fa
Feedback
Ministry of Education Ethiopia

Ministry of Education Ethiopia

رفتن به کانال در Telegram

This is Ministry of Education's Official Telegram Channel. For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Ministry of Education Ethiopia

کانال Ministry of Education Ethiopia (@ethio_moe) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 165 246 مشترک است و جایگاه 644 را در دسته آموزش و رتبه 148 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 165 246 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 15 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 10 980 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 354 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 27.48% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 12.78% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 45 405 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 21 118 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
This is Ministry of Education's Official Telegram Channel. For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 16 سپتامبر, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کرده‌اند.

165 246
مشترکین
+35424 ساعت
+2 1107 روز
+10 98030 روز
آرشیو پست ها
የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በሁሉም መስክ የወደፊቱ አገር መሪዎች የሚፈጠሩባቸው ተቋማት እንዲሆኑ እየተሰራ እንደሚገኝ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ ። -----------------------
+5
የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በሁሉም መስክ የወደፊቱ አገር መሪዎች የሚፈጠሩባቸው ተቋማት እንዲሆኑ እየተሰራ እንደሚገኝ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ ። ------------------------ // ------------------------- ‎ ‎(መስከረም 05/2019 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አዲስ ከተመደቡ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች መምህራን ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት ‎ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በሁሉም በኩል የወደፊቱ የአገር መሪ የሚሆኑ ዜጎች የሚፈልቁባቸው ተቋማት ይሆናሉ ብለዋል። ‎ ‎ትምህርት ቤቶቹ የነገዋን ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ፣ በሳይንስ፣ በፖለቲካ ፣በፍልስፍና በሌሎችም የሚገነቡ አገር ወዳድ ዜጎች መፍለቂያዎች እንደሚሆኑ ያላቸውን እምነት ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ‎ ‎አያይዘውም ለሁሉም እኩል የሚያስቡና ሁሉንም እኩል መምራትና ማገልገል የሚችሉና አገርን ከቅርቃርና ከችግር ማውጣት የሚችሉ ዜጎች የሚፈጠሩባቸው ተቋማት እንደሚሆኑም ጠቅሰዋል። ‎ ‎ትምህርት ቤቶቹ ከሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች የተውጣጡ ዜጎች የሚማሩባቸውና ከሁሉም ቦታ የተውጣጡ መምህራንና በችሎታ ተመርጠው የሚያስተምሩባቸው ተቋማት መሆናቸውንም ጠቁመዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/1Efqvo52qb/

photo content

2018 ዓ.ም. በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች በሌሎች የመንግስት ኒቨርስቲዎች እንዲመደቡ መወሰኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ፤ ሚኒስትሩ በትግ
+5
2018 ዓ.ም. በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች በሌሎች የመንግስት ኒቨርስቲዎች እንዲመደቡ መወሰኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ፤ ሚኒስትሩ በትግራይ ክልል ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ይማሩ የነበሩ ተማሪዎችን አነጋግረዋል፡፡ ………………………………….. // ……………………………. ‎(መስከረም 04/2018 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከተማሪዎቹ ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት በ2018 ዓ.ም. በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች ደህንነታቸው ወደሚጠበቁባቸው ሌሎች ዩኒቨርስቲዎች እንዲመደቡ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑን ተናግረዋል፡፡ ‎ ‎ክቡር ሚኒስትሩ እንደገለጹት ጦርነትና ግጭት ሸሽተው ከትግራይ የወጡ ተማሪዎች ብቻ ሳይሆን ትግራይ ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች ትምህርት ሚኒስቴር መምጣት ሳይጠበቅባቸው ከቻሉ ከትግራይ ወጥተው አሊያም ባሉበት በኦንላይ ለመማር የሚችሉበት ቦታ ላይ እንደሚመዘገቡና ትምህርትታቸውን መማር እንደሚችሉ አስረድተዋል፡፡ ‎ ‎ተማሪዎቹን ምዝገባ ለማካሄድ ትምህርት ሚኒስቴር በበይነ መረብ የምዝገባ ስርዓት ማዘጋጀቱን የገለጹት ሚኒስትሩ ሁሉም በትግራይ ክልል ባሉ አራቱ ዩኒቨርስቲዎች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች ከዛሬ ማታ ጀምሮ ይፋ በሚደረገው የኦንላይን መተግበሪያ ፕላት ፎርም በመሙላት እንዲመዘገቡ አሳውቀዋል፡፡ ሙሉ መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፤ https://web.facebook.com/share/p/1BgiGPjwXJ/

