ch
Feedback
Dr. Eyob Mamo

Dr. Eyob Mamo

前往频道在 Telegram

Life skill development! You can contact me @DrEyobmamo

显示更多

📈 Telegram 频道 Dr. Eyob Mamo 的分析概览

频道 Dr. Eyob Mamo (@dreyob) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 79 042 名订阅者,在 教育 类别中位列第 1 982,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 376

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 79 042 名订阅者。

根据 09 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -256,过去 24 小时变化为 33,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 11.78%。内容发布后 24 小时内通常能获得 5.62% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 9 307 次浏览,首日通常累积 4 443 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 71

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Life skill development! You can contact me @DrEyobmamo

凭借高频更新(最新数据采集于 10 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

79 042
订阅者
+3324 小时
+457
-25630
帖子存档
የብዙዎች ጥያቄ የሰኔውን ወር የንባብ አሁን ብንቀላቀልስ? መልስ፡- የሰኔ ወር ንባብ ዛሬ አራተኛ ቀኑን ይዟል፡፡ ዛሬ በመቀላቀልና ያለፋችሁን በማንበብ ከነገ ጀምሮ በየጠዋቱ የሚለቀቀውን ወሩን ሙሉ
የብዙዎች ጥያቄ የሰኔውን ወር የንባብ አሁን ብንቀላቀልስ? መልስ፡- የሰኔ ወር ንባብ ዛሬ አራተኛ ቀኑን ይዟል፡፡ ዛሬ በመቀላቀልና ያለፋችሁን በማንበብ ከነገ ጀምሮ በየጠዋቱ የሚለቀቀውን ወሩን ሙሉ በማንበብ መቀጠል ትችላላችሁ፡፡ ንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “ቀዩ መስመር” ንባቡ የጀመረበት ቀን - ሰኔ 1 / 2018 ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - ሰኔ 30 / 2018 ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡ Join now!!!

“እውቀትን ወደ ተግባር እንዴት መቀየር ይቻላል?” የሚለውን ትናንትና የጀመርኩትን ተከታይ ሃሳብ ይዤላችሁ ቀርቤአለሁ፡፡ 4. መርሆዎችን ወደ ግልጽ ተግባራት መቀየር አጠቃላይ እውቀት ብዙ ጊዜ ወደ ተግባር አይመራም። ለምሳሌ፣ “የበለጠ ዲሲፕሊን ማዳበር አለብኝ” ከማለት ይልቅ፣ “በየቀኑ ምሽት ላይ የነገውን ውሎ ለማቀድ 10 ደቂቃ እመድባለሁ” ብንልና ብናደርገው ተመራጭ ነው። “የሰው-ለሰው ግንኙነቶቼን ማሻሻል አለብኝ” ከማለት ይልቅ፣ “በየቀኑ ለአንድ ሰው የሚያበረታታ መልዕክት እልካለሁ” በማለት ተግበር የላቀ ነው። ግልጽ ተግባራት ግልጽ ውጤቶችን ያስገኛሉ። 5. ለተግባሩ ጊዜ መመደብ (ቀጠሮ መያዝ) ዕቅድ ወጥቶለትና የቀን ገደብ ተቀምጦለት በፕሮግራም የተያዘ ነገር፣ እንዲሁ በምኞት ብቻ ከሚታሰብ ነገር በላይ የመተግበር ዕድሉ ከፍተኛ ነው። ስለሆነም፣ ለመተግበር ያሰብናቸውን ነገሮች በካላንደችን ውስጥ መመዝገብና የጊዜ ገደብ ማስቀመጥ አስፈላጊ ነው፡፡ ለምሳሌ፣ “በዚህ ቀን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እጀምራለሁ”፤ “በዚህ ጊዜ ውስጥ አንድ መጽሐፍ ጀምሬ እጨርሳለሁ” እና የመሳሰሉት ማለት ነው፡፡ ያለ ጊዜ ምደባ የሚኖሩ መልካም ምኞቶች፣ እንዲሁ ምኞት ሆነው የመቅረት ዕድላቸው ሰፊ ነው። 6. ተጠያቂነትን መፍጠር ማድረግ የፈለግነውን ነገር ከማድረግ ብዙ ከታገልን ምን ለማድረግ እንዳቀድን ለአንድ የቅርብ ሰው መንገርና ተጠያቂነትን ማዳበር ጥሩ ልምምድ ነው። ሰዎች የገቡትን ቃል ሌላ ሰው እንደሚያውቅባቸው ሲረዱ፣ በተግባር የመተርጎም ዕድላቸው ሰፊ ነው። አማካሪ (Mentor) መፈለግ፣ የአንድ ቡድን አባል መሆን፣ ከጓደኛ ጋር በመጣመር አጋር መሆን፣ እድገታችንን በየጊዜው ሪፖርት የምናደርግለት ሰው መፈለግ፡፡ ተጠያቂነት ምኞትን ወደ ቁርጠኝነት ይቀይራል። 7. ትኩረታችን በድግግሞሹ ላይ እንጂ ፍጹም በመሆን ላይ አለማድረግ ብዙ ሰዎች አንድን የጀመሩትን ነገር ፍጹም አድርገው ስላልሠሩት ብቻ ማድረጉን ያቆማሉ። ግባችን መሆን ያለበት ግን፣ እንከን የለሽ አፈጻጸም ሳይሆን፣ ደጋግሞ መሥራት ላይ ነው። ማንኛውም ክህሎት የሚገነባው ፍጹም ባልሆነ አጀማመርና ካለማቋረጥ በሚደረግ ልምምድ ውስጥ ነው። እድገት የድግግሞሽ ውጤት ነው። ማሳሰቢያ፡- ኃሙስ ሰኔ 4/2018  ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 ድረስ በዚሁ የቴሌግራም ቻናሌ Live! የሚሰጠው ስልጠና አያምልጣችሁ፡፡ የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!” ወዳጆቻችሁ ይህንን channel join በማድረግ ስልጠናው እንዲካፈሉ ጋብዟቸው፡፡   https://t.me/Dreyob https://m.youtube.com/user/naeleyob623 https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/

እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል አራት)
እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል አራት)

ነገ ማታ ክ3 እስከ 4 ሰአት ነጻ የስልጠና እድል! Mark Your Calendar! ቀኑ፡- ኃሙስ ሰኔ 4/2018 ሰዓቱ፡- ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ት
ነገ ማታ ክ3 እስከ 4 ሰአት ነጻ የስልጠና እድል! Mark Your Calendar! ቀኑ፡- ኃሙስ ሰኔ 4/2018   ሰዓቱ፡- ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!” ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በቴሌግራም Live! የልጅነታችን “ትራውማ” . . . 💎 በማሕበራዊ ግንኙነታችን ላይ . . . 💎በፍቅር ግንኙነታችን ላይ . . . 💎 ከትዳር አጋራችን ጋር ባለን ግንኙነት ላይ . . . 💎 በስራው ዓለም ውስጥ ባለን የሰው-ለሰው ግንኙነት ላይ . . . ከፍተኛ የሆነ ተጽእኖ አለው፡፡ ይህ ነጻ ስልጠና . . . 1.       ለራሳችንም ሆነ ለሰዎች ግራ የሚገባንን የአቀራረብ ልማዶቻችንን ምንጭ ያመለከትናል፣ 2.      ለአያያዝ አስቸጋሪ የሆኑ ሰዎችን እንደዚያ የሆኑበትን መነሻ እንድንገነዘብ ያስችለናል፡፡ 3.      ሰዎችን በማማከር ዘርፍ ለተሰማራንና ለመሰማራት ለምንፈልግ ሰዎች ግንዛቤን ይሰጠናል፡፡ ስልጠናው የሚጠው በዋናው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ የቴሌግራም ቻናል ላይ Live ይሆናል፡፡ ይህንን ቻናል ጓደኞቻችሁ join እንዲያደርጉ በመጋበዝ ቆዩ! ስልጠናው የሚሰጠው በዚሁ ቻናል ላይ ሲሆን፣ ይህንን ስልጠናው የሚጥበትን ቻናል ለመቀላቀል እንዲችሉ ለወዳጆቻችሁ ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ማጋራት ትችላላችሁ፦ https://t.me/Dreyob

