fa
Feedback
Ministry of Education Ethiopia

Ministry of Education Ethiopia

رفتن به کانال در Telegram

This is Ministry of Education's Official Telegram Channel. For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Ministry of Education Ethiopia

کانال Ministry of Education Ethiopia (@ethio_moe) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 141 852 مشترک است و جایگاه 813 را در دسته آموزش و رتبه 179 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 141 852 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 05 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 371 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 71 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 26.05% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.74% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 36 902 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 10 957 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
This is Ministry of Education's Official Telegram Channel. For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 07 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کرده‌اند.

141 852
مشترکین
+7124 ساعت
+1187 روز
+37130 روز
آرشیو پست ها
በመጪው የትምህርት ዘመን 1452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ሥራ ለማስጀመር የግንባታ ማስጀመር ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ነው። (ግንቦት 28/2018 ዓ.ም )በትምህርት ሚኒስቴር እና
በመጪው የትምህርት ዘመን 1452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ሥራ ለማስጀመር የግንባታ ማስጀመር ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ነው። (ግንቦት 28/2018 ዓ.ም )በትምህርት ሚኒስቴር እና በክልል ትምህርት ቢሮዎች ትብብር እየተገነቡ የሚገኙ 1,452 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን እስከ መጪው ነሐሴ መጨረሻ ድረስ በማጠናቀቅ በአዲሱ የትምህርት ዘመን ለአገልግሎት ለማብቃት የግንባታ ማስጀመር ሥራዎች በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆናቸውን የትምህርት ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ከተማ መስቀላ ገልጸዋል። ዶ/ር ከተማ እንዳስታወቁት፣ ከአጠቃላይ 1,452 ትምህርት ቤቶች መካከል 726 በትምህርት ሚኒስቴር እና 726 በክልል ትምህርት ቢሮዎች አማካኝነት ይገነባሉ ብለዋል። የግንባታ ሂደቱንም ለማፋጠን እስካሁን በትምህርት ሚኒስቴር የሚገነቡ 341 ትምህርት ቤቶች እና በክልሎች የሚገነቡ 64 ትምህርት ቤቶች የኮንትራት ስምምነት ከተቋራጮች ጋር ተፈርሞ ወደ ሥራ የተገባ ሲሆን፣ 25 ትምህርት ቤቶች ደግሞ የግንባታ ሥራቸውን በይፋ መጀመራቸውን አብራርተዋል። እነዚህ ትምህርት ቤቶች በመጪው የትምህርት ዘመን ለአገልግሎት ሲበቁ ከ87,000 በላይ ሕፃናትን ተቀብለው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽነትን በ15 በመቶ እንደሚያሳድጉ ተገልጿል። ሥራ አስኪያጁ አክለውም በተለያዩ ምክንያቶች የግንባታ ሂደታቸው የዘገየባቸው ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ቀሪውን ጊዜ በተጠናከረ ቁርጠኝነት በመጠቀም ትምህርት ቤቶቹ በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ አስፈላጊውን ትኩረትና ክትትል እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡- በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/ በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe በትዊተር - http://twi
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡- በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/ በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe ዩቱዩብ- https://www.youtube.com/@ministry-of-education-ethiopia በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia በዌብሳይት - www.moe.gov.et

ትምህርት ሚኒስቴር ሙሉ በሙሉ በኦፍላይን የሚሰራና ራሱን ችሎ ውሳኔዎችን ማመንጨት የሚችል “ኤጀንቲክ መምህር ረዳት” (Agentic AI Teacher Assistant) የሰው ሰራሽ አስተውሎት መተግበሪ
+1
ትምህርት ሚኒስቴር ሙሉ በሙሉ በኦፍላይን የሚሰራና ራሱን ችሎ ውሳኔዎችን ማመንጨት የሚችል “ኤጀንቲክ መምህር ረዳት” (Agentic AI Teacher Assistant) የሰው ሰራሽ አስተውሎት መተግበሪያ አበልጽጎ በሙከራ ደረጃ ስራ ላይ አዋለ። (ግንቦት 28/2018 ዓም) ትምህርት ሚኒስቴር የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን የዕለት ተዕለት የሥራ ጫና በእጅጉ የሚቀንስ፣ ሙሉ በሙሉ ያለ ኢንተርኔት (Fully Offline) የሚሰራ እና ራሱን ችሎ ተግባራትን የሚያከናውን ኤጀንቲክ የሰው ሰራሽ አስተውሎት Agentic AI Teacher Assistant)  መተግበሪያ አበልጽጎ በሙከራ ደረጃ ስራ ላይ አውሏል። ‎ ‎የአይሲቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዘላለም አሰፋ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ይህ መተግበሪያ በማዕከላዊ ሰርቨር ወይም በክላውድ (Cloud) ቴክኖሎጂ ላይ የማይተማመን፣ ይልቁንም በአካባቢያዊ ኮምፒውተር (Local Machine) ላይ በቀላሉ ተጭኖ የሚሰራና በውስጥ አቅም የበለጸገ የቴክኖሎጂ ውጤት  መሆኑን ተናግረዋል። ሙሉ ዜናውን ለማግኘት https://web.facebook.com/share/p/1L47ihE7jo/

