uz
Feedback
Ministry of Education Ethiopia

Ministry of Education Ethiopia

Kanalga Telegram’da o‘tish

This is Ministry of Education's Official Telegram Channel. For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Ministry of Education Ethiopia analitikasi

Ministry of Education Ethiopia (@ethio_moe) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 143 394 obunachidan iborat bo'lib, Taʼlim toifasida 794-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 176-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 143 394 obunachiga ega bo‘ldi.

28 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 1 866 ga, so‘nggi 24 soatda esa 126 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.83% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 8.64% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 37 031 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 12 390 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 0 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
This is Ministry of Education's Official Telegram Channel. For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 29 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Taʼlim toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

143 394
Obunachilar
+12624 soatlar
+9557 kunlar
+1 86630 kunlar
Postlar arxiv
የፈተና ስርቆትን የሚጠየፍ ትውልድ በመፍጠር ሂደት ውስጥ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አሳሰቡ። ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 በበይነ መረብና በወረቀት የሚሰጠው
+4
የፈተና ስርቆትን የሚጠየፍ ትውልድ በመፍጠር ሂደት ውስጥ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አሳሰቡ። ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 በበይነ መረብና በወረቀት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተካሂዷል።              -------------------------- // ----------------------- በመድረኩ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የፈተና ስርቆትን የሚጠየፍ ትውልድ በመፍጠር ሂደት ውስጥ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል ፡፡ በተለይም በፈተና ሂደት ወቅት ፈተና ለመስረቅም ይሁን ለማሰረቅ የሚሞክሩ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሩ ለፈተናው ስኬታማነት ሚኒስቴር መስሪያቤቱ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡  የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው የፈተናው አጠቃላይ ሂደት ደህንነቱ የተጠበቀ በሰላምና በውጤታማነት እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ በተባበረ አግባብና በተቀናጀ ሁኔታ መሰራት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል፡፡ የዘንድሮ የ12ኛ ክል ብሄራዊ ፈተና ከአጠቃላይ ተፈታኞች መካከል በአብዛኛው በበይነ መረብ የሚሰጥ መሆኑና የፈተና ተቋማቱ በርከት ባለ ሁኔታ በክልል ደረጃ የተደራጁ መሆናቸው ልዩ እንደሚያርገውም ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም የፈተናውን ደህንነቱን የማረጋገጥ ጉዳይ ከሌላው ጊዜ በተለየ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚያፈልግ ሚኒስትር ዴኤታዋ ክብርት ወ/ሮ አየለች አስገንዝበዋል፡፡ ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/1HCE2Y1BwH/

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተልዕኮና የትኩረት መስክ ልየታ ከአካባቢ ልማትና ጸጋ ጋር የተያያዘ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ። ----------------------------- // ----------
+4
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተልዕኮና የትኩረት መስክ ልየታ ከአካባቢ ልማትና ጸጋ ጋር የተያያዘ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ።   ----------------------------- // ----------------------------- ‎ ‎(ሰኔ 19/2018 ዓ.ም) የቡሌሆራና ቀብሪደሃር ዩኒቨርስቲዎች በማዕድንና ነዳጅ ላይ አትኩሮ ከሚሰራው የኦስትሪያው ሊዮቤን ዩኒቨርስቲ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ። ‎ ‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት የዩኒቨርስቲዎች የተልዕኮና የትኩረት መስክ ልየታ ከአካባቢ የልማት ጸጋ ጋር የተያያዙ እንዲሆን እየተሰራ ነው። ‎ ‎ የትኩረት መስክን ከተፈጥሮ ፀጋ ጋር ማያያዝ ሀብት፣ ጊዜና አቅምን በአግባቡ በመጠቀም ውጤታማ አንደሚያደርግም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። ‎ ‎የቡሌሆራና የቀብሪደሃር ዩኒቨርስቲዎች   የተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነትም በመምህራን ልማትና ምርምር፣ በቴክኖሎጂ ሽግግርና የዩኒቨርስቲ ኢንዲስትሪ ትብብርን ለማጠናከር እንደሚያስችል ተናግረዋል ። ‎ ‎የቡሌሆራ ዩኒቨርስቲ ከሊዮቤን ዩኒቨስቲ እና ከሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ጋር ስምምነት መፈራረሙን ጠቅሰው ይህም በማዕድን ምህንድስና እና ቴክኖሎጂ ዘርፎች የተሻለ ተፎካካሪ እንዲሆን ያስችለዋል ብለዋል። ‎ ‎የቀብሪ ደሃር ዩኒቨርስቲም ከሊዮቤን ቴክኒካል ዩኒቨርስቲ ጋር የተፈራረመው ስምምነት ዩኒቨርስቲው በአገር ውስጥ ብዙም ባልዳበረው የነዳጅና ኤነርጂ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆን ያግዘዋል ብለዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/1E2Y46YHWQ/

