Dilla University Official
📈 تحلیل کانال تلگرام Dilla University Official
کانال Dilla University Official (@dprd9) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 17 492 مشترک است و جایگاه 11 586 را در دسته آموزش و رتبه 1 917 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 17 492 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 13 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 83 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -5 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 20.82% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.62% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 3 640 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 683 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 8 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“University of the Green Land”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 14 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 14 ژوئن | +6 | |||
| 13 ژوئن | 0 | |||
| 12 ژوئن | +23 | |||
| 11 ژوئن | +22 | |||
| 10 ژوئن | +35 | |||
| 09 ژوئن | +6 | |||
| 08 ژوئن | +6 | |||
| 07 ژوئن | +2 | |||
| 06 ژوئن | +2 | |||
| 05 ژوئن | 0 | |||
| 04 ژوئن | +5 | |||
| 03 ژوئن | +2 | |||
| 02 ژوئن | +1 | |||
| 01 ژوئن | 0 |
| 2 | بدون متن... | 1 336 |
| 3 | بدون متن... | 1 506 |
| 4 | 📍ማስታወቂያ 📍
===******===
በሶስተኛ ቀን ፈተና በቀን ዐ8/10/2018ዓ.ም በዲላ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል የመውጫ ፈተና የምትወስዱ ተፈታኞች የመፈተኛ ቦታ እና ተያያዥ መረጃዎችን ከስር ከተቀመጠው ሰንጠረዥ ላይ መመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
ለፈተና ሲመጡ የፋይዳ መታወቂያ፣ የዩኒቨርሲቲ መታወቂያ እንዲሁም የፈተና መግብያ ቲኬት ይዘው መገኘት ይጠበቅባችኋል።
ለተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ መልካም እድል እንዲገጥማችሁ እንመኛለን።
መረጃውን ለተፈታኝ ጓደኞችዎ ያጋሩ! የፈተናን ህግና ደንብ ያክብሩ
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#universityofthegreenland | 1 324 |
| 5 | بدون متن... | 1 295 |
| 6 | بدون متن... | 1 |
| 7 | بدون متن... | 1 |
| 8 | ማዕከሉን በማላቅ እንደ ሀገርም የሚጎበኝ ቦታ እንዲሆን እናደርጋለን - ቶላሳ ዳዲ (ዶ/ር)
==========*************==========
ዲዩ: ሰኔ 06/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
በይርጋጨፌ ወረዳ የዱመርሶ የቡና ችግኝ ቴክኖሎጂ ሽግግር ጣብያ እና ዘመናዊ የወተት ከብቶች እርባታ ጣብያ ላይ የመስክ ምልከታ ተደርጓል።
በቡና ችግኝ ጣቢያ ላይ ስላሉ አጠቃላይ መረጃዎችን በተመለከተ የማህበረሰብ ጉድኝት እና አረንጓዴ ልማት ኦፊሰር አቶ ብሩህ ተስፋሁን ለልዑኩ ገለፃ አድርገዋል።
አቶ ብሩህ በማዕከሉ የቡና ችግኝን አፍልቶ ለአርሶአደሩ በማሰራጨት ረገድ ባለፉት ጊዜያት በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። ከዚህም ባሻገር ከሜትሮሎጂ ኤጀንሲ ጋር በመተባበር የአየር ንብረት መረጃን ለገበሬዎች ለመስጠት የአየር ንብረት መረጃ መሰብሰብያ መሳሪያን በማዕከሉ ላይ ለመትከል ስምምነት ላይ መደረሱንና በቅርቡም የተከላ ስራ እንደሚከናወን ጠቁመዋል።
የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ሀብታሙ ተመስገን (ዶ/ር)፣ ይርጋጨፌ የጉድኝት ስራ በስፋት የሚሰራበት ቦታ መሆኑን ጠቁመው፣ ከዲላ ውጪ ካሉ 13 ማዕከላት መካከል ህጋዊ የይዞታ ካርታ ያለው ቦታ መሆኑን አንስተው፣ ለዚህም የአከባቢውን አመራሮች አመስግነዋል።
ማዕከሉን ወደ ምርምር ማዕከል ለማሳደግ በርካታ ቁሳቁሶች እንደሚያስፈልጉ የተናገሩት ዶ/ር ሀብታሙ፣ ይህንን የቤት ስራ ለመወጣት ሁሉም ባለድርሻ አካል እንዲተባበር ጠይቀዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ቶላሳ ዳዲ (ዶ/ር) በዚህ ቦታ ላይ ለተሰራው ስራ፣ ለትብብር በራቸውን ክፍት ያደረጉ የአከባቢውን አመራሮች አመስግነዋል።
በማዕከሉ ቅጥር ጊቢ ውስጥ የሚገኘውን የምንጭ ውሃ በመጠቀም በማዕከሉ የውሃ እጥረት እንዳይኖር ለማድረግ መስራት ያስፈልጋል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ዩኒቨርሲቲው ችግኞችን አፍልቶ ማሰራጨት ብቻ ሳይሆን፣ አርሶ አደሩ በእራሱ ማፍላት እንዲችል ማብቃት እና ማሰልጠን ይገባል ብለዋል።
አስፈላጊ የሆኑ ቅድምያ የሚሰጣቸው ችግሮችን በመለየት፣ መሟላት ያለባቸው ግብአቶችን እያሟላን እንሄዳለን ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ማዕከሉን በማላቅ እንደ ሀገርም የሚጎበኝ ቦታ እንዲሆን በማኔጅመንት ደረጃ እየተመካከርን ስራዎችን በተቻለ ፍጥነት ለማሳለጥ እንሞክራለን ብለዋል።
በተያያዘ ዜና በይርጋጨፌ ከተማ ላይ የሚገኘው ዘመናዊ የወተት ከብቶች እርባታ ጣብያ ላይም ምልከታ ተደርጓል። ጣብያው ላይ የምርምር ስራዎች እንደሚሰሩ፣ ዝርያቸው የተሻሻሉ ከብቶች በማምጣት የሰርቶ ማሳያ ስራ እንደሚሰራ እና ለአርሶአደሮች እየተላለፉ እንደሚገኙ የግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ዲን የሆኑት ዶ/ር ሳምሶን ሀይለማሪያም ተናግረዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ቶላሳ ዳዲ (ዶ/ር)የሰርቶ ማሳያ ጣቢያውን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ እና የእንስሳት መኖ እጥረት ለመቅረፍ በዩኒቨርሲቲው ያለውን የመኖ ማቀነባበሪያ ማሽን ወደ ስራ ማስገባት እንደሚገባ ተናግረዋል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#universityofthegreenland | 1 400 |
| 9 | بدون متن... | 1 496 |
| 10 | በይርጋጨፌ በሚገኘው የተማሪዎች ማረፍያ ቤት ላይ ጉብኝት ተደረገ
============*************============
ዲዩ: ሰኔ 06/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
በዩኒቨርሲቲው ስር የሚተዳደረው እና የጤና ተማሪዎች ለተግባር ትምህርት ሲወጡ የሚጠቀሙበት የተማሪ ማረፍያ ቤት ላይ የመስክ ምልከታ ተደርጓል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ትዝአለኝ ተስፋዬ የማረፊያ ስፍራውን በተመለከተ ለልዑኩ ገለፃ አድርገዋል።
ማረፍያ ቤቱ ለተማሪዎች የሚያስፈልጉ የተለያዩ የአገልግሎት መስጫ ቦታዎችን ያካተተ፣ ከዩኒቨርሲቲው ተልዕኮ ጋር የተቆራኘ መሆኑን የተናገሩት ዋና ስራ አስፈፃሚው፣ ፕሮጀክቱ ለተቋሙ የተግባር ትምህርት ተልዕኮ አጋዥ እንደሆነና፣ ተማሪዎች በቅርበት ከማህበረሰቡ ጋር ሆነው ስራዎችን እንዲሰሩ ለማስቻል እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።
ተማሪዎች በተግባር የሚለማመዱባቸው የጤና ተቋማት ላይ መሰማራት ይኖርባቸዋል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚው፣ ያንን ለማድረግ በነዚህ ተቋማት አከባቢ ላይ የተማሪ ማረፊያ ቦታዎችን እና በውስጡ አስፈላጊ መገልገያ መሳሪያዎችን ማዘጋጀት ተገቢ መሆኑን ጠቁመዋል።