በኢትዮጵያና በቤልጂየም መካከል ያለው የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተደረገ። -------------------------- // -----------------
+2
በኢትዮጵያና በቤልጂየም መካከል ያለው የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተደረገ። -------------------------- // ----------------------- ‎ ‎(ግንቦት 23/2018 ዓ.ም) የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፉ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በኢትዮጵያ የቤልጅየምን አምባሳደር የሆኑትን ዶ/ር አኔሊስ ቬርስቲቼልን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ‎ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ጊዜ በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ እየተተገበሩ ስላሉ ዋና ዋና የሪፎርም ተግባራት ለክብርት አምባሳደሯ አብራርተዋል። ‎ ‎በሁለቱ አገራት መካከል በትምህርት መስክ በሰው ኃይል ልማት ፣ በጥናትና ምርምር ፣በልምምድ ልውውጥና በሌሎችም ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ የትብብር ግንኙነቶች መኖሩን አንስተዋል። ‎ ‎የትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ ራስገዝነትን ጨምሮ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጥራት፣ ብቃትና ተወዳዳሪነት ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ጠቅሰዋል። ‎ ‎በኢትዮጵያና ጅቡቲ የቤልጂየም አምባሳደርና የአፍሪካ ሕብረት የኢጋድና የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቋሚ ተወካይ ዶክተር አኔሊስ ቨርስቲቼል በበኩላቸው በኢትዮጵያና በቤልጂየም መንግስታት መካከል 120 ዓመታትን ያስቆጠረ ወዳጅነትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መኖሩን ተናግረዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://www.facebook.com/share/p/1BGKjx7TpH/

photo content

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች ከመንግስት የሚሰጥ የበጀት ድጋፍ አፈጻጸም ረቂቅ ደንብን አጸደቀ። (ግንቦት 18/2018 ዓ.ም) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 55ኛ
+1
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች ከመንግስት የሚሰጥ የበጀት ድጋፍ አፈጻጸም ረቂቅ ደንብን አጸደቀ። (ግንቦት 18/2018 ዓ.ም) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 55ኛ መደበኛ ስብሰባ፣ ለራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች ከመንግስት የሚሰጥ የበጀት ድጋፍ አፈጻጸምን ለመደንገግ በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በስፋት ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። በዚህም ምክር ቤቱ በረቂቅ ደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ፣ አስፈላጊ ግብአቶችን በማከል ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን በሙሉ ድምፅ አጽድቆታል። ደንቡ ለራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጠውን የመንግስት የበጀት ድጋፍ በታወቀ የጥቅል በጀት ስርዓት ላይ በመመስረት፣ የፋይናንስ ተጠያቂነትን፣ ፍትሃዊነትን እና ውጤታማነትን ለማረጋገጥ ያለመ ሲሆን፣ ዩኒቨርሲቲዎች የራሳቸውን ወጪ በራሳቸው የመሸፈን አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እንዲያሳድጉ ያግዛል። በተጨማሪም፣ በተቋማቱ መካከል ተመጣጣኝ የመማርና ማስተማር ጥራት፣ የአገልግሎት ፍትሃዊነት እና ኃላፊነት የተሞላበት አሰራር እንዲጠናከር ያስችላል። ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡- በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/ በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe ዩቱዩብ- https://www.youtube.com/@ministry-of-education-ethiopia በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ See less