ሁሉም መሠረተ ልማት የተሟሉላቸው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እየተገነቡ ይገኛሉ። ---------------------- // --------------------- (
+2
ሁሉም መሠረተ ልማት የተሟሉላቸው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እየተገነቡ ይገኛሉ።   ---------------------- // ---------------------   (ሰኔ 18/2018 ዓ.ም) በዚህ መሠረት፣ በዛሬው ዕለት በትምህርት ሚኒስቴር ሙሉ ወጪ የሚገነባው የድሬዳዋ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የግንባታ ሥራ በይፋ ተጀምሯል።   የግንባታ ሥራውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጀዋር በጋራ አስጀምረውታል።   የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ ፕሮጀክቱ በሀገሪቱ የትምህርት ሪፎርም ጉዞ ውስጥ ጉልህ አስተዋጽኦ የሚኖረው ሲሆን እንደ ሀገር 50 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እየተሠራ መሆኑን ጠቅሰዋል።   የድሬዳዋ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ሲጠናቀቅ ዘመናዊ የመማሪያ ክፍሎች፣ የሳይንስ ላቦራቶሪዎች፣ የኮምፒውተር ማዕከላት፣ የስፖርትና የመዝናኛ ጨምሮ የተሟላ የትምህርት አካባቢ የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።   በተጨማሪም ትምህርት ቤቱ በአካባቢው ያለውን የተማሪ ክፍል ጥምርታ ለማሻሻል፣ ለተማሪዎች የተሻለ የመማሪያ አካባቢ ለመፍጠር እና የትምህርት ጥራትን በከፍተኛ ደረጃ ለማሻሻል የሚያስችል እንደሚሆንም ገልፀዋል ። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/18tBtY9TRj/

በትምህርት ዘርፉ ከተወሰዱ የሪፎርም ተግባራት ዋናውና ወሳኙ በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽነት ላይ እየተሰራ ያለው ሥራ ነው ሲሉ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ። -------------------
+3
በትምህርት ዘርፉ ከተወሰዱ የሪፎርም ተግባራት ዋናውና ወሳኙ በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽነት ላይ እየተሰራ ያለው ሥራ ነው ሲሉ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።   ---------------------- // ------------------------   (ሰኔ 18/2018 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የድሬዳዋ ከንቲባ አቶ ከድር ጀዋር በድሬዳዋ ከተማ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታን አስጀምረዋል።   በዚሁ ወቅት ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ለሕፃናት የመማር መሠረትን የሚጥል በመሆኑ በሀገር አቀፍ ደረጃ ተደራሽነቱን ለማስፋፋት ሰፊ ሥራ እየተከናወነ ነው።   በተለይም በትምህርት ሪፎርሙ ማዕቀፍ ውስጥ ለሁሉም ሕፃናት ፍትሃዊና ጥራት ያለው የመማር ዕድል ለመፍጠር የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታና ማስፋፊያ ሥራዎች ቅድሚያ ተሰጥቶት እየተሠራ መሆን ጠቅሰዋል።   ክቡር ከንቲባ ከድር ጀዋር በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በከተማው ያለውን የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ፍላጎት ለማሟላትና የሕፃናትን የመማር ዕድል ለማስፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ገልጸዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/18Xc4aqgiL/

