ar
Feedback
Ministry of Education Ethiopia

Ministry of Education Ethiopia

الذهاب إلى القناة على Telegram

This is Ministry of Education's Official Telegram Channel. For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Ministry of Education Ethiopia

تُعد قناة Ministry of Education Ethiopia (@ethio_moe) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 149 805 مشتركاً، محتلاً المرتبة 759 في فئة التعليم والمرتبة 169 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 149 805 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 28 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 6 310، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 154، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 42.69‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 10.75‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 63 911 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 16 093 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 0.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
This is Ministry of Education's Official Telegram Channel. For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 29 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.

149 805
المشتركون
+15424 ساعات
+2 6517 أيام
+6 31030 أيام
أرشيف المشاركات
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የኢንተርፕረነርሽፕ ስራ ፈጠራ ስልጠናዎችን ማስፋፋት የትምህርት ጥራትን እና የኢኮኖሚ እድገትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑ ተመላከተ፤ ----------------------
+3
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የኢንተርፕረነርሽፕ ስራ ፈጠራ ስልጠናዎችን ማስፋፋት የትምህርት ጥራትን እና የኢኮኖሚ እድገትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑ ተመላከተ፤   ------------------------- // ------------------------ ‎ ‎(ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም) የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ እንደገለጹት በከፍተኛ ትምህርት የኢንተርፕረነርሽፕ ስራ ፈጠራ ስልጠናን ማስፋፋት የትምህርት ጥራትን እና የኢኮኖሚ እድገትን ለማረጋገጥ ያስችላል። ‎ ‎የኢንተርፕረነርሽፕ የስራ ፈጠራ   ምሩቃንን ስራ ፈላጊና ቅጥር ጠባቂ ሳይሆኑ የራሳቸውን ስራ እንዲፈጥሩና ለሌሎችም የስራ እድል እንዲከፍቱ እድል እንደሚሰጥ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል።   ‎የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በኢንተርፕርነርሽፕ የስራ ፈጠራ ችግር ፈቺ የፈጠራ ሀሳቦችን በማዳበር ምሩቃን በየአካባቢያቸው ያሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች የመፍቻ እድል አድርገው እንዲያዩና መፍትሄ እንዲያፈልቁ ማገዝ እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል። ‎ ‎የኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዮት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሐሰን ሑሴን በበኩላቸው ኢኒስቲትዩቱ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የኢንተርፕረነርሽፕ ስራ ፈጠራን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለማዝለቅና አደረጃጀትን ለመፍጠር   እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ‎ ‎የኢንተርፕርነርሽፕ ስራ ፈጠራን   በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለማዋሃዱ የሚካሄደው ተግባር ለማጠናከርም ተቋማቱ በላቀ ቅንጅትና ትብብር መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ዶ/ር ሐሰን ተናግረዋል። ‎   ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡- በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/ በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe በትዊተር - http://tw

ማስታወቂያ በክረምት መርሃ ግብር ለመማር ለተመረጣችሁ መምህራን በሙሉ ትምህርት ሚኒስቴር በማስተማር ሥራ ላይ ያሉ መምህራንን ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ለመጀመር
ማስታወቂያ በክረምት መርሃ ግብር ለመማር ለተመረጣችሁ መምህራን በሙሉ   ትምህርት ሚኒስቴር በማስተማር ሥራ ላይ ያሉ መምህራንን ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ለመጀመር በርካታ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል። በቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ጋር የተናበበ የሥልጠና ማዕቀፍ፣ ፕሮግራሙን ለመምራት የሚያስችሉ የትግበራ ሰነዶችንና የሰልጣኝ መምህራንን ምልመላ፣ መረጣ እና ምደባ ተከናውነዋል። ስለሆነም ባለፉት አመታት በስልጠናው አሰጣጥ ጥራት ችግር ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን የመምህራን የክረምት የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና በዚህ ክረምት ለማስጀመር ስምንት ዩኒቨርሲቲዎች ተለይተዋል። እነዚህም ባህር ዳር ፣ ሀዋሳ ፣ መቀሌ ፣ ጂማ ፣ ሃሮማያ ፣ ጎንደር እና አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲዎች ሲሆኑ በ2018 ዓ.ም ክረምት 8273 መምህራንን ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ወደ ስልጠና ለማስገባት ዝግጅት ተጠናቋል፡፡   በዚህ መሰረት የመግቢያ ምዘና ወስዳችሁ ያለፋችሁ እና በየዩኒቨርሲቲዎች የተመደባችሁ ሰልጣኝ መምህራን ምዝገባው ሐምሌ 24 እና 25/2018 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን በተጠቀሱት ቀናት በየተመደባችሁባቸው ዩኒቨርስቲዎች በመገኘት እንድትመዘገቡ እያሳሰብን  የተመደባችሁበትን ዩኒቨርስቲ ለማዎቅ ይህንን   https://shorturl.at/ZjN9e        ማስፈንጠሪያ በመጫን ማወቅ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