የሰኔ ወር የንባብ challenge እንቀጠለ ነው፡፡ በመቶ የሚዎጠሩ አንባቢያን የሰኔ አንድ፣ ሁለትን እና የዛሬውን ክፍል አንበበዋል፡፡ ከዛሬው ንባብ የተቀነጨበ ላጋራችሁ፡- ቀዩ መስመር ስንል?! “ለአንድ ነገር የቀይ መስመር ገደብን ማስቀመጥ ማለት ራሳችንን በሚዛናዊነት ማክበርና መውደድ፣ ያንንም በማድረጋችን ምክንያት ሰዎች ቅር የመሰኘታቸውን አስቸጋሪ ሁኔታ ለመጋፈጥ ዝግጁ መሆን ማለት ነው” - Brené Brown እስቲ አስበው! አንድ ሃገር ከሌላው የጎረቤት ሃገር ጋር የሚለየው ወሰንና ድንበር ባይኖረው፡፡ በአሁኑ ጊዜ፣ እንኳን በየብስ ላይ ቀርቶ ውኃውና በአየሩ ላይ ሳይቀር “ባለቤት” እና “ወሰን” የሚለይበት ክልልአለው፡፡ እነዚህን ወሰኖች ደግሞ የማስከበሪያ አለም አቀፍ ሕጎች አሉ፡፡ እነዚህን ወሰኖች አለማክበር (ቀዩን መስመር መጣስ)የማሕበራዊና የግንኙነት ቀውስያለውን ያህል ወሰኖቹን አክብረው በሚኖሩ ሕብረተሰቦች መካከል ያለው ሰላምና ብልጽግና ደግሞ ይህ ነው አይባልም፡፡  አሁን ባለንበት ዘመን አንድ ሰው ከሌላው ሰው ጋር፣ አንድ ሕብረተሰብ ከሌላው ሕብረተሰብ ጋር፣ አንድ ድርጅት ከሌላው ድርጅት ጋር . . . በሚያደርገው ግንኙነትና ድርድር የሚቀመጡ ገደቦች “ቀይ መስመር” በመባል ይታወቃሉ፡፡ በዚህ ሃሳብ መሰረት “ቀዩ መስመር” የሚለውን አባባል እንደ አዑዱ ዘርፈ-ብዙ በሆነ መልኩ ልንገልጸው እንችላለን፡፡ ·       አንድን ግንኙነት የሚገዛ ሕግና መመሪያ፡፡ ·       በግንኙነት ውስጥ የሚፈቀደውንና የማይፈቀደውን የምንለይበት መንገድ፡፡ ·       “እሺ” ወይም “እምቢ” የምንላቸውን ነገሮች የሚለየው መስመር፡፡ ·       የአንድ ግንኙነትና ቅርበት ልክና ገደብ፡፡ ·       በግንኙነት ውስጥ ለሰዎች የምንሰጠውና ሰዎቹ ለእኛ የሚሰጡን የመብት ገደብ፡፡ ·       በማንኛውም የግንኙነት አውድ ውስጥ የሚገኝ የስልጣን ገደብ፡፡ ·       ለግንኙነት ቀውስ ምክንያት የሚሆኑ ልምምዶችን የምናሳውቅበት “ደንብ”፡፡ እነዚህ ከላይ የተጠቀሱትና መሰል ሃሳቦች የሌሉት ግንኙነት አጀማመሩ መልካም ቢመስልም ገና ከጅማሬው ለቀውስ የተወሰነ ግንኙነት ነው፡፡ የብዙ በሕብረተሰባችን መካከል የምናያቸው ንትርኮች፣ ጭቅጭቆችና ክሶች መንስኤው ይኸው የሰውን ቀይ መስመር የመጣስ ሁኔታ ነው፡፡ ይህንን ቀውስ ማስተካከያውና ማረሚያው መንገድ ደግሞ ተገቢውን የቀይ መስመር ወሰንና ገደብ መገንዘብና ያንንም መስመር በሚዛናዊነት ማስመር፣ እንዲሁም ማስከበር ነው፡፡ ንባቡን ለመቀላቀል ከዚህ በታች ባለው link inbox በማድረግ መረጃ ይቀበሉ፡፡ @DrEyobmamo