ትምህርት ሚኒስትሩ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታን አስጀመሩ -------------------------- // -----------------------
+3
ትምህርት ሚኒስትሩ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታን አስጀመሩ   -------------------------- // ----------------------------- (ሰኔ 18/2018 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጀዋር በትምህርት ሚኒስቴር ሙሉ ወጪ በድሬዳዋ ከተማ የሚገነባውን የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በይፋ አስጀምረዋል። በዚሁ ጊዜ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት መንግሥት የተሻለ የትምህርት ጥራትና የላቀ የትምህርት አካባቢ ለመፍጠር በመላ ሀገሪቱ የተመረጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸውን የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በተለያዩ አካባቢዎች እየገነባ መሆኑን ገልጸዋል። ሚኒስትሩ አክለውም፣ ዛሬ ግንባታው የተጀመረው ትምህርት ቤትም ከመላው ሀገሪቱ በብቃታቸው የተመረጡ ተማሪዎችን በመቀበል የሚያስተምር ሲሆን፣ ግንባታው በአንድ ዓመት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ ጠቅሰዋል። በተጨማሪም የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን የማስፋፋት ሥራ በቀጣይነት እንደሚቀጥል ገልጸው፣ በባህርዳር፣ አርባምንጭ እና አሶሳ ተመሳሳይ የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ግንባታ በቅርቡ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጀዋር በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር ለከተማዋ እድገትና ለትውልድ ግንባታ እያደረገ ላለው አስፈላጊ ድጋፍ ምስጋናቸውን ገልጸው፣ የከተማ አስተዳደሩ ፕሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤  https://web.facebook.com/share/p/1PuiqKwBrR/

ዩኒቨርስቲዎች ከፖለቲካ ጣልቃገብነት ተላቀው ነጻ እውቀትና ሃሳብ የሚፈልቅባቸው ተቋማት እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ። ---------------------
+4
ዩኒቨርስቲዎች ከፖለቲካ ጣልቃገብነት ተላቀው ነጻ እውቀትና ሃሳብ የሚፈልቅባቸው ተቋማት እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።               --------------------- //------------------------ (ሰኔ 17/2018 ዓ.ም) በቀጣይ ወደ ራስገዝነት የሚሸጋገሩ ዩኒቨርስቲዎች የዝግጁነት ግምገማ ውጤት በቀረበበት መድረክ ላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ የከፍተኛ ትምህርት ሪፎርሙ ዋና ዓላማ ለእውነትና ለእውቀት ቁርጠኛ፣ አገራቸውን የሚወዱና የሚለውጡ ዜጎችን ማፍራት መሆኑን ተናግረዋል። ‎ ‎የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ነጻና ከፖለቲካ ጣልቃ-ገብነት ተላቀው ነጻ ሃሳብ የሚፈልቅባቸው ተቋማት እንዲሆኑ ወደ ራስ-ገዝነት ማሸጋገር ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። ‎ ‎የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለእውነትና ለእውቀት ቁርጠኝነት ያላቸውና አገራቸውን የሚወዱና የሚለውጡ የሰው ሃይል የሚያፈሩ እንዲሆኑ ማስቻል የሪፎርሙ መሠረት መሆኑንም ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ‎ ‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው እንደገለጹት ወደ ራስገዝነት የሚሸጋገሩ ተቋማት ከአክሪዲቴሽን ጋር በተያያዘ በተለይ የሀገር ውስጥ እውቀት በእጅጉ ጠቃሚ መሆኑን አንስተዋል። ‎ ‎ከውስጥ ገቢ ጋር በተያያዘም ተቋማቱ በዘላቂና ብዝሃ ገቢ ማስገኛ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርገው ሊሰሩ እንደሚገባ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/1BFQ2MqAiN/

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት መምህራን የተጣለባቸውን ሀገራዊ ሀላፊነት በሚገባ እንዲወጡ ተጠየቀ። ------------------------- //--------------------------- (ሰኔ
+2
የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት መምህራን የተጣለባቸውን ሀገራዊ ሀላፊነት በሚገባ እንዲወጡ ተጠየቀ።   ------------------------- //--------------------------- (ሰኔ 17/2018 ዓ.ም) ብቃትን መሰረት ያደረገ መማር ማስተማርን በሚመለከት ልዩ የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመምህራን እየተሰጠ ይገኛል።       ትምህርት ሚኒስቴር ከመላው ሀገሪቱ የተውጣጡ ብቃት ያላቸውን ተማሪዎች በመምረጥና በፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በማስተማር የሀገሪቱን የወደፊት የሰው ሀብት ለመገንባት እየሰራ ይገኛል። እነዚህ ትምህርት ቤቶች በአካዳሚክ ብቃት፣ በሥነ-ምግባር፣ በአመራር ክህሎት እና በሀገራዊ እሴቶች የተገነባ ትውልድ ለማፍራት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወቱ የተገልጸ ሲሆን፣ ይህንን ሀገራዊ ተልዕኮ በተሻለ ብቃት ለማሳካትም በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ መምህራንን ብቃት መሰረት ባደረገና የመማርና የማስተማር ሥርዓት ላይ ያተኮረ ልዩ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጣቸው ይገኛል። ስልጠናው በትምህርት ቤቶቹ የሚሰጠውን የትምህርት ጥራት ወደ ላቀ ደረጃ ከማሸጋገሩም በላይ፣ መምህራን ተማሪዎችን የእውቀት ተቀባዮች ብቻ ሳይሆኑ ችግር ፈቺዎች፣ ፈጠራ ባለቤቶች እና ሀገራቸውን የሚያገለግሉ ዜጎች እንዲሆኑ የሚያስችሉ ዘመናዊ የማስተማር ስነ-ዘዴዎችን እንዲላበሱ ያስችላቸዋልም ተብሏል።

በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ቤቶች ምገባን የሚደግፍ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ የትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የተቋቋመውን የትምህርት ቤቶች
+4
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ቤቶች ምገባን የሚደግፍ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ የትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የተቋቋመውን የትምህርት ቤቶች ምገባ የሚደግፍን ፕሮጀክት በይፋ አስጀምረዋል። በማስጀመሪያ መርኃ ግብሩ ላይ የተገኙት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ፣ ፕሮጀክቱ የተጀመረወን የትምህርት ቤት ምገባ ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ እና ተማሪዎች በቂና ተመጣጣኝ ምግብ በማግኘት በትምህርታቸው ላይ የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልጸዋል። ለፕሮጀክቱ ስኬት የተለያዩ ድጋፎችን ላደረጉ አጋር ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ምስጋናቸውን ገልጸው፣ ተማሪዎች በጤናማ ሁኔታ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ የሚያስችሉ መሰል ፕሮጀክቶች በሌሎች የሀገራችን ክፍሎች እንዲስፋፉ ምሳሌ ይሆናል ብለዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የትምህርት ቤት ምገባ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሀርቢ ቡህ በበኩላቸው፣ ፕሮጀክቱ በሞዴልነት የሚጠቀስ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም የድሬዳዋ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልይ ከዚህ ቀደም በተበታተነ መልኩ ይከናወን የነበረው የትምህርት ቤት ምገባ አገልግሎት ወደ አንድ ማዕከላዊ ሥርዓት በማምጣት ትልቅ የሪፎርም ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል። ይህም የተማሪዎች የምግብ ዝግጅትና ስርጭት ሂደቱን ቀልጣፋ፣ ወጪ ቆጣቢና ዘላቂ እንዲሆን እንደሚያስችል ተናግረዋል። ሙሉ ዜናውን ለማግኘት https://web.facebook.com/share/p/14fY9nME2GB/

በኢትዮጵያ የሚካሄዱ ሳይንሳዊ ምርምሮች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁና የሰዎችን ደኅንነት ያከበሩ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚያስችል የምርምር ሥነ-ምግባር ግምገማና እውቅና አሰጣጥ ሥርዓት ለመዘርጋት እ
+3
በኢትዮጵያ የሚካሄዱ ሳይንሳዊ ምርምሮች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁና የሰዎችን ደኅንነት ያከበሩ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚያስችል የምርምር ሥነ-ምግባር ግምገማና እውቅና አሰጣጥ ሥርዓት ለመዘርጋት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ። ====================================== (ሰኔ 5 /2018 .ም) በኢትዮጵያ የሚካሄዱ ሳይንሳዊ ምርምሮች ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃዎችን የጠበቁና የሰዎችን ደኅንነት ያከበሩ እንዲሆኑ የሚያስችል የምርምር ሥነ-ምግባር ግምገማና እውቅና አሰጣጥ ሥርዓት ለመዘርጋት እየተሰራ መሆኑን የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ገልጸዋል። ይህ አዲሱ ሥርዓት በተለይም ከሰዎች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው ምርምሮች ከመጀመራቸው በፊት የሰዎችን ጥቅምና ጉዳት፣ ሂደቱን እንዲሁም የምርምር ቦታውን በጥብቅ መስፈርት በመመዘን ፍቃድ ለመስጠትና ለመከልከል የሚያስችል ጠንካራ መዋቅር የሚዘረጋ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ ይህንን የግምገማ ሥርዓት ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ በዚህ ረገድ የተሻለ ልምድ ካለው ከኡጋንዳ ብሔራዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ምክር ቤት ጋር ጠንካራ የሁለትዮሽ ትብብርን አጠናክራ የምትቀጥል መሆኑንም ገለጸዋል፡፡ ክቡር ሚኒሰትር ዴኤታው አከለውም ይህ ሥርዓት፣ የሀገሪቱ የሳይንስና ምርምር ዘርፍ በሕዝብና ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ዘንድ ፍጹም አመኔታና ግልጽነት እንዲኖረው ለማድረግ ያለመ መሆኑንም ተናገረዋል። ሙሉ ዜናውን ለማግኘት ፦ https://web.facebook.com/share/p/18sgZ3qPzG/