በኢትዮጵያ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርትን ለማሻሻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፤ የትምህርት ሚኒስቴር ከብሪቲሽ ካውንስል ጋር በመተባበር የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርትን ለማጠናከርና ጥራቱን ለማሻሻ
+3
በኢትዮጵያ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርትን ለማሻሻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፤ የትምህርት ሚኒስቴር ከብሪቲሽ ካውንስል ጋር በመተባበር የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርትን ለማጠናከርና ጥራቱን ለማሻሻል የተዘጋጀውን የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ ፕሮጀክት ወደ ተግባር ለማስገባት ቴክኒካል ሥራዎች በጋራ እየተሰሩ ነው።               ---------------------------- // ---------------------------- (ሐምሌ 21/2081 ዓ.ም) በፕሮጀክቱ ትውውቅ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና የመምህራንን ሙያዊ ብቃት ለማጎልበት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት በተማሪዎች የወደፊት ትምህርታዊና ሙያዊ እድገት ላይ ወሳኝ ሚና ያለው በመሆኑ፣ ተማሪዎች በመንግሥትም ሆነ በግል ትምህርት ቤቶች በእኩል ዕድል የቋንቋውን ክህሎት እንዲያገኙ ማድረግ ቀዳሚ ትኩረት የሚሻ ጉዳይ መሆኑንም ሚኒስትሩ አብራርተዋል። በተጨማሪም፣ በዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶች ፈጣን ምላሽ የሚፈልጉ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መምህራንን አቅም የመገንባት፣ የማስተማር ብቃታቸውን የማጎልበትና ውጤታማነታቸውን የማረጋገጥ ሥራዎች በተጠናከረ ሁኔታ ማከናወን እንደሚገባ ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር ዳረን ዌልች በበኩላቸው፣ ትምህርት ከማንኛውም ኢንቨስትመንት በላይ ዘላቂ ለውጥ የሚያመጣ ቁልፍ ዘርፍ መሆኑን ገልጸው፣ የእንግሊዝ መንግሥት በኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፍ የሚደረጉ ማሻሻያዎችን በቀጣይነት እንደሚደግፍ አስታውቀዋል። አምባሳደሩ አክለውም፣ በቅርቡ በትምህርት ሚኒስቴርና በብሪቲሽ ካውንስል ትብብር በይፋ የተጀመረው የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዚህ ቁርጠኝነት አካል መሆኑን

ማስታወቂያ ትምህርት ሚኒስቴር በነባርና አዲስ ትምህርት በሚጀመርባቸው የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራንና ርዕሳነ መምህራንን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። በመሆኑም መፈርቱን
+1
ማስታወቂያ ትምህርት ሚኒስቴር በነባርና አዲስ ትምህርት በሚጀመርባቸው የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራንና ርዕሳነ መምህራንን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። በመሆኑም መፈርቱን የምታሟሉ በሙሉ በበየነ መረብ ባልችሁበት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገልጽን በመምህርነት መመዝገብ ለምትፈልጉ በ https://sbs.moe.gov.et/career/teacher በርዕሰ መመህርነት ለመመዝገብ የምትፈልጉ https://sbs.moe.gov.et/directors መጠቀም የምትችሉ መሆኑ እናሳውቃለን።

