Dilla University Official
📈 Telegram kanali Dilla University Official analitikasi
Dilla University Official (@dprd9) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 17 577 obunachidan iborat bo'lib, Taʼlim toifasida 11 392-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 1 919-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 17 577 obunachiga ega bo‘ldi.
12 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 84 ga, so‘nggi 24 soatda esa 5 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 21.35% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.52% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 752 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 673 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 13 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“University of the Green Land”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 13 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Taʼlim toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 13 Iyul | +11 | |||
| 12 Iyul | +5 | |||
| 11 Iyul | +7 | |||
| 10 Iyul | +1 | |||
| 09 Iyul | +3 | |||
| 08 Iyul | +3 | |||
| 07 Iyul | 0 | |||
| 06 Iyul | +6 | |||
| 05 Iyul | 0 | |||
| 04 Iyul | +6 | |||
| 03 Iyul | +4 | |||
| 02 Iyul | +5 | |||
| 01 Iyul | +2 |
| 2 | የሀዘን መግለጫ
===***===
በዩኒቨርሲቲያችን ነባሩ ጊቢ ካምፓስ የጠቅላላ አገልግሎት ኃላፊ የነበሩት አቶ ግዛው ደቃሞ ወራሶ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት በዩኒቨርሲቲው ሰራተኛ ህልፈት የተሰማውን መሪር ሀዘን እየገለፀ፣ ለሟች ቤተሰቦች፣ ለስራ ባልደረቦቹ እና ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ መጽናናትን ይመኛል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#UniversityOfTheGreenland | 2 123 |
| 3 | 📢 ማስታወቂያ 🔔
===******===
የቦታ ለውጥ መደረጉን ስለማሳወቅ
በዲላ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና ማስተማሪያ ሆስፒታል አዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ በወጣው ማስታወቂያ ተወዳድራችሁ፣ ለፅሁፍ ፈተና የተመረጣችሁ ተወዳዳሪዎች፣ ከዚህ በፊት በንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለፈተና እንድትገኙ ማሳወቃችን የሚታወስ ነው።
ይሁን እንጂ በተለያዩ ምክንያቶች የቦታ ለውጥ ማድረጋችንን እያሳወቅን፣ በዳግማዊ ሚኒሊክ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሐምሌ 05/2018ዓ.ም ከጧቱ 2:30 ጀምሮ እንድትገኙ እናሳውቃለን።
መረጃውን ለጓደኞችዎ ያጋሩ!
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#UniversityOfTheGreenland | 2 676 |
| 4 | Matn yo'q... | 2 516 |
| 5 | ህልምን ለማሳካት - መራራ ሀዘንን የመቋቋም ብቃት
============*********===========
ዲ.ዩ: ሐምሌ 3/2018ዓ.ም(ህ.ዓ.ግ)
የ12 ዓመታት ልፋትና ህልምን ለማሳካት የወላጅ እናቱ ህልፈትን ተከትሎ የመጣበትን መራራ ሀዘን ተቋቁሞ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የተፈተነው ተፈታኝ ፈተናውን አጠናቋል።
ተማሪ ሚኤሳ ባሊ ይባላል። በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን፣ ቦሬ ወረዳ፣ የሀሮ ገርብቾ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪ ነው።
ትምህርቱን በትኩረት የሚከታተል፣ በየደረጃው ጥሩ ውጤት እያስመዘገበ የመጣ፣ በዘንድሮው ዓመት የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ሲሆን፣ ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ዩኒቨርሲቲ መግባት ህልሙ እንደሆነ ገልፆልናል።
ሚኤሳ፣ ፈተናውን በስኬት ለማጠናቀቅ የሚችለውን ሁሉ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ወደ ተመደበበት ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለመጓዝ አንድ ቀን ሲቀረው፣ በዕለተ ዋዜማው መጥፎ ክስተት ተፈጠረ። ወላጅ እናቱ ወ/ሮ ቀጫቱ ዋሬ ባደረባቸው ህመም ምክንያት አረፉ። በዚህ ምክንያት ሚኤሳም መራራ ሀዘን ውስጥ መግባቱንና ክፉኛ መጎዳቱን ይናገራል።
በደረሰበት መራራ ሀዘን ምክንያት ፈተና ወደሚወስድበት ለመሄድና ላለመሄድ ውሳኔ ላይ ለመድረስ መቸገሩን ይገልጻል። የመጣውን ክስተት አሜን ብሎ የተቀበለው ተማሪ ሚኤሳ፣ ወላጅ እናቱ ባረፈችበት ማግስት ሰኔ 28/2018ዓ.ም ወደ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ገባ። እራሱን በማጠንከር የ12 ዓመታት ልፋቱን እንዲሁም የወደፊት ህለሙን እውን ለማድረግ መራራ ሀዘኑን መቋቋም እንዳለበት ቤተሰብና ጓደኞቹ ምክር እንደለገሱለትም ገልፆልናል።
እዚህ ከባድ ውሳኔ ላይ መድረስ የግል ጥንካሬው ብቻ አለመሆኑን የሚገልፀው ተማሪ ሚኤሳ፣ በህይወት እያለች አደራ የሰጠችሁን የእናቱን ኑዛዜ ለመፈፀም የቻለውን ሁሉ ማድረጉን ተናግሯል።
ተማሪ ሚኤሳ ከሐምሌ 1-3/2018ዓ.ም የተሰጠውን ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና በተሳካ መልኩ አጠናቋል።
ተማሪ ሚኤሳ ሀዘኑን ተቋቁሞ ፈተናውን እንዲወስድ ላበራታቱት ለቤተሶቦቹ፣ ለጓደቹ፣ ለወረዳው ትምህርት ፅ/ቤት ተወካዮች እንዲሁም መልካም አቀባበል ላደረገለት ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ምስገናውን አቅርቧል።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሚኤሳ መልካም ውጤት አምጥቶ የህልሙን ይኖር ዘንድ መልካም ምኞቱን ይገልፃል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#UniversityOfTheGreenland | 2 356 |
| 6 | Matn yo'q... | 2 093 |
| 7 | 🔔 ማስታወቂያ 📢
====****====
ለዲላ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ማስተማሪያ ሆስፒታል በወጣው ማስታወቂያ ላይ ለተወዳደራችሁ አመልካቾች በሙሉ
ሚያዝያ 07/2018ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ በወጣው ማስታወቂያ መሠረት ተወዳድራችሁ ለፅሁፍ ፈተና የተመረጣችሁ አመልካቾች፣
📍ኦርጂናል የትምህርት ማስረጃ፣
📍የሙያ ፍቃድ፣ እና
📍ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ፣
እሁድ በቀን 05/11/2018ዓ.ም ንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከጧቱ 02:30 ላይ እንድትገኙ እናሳስባለን።
መረጃውን ለጓደኞችዎ ያጋሩ!
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#UniversityOfTheGreenland | 3 319 |
| 8 | "ተባብረን ከሰራን ዩኒቨርሲቲውን ዩኒቨርሲቲ ማድረግ የሚችል ስራ መስራት ይቻላል" - ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር)
============************=============
ዲዩ: ሐምሌ 02/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር)፣ ከዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን በምህንድስናና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ስር ባሉ ዎርክሾፖች ላይ ምልከታ አድርገዋል።
በኢንጅነሪንግ ኮሌጅ ውስጥ ያሉ ዎርክሾፖችን እንዲሁም በውስጡ እየተሰሩ ያሉ ተግባራትን በተመለከተ የዩኒቨርሲቲው የምህንድስናና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ዲን አቶ ፍቅሩ ታደሰ ለልዑካኑ ገለፃ አድርገዋል።