በኢትዮጵያ ትምህርት የቻይንኛ ቋንቋን ለማስተማር የሚያስችል የሁለትዮሽ የትብብር ስምምነት ትላንት ተፈርሟል። ስምምነቱን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት እና በኢትዮጵያ የቻ
+4
በኢትዮጵያ ትምህርት የቻይንኛ ቋንቋን ለማስተማር የሚያስችል የሁለትዮሽ የትብብር ስምምነት ትላንት ተፈርሟል። ስምምነቱን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት እና በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቺን ሃይ በጋራ ፈርመውታል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ታሪካዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ በተለይም በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በባህል ልውውጥ ዙሪያ አዳዲስ ምዕራፎችን የሚከፍት መሆኑ ተመልክቷል። በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ባስተላለፉት መልዕክት፣ ስምምነቱ ከዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ባለፈ በቱሪዝም፣ በህዝብ ለህዝብ ትስስር እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል። "ዜጎቻችን የተለያዩ ቋንቋዎችን እንዲማሩ መደረጉ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሆነው እንዲወጡ ትልቅ እድል ይፈጥራል" ያሉት ፕሮፌሰር ክንደያ፣ በተለይም ቻይና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂ ዘርፍ የደረሰችበትን የላቀ ደረጃ እና የነፃ የትምህርት ዕድል (Scholarship) ለኢትዮጵያውያን የምታመቻችበትን ሁኔታ ለማሳለጥ ስምምነቱ መሠረት መሆኑን አብራርተዋል። ስምምነቱ በስርዓተ ትምህርት ዝግጅት፣ በመምህራን ስልጠና እና በቁሳቁስ አቅርቦት ላይ የቴክኒክና የቻይና ቋንቋ መምህራንን ድጋፍ የሚያጠቃልል ሲሆን፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የዕውቀት ልውውጥን እና የስኮላርሺፕ ዕድሎችንም ያሰፋል ተብሏል። በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቺን ሃይ በበኩላቸው፣ ይህ ስምምነት በፍጥነት እያደገ የመጣውን የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑን ገልጸዋል። አምባሳደሩ አክለውም፣ በአሁኑ ወቅት በቻይና ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የአማር

በኢትዮጵያ ትምህርት የቻይንኛ ቋንቋን ለማስተማር የሚያስችል የሁለትዮሽ የትብብር ስምምነት ትላንት ተፈርሟል። ስምምነቱን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት እና በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቺን ሃይ በጋራ ፈርመውታል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ታሪካዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ በተለይም በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በባህል ልውውጥ ዙሪያ አዳዲስ ምዕራፎችን የሚከፍት መሆኑ ተመልክቷል። በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ባስተላለፉት መልዕክት፣ ስምምነቱ ከዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ባለፈ በቱሪዝም፣ በህዝብ ለህዝብ ትስስር እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል። "ዜጎቻችን የተለያዩ ቋንቋዎችን እንዲማሩ መደረጉ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሆነው እንዲወጡ ትልቅ እድል ይፈጥራል" ያሉት ፕሮፌሰር ክንደያ፣ በተለይም ቻይና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂ ዘርፍ የደረሰችበትን የላቀ ደረጃ እና የነፃ የትምህርት ዕድል (Scholarship) ለኢትዮጵያውያን የምታመቻችበትን ሁኔታ ለማሳለጥ ስምምነቱ መሠረት መሆኑን አብራርተዋል። ስምምነቱ በስርዓተ ትምህርት ዝግጅት፣ በመምህራን ስልጠና እና በቁሳቁስ አቅርቦት ላይ የቴክኒክና የቻይና ቋንቋ መምህራንን ድጋፍ የሚያጠቃልል ሲሆን፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የዕውቀት ልውውጥን እና የስኮላርሺፕ ዕድሎችንም ያሰፋል ተብሏል። በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቺን ሃይ በበኩላቸው፣ ይህ ስምምነት በፍጥነት እያደገ የመጣውን የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑን ገልጸዋል። አምባሳደሩ አክለውም፣ በአሁኑ ወቅት በቻይና ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የአማርኛ ቋንቋን ማስተማር መጀመሩ የሀገራቱን ታሪካዊ ግንኙነት ይበልጥ ያጠናከረና በባህል ልውውጥ ረገድ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑን በልዩነት አንስተዋል። ይህ የጋራ ስምምነት የሁለቱን ሀገራት ትብብር ማጠናከሪያ ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያን ተማሪዎች የክህሎት አድማስ በማስፋት ለነገው ዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ እና ለዲጂታል ዘመን ብቁ የማድረጉ ሂደት አካል መሆኑም ተጠቁሟል።