የቡኢ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በፍጥነት እየተጠናቀቀ መሆኑ ተገለጸ። ----------------------- // ------------------------ (ሐምሌ 20/2018 ዓ.
+5
የቡኢ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በፍጥነት እየተጠናቀቀ መሆኑ ተገለጸ።          ----------------------- // ------------------------ (ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም) የቡኢ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በ2019 የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን ለመቀበል በሚያስችል ሁኔታ በፍጥነትና በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል። የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት የተመራ ልዑክ የትምህርት ቤቱ የግንባታ ሥራ የደረሰበትን ወቅታዊ ደረጃ በቦታው በመገኘት ተዘዋውሮ ተመልክቷል። በጉብኝቱ ወቅት የሕንጻዎቹ የግንባታ ሂደት በዝርዝር የተገመገመ ሲሆን፣ ትምህርት ቤቱ በ2019 የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጁ እንዲሆን ከሥራ ተቋራጩ ጋር በቀሪ ሥራዎችና በማጠናቀቂያ ሂደት ላይ ዝርዝር ውይይት ተካሂዷል። በተጨማሪም ከግንባታው ጎን ለጎን ትምህርት ቤቱን ለማስጀመር የሚያስፈልገውን የሰው ኃይል ምልመላና ምደባ ጨምሮ ሁሉንም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ከመስከረም 2019 ዓ.ም በፊት ለማጠናቀቅ በቅንጅት እየተሠራ መሆኑ ተገልጿል። በውይይቱ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት፣ የቡኢ ከተማ ከንቲባ፣ የሥራ ተቋራጩ ተወካዮች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል። ተሳታፊዎቹም ግንባታው በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅና ትምህርት ቤቱ በወቅቱ ተማሪዎችን እንዲቀበል የየድርሻቸውን ኃላፊነት በሙሉ እንደሚወጡ ገልጸዋል። ሙሉ መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ፤  https://www.facebook.com/share/p/1BkueAVRCc/

photo content

photo content

የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በተለያዩ ዙሮች በስኬት እየተካሄደ እንደሚገኝ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ። ************** የ2018 ትምህርት ዘ
የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በተለያዩ ዙሮች በስኬት እየተካሄደ እንደሚገኝ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ። ************** የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በተለያዩ ዙሮች በስኬት እየተካሄደ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል። አገልግሎቱ እንዳመለከተው፣ ፈተናው በበይነ መረብ (ኦንላይን) መሰጠት የጀመረ ሲሆን፣ ተፈታኞች በስድስት ዙሮች ተከፋፍለው በተሳካ ሁኔታ ፈተናቸውን እየወሰዱ ይገኛሉ ብሏል። ሆኖም የተወሰኑ የመሠረተ ልማት ተደራሽነትና የኮምፒውተር እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች ፈተናውን በአራት ዙሮች በወረቀት ለመስጠት አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መደረጉ ተገልጿል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ በትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በበይነ መረብ ለመፈተን ለተመዘገቡ 14 ሺህ 755 ተፈታኞች በስድስቱ ዙር ከሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ፈተናው እየተሰጠ ይገኛል። በሌላ በኩል በወረቀት ለመፈተን ለተመዘገቡ 15 ሺህ 325 የክልሉ ተፈታኞች ፈተናው ከሐምሌ 22 እስከ 24 ቀን 2018 ዓ.ም በመቐለ እና በአክሱም ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ ተመላክቷል። እነዚህ በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎች ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ መቐለ እና አክሱም ዩኒቨርሲቲዎች በመግባት፣ ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የሚሰጠውን ገለጻ (ኦሬንቴሽን) በመከታተል ፈተናቸውን መውሰድ እንደሚችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ጨምሮ ገልጿል።