photo content

photo content

photo content

በትምህርት ሚኒስቴር፣ በውጭ አገራት የጋራ ሀብት ልማት ቢሮ (FCDO) እና በብሪቲሽ ካውንስል መካከል የ5 ሚሊዮን ፓውንድ ስምምነት ተፈረመ፤ ------------------------------- //
+2
በትምህርት ሚኒስቴር፣ በውጭ አገራት የጋራ ሀብት ልማት ቢሮ (FCDO) እና በብሪቲሽ ካውንስል መካከል የ5 ሚሊዮን ፓውንድ ስምምነት ተፈረመ፤ ------------------------------- // ---------------------------- (ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) በትምህርት ሚኒስቴር፣ በዩናይትድ ኪንግደም የውጭ አገራት የጋራ ሀብት ልማት ቢሮ (FCDO) እና በብሪቲሽ ካውንስል መካከል በኢትዮጵያ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርትን ለማሻሻል የሚያስችል የሶስትዮሽ ስምምነት ተፈራርመዋል። በለንደን ከተማ እየተካሄደ ከሚገኘው የአለም የትምህርት ፎረም 2026 ጎን ለጎን የትምህርት ሚኒስቴር፣ በውጭ አገራት የጋራ ሀብት ልማት ቢሮ (FCDO) እና በብሪቲሽ ካውንስል መካከል የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርትን ለማጠናከርና ለማሻሻል የሚያስችል የአምስት ሚሊየን ፓውንድ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱ በኢትዮጵያ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት ጥራትን ለማሻሻል፣ የመምህራን አቅምን ለማጎልበት እና የተማሪዎችን የቋንቋ ክህሎት ተገልጿል። ይህ ስምምነት የአምስት ሚሊየን ፓውንድ ፕሮጀክት ሲሆን በኢትዮጵያ የእንግሊዝኛ ቋንቋን በማሻሻል ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋልም ተብሏል። በተጨማሪም ስምምነቱ በትምህርት ዘርፉ ያለውን ዓለም አቀፍ ትብብር የሚያጠናክር ሲሆን፣ ተማሪዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጋቸውን የቋንቋ ክህሎት እንዲያዳብሩ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

በአጣዬ ከተማ በትምህርት ሚኒስቴር ድጋፍ የተገነባ የአጣዬ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ማስፋፊያ ፕሮጀክት ተመረቀ፤ ------------------------ // ----------------------
+1
በአጣዬ ከተማ በትምህርት ሚኒስቴር ድጋፍ የተገነባ የአጣዬ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ማስፋፊያ ፕሮጀክት ተመረቀ፤ ------------------------ // ---------------------- (ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) በትምህርት ሚኒስቴር ድጋፍ በአጣዬ ከተማ የተገነባው የአጣዬ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመማሪያ ክፍል ማስፋፊያ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ትምህርት ሚኒስቴር ከ33 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ያስገነባው ይህ ፕሮጀክት ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን እና ዘመናዊ መፀዳጃ ቤቶችን ያካተተ ሲሆን የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች፣ የአካባቢው አስተዳደር፣ የትምህርት ዘርፍ ኃላፊዎች እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በይፋ ተመርቋል። የግንባታ ፕሮጀክቱ 10 ዘመናዊ የመማሪያ ክፍሎችን ያካተተ ሲሆን፣ ለወንድና ለሴት ተማሪዎች የተለያዩ መፀዳጃ ክፍሎችን ይዟል። ፕሮጀክቱ በአካባቢው የትምህርት ተደራሽነትን እና ምቹ የመማር ማስተማር ሂደትን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረውም ተገልጿል። በተጨማሪም በ“ትምህርት ለትውልድ” የትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ የትምህርት ማህበረሰቡን፣ የቀድሞ ተማሪዎችን፣ ባለሃብቶችን መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በማስተባበር በመላ ሀገሪቱ በሺዎች የሚቆጠሩ የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ፣ የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገና እና የትምህርት ተቋማት መሰረተ ልማት ማሻሻያ ሥራዎች በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ይታወቃል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://www.facebook.com/share/p/1DFY3PiS8w/