በመጪው የትምህርት ዘመን 1452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ሥራ ለማስጀመር የግንባታ ማስጀመር ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ነው። (ግንቦት 28/2018 ዓ.ም )በትምህርት ሚኒስቴር እና
በመጪው የትምህርት ዘመን 1452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ሥራ ለማስጀመር የግንባታ ማስጀመር ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ነው። (ግንቦት 28/2018 ዓ.ም )በትምህርት ሚኒስቴር እና በክልል ትምህርት ቢሮዎች ትብብር እየተገነቡ የሚገኙ 1,452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን እስከ መጪው ነሐሴ መጨረሻ ድረስ በማጠናቀቅ በአዲሱ የትምህርት ዘመን ለአገልግሎት ለማብቃት የግንባታ ማስጀመር ሥራዎች በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆናቸውን የትምህርት ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ከተማ መስቀላ ገልጸዋል። ዶ/ር ከተማ እንዳስታወቁት፣ ከአጠቃላይ 1,452 ትምህርት ቤቶች መካከል 726 በትምህርት ሚኒስቴር እና 726 በክልል ትምህርት ቢሮዎች አማካኝነት ይገነባሉ ብለዋል። የግንባታ ሂደቱንም ለማፋጠን እስካሁን በትምህርት ሚኒስቴር የሚገነቡ 341 ትምህርት ቤቶች እና በክልሎች የሚገነቡ 64 ትምህርት ቤቶች የኮንትራት ስምምነት ከተቋራጮች ጋር ተፈርሞ ወደ ሥራ የተገባ ሲሆን፣ 25 ትምህርት ቤቶች ደግሞ የግንባታ ሥራቸውን በይፋ መጀመራቸውን አብራርተዋል። እነዚህ ትምህርት ቤቶች በመጪው የትምህርት ዘመን ለአገልግሎት ሲበቁ ከ87,000 በላይ ሕፃናትን ተቀብለው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽነትን በ15 በመቶ እንደሚያሳድጉ ተገልጿል። ሥራ አስኪያጁ አክለውም በተለያዩ ምክንያቶች የግንባታ ሂደታቸው የዘገየባቸው ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ቀሪውን ጊዜ በተጠናከረ ቁርጠኝነት በመጠቀም ትምህርት ቤቶቹ በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ አስፈላጊውን ትኩረትና ክትትል እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡- በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/ በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe በትዊተር - http://twi
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡- በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/ በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe ዩቱዩብ- https://www.youtube.com/@ministry-of-education-ethiopia በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia በዌብሳይት - www.moe.gov.et