የፈተና ስርቆትን የሚጠየፍ ትውልድ በመፍጠር ሂደት ውስጥ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አሳሰቡ። ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 በበይነ መረብና በወረቀት የሚሰጠው
+4
የፈተና ስርቆትን የሚጠየፍ ትውልድ በመፍጠር ሂደት ውስጥ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አሳሰቡ። ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 በበይነ መረብና በወረቀት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተካሂዷል።              -------------------------- // ----------------------- በመድረኩ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የፈተና ስርቆትን የሚጠየፍ ትውልድ በመፍጠር ሂደት ውስጥ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል ፡፡ በተለይም በፈተና ሂደት ወቅት ፈተና ለመስረቅም ይሁን ለማሰረቅ የሚሞክሩ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሩ ለፈተናው ስኬታማነት ሚኒስቴር መስሪያቤቱ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡  የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው የፈተናው አጠቃላይ ሂደት ደህንነቱ የተጠበቀ በሰላምና በውጤታማነት እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ በተባበረ አግባብና በተቀናጀ ሁኔታ መሰራት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል፡፡ የዘንድሮ የ12ኛ ክል ብሄራዊ ፈተና ከአጠቃላይ ተፈታኞች መካከል በአብዛኛው በበይነ መረብ የሚሰጥ መሆኑና የፈተና ተቋማቱ በርከት ባለ ሁኔታ በክልል ደረጃ የተደራጁ መሆናቸው ልዩ እንደሚያርገውም ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም የፈተናውን ደህንነቱን የማረጋገጥ ጉዳይ ከሌላው ጊዜ በተለየ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚያፈልግ ሚኒስትር ዴኤታዋ ክብርት ወ/ሮ አየለች አስገንዝበዋል፡፡ ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/1HCE2Y1BwH/

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተልዕኮና የትኩረት መስክ ልየታ ከአካባቢ ልማትና ጸጋ ጋር የተያያዘ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ። ----------------------------- // ----------
+4
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተልዕኮና የትኩረት መስክ ልየታ ከአካባቢ ልማትና ጸጋ ጋር የተያያዘ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ።   ----------------------------- // ----------------------------- ‎ ‎(ሰኔ 19/2018 ዓ.ም) የቡሌሆራና ቀብሪደሃር ዩኒቨርስቲዎች በማዕድንና ነዳጅ ላይ አትኩሮ ከሚሰራው የኦስትሪያው ሊዮቤን ዩኒቨርስቲ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ። ‎ ‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት የዩኒቨርስቲዎች የተልዕኮና የትኩረት መስክ ልየታ ከአካባቢ የልማት ጸጋ ጋር የተያያዙ እንዲሆን እየተሰራ ነው። ‎ ‎ የትኩረት መስክን ከተፈጥሮ ፀጋ ጋር ማያያዝ ሀብት፣ ጊዜና አቅምን በአግባቡ በመጠቀም ውጤታማ አንደሚያደርግም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። ‎ ‎የቡሌሆራና የቀብሪደሃር ዩኒቨርስቲዎች   የተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነትም በመምህራን ልማትና ምርምር፣ በቴክኖሎጂ ሽግግርና የዩኒቨርስቲ ኢንዲስትሪ ትብብርን ለማጠናከር እንደሚያስችል ተናግረዋል ። ‎ ‎የቡሌሆራ ዩኒቨርስቲ ከሊዮቤን ዩኒቨስቲ እና ከሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ጋር ስምምነት መፈራረሙን ጠቅሰው ይህም በማዕድን ምህንድስና እና ቴክኖሎጂ ዘርፎች የተሻለ ተፎካካሪ እንዲሆን ያስችለዋል ብለዋል። ‎ ‎የቀብሪ ደሃር ዩኒቨርስቲም ከሊዮቤን ቴክኒካል ዩኒቨርስቲ ጋር የተፈራረመው ስምምነት ዩኒቨርስቲው በአገር ውስጥ ብዙም ባልዳበረው የነዳጅና ኤነርጂ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆን ያግዘዋል ብለዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/1E2Y46YHWQ/

ሁሉም መሠረተ ልማት የተሟሉላቸው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እየተገነቡ ይገኛሉ። ---------------------- // --------------------- (
+2
ሁሉም መሠረተ ልማት የተሟሉላቸው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እየተገነቡ ይገኛሉ።   ---------------------- // ---------------------   (ሰኔ 18/2018 ዓ.ም) በዚህ መሠረት፣ በዛሬው ዕለት በትምህርት ሚኒስቴር ሙሉ ወጪ የሚገነባው የድሬዳዋ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የግንባታ ሥራ በይፋ ተጀምሯል።   የግንባታ ሥራውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጀዋር በጋራ አስጀምረውታል።   የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ ፕሮጀክቱ በሀገሪቱ የትምህርት ሪፎርም ጉዞ ውስጥ ጉልህ አስተዋጽኦ የሚኖረው ሲሆን እንደ ሀገር 50 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እየተሠራ መሆኑን ጠቅሰዋል።   የድሬዳዋ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ሲጠናቀቅ ዘመናዊ የመማሪያ ክፍሎች፣ የሳይንስ ላቦራቶሪዎች፣ የኮምፒውተር ማዕከላት፣ የስፖርትና የመዝናኛ ጨምሮ የተሟላ የትምህርት አካባቢ የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።   በተጨማሪም ትምህርት ቤቱ በአካባቢው ያለውን የተማሪ ክፍል ጥምርታ ለማሻሻል፣ ለተማሪዎች የተሻለ የመማሪያ አካባቢ ለመፍጠር እና የትምህርት ጥራትን በከፍተኛ ደረጃ ለማሻሻል የሚያስችል እንደሚሆንም ገልፀዋል ። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/18tBtY9TRj/

