ch
Feedback
Ministry of Education Ethiopia

Ministry of Education Ethiopia

前往频道在 Telegram

This is Ministry of Education's Official Telegram Channel. For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

显示更多

📈 Telegram 频道 Ministry of Education Ethiopia 的分析概览

频道 Ministry of Education Ethiopia (@ethio_moe) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 165 296 名订阅者,在 教育 类别中位列第 643,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 147

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 165 296 名订阅者。

根据 15 九月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 10 980,过去 24 小时变化为 354,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 27.48%。内容发布后 24 小时内通常能获得 12.78% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 45 405 次浏览,首日通常累积 21 118 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
This is Ministry of Education's Official Telegram Channel. For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

凭借高频更新(最新数据采集于 16 九月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

165 296
订阅者
+35424 小时
+2 1107 天
+10 98030 天
帖子存档
ማስታወቂያ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የዩኒቨርሲቲ ምደባን ይመለከታል በትምህርት ሚኒስቴር በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች
ማስታወቂያ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የዩኒቨርሲቲ ምደባን ይመለከታል በትምህርት ሚኒስቴር በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን ወደ መንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የመመደብ ሂደትን አጠናቋል። ምደባው ፍትሐዊነትን፣ ግልጽነትን፣ እኩል ዕድልን እና ሚዛናዊ ስርጭትን በሚያረጋግጥ መልኩ፣ የተማሪዎችን ውጤትና ምርጫ፣ የዩኒቨርሲቲዎችን የቅበላ አቅም እንዲሁም ሌሎች የምደባ መስፈርቶችን ታሳቢ በማድረግ ተከናውኗል። 1. የምደባው ዋና መስፈርቶች 1.1. የተማሪዎች አጠቃላይ ውጤት እና የዩኒቨርሲቲ ምርጫ የተማሪዎች አጠቃላይ የብሔራዊ ፈተና ውጤት የምደባው ዋና የቅደም ተከተል መስፈርት ሆኖ ተወስዷል። በዚህም መሠረት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች በምርጫቸው መሠረት የመመደብ ቅድሚያ እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን በተቻለ መጠን ከመረጧቸው የመጀመሪያ ሦስት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲመደቡ ተደርጓል። 1.2. የዩኒቨርስቲዎች የተማሪ ቅበላ አቅም የእያንዳንዱ ዩኒቨርስቲ የተማሪ ቅበላ አቅም በምደባው ሂደት ታሳቢ ተደርጓል። በመሆኑም የተማሪው ውጤትና ምርጫ ከዩኒቨርስቲዎች የቅበላ አቅም ጋር በማጣጣም ምደባው ተከናውኗል። 1.3. የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ እና የትምህርት ቤት ስርጭት በዩኒቨርሲቲዎቻችን ብዝሃነትን ለማጠናከር እና የተማሪዎችን ሚዛናዊ ስርጭት ለማረጋገጥ፦ • 70 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ከተማሩበት ክልል ወይም ዞን ውጭ ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲመደቡ፤ • 30 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ደግሞ በተማሩበት ክልል ወይም ዞን ውስጥ ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲመደቡ  ተደርጓል። በተጨማሪም የዞን፣ የወረዳ እና የትምህርት ቤት ስርጭት በምደባው ሂደት ታሳቢ ተደርጓል። ሙሉ መረጃውን ለየት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com

ማስታወቂያ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የዩኒቨርሲቲ ምደባን ይመለከታል የትምህርት ሚኒስቴር በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች
+1
ማስታወቂያ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የዩኒቨርሲቲ ምደባን ይመለከታል የትምህርት ሚኒስቴር በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን ወደ መንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የመመደብ ሂደት አጠናቆ የምደባ ውጤቱን ይፋ አድርጓል።   የተማሪዎች ምደባ ፍትሐዊነትን፣ ግልጽነትን፣ እኩል ዕድልን እና ሚዛናዊ ስርጭትን በሚያረጋግጥ መልኩ፣ የተማሪዎችን ውጤትና ምርጫ፣ የዩኒቨርሲቲዎችን የቅበላ አቅም እንዲሁም ሌሎች የምደባ መስፈርቶችን ታሳቢ በማድረግ ተከናውኗል። 1. የምደባው ዋና መስፈርቶች 1.1. የተማሪዎች አጠቃላይ ውጤት እና የዩኒቨርሲቲ ምርጫ የተማሪዎች አጠቃላይ የብሔራዊ ፈተና ውጤት የምደባው ዋና የቅደም ተከተል መስፈርት ሆኖ ተወስዷል። በዚህም መሠረት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች በምርጫቸው መሠረት የመመደብ ቅድሚያ እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን በተቻለ መጠን ከመረጧቸው የመጀመሪያ ሦስት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲመደቡ ተደርጓል። 1.2. የዩኒቨርስቲዎች የተማሪ ቅበላ አቅም የእያንዳንዱ ዩኒቨርስቲ የተማሪ ቅበላ አቅም በምደባው ሂደት ታሳቢ ተደርጓል። በመሆኑም የተማሪው ውጤትና ምርጫ ከዩኒቨርስቲዎች የቅበላ አቅም ጋር በማጣጣም ምደባው ተከናውኗል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/14oM1pUCTJR/