📢 ማስታወቂያ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ነገ መስከረም 05 ቀን 2019 ዓ.ም ይጀምራል! ውድ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆች/አሳዳጊዎች እና መላው የትምህርት ማኅበረሰብ፤ እንኳን ለ2019 አ
📢 ማስታወቂያ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ነገ መስከረም 05 ቀን 2019 ዓ.ም ይጀምራል! ውድ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆች/አሳዳጊዎች እና መላው የትምህርት ማኅበረሰብ፤ እንኳን ለ2019 አዲሱ ዓመት እና የትምህርት ዘመን አደረሳችሁ! በትምህርት ካሌንደሩ መሠረት፣ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በመላ ሀገሪቱ ነገ፣ መስከረም 05 ቀን 2019 ዓ.ም፣ በይፋ ይጀምራል። በዚህም ትምህርት ቤቶች ለአዲሱ የትምህርት ዘመን የሚያስፈልጉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በማጠናቀቅ እናንተን ለመቀበልና የመማር–ማስተማር ሂደቱን በተቀመጠው የትምህርት ካሌንደር መሠረት ለመጀመር እየተጠባበቁ ይገኛል። ስለሆነም፣ ወላጆች/አሳዳጊዎች እና ሁላችሁም የሚመለከታችሁ አካላት ለትምህርት የደረሱ ልጆችን  አስፈላጊውን የትምህርት ግብዓት በማሟላት ወደ ትምህርት ቤት እንዲሄዱ በማድረግ፣ የድርሻችሁን እንድትወጡ በዚህ አጋጣሚ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን። 🌟 መልካም የትምህርት ዘመን! ትምህርት ሚኒስቴር

photo content

photo content

ማስታወቂያ ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ ትምህርት በሚጀምርባቸውና እና ለነባር የፌደራል አዳሪ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራንን ለመልመል ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት የጽሁፍ እና የቃል ፈተ
+5
ማስታወቂያ ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ ትምህርት በሚጀምርባቸውና እና ለነባር የፌደራል አዳሪ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራንን ለመልመል ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት የጽሁፍ እና የቃል ፈተና ወስዳችሁ   ያለፋችሁ መምህራን ዝርዝራችሁን መመልከት የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን። ያለፋችሁ መምህራን መስከረም 5/2019 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ የትምህርት ቤት ምደባ እና ስልጠና የሚሰጣችሁ በመሆኑ ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ በተጠቀሰው ቀን በትምህርት ሚኒስቴር ዋናው ግቢ የመሰብሰቢያ አዳራሽ እንድትገኙ እናሳውቃለን።   ማሳሰቢያ፦ በዚህ ስልጠና እና ኦረንቴሽን የማይገኝ ማንኛውም መምህር ከምደባው የሚሰረዝ መሆኑን እንገልጻለን፡፡   በተጨማሪም መስከረም 7 እና 8/2019 ዓ.ም በየተመደባችሁበት ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ዩኒቨርሲቲዎች)አስፈላጊውን መረጃ በመያዝ ሪፖርት ማድረግ የሚጠበቅባችሁ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።

+1
ማስታወቂያ በ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ሰርተፊኬት ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስክ ምርጫ ማጠናቀቂያ ቀን እስከ መስከረም 5 ቀን የተራዘመ መሆኑን እንገልጻለን።   ስለሆነም በተለያዩ ምክንያቶች እስካሁን ምርጫችሁን ያላስገባችሁ ተማሪዎች በ https://student.ethernet.edu.et  ድህረ ገጽ በመግባት የራሳችሁን ፋይዳ (የመለያ ቁጥር) በመጠቀም ምርጫችሁን እንድታጠናቅቁ እናሳውቃለን።

photo content

ማስታወቂያ ለ2019 የትምህርት ዘመን በፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመማር ተመዝግባችሁ የመግቢያ ፈተና ለወሰዳችሁ የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ፤ በተመዘገባችሁበት ሊንክ በመግባት መለያ ቁጥራችሁንና የይለፍ ቃል በማስገባት ማለፍ ወይም አለማለፋችሁን ማረጋገጥ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ያለፋችሁ ተማሪዎች የተመደባችሁበትን ትምህርት ቤትም እዛው ላይ ማየት የምትችሉ ሲሆን ትምህርት የሚጀመረው በሁሉም የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች መስከረም 5/2019 መሆኑ ለማሳወቅ እንወዳለን። ማሳሰቢያ ፦ ተማሪዎች የተመረጡት ባመጡት ውጤት መሰረት በጥንቃቄ የተሰራ በመሆኑ ከውጤት እንዲሁም ከተማደባችሁበት ትምህርት ቤት ጋር በተያያዘ ምንም ዓይነት ቅሬታ የማንቀበል መሆኑን እንገልጻለን።