በትምህርት ዘርፉ ከተወሰዱ የሪፎርም ተግባራት ዋናውና ወሳኙ በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽነት ላይ እየተሰራ ያለው ሥራ ነው ሲሉ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ። -------------------
+3
በትምህርት ዘርፉ ከተወሰዱ የሪፎርም ተግባራት ዋናውና ወሳኙ በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽነት ላይ እየተሰራ ያለው ሥራ ነው ሲሉ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።   ---------------------- // ------------------------   (ሰኔ 18/2018 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የድሬዳዋ ከንቲባ አቶ ከድር ጀዋር በድሬዳዋ ከተማ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታን አስጀምረዋል።   በዚሁ ወቅት ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ለሕፃናት የመማር መሠረትን የሚጥል በመሆኑ በሀገር አቀፍ ደረጃ ተደራሽነቱን ለማስፋፋት ሰፊ ሥራ እየተከናወነ ነው።   በተለይም በትምህርት ሪፎርሙ ማዕቀፍ ውስጥ ለሁሉም ሕፃናት ፍትሃዊና ጥራት ያለው የመማር ዕድል ለመፍጠር የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታና ማስፋፊያ ሥራዎች ቅድሚያ ተሰጥቶት እየተሠራ መሆን ጠቅሰዋል።   ክቡር ከንቲባ ከድር ጀዋር በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በከተማው ያለውን የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ፍላጎት ለማሟላትና የሕፃናትን የመማር ዕድል ለማስፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ገልጸዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/18Xc4aqgiL/

ትምህርት ሚኒስትሩ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታን አስጀመሩ -------------------------- // -----------------------
+3
ትምህርት ሚኒስትሩ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታን አስጀመሩ   -------------------------- // ----------------------------- (ሰኔ 18/2018 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጀዋር በትምህርት ሚኒስቴር ሙሉ ወጪ በድሬዳዋ ከተማ የሚገነባውን የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በይፋ አስጀምረዋል። በዚሁ ጊዜ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት መንግሥት የተሻለ የትምህርት ጥራትና የላቀ የትምህርት አካባቢ ለመፍጠር በመላ ሀገሪቱ የተመረጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸውን የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በተለያዩ አካባቢዎች እየገነባ መሆኑን ገልጸዋል። ሚኒስትሩ አክለውም፣ ዛሬ ግንባታው የተጀመረው ትምህርት ቤትም ከመላው ሀገሪቱ በብቃታቸው የተመረጡ ተማሪዎችን በመቀበል የሚያስተምር ሲሆን፣ ግንባታው በአንድ ዓመት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ ጠቅሰዋል። በተጨማሪም የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን የማስፋፋት ሥራ በቀጣይነት እንደሚቀጥል ገልጸው፣ በባህርዳር፣ አርባምንጭ እና አሶሳ ተመሳሳይ የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ግንባታ በቅርቡ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጀዋር በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር ለከተማዋ እድገትና ለትውልድ ግንባታ እያደረገ ላለው አስፈላጊ ድጋፍ ምስጋናቸውን ገልጸው፣ የከተማ አስተዳደሩ ፕሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤  https://web.facebook.com/share/p/1PuiqKwBrR/

