እድገት መጠበቅ አንችልም፡፡ ከተጠበቀብን በላይ በትጋት ስንሰራ በሰዎች አመኔታን እናዳብራለን፣ አቅማችንን እንገነባለን፣ እንዲሁም የምናገኛቸው እድሎች እየሰፉ ይሄዳሉ፡፡ https://t.me/Dreyob https://m.youtube.com/user/naeleyob623 https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/

ታላቅ ወደ መሆን የምናድገው!!! ታላቅ ወደ መሆን የምናድረገው ስላልወደቅን ወይም ስላልተሳሳት አይደለም፡፡ ታላቅ ወደ መሆን የምናድረገው ውድቀታችንም ሆነ ስህተታችን ስላላስቆመን ነው፡፡ ውድቀታችሁና
ታላቅ ወደ መሆን የምናድገው!!! ታላቅ ወደ መሆን የምናድረገው ስላልወደቅን ወይም ስላልተሳሳት አይደለም፡፡ ታላቅ ወደ መሆን የምናድረገው ውድቀታችንም ሆነ ስህተታችን ስላላስቆመን ነው፡፡ ውድቀታችሁና ስህተታችሁ በፍጹም አያስቁማችሁ! ፈጣሪ ያግዛችሁ የምወዳችሁ የሃገሬ ሰዎች! https://t.me/Dreyob https://m.youtube.com/user/naeleyob623 https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/

Repost from Dr. Eyob Mamo
አምስቱ የስኬታማ ሰዎች ልምምዶች!!! ወደ ስኬት ጎዳና የሚወስዱ መርሆች እጅግ በርካታ ናቸው፡፡ ለዚህ ነው የተለያዩ ሰዎች ከግል ልምምዳቸው በመነሳት የሚለግሱን ሃሳቦች የተለያዩ የሚመስሉት፡፡ የስኬት መንገድ በርካታ የመሆኑን እውነታ አመንነውም አላመንነው፣ በዚህ ትምህርት ውስጥ የምታገኟቸው አምስት ሃሳቦች መሰረታዊ ናቸውና ይከታተሏቸው፡፡ ከዚህ በታች ያለውን Link በመጫን ይከታተሉ፡፡ https://youtu.be/2rj5YOclGDc Please SUBSCRIBE !!! Please SHARE !!!

MAKE-UP !!! ትናንት ኃሙስ ምሽት “የአመራር እውነታዎች እና ልምምዶች” (Leadership Facts and Practices) የተሰኘው ስልጠና በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች ተሳታፊ በሆኑበት ተጀምሯል፡፡
MAKE-UP !!! ትናንት ኃሙስ ምሽት “የአመራር እውነታዎች እና ልምምዶች” (Leadership Facts and Practices) የተሰኘው ስልጠና በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች ተሳታፊ በሆኑበት ተጀምሯል፡፡ ሁለት ኃሙሶች ይቀሩናል፡፡ አሁን join የማድረግ ፍላጎት ያላችሁ join ማድረግ ትችላላችሁ፡፡ ያለፋችሁ pdf note እና audio ቅጅ ቡድኑ ውስጥ ይገኛል፡፡  ስልጠናው የሚሰጠው፡- በዶ/ር ኢዮብ ማሞ ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በ online (telegram live) የስልጠናው ቀናት፡- ነሃሴ 14፣ ነሃሴ 21 እና ነሃሴ 28 (ሶስት የነሃሴ ወር ኃሙሶች) የስልጠናው ሰዓት፡- ለሶስቱም ኃሙስ ምሽቶች ከ3፡00 እስከ 4፡30 (በኢትዮጲያ አቆጣጠር) የስልጠናው ክፍያ፡- ክፍያው 300 ብር ብቻ፡፡ ክፍያውን ከፍለው screenshot ሲልኩ ለዚህ ስልጠና ተመዝጋቢዎች ብቻ ወደሚዘጋጅ ቴሌግራም ግሩም እንቀላቅሎታለን፡፡ የክፍያ መረጃ:- ንግድ ባንክ Eyob Mamo Account # 1000614499056 አዋሽ ባንክ Eyob Mamo Acc# 013201772901100 ቴሌብር Dr. Eyob ስልክ ቁጥር 0945087238 እናመሰግናለን!