የትምህርት ሚኒስቴር ሠራተኞችና አመራሮች «በህብር እንደጋገፍ፤ አዲስ ዓመትን በአዲስ ተስፋ እንቀበል» በሚል መሪ ቃል የህብር ቀንን አከበሩ። -------------------- // -----------
+8
የትምህርት ሚኒስቴር ሠራተኞችና አመራሮች «በህብር እንደጋገፍ፤ አዲስ ዓመትን በአዲስ ተስፋ እንቀበል» በሚል መሪ ቃል የህብር ቀንን አከበሩ። -------------------- // -------------------- (ጳግሜ 4/2018) የትምህርት ሚኒስቴር ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሠራተኞቹ ለአዲስ አመት በዓል መዋያ የሚሆን ድጋፍ አደረገ። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ ባስተላለፉት መልዕክት በበዓላት መደጋገፍና መተጋገዝ የቆየና ውብ የሆነ የኢትዮጵያውያን እሴት መሆኑን አብራርተዋል። አክለውም የሀገሪቱ ኢኮኖሚ በተጠበቀው ልክ አድጎና ተጠናክሮ እያንዳንዱ ዜጋ ሰርቶ ራሱንና ቤተሰቡን በሙሉ አቅም መደጎም የሚችልበት ደረጃ እስኪደርስ ድረስ እንዲህ ያሉ የመደጋገፍና የመረዳዳት ባህሎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ እንዲሁም የህብር ቀን አከባበር ቴክኒክ ኮሚቴ አባል የሆኑት ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ እንደገለጹት በትምህርት ዘርፉ ስር ባሉ ልዩ ልዩ የትምህርት ተቋማት የበጎ ፈቃድና የተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ አብራርተዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/14sth2kRq9P/

photo content

ማስታወቂያ ለ2019 ዓ/ም አዲስ ለተቋቋሙና ለነባር የፌደራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመምህርነት ሙያ ተቀጥረው ለማገልገል የፅሁፍ ፈተና በመውሰድ የማለፊያ ውጤት አምጥታችሁ ለቃለ መጠ
+3
ማስታወቂያ ለ2019 ዓ/ም አዲስ ለተቋቋሙና ለነባር የፌደራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመምህርነት ሙያ ተቀጥረው ለማገልገል የፅሁፍ ፈተና በመውሰድ የማለፊያ ውጤት አምጥታችሁ ለቃለ መጠይቅ ለተመረጣችሁ መምህራን በሙሉ፣ ቃለ መጠይቁ የሚካሄደው ጳጉሜ 3/2018 ዓ. ም ማክሰኞ በኦንላይን የሚካሄደ ሲሆን በምዝገባ ወቅት በሰጣችሁት ስልክ ቁጥር ዋትስአፕ ላይ በመግባት እንዴት ኢንተር ቪውን በሞባይልና በላፕቶብ ማድረግ እንደምትችሉ የተጫነውን መመሪያ መሰረት በማድረግ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን!

photo content
+9

ማስታወቂያ ለ2019 ዓ/ም አዲስ ለተቋቋሙና ለነባር የፌደራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመምህርነት ሙያ ተቀጥረው ለማገልገል የፅሁፍ ፈተና በመውሰድ የማለፊያ ውጤት አምጥታችሁ ለቃለ መጠይቅ ለተመረጣችሁ መምህራን በሙሉ፣ ቃለ መጠይቁ የሚካሄደው ጳጉሜ 3/2018 ዓ. ም ማክሰኞ በኦንላይን የሚካሄደ ሲሆን በምዝገባ ወቅት በሰጣችሁት ስልክ ቁጥር ዋትስአፕ ላይ በመግባት እንዴት ኢንተር ቪውን በሞባይልና በላፕቶብ ማድረግ እንደምትችሉ የተጫነውን መመሪያ መሰረት በማድረግ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን!