ዩኒቨርስቲዎች ከፖለቲካ ጣልቃገብነት ተላቀው ነጻ እውቀትና ሃሳብ የሚፈልቅባቸው ተቋማት እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ። ---------------------
+4
ዩኒቨርስቲዎች ከፖለቲካ ጣልቃገብነት ተላቀው ነጻ እውቀትና ሃሳብ የሚፈልቅባቸው ተቋማት እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።               --------------------- //------------------------ (ሰኔ 17/2018 ዓ.ም) በቀጣይ ወደ ራስገዝነት የሚሸጋገሩ ዩኒቨርስቲዎች የዝግጁነት ግምገማ ውጤት በቀረበበት መድረክ ላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ የከፍተኛ ትምህርት ሪፎርሙ ዋና ዓላማ ለእውነትና ለእውቀት ቁርጠኛ፣ አገራቸውን የሚወዱና የሚለውጡ ዜጎችን ማፍራት መሆኑን ተናግረዋል። ‎ ‎የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ነጻና ከፖለቲካ ጣልቃ-ገብነት ተላቀው ነጻ ሃሳብ የሚፈልቅባቸው ተቋማት እንዲሆኑ ወደ ራስ-ገዝነት ማሸጋገር ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። ‎ ‎የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለእውነትና ለእውቀት ቁርጠኝነት ያላቸውና አገራቸውን የሚወዱና የሚለውጡ የሰው ሃይል የሚያፈሩ እንዲሆኑ ማስቻል የሪፎርሙ መሠረት መሆኑንም ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ‎ ‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው እንደገለጹት ወደ ራስገዝነት የሚሸጋገሩ ተቋማት ከአክሪዲቴሽን ጋር በተያያዘ በተለይ የሀገር ውስጥ እውቀት በእጅጉ ጠቃሚ መሆኑን አንስተዋል። ‎ ‎ከውስጥ ገቢ ጋር በተያያዘም ተቋማቱ በዘላቂና ብዝሃ ገቢ ማስገኛ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርገው ሊሰሩ እንደሚገባ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/1BFQ2MqAiN/

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት መምህራን የተጣለባቸውን ሀገራዊ ሀላፊነት በሚገባ እንዲወጡ ተጠየቀ። ------------------------- //--------------------------- (ሰኔ
+2
የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት መምህራን የተጣለባቸውን ሀገራዊ ሀላፊነት በሚገባ እንዲወጡ ተጠየቀ።   ------------------------- //--------------------------- (ሰኔ 17/2018 ዓ.ም) ብቃትን መሰረት ያደረገ መማር ማስተማርን በሚመለከት ልዩ የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመምህራን እየተሰጠ ይገኛል።       ትምህርት ሚኒስቴር ከመላው ሀገሪቱ የተውጣጡ ብቃት ያላቸውን ተማሪዎች በመምረጥና በፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በማስተማር የሀገሪቱን የወደፊት የሰው ሀብት ለመገንባት እየሰራ ይገኛል። እነዚህ ትምህርት ቤቶች በአካዳሚክ ብቃት፣ በሥነ-ምግባር፣ በአመራር ክህሎት እና በሀገራዊ እሴቶች የተገነባ ትውልድ ለማፍራት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወቱ የተገልጸ ሲሆን፣ ይህንን ሀገራዊ ተልዕኮ በተሻለ ብቃት ለማሳካትም በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ መምህራንን ብቃት መሰረት ባደረገና የመማርና የማስተማር ሥርዓት ላይ ያተኮረ ልዩ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጣቸው ይገኛል። ስልጠናው በትምህርት ቤቶቹ የሚሰጠውን የትምህርት ጥራት ወደ ላቀ ደረጃ ከማሸጋገሩም በላይ፣ መምህራን ተማሪዎችን የእውቀት ተቀባዮች ብቻ ሳይሆኑ ችግር ፈቺዎች፣ ፈጠራ ባለቤቶች እና ሀገራቸውን የሚያገለግሉ ዜጎች እንዲሆኑ የሚያስችሉ ዘመናዊ የማስተማር ስነ-ዘዴዎችን እንዲላበሱ ያስችላቸዋልም ተብሏል።

በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ቤቶች ምገባን የሚደግፍ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ የትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የተቋቋመውን የትምህርት ቤቶች
+4
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ቤቶች ምገባን የሚደግፍ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ የትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የተቋቋመውን የትምህርት ቤቶች ምገባ የሚደግፍን ፕሮጀክት በይፋ አስጀምረዋል። በማስጀመሪያ መርኃ ግብሩ ላይ የተገኙት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ፣ ፕሮጀክቱ የተጀመረወን የትምህርት ቤት ምገባ ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ እና ተማሪዎች በቂና ተመጣጣኝ ምግብ በማግኘት በትምህርታቸው ላይ የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልጸዋል። ለፕሮጀክቱ ስኬት የተለያዩ ድጋፎችን ላደረጉ አጋር ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ምስጋናቸውን ገልጸው፣ ተማሪዎች በጤናማ ሁኔታ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ የሚያስችሉ መሰል ፕሮጀክቶች በሌሎች የሀገራችን ክፍሎች እንዲስፋፉ ምሳሌ ይሆናል ብለዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የትምህርት ቤት ምገባ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሀርቢ ቡህ በበኩላቸው፣ ፕሮጀክቱ በሞዴልነት የሚጠቀስ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም የድሬዳዋ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልይ ከዚህ ቀደም በተበታተነ መልኩ ይከናወን የነበረው የትምህርት ቤት ምገባ አገልግሎት ወደ አንድ ማዕከላዊ ሥርዓት በማምጣት ትልቅ የሪፎርም ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል። ይህም የተማሪዎች የምግብ ዝግጅትና ስርጭት ሂደቱን ቀልጣፋ፣ ወጪ ቆጣቢና ዘላቂ እንዲሆን እንደሚያስችል ተናግረዋል። ሙሉ ዜናውን ለማግኘት https://web.facebook.com/share/p/14fY9nME2GB/

በኢትዮጵያ የሚካሄዱ ሳይንሳዊ ምርምሮች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁና የሰዎችን ደኅንነት ያከበሩ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚያስችል የምርምር ሥነ-ምግባር ግምገማና እውቅና አሰጣጥ ሥርዓት ለመዘርጋት እ
+3
በኢትዮጵያ የሚካሄዱ ሳይንሳዊ ምርምሮች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁና የሰዎችን ደኅንነት ያከበሩ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚያስችል የምርምር ሥነ-ምግባር ግምገማና እውቅና አሰጣጥ ሥርዓት ለመዘርጋት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ። ====================================== (ሰኔ 5 /2018 .ም) በኢትዮጵያ የሚካሄዱ ሳይንሳዊ ምርምሮች ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃዎችን የጠበቁና የሰዎችን ደኅንነት ያከበሩ እንዲሆኑ የሚያስችል የምርምር ሥነ-ምግባር ግምገማና እውቅና አሰጣጥ ሥርዓት ለመዘርጋት እየተሰራ መሆኑን የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ገልጸዋል። ይህ አዲሱ ሥርዓት በተለይም ከሰዎች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው ምርምሮች ከመጀመራቸው በፊት የሰዎችን ጥቅምና ጉዳት፣ ሂደቱን እንዲሁም የምርምር ቦታውን በጥብቅ መስፈርት በመመዘን ፍቃድ ለመስጠትና ለመከልከል የሚያስችል ጠንካራ መዋቅር የሚዘረጋ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ ይህንን የግምገማ ሥርዓት ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ በዚህ ረገድ የተሻለ ልምድ ካለው ከኡጋንዳ ብሔራዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ምክር ቤት ጋር ጠንካራ የሁለትዮሽ ትብብርን አጠናክራ የምትቀጥል መሆኑንም ገለጸዋል፡፡ ክቡር ሚኒሰትር ዴኤታው አከለውም ይህ ሥርዓት፣ የሀገሪቱ የሳይንስና ምርምር ዘርፍ በሕዝብና ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ዘንድ ፍጹም አመኔታና ግልጽነት እንዲኖረው ለማድረግ ያለመ መሆኑንም ተናገረዋል። ሙሉ ዜናውን ለማግኘት ፦ https://web.facebook.com/share/p/18sgZ3qPzG/