የሰኔ ወር የንባብ challenge እንቀጠለ ነው፡፡
የሰኔ ወር የንባብ challenge እንቀጠለ ነው፡፡

እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል ሶስት) ትናንትና እና ከትናንት ወዲያ የተመለከትናቸው ሃሳቦች ሊያስከት የሚችሉትን ጥያቄ በማሰብ፣ “እውቀትን ወደ ተግባር እንዴት መቀየር ይቻላል?” የሚል ተከታታይ ሃሳብ ይዤላችሁ ቀርቤአለሁ፡፡ እውቀት በአእምሮ ውስጥ ይከማቻል፤ ተግባር ግን ሕይወትን ይለውጣል፡፡ በቀደሙት ፖቶች እንደተመለከትነው፣ ብዙ ሰዎች የሚቸገሩት በእውቀት ማጣት ሳይሆን በተግባር የመተርጎም (የማስፈጸም) ብቃት በማጣታቸው ነው። ዋናው ቁልፍ በመማር እና በማድረግ መካከል ድልድይ መገንባት ነው። እውቀትን ወደ ተግባር እንዴት መቀየር ይቻላል? 1. ማጥናትን ቀነስ፣ መተግበርን በዛ ማድረግ! መጀመሪያ ያወቅነውን ነገር ከመተግበራችን በፊት ተጨማሪ መረጃን ብቻ የመሰብሰብ ፍላጎትን መቆጣጠር አስፈላጊ ነው። ለተማርነው ለእያንዳንዱ ትምህርት፣ የምንወስደውን አንድ የተግባር እርምጃ ለይተን እንወቅ። “ቀጥሎ ምን መማር አለብኝ?” ብለን ከመጠየቅ ይልቅ፣ “አሁን በማውቀው ነገር ምን ማድረግ አለብኝ?” ብለን እንጠይቅ። 2. በትንሹ መጀመር ብዙ መልካም ዓላማዎች የሚከሽፉት የመጀመሪያውን እርምጃ በጣም ትልቅ ለማድረግ ስምንሞክር ነው። ለምሳሌ፣ በየቀኑ ለአንድ ሰዓት ከማንበብ ይልቅ፣ በ10 ደቂቃ መጀመር። ለአንድ ሰዓት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ከማድረግ ይልቅ፣ በ10 ደቂቃ እንቅስቃሴ መጀመር። ትናንሽ እርምጃዎችን ለመጀመርም ሆነ ደጋግሞ ለመስራት ቀላል ናቸው፡፡ ቀጣይነት (ፅናት) ከአንድ ጊዜ ከፍተኛ ጥረት ይበልጣል። 3. ወዲያውኑ መተግበር ያወቅነውን እውቀት ለመተግበር በቆየን ቁጥር፣ የማድረግ ዕድላችን እየቀነሰ ይሄዳል። ጠቃሚ ነገር ስንማር፣ ዛሬውኑ እንተግብረው፡፡ ለመለማመድ ከሁሉ የተሻለው ጊዜ ትምህርቱ ገና በአእምሯች ውስጥ ትኩስ እያለ ነው። የተገበርነውን ነገር ደግሞ በቶሎ እንገምግመው፡፡ ባደረግነው ግምገማ መሰረት ደግሞ እርማት ለሚያስፈልገው ነገር እርማት እንስጥ፡፡ በዚህ መልኩ ጥጉ ድረስ ከደረስን በኋላ ሌላ እውቀትንና ሌላ ተግባርን ለመለማመድ ራሳችን ማዘጋጀት እንችላለን፡፡ ይቀጥላል . . . ማሳሰቢያ፡- ኃሙስ ሰኔ 4/2018  ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 ድረስ በዚሁ የቴሌግራም ቻናሌ Live! የሚሰጠው ስልጠና አያምልጣችሁ፡፡ የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!” ወዳጆቻችሁ ይህንን channel join በማድረግ ስልጠናው እንዲካፈሉ ጋብዟቸው፡፡  https://t.me/Dreyob https://m.youtube.com/user/naeleyob623 https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/

እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል ሶስት)
እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል ሶስት)