ማስታወቂያ በ2019 የትምህርት ዘመን በፌዴራል አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለመማር ተመዝግባችሁ በተለያየ ምክንያት የመግቢያ ፈተና ላልተፈተናችሁ ተማሪዎች በሙሉ፣   የትምህርት ሚኒስቴር በ2019 የትምህርት ዘመን በፌዴራል 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ተመዝግበው ለፈተና የተመረጡ ተማሪዎችን መፈተኑ ይታወሳል። ይሁን እንጂ ለፈተና ተመርጣችሁ በተለያየ ምክንያት ፈተና ያልተፈተናችሁ ተማሪዎች ጷጉሜ 02/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በአቅራቢያችሁ በሚገኝ የፈተና መስጫ ማዕከል በመገኘት መፈተን የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። ማሳሰቢያ፤ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ፈተና የወሰዳችሁ ተማሪዎች በድጋሜ መፈተን የማይቻል መሆን እንገልጻለን።

+1
ማስታወቂያ የዩኒቨርስቲ ምደባ በመጠባበቅ ላይ ላላችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤ የዩኒቨርሲቲ እና የባንድ ምርጫችሁን፣ እንዲሁም የልዩ ድጋፍ ማመልከቻ ለማቅረብ ከታች ያለውን ቪዲዮ መመሪያ በመከታተል መሙላት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን

+1
ማስታወቂያ የዩኒቨርስቲ ምደባ በመጠባበቅ ላይ ላላችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤ የዩኒቨርሲቲ እና የባንድ ምርጫችሁን፣ እንዲሁም የልዩ ድጋፍ ማመልከቻ ለማቅረብ ከታች ያለውን ቪዲዮ መመሪያ በመከታተል መሙላት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ዩኒቨርስቲዎች ሀገርን የሚያሻግሩ የእውቀት ማዕከላት ሊሆኑ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ገለጹ፤ ---------------------- // --------------------- (ነሐሴ 28/2018 ዓ.
+2
ዩኒቨርስቲዎች ሀገርን የሚያሻግሩ የእውቀት ማዕከላት ሊሆኑ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ገለጹ፤ ---------------------- // ---------------------   (ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም) ዩኒቨርስቲዎች ሀገርን የሚያሻግሩ የእውቀት ማዕከላት ሊሆኑ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከመንግስት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ጋር ባደረጉት የምክክር መድረክ አስገነዘቡ።   ፕሮፌሰር ብርሃኑ በንግግራቸው፤ ዩኒቨርስቲዎች የሙያና የስነ-ምግባር እሴቶች የሚገነቡባቸው  የአካዳሚክና የምርምር ተቋማት መሆናቸውን ገልጸው የህብረተሰቡ የሞራልና የእውቀት መሪዎች በመሆናቸው፣ የሙያ ስነ-ምግባርንና የሞራል እሴቶችን በመላበስ ማህበረሰቡን በእውቀትና በሙያ ሊደግፉ እንደሚገባ አሳስበዋል።   አክለውም፤ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ስብጥር ብዝሃነትን ባካተተ፣ መተዋወቅን፣ መከባበርን፣ መቻቻልንና ሀገራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ሊሆን እንደሚገባ ጠቁመዋል።   ከዚሁ ጋር ተያይዞ፣ በዩኒቨርስቲዎች ከተማሪዎች ምደባና ዝውውር ጋር ተያይዘው የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ከቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጀምሮ በትምህርት ሚኒስቴር በቴክኖሎጂ የታገዘ አዲስ የአሰራር ስርዓት እንደሚዘረጋ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ከበጀት አጠቃቀም ረገድም ተቋማቱ የተመደበላቸውን በጀት ለታቀደለት ዓላማ ብቻ በቁጠባና በተጠያቂነት መንፈስ ማዋል እንዳለባቸው አሳስበዋል። ሙሉ መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ፤ https://web.facebook.com/share/p/1EPYjkE9WK/

ማስታወቂያ የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና  ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፡-   Ø የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን ከነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (Link) በመጠቀም ምርጫችሁን ት/ቤት መሄድ ሳይጠበቅባችሁ ባላችሁበት ቦታ እራሳችሁ በመሙላት እንድታሳውቁ እንገልጻለን። Ø  ማስፈንጠሪያ (Link)  https://student.ethernet.edu.et/ ማሳሰቢያ፡- v የህክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከ6 ወር በታች ህፃን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል።   የትምህርት ሚኒስቴር