ኢትዮጵያ በለንደን በተካሄደው ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎረም 2026 በትምህርቱ ዘርፍ ያላትን ተሞክሮ አካፈለች፤ ----------------------- // ---------------------- ኢትዮጵ
+2
ኢትዮጵያ በለንደን በተካሄደው ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎረም 2026 በትምህርቱ ዘርፍ ያላትን ተሞክሮ አካፈለች፤ ----------------------- // ---------------------- ኢትዮጵያ በለንደን ከተማ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎረም 2026 ላይ ፍትሃዊ፣ ሁሉን አቀፍ እና ጥራት ያለው የትምህርት ሥርዓት በመገንባት ረገድ ያላትን ልምድ አቅርባለች። በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በፎረሙ ላይ ኢትዮጵያ በትምህርት ተደራሽነት፣ አካታችነት እና የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ዙሪያ ያከናወነቻቸውን ተግባራት አብራርተዋል። በዚህም፦ ✅ በገጠርና አገልግሎት በማይደርስባቸው አካባቢዎች ትምህርት ቤቶችን በመገንባት የትምህርት ተደራሽነትን ማስፋፋት፣ ✅ የቅድመ ልጅነት እድገት (ECD) እና የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ለማጠናከር የተወሰዱ እርምጃዎች፣ ✅ የአካል ጉዳተኞችንና የልዩ ትምህርት ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች የሚደግፉ አካታች ፖሊሲዎችን መተግበር፣ ✅ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት የአፍ መፍቻ ቋንቋ ትምህርትን በማስፋፋት የተማሪዎችን ተሳትፎና መሰረታዊ ትምህርት ማሻሻል፣ ✅ የሴቶችን የትምህርት ተሳትፎ እና ቆይታ ለማሳደግ የተሰሩ ሥራዎች፣ ✅ ለአርብቶ አደርና ለመድረስ አስቸጋሪ ማህበረሰቦች አማራጭ የትምህርት ፕሮግራሞችን መተግበር፣ ✅ የትምህርት ጥራትን፣ ፍትሃዊነትንና አካታችነትን ለማጠናከር የመምህራን ልማትን ማበረታታት የሚሉ ቁልፍ ተሞክሮዎች አቅርባዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://www.facebook.com/share/p/1HGemmb6B2/

ኢትዮጵያ በለንደን በተካሄደው ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎረም 2026 በትምህርቱ ዘርፍ ያላትን ተሞክሮ አካፈለች፤ ----------------------- // ---------------------- ኢትዮጵያ በለንደን ከተማ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎረም 2026 ላይ ፍትሃዊ፣ ሁሉን አቀፍ እና ጥራት ያለው የትምህርት ሥርዓት በመገንባት ረገድ ያላትን ልምድ አቅርባለች። በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በፎረሙ ላይ ኢትዮጵያ በትምህርት ተደራሽነት፣ አካታችነት እና የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ዙሪያ ያከናወነቻቸውን ተግባራት አብራርተዋል። በዚህም፦ ✅ በገጠርና አገልግሎት በማይደርስባቸው አካባቢዎች ትምህርት ቤቶችን በመገንባት የትምህርት ተደራሽነትን ማስፋፋት፣ ✅ የቅድመ ልጅነት እድገት (ECD) እና የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ለማጠናከር የተወሰዱ እርምጃዎች፣ ✅ የአካል ጉዳተኞችንና የልዩ ትምህርት ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች የሚደግፉ አካታች ፖሊሲዎችን መተግበር፣ ✅ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት የአፍ መፍቻ ቋንቋ ትምህርትን በማስፋፋት የተማሪዎችን ተሳትፎና መሰረታዊ ትምህርት ማሻሻል፣ ✅ የሴቶችን የትምህርት ተሳትፎ እና ቆይታ ለማሳደግ የተሰሩ ሥራዎች፣ ✅ ለአርብቶ አደርና ለመድረስ አስቸጋሪ ማህበረሰቦች አማራጭ የትምህርት ፕሮግራሞችን መተግበር፣ ✅ የትምህርት ጥራትን፣ ፍትሃዊነትንና አካታችነትን ለማጠናከር የመምህራን ልማትን ማበረታታት የሚሉ ቁልፍ ተሞክሮዎች አቅርባዋል። በመድረኩ ላይ ኢትዮጵያ ለሁሉም ዜጎች ፍትሃዊ፣ ሁሉን አቀፍ እና ጥራት ያለው ትምህርት ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት እንደገና አረጋግጣለች። በተጨማሪም ክቡር ሚኒስትሩ ጎን ለጎን በተካሄደው የአፍሪካ ትምህርት ሚኒስትሮች መድረክ ላይ “በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት ማሻሻል” ንቅናቄ በህብረተሰብ ተሳትፎ የተከናወኑ ሰፊ የትምህርት ልማት ተግባራትን በማቅረብ የኢትዮጵያን ተሞክሮ አካፍለዋል። #EducationForum2026 #Ethiopia #Education #InclusiveEducation #London Forum #ትምህርት #EthiopiaEducation