ኢትዮጵያና ስሎቫኪያ በትምህርት ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ ---------------------- // ------------------------- (መስከረም 06
+3
ኢትዮጵያና ስሎቫኪያ በትምህርት ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ ---------------------- // ------------------------- (መስከረም 06/2019 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የስሎቫኪያ ሪፐብሊክ አምባሳደር በኢትዮጵያ ራስቲስላቭ ክሪዛንን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው በሁለቱ ሀገራት መካከል በትምህርቱ ዘርፍ ሊኖር ስለሚችለው ትብብር ተወያይተዋል። በውይይቱ ወቅት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ኢትዮጵያ ከስሎቫኪያ ጋር በትምህርት ዘርፍ ያላትን ትብብር የበለጠ ማጠናከር እንደምትፈልግ ገልጸው፣ በሀገሪቱ እየተካሄዱ ስላሉ የትምህርት ሪፎርም ሥራዎች ለአምባሳደሩ አብራርተዋል። በተለይም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ዩኒቨርሲቲዎችን በተልዕኮና በትኩረት መስክ በመለየት እንዲደራጁ እየተሠራ መሆኑን ጠቁመው፣ ዩኒቨርሲቲዎች የበለጠ አስተዳደራዊ ነፃነት እንዲኖራቸው ራስ ገዝ በሆነ መልኩ እንዲደራጁ እየተደረገ መሆኑንም አንስተዋል። የትምህርት ሪፎርሙ የበለጠ ውጤታማና ዘላቂ ውጤት እንዲያመጣ የተለያዩ የድጋፍና የትብብር አማራጮች እንደሚያስፈልጉ የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በአዲስ የኢኮኖሚ ሪፎርም ላይ በመገኘቷ ከዚህ ጋር በተያያዙ አዳዲስና ተፈላጊ የትምህርት መስኮች በትብብር መሥራት እንደምትፈልግ ጠቁመዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/1HF5jLJ5fu/