"ትናንትና ሰኔ 1 ቀን የተጀመረውን የንባብ challenge ዛሬ መቀላቀል እንችላለን?" ለምትሉ መልሱ አዎን ትችላላችሁ ነው።

ከነገ ወዲያ ማታ ክ3 እስከ 4 ሰአት ነጻ የስልጠና እድል! ቀኑ፡- ኃሙስ ሰኔ 4/2018 ሰዓቱ፡- ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma'
ነገ ወዲያ ማታ ክ3 እስከ 4 ሰአት ነጻ የስልጠና እድል! ቀኑ፡- ኃሙስ ሰኔ 4/2018   ሰዓቱ፡- ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!” ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በቴሌግራም Live! የልጅነታችን “ትራውማ” . . . 💎 በማሕበራዊ ግንኙነታችን ላይ . . . 💎በፍቅር ግንኙነታችን ላይ . . . 💎 ከትዳር አጋራችን ጋር ባለን ግንኙነት ላይ . . . 💎 በስራው ዓለም ውስጥ ባለን የሰው-ለሰው ግንኙነት ላይ . . . ከፍተኛ የሆነ ተጽእኖ አለው፡፡ ይህ ነጻ ስልጠና . . . 1.       ለራሳችንም ሆነ ለሰዎች ግራ የሚገባንን የአቀራረብ ልማዶቻችንን ምንጭ ያመለከትናል፣ 2.      ለአያያዝ አስቸጋሪ የሆኑ ሰዎችን እንደዚያ የሆኑበትን መነሻ እንድንገነዘብ ያስችለናል፡፡ 3.      ሰዎችን በማማከር ዘርፍ ለተሰማራንና ለመሰማራት ለምንፈልግ ሰዎች ግንዛቤን ይሰጠናል፡፡ ስልጠናው የሚጠው በዋናው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ የቴሌግራም ቻናል ላይ Live ይሆናል፡፡ ይህንን ቻናል ጓደኞቻችሁ join እንዲያደርጉ በመጋበዝ ቆዩ! ስልጠናው የሚሰጠው በዚሁ ቻናል ላይ ሲሆን፣ ይህንን ስልጠናው የሚጥበትን ቻናል ለመቀላቀል እንዲችሉ ለወዳጆቻችሁ ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ማጋራት ትችላላችሁ፦ https://t.me/Dreyob

ነጻ የስልጠና እድል! Mark Your Calendar! ቀኑ፡- ኃሙስ ሰኔ 4/2018 ሰዓቱ፡- ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀ
ነጻ የስልጠና እድል! Mark Your Calendar! ቀኑ፡- ኃሙስ ሰኔ 4/2018   ሰዓቱ፡- ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!” ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በቴሌግራም Live! የልጅነታችን “ትራውማ” . . . 💎 በማሕበራዊ ግንኙነታችን ላይ . . . 💎በፍቅር ግንኙነታችን ላይ . . . 💎 ከትዳር አጋራችን ጋር ባለን ግንኙነት ላይ . . . 💎 በስራው ዓለም ውስጥ ባለን የሰው-ለሰው ግንኙነት ላይ . . . ከፍተኛ የሆነ ተጽእኖ አለው፡፡ ይህ ነጻ ስልጠና . . . 1.       ለራሳችንም ሆነ ለሰዎች ግራ የሚገባንን የአቀራረብ ልማዶቻችንን ምንጭ ያመለከትናል፣ 2.      ለአያያዝ አስቸጋሪ የሆኑ ሰዎችን እንደዚያ የሆኑበትን መነሻ እንድንገነዘብ ያስችለናል፡፡ 3.      ሰዎችን በማማከር ዘርፍ ለተሰማራንና ለመሰማራት ለምንፈልግ ሰዎች ግንዛቤን ይሰጠናል፡፡ ስልጠናው የሚጠው በዋናው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ የቴሌግራም ቻናል ላይ Live ይሆናል፡፡ ይህንን ቻናል ጓደኞቻችሁ join እንዲያደርጉ በመጋበዝ ቆዩ! ስልጠናው የሚጥበትን ቻናል ለመቀላቀል ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ https://t.me/Dreyob

እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል ሁለት) ትናንትና የጀመርነውን ሃሳብ በመቀጠል የሚቀጥሉትን ተጨማሪ ሃሳቦች አቀርባለሁ  . . . 4. ተግባር የሌለው እውቀት ወደ ኩራት ሊመራ ይችላል አንዳንድ ጊዜ ሰዎች ራሳቸውን የሚመዝኑት ባከናወኑት ነገር ሳይሆን በሚያውቁት ነገር ልክ ነው። ሳይመሩ ስለ አመራር ጥበብ ሊወያዩ፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ሳያደርጉ ስለ ጤና ሊያወሩ፣ ወይም ራሳቸው የማይከተሉትን መርሆዎች ሊያስተምሩ ይችላሉ። እውቀት፣ አንድ ሰው ምንም ዓይነት እውነተኛ ስኬት ሳያስመዘግብ አስቀድሞ ስኬታማ እንደሆነ እንዲሰማው ሊያደርግ ይችላል። መረጃ ሰውን ሳያሳድግና ባህሪውን ሳይለውጥ፣ ኩራቱን ብቻ ሊያሳብጥበት ይችላል። 5. ተግባር እውነተኛ እውቀታችንን ያሳያል ብዙ ነገሮች በተግባር ለመሥራት እስክንሞክራቸው ድረስ ቀላል ይመስላሉ። ለምሳሌ፣ አመራርን በንግግር ማስረዳት ቀላል ነው፤ ነገር ግን በተግባር መምራት ከባድ ነው። ይቅርታን መስበክ ቀላል ነው፤ ነገር ግን በተግባር ይቅር ማለት ከባድ ነው። ትዕግስተኛን ሰው ማድነቅ ቀላል ነው፤ ነገር ግን በተግባር ማሳየት ከባድ ነው። ተግባር በንድፈ-ሀሳብ ግንዛቤ እና በእውነተኛ ክህሎት መካከል ያለውን ልዩነት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። አንድን ነገር በተግባር እስካልኖርነው ድረስ በእውነት አናውቀውም። 6. በእውቀትና በተግባር መካከል ያለው ክፍተት ብስጭትን ይፈጥራል ሰዎች ሁል ጊዜ እየተማሩ ነገር ግን ምንም ዓይነት ለውጥ ስለማያዩ ተስፋ ሊቆርጡ ይችላሉ። ችግሩ አብዛኛውን ጊዜ የመረጃ እጥረት ሳይሆን የመተግበር እጥረት ነው። አንድ ሰው፣ ገንዘብን እንዴት ማስተዳደር እንዳለበት፣ ግንኙነቶችን እንዴት ማሻሻል እንደሚቻል፣ ጤናን እንዴት መጠበቅ እንደሚችል ሊያው ይችላል፣ ሆኖም ግን፣ ተግባር እውቀትን ተከትሎ ስላልመጣ ህይወት በነበረችበት ትቀጥላለች። እውነተኛ ለውጥ የሚመጣው በመማር እና በማድረግ መካከል ባለው ክፍተት ውስጥ ነው። 7. ጥቂት ተግባር ከብዙ መረጃ ይበልጣል በተግባር የዋለ አንድ መርህ፣ እያወቅን ችላ ካልናቸው መቶ ትምህርቶች የበለጠ ዋጋ አለው። አንድ ምዕራፍ አንብቦ በተግባር ማዋል፣ ሙሉ ቤተ-መጽሐፍትን አንብቦ ምንም ነገር ከመለወጥ የበለጠ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡ ስኬት የሚለካው በምናውቀው መጠን ሳይሆን በተገበርነው መጠን ነው። ማሳሰቢያ፡- ኃሙስ ሰኔ 4/2018  ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 ድረስ በዚሁ የቴሌግራም ቻናሌ Live! የሚሰጠው ስልጠና አያምልጣችሁ፡፡ የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!” ወዳጆቻችሁ ይህንን channel join በማድረግ ስልጠናው እንዲካፈሉ ጋብዟቸው፡፡  https://t.me/Dreyob https://m.youtube.com/user/naeleyob623 https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/

እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል ሁለት)
እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል ሁለት)

የሰኔ ወር ንባብ ዛሬ ጀምሯል፡፡ በተለያየ ምክንያት አምልጧችሁ ከሆነ ዛሬውኑ መቀላቀል ትችላላችሁ! በመቶ የሚቆጠሩ አንባቢያን ተቀላቅለዋል፡፡ እርስዎም ዛሬ ይቀላቀሉ ነገ ማንበብን ይጀምሩ! ለንባብ
የሰኔ ወር ንባብ ዛሬ ጀምሯል፡፡ በተለያየ ምክንያት አምልችሁ ከሆነ ዛሬውኑ መቀላቀል ትችላላችሁ! በመቶ የሚቆጠሩ አንባቢያን ተቀላቅለዋል፡፡ እርስዎም ዛሬ ይቀላቀሉ ነገ ማንበብን ይጀምሩ! ለንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “ቀዩ መስመር” ንባቡ የሚጀመርበት ቀን - ሰኔ 1 / 2018 ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - ሰኔ 30 / 2018 ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡ Join now!!!