አቶ ፍቅሩ በገለጻቸው ላይ፣ ዎርክሾፖቹን በተሻለ ደረጃ ማደራጀት እና የቦታ ጥበቱን መፍታት ቢቻል አሁን ላይ ከታየው በላይ የመስራት አቅም ስለመኖሩ ጠቁመዋል። በዎርክሾፖቹ ውስጥ ያሉ አንዳንድ የግብአት እጥረቶችን ማሟላት እንደሚያስፈልግ አንስተው፣ መጠነኛ የእድሳት ስራ እንዲሰራላቸውም ጠይቀዋል።
አቶ ፍቅሩ አክለውም አስፈላጊው እገዛ ቢደረግ፣ ከዚህ የሚሰሩ ስራዎች በውጪውም ዘንድ ተፈላጊነት ስለሚኖራቸው፣ የተሻለ ገቢ ማመንጨት እንደሚቻል ጠቁመዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር)፣ በምልከታቸው ባዩት ነገር እጅጉን መደሰታቸውን ገልጸው፣ በተለይ በየዎርክሾፖቹ ውስጥ የሚገኙ ግብአቶች ከመማር ማስተማር ባለፈ ለምርምር ጭምር የሚያግዙ በመሆናቸው በተገቢው መንገድ መጠቀም እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።
"ተባብረን ከሰራን ዩኒቨርሲቲውን ዩኒቨርሲቲ ማድረግ የሚችል ስራ መስራት ይቻላል" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ዎርክሾፖቹን በሚገባ በማደራጀት ሀብቱን ጥቅም ላይ በማዋል ለተቋሙ አማራጭ የገቢ ምንጭ መፍጠር እንደሚያስፈልግ አፅንዖት ሰጥተዋል።
እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለፃ፣ በሚፈለገው ልክ ለስራው ቁርጠኛ የሆኑ መምህራን ባሉበት ተቋሙ ስራዎቹን የማይደግፍበት ምክንያት አይኖርም።
ኮሌጁ የአጭር ጊዜና የረጅም ጊዜ ጥናት እንድያጠና እና እቅዱን እንድያስገባ ያሳሰቡት ፕሬዝዳንቱ፣ የሀይል መቆራረጥ ችግር እንዳይኖር የተለየ የኤሌክትሪክ መስመር መዘርጋት እንደሚያስፈልግ እና ያሉ ማሽነሪዎች በሙሉ አቅማቸው እንዲሰሩ ማገዝ እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።
ፕሬዝዳንቱ እየተጠኑ ያሉ የአዋጭነት ጥናቶች ተጠናቀው ሲቀርቡ በየዎርክሾፖቹ የሚሰሩ ስራዎች ወደ ገበያ እንዲወጡ በዩኒቨርሲቲው ኢንተርፕራይዝ ስር ሆነው የተሻለ ገቢ እንድያስገቡ ለማስቻል በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በምልከታው ላይ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የኮሌጁ ሀላፊዎች እና መምህራን ተገኝተዋል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#UniversityOfTheGreenland | 2 943 |
| 9 | Matn yo'q... | 2 893 |
| 10 | የኤሌክትሪካል ስራዎች ማጠናቀቂያ ግብአቶች ሳይት መድረሳቸው ተገለፀ
==========****==========
ዲ.ዩ: ሰኔ 26 /2018 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
ለአዲሱ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል እና ማስተማሪያ ሆስፒታል ቀሪ የኤሌክትሪካል ስራዎች ማጠናቀቂያ ግብአቶች (ኤሌክትሪካል ፊቲንግ) ወደ ሳይት ገብተዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት፣ ለአዲሱ ሆስፒታል ማጠናቀቂያ የሚሆኑ የኤሌክትሪካል ግብአቶች በዛሬው እለት ተጠናቀው ወደ ሳይት መግባታቸው እንዳስደሰታቸው ገልጸው፣ ግብአቶቹ ሳይት ላይ ሳይቆዩ በፍጥነት ወደ ገጠማ ስራ መግባት አለባቸው።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ አሁን ላይ በአዲሱ ሆስፒታል እየተሰሩ ያሉ የፍኒሽንግ ስራዎች በአብዛኛው እየተጠናቀቁ መሆናቸውን በመግለጽ ቀሪ ውስን ስራዎችንም በአጭር ጊዜ ለማገባደድ ስራዎች ተጠናክረው እየተሰሩ መሆኑን አብራርተዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር በፍቃዱ መኩሪያ በበኩላቸው፣ በዛሬው እለት ወደ አዲሱ ሆስፒታሉ የገቡ እቃዎች ቀደም ሲል ቻይና ላይ ከአምራች ድርጅቱ ጋር ውል በተገባው መሰረት የሆስፒታሉን ሙሉ የኤሌክትሪክ ፊቲንግ ማጠናቀቅ የሚያስችሉ ከ5 ሺህ በላይ ግብአቶችን የያዙ ሁለት ተሳቢ ኮንቲነሮች እንደሆኑ ገልጸዋል። የገቡ ግብአቶች ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ ትልቅ አስተዋጽኦ ያላቸው መሆናቸውንም ተናግረዋል።
ኢንጅነር በፍቃዱ አክለውም፣ የሆስፒታሉን የኤሌክትሪክ መስመር የሚያዘረጉ ሲስተሞች እንዲሁም ቀሪ የፍኒሽንግ ግብአቶችን የያዙ ወደ 5 የሚደርሱ ኮንቲነሮች ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው ጉምሩክ ላይ የሚገኙ መሆናቸውን ገልፀዋል። ግብዓቶቹ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠቃለው ወደ ሳይት እንዲገቡ ጥረት እንደሚደረግ ተናግረዋል።