በመላው ሀገራችን ለሚገኙ ተማሪዎቻችን አዲሱ የትምህርት ዘመን ስኬታማ እንዲሆን እንመኛለን! ‎ ‎ወጣቱ ትውልድ ለኢትዮጵያ ትልቁ ሀብቷ በመሆኑ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጅማሮን ተከትሎ፤ እያን
በመላው ሀገራችን ለሚገኙ ተማሪዎቻችን አዲሱ የትምህርት ዘመን ስኬታማ እንዲሆን እንመኛለን! ‎ ‎ወጣቱ ትውልድ ለኢትዮጵያ ትልቁ ሀብቷ በመሆኑ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጅማሮን ተከትሎ፤ እያንዳንዱ ተማሪ ለላቀ እውቀት በትጋትና ጉጉት ትምህርቱን እንዲከታተል፣ ለጥሩ ውጤት በጽናት እንዲተጋ፣ እንዲሁም የሀገራችንን የወደፊት ዕድል መቅረጽ በሚያስችሉ ክህሎቶች እንዲገነባ አበረታታለሁ። ‎ ‎ዛሬ እየተገበርነው ያለው በርካታ የልማት ሥራዎች የነገን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ በመሆናቸው፣ የዚህ ቀጣይ ዕድል ተጠቃሚ እና ባለአደራ እንደመሆናችሁ መጠን፣ የኢትዮጵያን ታላቅ የስልጣኔ ታሪክ ወደፊት ለማስቀጠል የእናንተ ቁርጠኝነት መሠረት እንደሆነ ሙሉ እምነቴ ነው። ‎ ‎ብቁ እና በራሱ የሚተማመን ትውልድ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመምህራኖቻችን ትጋትና መሰጠት መሰረታዊ ምሰሶ ነው። ተማሪዎቻችንን ማነቃቃት፣ አቅማቸውን ማውጣት፣ እንዲሁም ነገ ተፎካካሪ ሆነው እንዲወጡ የሚያስችሏቸውን ዕውቀት፣ ክህሎትና እሴቶችን የማስታጠቅ አደራን ቀጥሉበት ስል በትህትና አሳስባለው። ‎ ‎በትምህርት ዘርፉ ውስጥ ለምትገኙ ባለድርሻ አካላት በሙሉ፤ ስኬታማ እና ፍሬያማ የትምህርት ዘመን እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በሁሉም መስክ የወደፊቱ አገር መሪዎች የሚፈጠሩባቸው ተቋማት እንዲሆኑ እየተሰራ እንደሚገኝ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ ። -----------------------
+5
የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በሁሉም መስክ የወደፊቱ አገር መሪዎች የሚፈጠሩባቸው ተቋማት እንዲሆኑ እየተሰራ እንደሚገኝ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ ። ------------------------ // ------------------------- ‎ ‎(መስከረም 05/2019 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አዲስ ከተመደቡ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች መምህራን ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት ‎ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በሁሉም በኩል የወደፊቱ የአገር መሪ የሚሆኑ ዜጎች የሚፈልቁባቸው ተቋማት ይሆናሉ ብለዋል። ‎ ‎ትምህርት ቤቶቹ የነገዋን ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ፣ በሳይንስ፣ በፖለቲካ ፣በፍልስፍና በሌሎችም የሚገነቡ አገር ወዳድ ዜጎች መፍለቂያዎች እንደሚሆኑ ያላቸውን እምነት ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ‎ ‎አያይዘውም ለሁሉም እኩል የሚያስቡና ሁሉንም እኩል መምራትና ማገልገል የሚችሉና አገርን ከቅርቃርና ከችግር ማውጣት የሚችሉ ዜጎች የሚፈጠሩባቸው ተቋማት እንደሚሆኑም ጠቅሰዋል። ‎ ‎ትምህርት ቤቶቹ ከሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች የተውጣጡ ዜጎች የሚማሩባቸውና ከሁሉም ቦታ የተውጣጡ መምህራንና በችሎታ ተመርጠው የሚያስተምሩባቸው ተቋማት መሆናቸውንም ጠቁመዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/1Efqvo52qb/

photo content

2018 ዓ.ም. በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች በሌሎች የመንግስት ኒቨርስቲዎች እንዲመደቡ መወሰኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ፤ ሚኒስትሩ በትግ
+5
2018 ዓ.ም. በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች በሌሎች የመንግስት ኒቨርስቲዎች እንዲመደቡ መወሰኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ፤ ሚኒስትሩ በትግራይ ክልል ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ይማሩ የነበሩ ተማሪዎችን አነጋግረዋል፡፡ ………………………………….. // ……………………………. ‎(መስከረም 04/2018 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከተማሪዎቹ ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት በ2018 ዓ.ም. በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች ደህንነታቸው ወደሚጠበቁባቸው ሌሎች ዩኒቨርስቲዎች እንዲመደቡ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑን ተናግረዋል፡፡ ‎ ‎ክቡር ሚኒስትሩ እንደገለጹት ጦርነትና ግጭት ሸሽተው ከትግራይ የወጡ ተማሪዎች ብቻ ሳይሆን ትግራይ ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች ትምህርት ሚኒስቴር መምጣት ሳይጠበቅባቸው ከቻሉ ከትግራይ ወጥተው አሊያም ባሉበት በኦንላይ ለመማር የሚችሉበት ቦታ ላይ እንደሚመዘገቡና ትምህርትታቸውን መማር እንደሚችሉ አስረድተዋል፡፡ ‎ ‎ተማሪዎቹን ምዝገባ ለማካሄድ ትምህርት ሚኒስቴር በበይነ መረብ የምዝገባ ስርዓት ማዘጋጀቱን የገለጹት ሚኒስትሩ ሁሉም በትግራይ ክልል ባሉ አራቱ ዩኒቨርስቲዎች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች ከዛሬ ማታ ጀምሮ ይፋ በሚደረገው የኦንላይን መተግበሪያ ፕላት ፎርም በመሙላት እንዲመዘገቡ አሳውቀዋል፡፡ ሙሉ መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፤ https://web.facebook.com/share/p/1BgiGPjwXJ/