photo content

በፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የሚመሩት የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በለንደኑ ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎረም 2026 በመሳተፍ ላይ ነው፤ --------------------------- // --------------
+2
በፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የሚመሩት የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በለንደኑ ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎረም 2026 በመሳተፍ ላይ ነው፤ --------------------------- // --------------------------- (ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) በትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተመራው የኢትዮጵያ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በለንደን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም የትምህርት ፎረም (World Education Forum 2026) ላይ በመሳተፍ ላይ ይገኛል። የዘንድሮው ፎረም "ለጋራ የወደፊት ጊዜ ትምህርት መስጠት፡ ሰላም፣ ፕላኔት፣ ዓላማ እና መንገዶች በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን ይህ መድረክ በዓለም አቀፍ ደረጃ በትልቁ የሚጠቀስ የትምህርት እና የክህሎት ሚኒስትሮች ስብሰባ ነው። በዚህ ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎረም ላይ ከመላው ዓለም የመጡ ሚኒስትሮችን፣ ፖሊሲ አውጪዎችን፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችን፣ ዩኒቨርሲቲዎችን፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን እና የትምህርት ቴክኖሎጂ መሪዎችን በአጠቃላይ ከ125 አገሮች የመጡ ከ1500 በላይ የሚኒስትሮች የልኡካን ቡድን ተገኝተዋል። ይህ ታላቅ ፎረም ሚኒስትሮች እና የትምህርት መሪዎች የፖሊሲ ልምዶችን እንዲለዋወጡ፣ አዳዲስ ስልታዊ አጋርነቶችን እንዲፈጥሩ፣ በትምህርት ፋይናንስ እና ማሻሻያዎች ላይ እንዲወያዩ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ትምህርትን ቀጣይ አቅጣጫ ለመቅረጽ ከፍተኛ ዕድል የሚፈጥር መድረክ መሆኑም ተመላክቷል። ልዑካን ቡድኑ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የትምህርት ሪፎርም እና ተሞክሮዎች ያካፈለ ሲሆን፣ በቀጣይ የሀገሪቱን የትምህርት ጥራት ለማሻሻል በሚረዱ ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ውይይቶችን አድርጓል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘይ ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://www.facebook.com/share/p/1Bcenwfo5f/

photo content

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠት 667 የፈተና ማዕከላት ተዘጋጁ። ------------------------ // ----------------------------- (ግንቦት 11/2018 ዓ.ም)
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠት 667 የፈተና ማዕከላት ተዘጋጁ። ------------------------ // ----------------------------- (ግንቦት 11/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና በ667 የፈተና ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነመሆኑን ገልጿል ። የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) እንደገለጹት፥ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናን በ97 ዩኒቨርሲቲዎች እና በ570 የክልል ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል። ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ፈተና መደበኛ ተማሪዎችን ጨምሮ በሁሉም ፕሮግራሞች በተፈጥሮ ሳይንስ 306 ሺህ 964 እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ 257 ሺህ 255 በድምሩ 564 ሺህ 219 ተማሪዎች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ ፈተናውን በሙሉ አቅም በበይነ መረብ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በተለያዩ ምክንያቶች ቁጥራቸው አነስተኛ የሆኑ በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎች እንደሚኖሩም ጠቁመዋል። በየክልሎች እና የፈተና ማዕከላት ያለው አቅም የተለያየ ቢሆንም በርካታ ኮምፒዩተሮች ለፈተና ዝግጁ እየተደረጉ እንደሚገኙ አመልክተዋል። ከባለፈው አርብ ጀምሮ ለተፈታኞች የበይነ መረብ የሙከራ ፈተና መሰጠት መጀመሩን አንስተዋል። ፈተናው በ6 ዙር እንደሚሰጥና በማህበራዊ ሳይንስ በሶስት ዙር በተመሳሳይ በተፈጥሮ ሳይንስ ደግሞ በሶስት ዙር በመሆኑ አንድ ኮምፒዩተር ስድስት ተማሪን ያስተናግዳል ብለዋል። ተማሪዎች የፈተና ስርዓቱን እንዲለማመዱና ትምህርት ቤቶች እና ወላጆች ለተፈታኝ ተማሪዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉም አስገንዝበዋል።

photo content

ምንም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሌላቸው ወረዳዎችን ተደራሽ ማድረግ አስመለክቶ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የሰጡት ማብራሪያ https://youtu.be/0kf4c2D7-YA YouTube

photo content