የፊሊንትስቶን ኢንጂነሪንግ የዲላ ማስተማሪያ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ዘገየ ቶሎሳ በአንጻሩ፣ በሳይት ላይ የደረሱ ግብዓቶችን በፍጥነት ወደ ስራ ለማስገባት እንደወትሮው ሁሉ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ቶሎሳ ዳዲ ከዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን የአዲሱ ሆስፒታል የፍኒሽንግ ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#UniversityOfTheGreenland | 4 656 |
| 11 | Matn yo'q... | 4 074 |
| 12 | ፕሬዝዳንቱ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሂደትን ጎበኙ
=========************========
ዲ.ዩ: ሰኔ 26/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) እና የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ሁለተኛውን ዙር የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሂደትን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) እንደገለፁት፣ ዩኒቨርሲቲው ሀገራዊ ተልዕኮውን ለመወጣት የሚያስችለውን በቂ ቅድመ ዝግጅት በማጠናቀቅ በፈተናዎች አገልግሎት በወጣው መርሐግብር መሰረት የመጀመሪያውን ዙር ፈተና በሰላምና በተሳካ ሁኔታ አጠናቋል።
በዛሬው ዕለት የተጀመረው ሁለተኛው ዙር በሰላም እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ዝግጅት መደረጉን ያወሱት ፕሬዝዳንቱ፣ በምልከታው የፈተና አሰጣጥ ሃደቱን ለመገምገምና በፈተናው የሚሳተፉ ባለድርሻ አካላትን ለማበረታታት መሆኑን ጠቁመዋል።
ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም ፈተናው በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረጉ ያሉት የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ የትምህርት ሚኒስቴር ተወካዮችና፣ ፈታኝ መምህራኖች፣ የፀጥታ አካላት፣ የአይሲቲ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላትን አመስግነዋል።
ሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ከዛሬ ጀምሮ በመካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ያለ ምንም የፀጥታ ችግር በመሠጠት ላይ ይገኛል።
ዩኒቨርሲቲው ለተፈታኝ ተማሪዎች መልካሙን ሁሉ ይመኛል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#UniversityOfTheGreenland | 3 073 |
| 13 | Matn yo'q... | 4 185 |
| 14 | ለዲላ ዩንቨርሲቲ ማህበረሰብ ሬዲዮ ጣቢያ ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ
======*********=======
ዲዩ፡ ሰኔ 25/2018 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ሬዲዮ ጣቢያ ጋዜጠኞችና ባለሙያዎች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጥቷል።
ስልጠናውን የዩኒቨርሲቲው የጋዜጠኝነት እና ስነ ተግባቦት መምህራን የሰጡ ሲሆን፣ ከሙያው ስነ ምግባር ጋር የተያያዙ እንዲሁም የሚታዩ የሙያ ክፍተቶችን ለመቅረፍ በሚያስችል መልኩ መሠጠቱ ነው የተገለፀው።
በስልጠናው ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የዩንቨርሲቲው የፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይመኑ ዳካ፣ በየጊዜው የሚሰጡ ስልጠናዎች የባለሙያውን አቅም በማጎልበት የሚፈለገውን ውጤት ለማረጋገጥ ፋይዳቸው የጎላ መሆኑን ገልፀዋል።
አቶ ይመኑ አክለውም ወቅቱን የጠበቀ ስልጠና በማዘጋጀት ጥራት ያለውና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ባለሙያዎች ላይ ቀጣይነት ባለው መልኩ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አስገንዝበዋል።
በተለይም በሬዲዮ ጣቢያው የሚታዩ የሰው ኃይል እጥረት እና የግብዓት ችግርን ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ አስረድተዋል።