📢 ማስታወቂያ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ነገ መስከረም 05 ቀን 2019 ዓ.ም ይጀምራል! ውድ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆች/አሳዳጊዎች እና መላው የትምህርት ማኅበረሰብ፤ እንኳን ለ2019 አ
📢 ማስታወቂያ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ነገ መስከረም 05 ቀን 2019 ዓ.ም ይጀምራል! ውድ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆች/አሳዳጊዎች እና መላው የትምህርት ማኅበረሰብ፤ እንኳን ለ2019 አዲሱ ዓመት እና የትምህርት ዘመን አደረሳችሁ! በትምህርት ካሌንደሩ መሠረት፣ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በመላ ሀገሪቱ ነገ፣ መስከረም 05 ቀን 2019 ዓ.ም፣ በይፋ ይጀምራል። በዚህም ትምህርት ቤቶች ለአዲሱ የትምህርት ዘመን የሚያስፈልጉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በማጠናቀቅ እናንተን ለመቀበልና የመማር–ማስተማር ሂደቱን በተቀመጠው የትምህርት ካሌንደር መሠረት ለመጀመር እየተጠባበቁ ይገኛል። ስለሆነም፣ ወላጆች/አሳዳጊዎች እና ሁላችሁም የሚመለከታችሁ አካላት ለትምህርት የደረሱ ልጆችን  አስፈላጊውን የትምህርት ግብዓት በማሟላት ወደ ትምህርት ቤት እንዲሄዱ በማድረግ፣ የድርሻችሁን እንድትወጡ በዚህ አጋጣሚ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን። 🌟 መልካም የትምህርት ዘመን! ትምህርት ሚኒስቴር

photo content

photo content

ማስታወቂያ ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ ትምህርት በሚጀምርባቸውና እና ለነባር የፌደራል አዳሪ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራንን ለመልመል ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት የጽሁፍ እና የቃል ፈተ
+5
ማስታወቂያ ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ ትምህርት በሚጀምርባቸውና እና ለነባር የፌደራል አዳሪ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራንን ለመልመል ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት የጽሁፍ እና የቃል ፈተና ወስዳችሁ   ያለፋችሁ መምህራን ዝርዝራችሁን መመልከት የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን። ያለፋችሁ መምህራን መስከረም 5/2019 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ የትምህርት ቤት ምደባ እና ስልጠና የሚሰጣችሁ በመሆኑ ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ በተጠቀሰው ቀን በትምህርት ሚኒስቴር ዋናው ግቢ የመሰብሰቢያ አዳራሽ እንድትገኙ እናሳውቃለን።   ማሳሰቢያ፦ በዚህ ስልጠና እና ኦረንቴሽን የማይገኝ ማንኛውም መምህር ከምደባው የሚሰረዝ መሆኑን እንገልጻለን፡፡   በተጨማሪም መስከረም 7 እና 8/2019 ዓ.ም በየተመደባችሁበት ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ዩኒቨርሲቲዎች)አስፈላጊውን መረጃ በመያዝ ሪፖርት ማድረግ የሚጠበቅባችሁ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።

+1
ማስታወቂያ በ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ሰርተፊኬት ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስክ ምርጫ ማጠናቀቂያ ቀን እስከ መስከረም 5 ቀን የተራዘመ መሆኑን እንገልጻለን።   ስለሆነም በተለያዩ ምክንያቶች እስካሁን ምርጫችሁን ያላስገባችሁ ተማሪዎች በ https://student.ethernet.edu.et  ድህረ ገጽ በመግባት የራሳችሁን ፋይዳ (የመለያ ቁጥር) በመጠቀም ምርጫችሁን እንድታጠናቅቁ እናሳውቃለን።

photo content

ማስታወቂያ ለ2019 የትምህርት ዘመን በፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመማር ተመዝግባችሁ የመግቢያ ፈተና ለወሰዳችሁ የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ፤ በተመዘገባችሁበት ሊንክ በመግባት መለያ ቁጥራችሁንና የይለፍ ቃል በማስገባት ማለፍ ወይም አለማለፋችሁን ማረጋገጥ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ያለፋችሁ ተማሪዎች የተመደባችሁበትን ትምህርት ቤትም እዛው ላይ ማየት የምትችሉ ሲሆን ትምህርት የሚጀመረው በሁሉም የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች መስከረም 5/2019 መሆኑ ለማሳወቅ እንወዳለን። ማሳሰቢያ ፦ ተማሪዎች የተመረጡት ባመጡት ውጤት መሰረት በጥንቃቄ የተሰራ በመሆኑ ከውጤት እንዲሁም ከተማደባችሁበት ትምህርት ቤት ጋር በተያያዘ ምንም ዓይነት ቅሬታ የማንቀበል መሆኑን እንገልጻለን።