ትምህርት ሚኒስቴር ሙሉ በሙሉ በኦፍላይን የሚሰራና ራሱን ችሎ ውሳኔዎችን ማመንጨት የሚችል “ኤጀንቲክ መምህር ረዳት” (Agentic AI Teacher Assistant) የሰው ሰራሽ አስተውሎት መተግበሪ
+1
ትምህርት ሚኒስቴር ሙሉ በሙሉ በኦፍላይን የሚሰራና ራሱን ችሎ ውሳኔዎችን ማመንጨት የሚችል “ኤጀንቲክ መምህር ረዳት” (Agentic AI Teacher Assistant) የሰው ሰራሽ አስተውሎት መተግበሪያ አበልጽጎ በሙከራ ደረጃ ስራ ላይ አዋለ። (ግንቦት 28/2018 ዓም) ትምህርት ሚኒስቴር የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን የዕለት ተዕለት የሥራ ጫና በእጅጉ የሚቀንስ፣ ሙሉ በሙሉ ያለ ኢንተርኔት (Fully Offline) የሚሰራ እና ራሱን ችሎ ተግባራትን የሚያከናውን ኤጀንቲክ የሰው ሰራሽ አስተውሎት Agentic AI Teacher Assistant)  መተግበሪያ አበልጽጎ በሙከራ ደረጃ ስራ ላይ አውሏል። ‎ ‎የአይሲቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዘላለም አሰፋ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ይህ መተግበሪያ በማዕከላዊ ሰርቨር ወይም በክላውድ (Cloud) ቴክኖሎጂ ላይ የማይተማመን፣ ይልቁንም በአካባቢያዊ ኮምፒውተር (Local Machine) ላይ በቀላሉ ተጭኖ የሚሰራና በውስጥ አቅም የበለጸገ የቴክኖሎጂ ውጤት  መሆኑን ተናግረዋል። ሙሉ ዜናውን ለማግኘት https://web.facebook.com/share/p/1L47ihE7jo/

በኢትዮጵያና በቤልጂየም መካከል ያለው የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተደረገ። -------------------------- // -----------------
+2
በኢትዮጵያና በቤልጂየም መካከል ያለው የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተደረገ። -------------------------- // ----------------------- ‎ ‎(ግንቦት 23/2018 ዓ.ም) የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፉ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በኢትዮጵያ የቤልጅየምን አምባሳደር የሆኑትን ዶ/ር አኔሊስ ቬርስቲቼልን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ‎ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ጊዜ በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ እየተተገበሩ ስላሉ ዋና ዋና የሪፎርም ተግባራት ለክብርት አምባሳደሯ አብራርተዋል። ‎ ‎በሁለቱ አገራት መካከል በትምህርት መስክ በሰው ኃይል ልማት ፣ በጥናትና ምርምር ፣በልምምድ ልውውጥና በሌሎችም ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ የትብብር ግንኙነቶች መኖሩን አንስተዋል። ‎ ‎የትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ ራስገዝነትን ጨምሮ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጥራት፣ ብቃትና ተወዳዳሪነት ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ጠቅሰዋል። ‎ ‎በኢትዮጵያና ጅቡቲ የቤልጂየም አምባሳደርና የአፍሪካ ሕብረት የኢጋድና የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቋሚ ተወካይ ዶክተር አኔሊስ ቨርስቲቼል በበኩላቸው በኢትዮጵያና በቤልጂየም መንግስታት መካከል 120 ዓመታትን ያስቆጠረ ወዳጅነትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መኖሩን ተናግረዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://www.facebook.com/share/p/1BGKjx7TpH/

photo content

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች ከመንግስት የሚሰጥ የበጀት ድጋፍ አፈጻጸም ረቂቅ ደንብን አጸደቀ። (ግንቦት 18/2018 ዓ.ም) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 55ኛ
+1
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች ከመንግስት የሚሰጥ የበጀት ድጋፍ አፈጻጸም ረቂቅ ደንብን አጸደቀ። (ግንቦት 18/2018 ዓ.ም) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 55ኛ መደበኛ ስብሰባ፣ ለራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች ከመንግስት የሚሰጥ የበጀት ድጋፍ አፈጻጸምን ለመደንገግ በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በስፋት ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። በዚህም ምክር ቤቱ በረቂቅ ደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ፣ አስፈላጊ ግብአቶችን በማከል ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን በሙሉ ድምፅ አጽድቆታል። ደንቡ ለራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጠውን የመንግስት የበጀት ድጋፍ በታወቀ የጥቅል በጀት ስርዓት ላይ በመመስረት፣ የፋይናንስ ተጠያቂነትን፣ ፍትሃዊነትን እና ውጤታማነትን ለማረጋገጥ ያለመ ሲሆን፣ ዩኒቨርሲቲዎች የራሳቸውን ወጪ በራሳቸው የመሸፈን አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እንዲያሳድጉ ያግዛል። በተጨማሪም፣ በተቋማቱ መካከል ተመጣጣኝ የመማርና ማስተማር ጥራት፣ የአገልግሎት ፍትሃዊነት እና ኃላፊነት የተሞላበት አሰራር እንዲጠናከር ያስችላል። ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡- በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/ በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe ዩቱዩብ- https://www.youtube.com/@ministry-of-education-ethiopia በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ See less

photo content

photo content

photo content