ለምን የራሳችንን ምርጫና ውሳኔ ማድረግ እንቸገራለን? ምርጫ እና ውሳኔ ማዘግየት፣ ማስተላለፍ ወይም ፈጽሞ የማድረግ ችግር ካለባችሁ፣ መንስኤውን በመለየት መፍትሄ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ 1.      የተሳሳተ ውሳኔ ማድረግን መፍራት መሳሳትን፣ መውደቅን ወይም በኋላ መጸጸትን በመፍራት ውሳኔ ካማድረግ ሊከለክለን ይችላል፡፡ ይህንን ችግር ለመቅረፍ፣ በመጀመሪያ ስህተትን መፍራትን ለጥንቃቄ እንደሚጠቅም ከተገነዘብነ በኋል፣ በትክክል በማቀድና ሊከሰቱ ለሚችሉ ችግሮች አማራጭ በመፈለግ መራመድ እንችላለን፡፡ 2.     ሌሎች ሰዎች ምን ይሉኛል የሚለው ፍርሃት ቤተሰብ፣ ጓደኞች፣ ወይም ማህበረሰብ ምን እንደሚያስቡ ከመጠን በላይ ስንጨነቅ የራሳችንን ውሳኔ ማድረግ እንቸገራለን። ይህንን ችግር ለመቅረፍ፣ በመጀመሪያ የሰዎች ሃሳብ ራሳችንን ለመመልከት በመጠቀም፣ አመለካከታቸው የራሳቸውን ልማድና የብስለት ደረጃ እንደሚያን በማሰብ ያመንንበትን ወደማድረግ መንቀሳቀስ እንችላለን፡፡ 3.     በራስ አለመተማመን የራሳችንን አስተሳሰብና ውሳኔ ስንጠራጠር ሁልጊዜ የሌሎች ሰዎችን ምክርና ሃሳብ እንጠብቃለን። ይህንን ችግር ለመቅረፍ፣ በመጀመሪያ አቅማችንን በሚገባ በፈተሸ ብርቱና ደካማ ጎናችን ከለየን በኋላ ደካማውን በማሻሻል፣ በብርቱው ላይ በመገንባት ወደፊት መራመድ እንችላለን፡፡ 4.     ከመጠን በላይ ማሰብ ስህተት የሌለው አማራጭ፣ አንዱን መረጃ ስናገኝ ሌላ ተጨማሪ መረጃ መፈለግ ወይም ሙሉ እርግጠኝነት እስክናገኝ ድረስ ስንጠብቅ ውሳኔ ማድረግ እንዘገያለን። ይህንን ችግር ለመቅረፍ፣ በመጀመሪያ ምርጫዎቻችንን ዘርዝረን ከመዘገብን በኋላ ቀስ በቀስ እያጠበብን በመሄድ የተሻለውን ምርጫ መምረጥ እንችላለን፡፡ 5.     ስለ ግቦቻችን ግልጽ አለመሆን አንድን ነገር ለማድረግ ስንወስንና ምርጫዎች ፊታችን ሲመጡ፣ ቀድሞውኑ ዋና ዓላማችን ግልጽ ካልሆነ ሁሉም አማራጮች እኩል ይመስሉንና እንወላውላለን። ይህንን ችግር ለመቅረፍ፣ በመመሪያ ለምርጫና ውሳኔ የተነሳንለትን ዓላማ ካጠራን በኋላ ከዋና ዓላማችን ጋር ጠጋ የሚለውን ምርጫ መምረጥ እንችላለን፡፡ https://t.me/Dreyob https://m.youtube.com/user/naeleyob623 https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/