በኢትዮጵያ ትምህርት የቻይንኛ ቋንቋን ለማስተማር የሚያስችል የሁለትዮሽ የትብብር ስምምነት ትላንት ተፈርሟል። ስምምነቱን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት እና በኢትዮጵያ የቻ
+4
በኢትዮጵያ ትምህርት የቻይንኛ ቋንቋን ለማስተማር የሚያስችል የሁለትዮሽ የትብብር ስምምነት ትላንት ተፈርሟል። ስምምነቱን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት እና በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቺን ሃይ በጋራ ፈርመውታል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ታሪካዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ በተለይም በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በባህል ልውውጥ ዙሪያ አዳዲስ ምዕራፎችን የሚከፍት መሆኑ ተመልክቷል። በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ባስተላለፉት መልዕክት፣ ስምምነቱ ከዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ባለፈ በቱሪዝም፣ በህዝብ ለህዝብ ትስስር እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል። "ዜጎቻችን የተለያዩ ቋንቋዎችን እንዲማሩ መደረጉ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሆነው እንዲወጡ ትልቅ እድል ይፈጥራል" ያሉት ፕሮፌሰር ክንደያ፣ በተለይም ቻይና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂ ዘርፍ የደረሰችበትን የላቀ ደረጃ እና የነፃ የትምህርት ዕድል (Scholarship) ለኢትዮጵያውያን የምታመቻችበትን ሁኔታ ለማሳለጥ ስምምነቱ መሠረት መሆኑን አብራርተዋል። ስምምነቱ በስርዓተ ትምህርት ዝግጅት፣ በመምህራን ስልጠና እና በቁሳቁስ አቅርቦት ላይ የቴክኒክና የቻይና ቋንቋ መምህራንን ድጋፍ የሚያጠቃልል ሲሆን፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የዕውቀት ልውውጥን እና የስኮላርሺፕ ዕድሎችንም ያሰፋል ተብሏል። በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቺን ሃይ በበኩላቸው፣ ይህ ስምምነት በፍጥነት እያደገ የመጣውን የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑን ገልጸዋል። አምባሳደሩ አክለውም፣ በአሁኑ ወቅት በቻይና ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የአማር

በኢትዮጵያ ትምህርት የቻይንኛ ቋንቋን ለማስተማር የሚያስችል የሁለትዮሽ የትብብር ስምምነት ትላንት ተፈርሟል። ስምምነቱን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት እና በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቺን ሃይ በጋራ ፈርመውታል። ይህ ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ታሪካዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ በተለይም በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በባህል ልውውጥ ዙሪያ አዳዲስ ምዕራፎችን የሚከፍት መሆኑ ተመልክቷል። በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ባስተላለፉት መልዕክት፣ ስምምነቱ ከዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ባለፈ በቱሪዝም፣ በህዝብ ለህዝብ ትስስር እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል። "ዜጎቻችን የተለያዩ ቋንቋዎችን እንዲማሩ መደረጉ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሆነው እንዲወጡ ትልቅ እድል ይፈጥራል" ያሉት ፕሮፌሰር ክንደያ፣ በተለይም ቻይና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂ ዘርፍ የደረሰችበትን የላቀ ደረጃ እና የነፃ የትምህርት ዕድል (Scholarship) ለኢትዮጵያውያን የምታመቻችበትን ሁኔታ ለማሳለጥ ስምምነቱ መሠረት መሆኑን አብራርተዋል። ስምምነቱ በስርዓተ ትምህርት ዝግጅት፣ በመምህራን ስልጠና እና በቁሳቁስ አቅርቦት ላይ የቴክኒክና የቻይና ቋንቋ መምህራንን ድጋፍ የሚያጠቃልል ሲሆን፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የዕውቀት ልውውጥን እና የስኮላርሺፕ ዕድሎችንም ያሰፋል ተብሏል። በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቺን ሃይ በበኩላቸው፣ ይህ ስምምነት በፍጥነት እያደገ የመጣውን የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑን ገልጸዋል። አምባሳደሩ አክለውም፣ በአሁኑ ወቅት በቻይና ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የአማርኛ ቋንቋን ማስተማር መጀመሩ የሀገራቱን ታሪካዊ ግንኙነት ይበልጥ ያጠናከረና በባህል ልውውጥ ረገድ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑን በልዩነት አንስተዋል። ይህ የጋራ ስምምነት የሁለቱን ሀገራት ትብብር ማጠናከሪያ ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያን ተማሪዎች የክህሎት አድማስ በማስፋት ለነገው ዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ እና ለዲጂታል ዘመን ብቁ የማድረጉ ሂደት አካል መሆኑም ተጠቁሟል።