የዲላ ዩንቨርሲቲ ማህበረሰብ ሬዲዮ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ እንዳሻው መለሰ በበኩላቸው፣ ባለሙያዎች ከስልጠናው ያገኙትን ግንዛቤ እንደ ግብዓት በመጠቀም ተቋሙን ውጤታማ ለማድረግ በትጋት እንዲሰሩ አሳስበዋል።
ስልጠናው መሰረታዊ የዜና አጻጻፍ የፕሮግራም እና የሬድዮ ይዘት አቀራረብ ባህሪያትን ያካተተ እንደሆነ ተገልጿል።
ስልጠናውን ከሰጡት መካከል የዩኒቨርሲቲው የጋዜጠኝነት እና ስነ ተግባቦት ትምህርት ክፍል ባልደረባ የሆኑት መምህርት ሰላማዊት ታፈረ፣ ከስልጠና ባለፈ የዳሰሳ ጥናት በማካሄድ ማህበረሰቡን ያማከሉ ፕሮግራሞችን መቅረጽ እንደሚገባ ገልፀው፣ ሰልጣኞች የሙያ ጊዴታቸውን በብቃት እንዲወጡ መሠል ስልጠናዎች ቀጣይነት ሊኖራቸው እንደሚገባ አሳስበዋል።
===###=== | 3 160 |
| 15 | Matn yo'q... | 2 652 |
| 16 | Matn yo'q... | 1 |
| 17 | ዕድሜ፣ እናትነት ከትምህርት ያልገታቸው ብርቱ እናት
=========*************=========
ዲ.ዩ: ሰኔ 24/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
ዕድሜና እናትነት ከትምህርት ያልገታቸው፣ ለብዙዎች አርዓያ የሆኑ ብርቱ እናት፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተናን በመውሰድ ላይ ይገኛሉ።
ወ/ሮ አልማዝ አሻራው ይባላሉ። የገደብ ወረዳ ነዋሪ ሲሆኑ፣ በቤተሰብ ጫና ምክንያት በ1982ዓ/ም ከ4ኛ ክፍል ትምህርታቸውን እንዳቋረጡ ይገልፃሉ። የረጅም ጊዜ ህልማቸው የነበረውን ትምህርት ለማቋረጥ ሲገደዱ፣ አንድ ቀን ግን ተመልሰው ህልማቸውን እንደሚኖሩ እርግጠኛ እንደነበሩ አጋርተውናል። በ1983ዓ.ም ትዳር መስርተው መኖር የጀመሩት እኚህ እናት፣ የተለያዩ ፈተናዎችንና ተግዳሮቶችን ተሻግረው እዚህ ደርሰዋል። ስምንት ልጆችንም አፍርተዋል።
ወ/ሮ አልማዝ አራት ልጆቻቸውን እሰከ ዩኒቨርሲቲ ድረስ አስተምረው፣ ለወግ መዓረግ ያበቁ፣ የልጅ ልጆቻቸውን ያዩ ስለመሆናቸውም ነግረውናል። የቀሩት አራት ልጆቻቸው ደግሞ ከ5ኛ እሰከ 12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተናግረዋል።
ትምህርታቸውን ዳግም መማር ያሰቡት ትላንት ያላሳኩትን፣ ያልኖሩትን ህልማቸውን ዳግም ለመኖር እንደሆነ ወ/ሮ አልማዝ ይገልፃሉ። እኚህ ብርቱ እናት ለትምህርት ያላቸው ፍቅር ልዩ እንደሆነ፣ ከህይወት ጉዟቸው መረዳት ይቻላል።
ወ/ሮ አልማዝ በዘንድሮው ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው በመጀመሪያው ዙር በበይነ መረብ ፈተናቸውን መውሰድ ጀምረዋል። ጥሩ ውጤት በማስመዝገብ ወደ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ተምረው መመረቅ ህልማቸው እንደሆነም ገልፀውልናል።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለወ/ሮ አልማዝ መልካሙን ሁሉ ይመኛል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#UniversityOfTheGreenland | 4 093 |
| 18 | Matn yo'q... | 3 733 |
| 19 | ዲላ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞችን እየተቀበለ ነው
===========***********===========
ዲ.ዩ ሰኔ 21/2018 ዓ.ም(ህ.ዓ.ግ)
ዲላ ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተናን ለመውሰድ በዩኒቨርስቲው የፈተና ማዕከላት የተመደቡ ተፈታኞችን እየተቀበለ ነው።
ከተለያዩ የጌዴኦ ዞን አከባቢዎች እንዲሁም አጎራባች ክልሎች በዘንድሮው ዓመት በዲላ ዩኒቨርሲቲ በሁለቱም የፈተና ማዕከላት ላይ የተመደቡ ተማሪዎች ከረፋድ ጀምሮ በመግባት ላይ ይገኛሉ።
ፈተናው ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ በስድስት ዙሮች የሚሰጥ ሲሆን፣ በስድስቱም ዙሮች 7ሺህ የሚደርሱ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው እንደሚፈተኑ ይጠበቃል።
ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ፈተናው በሰላም እንዲጠናቀቅ ባዋቀራቸው ግብረ ሀይሎች አማካኝነት ውጤታማ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለተፈታኞች መልካም ፈተና እንዲሆን ይመኛል።
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#universityofthegreenland
#EntranceExams | 5 822 |
| 20 | Matn yo'q... | 5 745 |