የማይካድ ሀቅ!!! • ለራሳችሁ ፕሮግራም ካላወጣችሁ፣ ሰዎች ፕሮግራም ያወጡላችኋል፡፡ • የራሳችሁን ሕይወት ካልመራችሁ፣ ሰዎች ወደፈለጉበት ይመሯችኋል፡፡ • ሕይወታችሁን በመልክ በመልኩ ካላደረጃችሁት
የማይካድ ሀቅ!!! • ለራሳችሁ ፕሮግራም ካላወጣችሁ፣ ሰዎች ፕሮግራም ያወጡላችኋል፡፡ • የራሳችሁን ሕይወት ካልመራችሁ፣ ሰዎች ወደፈለጉበት ይመሯችኋል፡፡ • ሕይወታችሁን በመልክ በመልኩ ካላደረጃችሁት፣ የመጣውን ሁኔታ ሁሉ እየተቀበላችሁ ለመኖር ትገደዳላችሁ፡፡ • እቅድ አውጥታችሁ የምትከተሉት ነገር ከሌላችሁ፣ ከሁኔታዎች እንደሸሻችሁ ትኖራላችሁ፡፡ • ብዙ እምቅ ብቃት ኖሯችሁ ካለምንም እቅድ እና አደረጃጀት ከኖራችሁ፣ ምንም እውቀት የሌላቸውና የተደራጁት እንደነዷችሁ ትኖላችሁ፡፡ አስቡበት

የሰኔ ወር ንባብ ዛሬ ጀምሯል፡፡ በተለያየ ምክንያት አምልቷችሁ ከሆነ ዛሬውኑ መቀላቀል ትችላላችሁ! በመቶ የሚቆጠሩ አንባቢያን ተቀላቅለዋል፡፡ እርስዎም ዛሬ ይቀላቀሉ ነገ ማንበብን ይጀምሩ! ለንባብ
የሰኔ ወር ንባብ ዛሬ ጀምሯል፡፡ በተለያየ ምክንያት አምልቷችሁ ከሆነ ዛሬውኑ መቀላቀል ትችላላችሁ! በመቶ የሚቆጠሩ አንባቢያን ተቀላቅለዋል፡፡ እርስዎም ዛሬ ይቀላቀሉ ነገ ማንበብን ይጀምሩ! ለንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “ቀዩ መስመር” ንባቡ የሚጀመርበት ቀን - ሰኔ 1 / 2018 ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - ሰኔ 30 / 2018 ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡ Join now!!!

እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል አንድ) ሰላም ተከታታዮቼ! ዛሬን ጨምሮ ለአምስት ቀናት፣ “እውቀትን ወደ ተግባር!” በሚል ርእስ ስር ለሕይወታችሁ ጠቃሚ መመሪያዎችን አጋራችኋለሁ፡፡ በማንበብ፣ በስልጠናም ሆነ በመደበኛ ትምህርት አንድን እውቀት ካገኛችሁ በኋላ የሚቀጥለው የቤት ስራችሁ ያንን እውቀት ተግባራዊ ማድረግ ነው፡፡ ያንን ካላደረጋችሁ ሁል ጊዜ ባላችሁበት የምትረግጡና ቀስ በቀስ ወደ ኋላ የምትቀሩ ትሆናላችሁ፡፡ “እውቀት መንገዱን ያሳያል፤ ተግባር ግን እግርን ያንቀሳቅሳል” የሚባለው ለዚህ ነው፡፡ “የምናውቀው ነገር ሌሎችን ያስደንቃል፤ የምንተገብረው ነገር ግን እኛን ወደ ፊት ያራምዳል” የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡ 1. ተግባር የሌለው እውቀት የሐሰት በራስ መተማመንን ይፈጥራል አንድ ሰው ምን ማድረግ እንዳለበት እያወቀ ሊወድቅ ይችላል፤ ምክንያቱም ማወቅና ማድረግ አንድ አይደሉም። ለምሳሌ፣ ስለ ውኃ ዋና መጽሐፍትን ያነበበ፣ ነገር ግን ፈጽሞ ውሃ ውስጥ የማይገባ ሰው መዋኘት አይችልም። ብቃት የሚመጣው ከተግባር እንጂ ከመረጃ አይደለም።ማወቅ ብቻ በቂ አይደለም፤ በተግባር ማዋል አለብን። መመኘት ብቻ በቂ አይደለም፤ ማድረግ አለብን!!! 2. ጥቅም ላይ ያልዋለ እውቀት ቀስ በቀስ ኃይሉን ያጣል እውቀት ልክ እንደ ጡንቻ ነው። ካልተንቀሳቀሰና ካልተሠራበት ይደክማል። ብዙ ሰዎች በመደበኛ ትምህርት ላይ ይሳተፋሉ፣ መጽሐፍትን ያነባሉ፣ ስልጠናዎችን ይወስዳሉ፤ ነገር ግን የተማሩትን ነገር ፈጽሞ በተግባር አይተረጉሙትም። ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ትምህርቶቹ የራቁ ትውስታዎች ብቻ ሆነው ይቀራሉ። በተግባር ያልተገለጠ ነገር ውሎ አድሮ መረሳቱ አይቀሬ ነው። 3. እውቀት ኃላፊነትን ይጨምራል ባወቅን ቁጥር፣ ላለመንቀሳቀስ የምንሰጠው ሰበብ እየቀነሰ ይሄዳል። የታማኝነትን፣ የዲሲፕሊንን፣ የአካል ጤና መመሪያዎችን ወይም የዓላማን አስፈላጊነት እያወቀ ነገር ግን ችላ የሚል ሰው በእውቀቱና በተግባሩ መካከል ላለው ክፍተት ተጠያቂ ነው። እውቀት ስጦታ የመሆኑን ያህል ኃላፊነትም ነው። በአንድ ነገር ላይ ካወቅን በኋላ ማንንም መውቀስ አንችልም፡፡ ሃላፊነቱ የእኛው ነው፡፡ በነገው ፖስቴ አራት ነጥብ የያዘውን ክፍል ሁለት ይዤ እመለሳሁ፡፡ ማሳሰቢያ፡- ኃሙስ ሰኔ 4/2018  ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 ድረስ በዚሁ የቴሌግራም ቻናሌ Live! የሚሰጠው ስልጠና አያምልጣችሁ፡፡ የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!” ወዳጆቻችሁ ይህንን channel join በማድረግ ስልጠናው እንዲካፈሉ ጋብዟቸው፡፡   https://t.me/Dreyob https://m.youtube.com/user/naeleyob623 https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/

እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል አንድ)
እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል አንድ)

ነገ ሰኔ አንድ ነው!!! የወሩ reading challenge ነገ ማለዳ ይጀምራል፡፡ በመቶ የሚቆጠሩ አንባቢያን ተቀላቅለዋል፡፡ እርስዎም ዛሬ ይቀላቀሉ ነገ ማንበብን ይጀምሩ! ለንባብ የተመረጠው መጽሐ
ነገ ሰኔ አንድ ነው!!! የወሩ reading challenge ነገ ማለዳ ይጀምራል፡፡ በመቶ የሚቆጠሩ አንባቢያን ተቀላቅለዋል፡፡ እርስዎም ዛሬ ይቀላቀሉ ነገ ማንበብን ይጀምሩ! ለንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “ቀዩ መስመር” ንባቡ የሚጀመርበት ቀን - ሰኔ 1 / 2018 ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - ሰኔ 30 / 2018 ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡ Join now!!!

ስህተት እና ስኬት! ▶️ የሰዎችን ስህተትና ውድቀት ለትምህርት ተጠቀሙበት እንጂ ለትችት አታውሉት፡፡ ▶️ የሰዎችን ስኬት ለመነሳሳት ተጠቀሙበት እንጂ ቅንአት መንፈስ አታስቡት፡፡ ▶️ የራሳችሁን ስህ
ስህተት እና ስኬት! ▶️ የሰዎችን ስህተትና ውድቀት ለትምህርት ተጠቀሙበት እንጂ ለትችት አታውሉት፡፡ ▶️ የሰዎችን ስኬት ለመነሳሳት ተጠቀሙበት እንጂ ቅንአት መንፈስ አታስቡት፡፡ ▶️ የራሳችሁን ስህተትና እንደ አንድ ክስተት ተመልከቱት እንጂ ከማንነታችሁ ጋር አታነካኩት፡፡ ▶️ የራሳችሁን ስኬት ለሚቀጥለው ደረጃ እንደ መሻገሪያ ተጠቀሙበት እንጂ አትኩራሩበት፡፡ መልካም ምሽት!!!