የትምህርት ሚኒስቴር ሠራተኞችና አመራሮች «በህብር እንደጋገፍ፤ አዲስ ዓመትን በአዲስ ተስፋ እንቀበል» በሚል መሪ ቃል የህብር ቀንን አከበሩ። -------------------- // -----------
+8
የትምህርት ሚኒስቴር ሠራተኞችና አመራሮች «በህብር እንደጋገፍ፤ አዲስ ዓመትን በአዲስ ተስፋ እንቀበል» በሚል መሪ ቃል የህብር ቀንን አከበሩ። -------------------- // -------------------- (ጳግሜ 4/2018) የትምህርት ሚኒስቴር ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሠራተኞቹ ለአዲስ አመት በዓል መዋያ የሚሆን ድጋፍ አደረገ። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ ባስተላለፉት መልዕክት በበዓላት መደጋገፍና መተጋገዝ የቆየና ውብ የሆነ የኢትዮጵያውያን እሴት መሆኑን አብራርተዋል። አክለውም የሀገሪቱ ኢኮኖሚ በተጠበቀው ልክ አድጎና ተጠናክሮ እያንዳንዱ ዜጋ ሰርቶ ራሱንና ቤተሰቡን በሙሉ አቅም መደጎም የሚችልበት ደረጃ እስኪደርስ ድረስ እንዲህ ያሉ የመደጋገፍና የመረዳዳት ባህሎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ እንዲሁም የህብር ቀን አከባበር ቴክኒክ ኮሚቴ አባል የሆኑት ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ እንደገለጹት በትምህርት ዘርፉ ስር ባሉ ልዩ ልዩ የትምህርት ተቋማት የበጎ ፈቃድና የተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ አብራርተዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/14sth2kRq9P/

photo content

ማስታወቂያ ለ2019 ዓ/ም አዲስ ለተቋቋሙና ለነባር የፌደራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመምህርነት ሙያ ተቀጥረው ለማገልገል የፅሁፍ ፈተና በመውሰድ የማለፊያ ውጤት አምጥታችሁ ለቃለ መጠ
+3
ማስታወቂያ ለ2019 ዓ/ም አዲስ ለተቋቋሙና ለነባር የፌደራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመምህርነት ሙያ ተቀጥረው ለማገልገል የፅሁፍ ፈተና በመውሰድ የማለፊያ ውጤት አምጥታችሁ ለቃለ መጠይቅ ለተመረጣችሁ መምህራን በሙሉ፣ ቃለ መጠይቁ የሚካሄደው ጳጉሜ 3/2018 ዓ. ም ማክሰኞ በኦንላይን የሚካሄደ ሲሆን በምዝገባ ወቅት በሰጣችሁት ስልክ ቁጥር ዋትስአፕ ላይ በመግባት እንዴት ኢንተር ቪውን በሞባይልና በላፕቶብ ማድረግ እንደምትችሉ የተጫነውን መመሪያ መሰረት በማድረግ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን!

photo content
+9

ማስታወቂያ ለ2019 ዓ/ም አዲስ ለተቋቋሙና ለነባር የፌደራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመምህርነት ሙያ ተቀጥረው ለማገልገል የፅሁፍ ፈተና በመውሰድ የማለፊያ ውጤት አምጥታችሁ ለቃለ መጠይቅ ለተመረጣችሁ መምህራን በሙሉ፣ ቃለ መጠይቁ የሚካሄደው ጳጉሜ 3/2018 ዓ. ም ማክሰኞ በኦንላይን የሚካሄደ ሲሆን በምዝገባ ወቅት በሰጣችሁት ስልክ ቁጥር ዋትስአፕ ላይ በመግባት እንዴት ኢንተር ቪውን በሞባይልና በላፕቶብ ማድረግ እንደምትችሉ የተጫነውን መመሪያ መሰረት በማድረግ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን!

ማስታወቂያ በ2019 የትምህርት ዘመን በፌዴራል አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለመማር ተመዝግባችሁ በተለያየ ምክንያት የመግቢያ ፈተና ላልተፈተናችሁ ተማሪዎች በሙሉ፣   የትምህርት ሚኒስቴር በ2019 የትምህርት ዘመን በፌዴራል 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ተመዝግበው ለፈተና የተመረጡ ተማሪዎችን መፈተኑ ይታወሳል። ይሁን እንጂ ለፈተና ተመርጣችሁ በተለያየ ምክንያት ፈተና ያልተፈተናችሁ ተማሪዎች ጷጉሜ 02/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በአቅራቢያችሁ በሚገኝ የፈተና መስጫ ማዕከል በመገኘት መፈተን የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። ማሳሰቢያ፤ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ፈተና የወሰዳችሁ ተማሪዎች በድጋሜ መፈተን የማይቻል መሆን እንገልጻለን።