በይርጋጨፌ ያለው ማረፊያ ቤት ወደ አገልግሎት እንዲገባ ማኔጅመንቱ ትኩረት በመስጠቱም አመስግነዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ቶላሳ ዳዲ (ዶ/ር) የማረፍያ ስፍራው ከዚህ በፊት ትኩረት የተነፈገው ቦታ መሆኑን ጠቁመው፣ የጤና ተማሪዎች አብዛኛው ጊዜያቸውን የሚያጠፉት በተግባር የመስክ ስራዎች ላይ በመሆኑ፣ ይህንን ማዕከል ማስተካከል እና ማደስ ብሎም ወደ ስራ እንዲገባ መደገፍ እንደሚገባ ገልፀዋል።
የማረፍያ ስፍራው ላይ ያሉ ቤቶች ጥገና የሚያስፈልጋቸው መሆናቸውን የገለፁት ፕሬዝዳንቱ፣ ሀብቱ መኖሩ በራሱ ትልቅ ነገር በመሆኑ፣ እንዲሁ እንዳይባክን የቤት ስራ መውሰድ እንደሚገባ ተናግረዋል።
የይርጋጨፌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልንም መደገፍ ይገባል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ የታካሚዎችን ፍሰት ለማስቀረት እና የህክምና አገልግሎቱን እዚሁ ለመጨረስ ከዩኒቨርሲቲው ሆስፒታል ጋር ማቆራኘት እንደሚገባ አውስተዋል። በዚሁ ረገድ የተጀመሩ ስራዎችንም ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#universityofthegreenland | 1 378 |
| 11 | بدون متن... | 1 292 |
| 12 | የሞዴል አርሷአደር አቶ ዳንኤል ደምሴ የቡና ማሳ ላይ ጉብኝት ተደረገ
============***********=============
ዲዩ: ሰኔ 06/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
በይርጋጨፌ ቆንጋ ቀበሌ የሞዴል አርሶአደር አቶ ዳንኤል ደምሴ የቡና ማሳ ላይ በዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ቶላሳ ዳዲ የተመራው የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት ልዑክ የመስክ ምልከታ አድርጓል።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ2011 ጀምሮ ያረጁ የቡና ዛፎችን በመንቀል ዝርያቸው በተሻሻሉ ቡናዎች የመተካት ስራ በስፋት ሰርቷል።
የይርጋጨፌ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ቡኔ የዩኒቨርሲቲውን ፕሬዝዳንት እና ልዑካቸውን እንኳን ደህና መጥታችሁ በማለት ዩኒቨርሲቲው ባለፉት ጊዜያት በርካታ ስራዎችን ስለመስራቱ ተናግረዋል።
ዩኒቨርሲቲው የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ረገድ አቅም ለሌላቸው አርሶአደሮች ጭምር ዝርያቸው የተሻሻሉ የእንሰት ችግኞችን በነፃ በማከፋፈል አሁን ለተመዘገበው አመርቂ ውጤት የማይተካ ሚና መወጣቱን ጠቁመዋል። በቡና ዘርፍም ዝርያቸው የተሻሻሉ ችግኞችን ለአርሶአደሮች በማከፋፈልና በምርምር በመደገፍ ምርታማነትን ለማሳደግ የሰራው ስራ የሚያኮራና የሚያስመሰግን ነው ብለዋል።
የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ሀብታሙ ተመስገን (ዶ/ር)፣ ዩኒቨርሲቲው በአከባቢው አራት የቡና ምርምር ጣብያዎች ላይ ላለፉት ሰባት ስምንት አመታት የቡና ችግኞችን በማፍላት ሰፋፊ ስራዎችን መስራቱን ጠቁመው፣ የቡና ችግኝ የማዘጋጀት ስራ አድካሚ መሆኑን አንስተዋል።
የቡና ችግኞችን በማፍላት ለገበሬዎች በማከፋፈል ረገድ ዩኒቨርሲቲው ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ማከናወኑን የጠቆሙት ዶ/ር ሀብታሙ፣ በኩታ ገጠም እየለማ የሚገኝ የቡና ማሳ ላይ የሚገኘው ምርት ከከዚህ በፊቱ ጋር ሲነፃፀር የተሻለ መሆኑን አንስተዋል። በቆንጋ የቡና ማሳ ላይ ለሌሎች አከባቢዎችም ጭምር አርዓያ የሚሆን ስራ መሠራቱን ጠቁመዋል።
የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም ዳይሬክተር አለሙ ደሳ (ዶ/ር) ውጤቱ እንዲመጣ የአከባቢው አርሶአደሮች ትብብር እና ቁርጠኝነት የላቀ መሆኑን አንስተዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶላሳ ደሳ (ዶ/ር) መሬቱም አከባቢውም ቀና እና የዋህ ህዝብ ያለበት በመሆኑ እጅጉን ይማርካል በማለት፣ መሬቱም እንዲሁ የሰጡትን የሚያበቅል በመሆኑ ባለው ሀብት ላይ እሴት መጨመር እንደሚገባ ገልፀዋል።
አርሶአደሮች ልምዳቸውን ለማካፈል ከሀገርም አልፈው ከሀገር ውጭ እንዲሄዱ ማድረግ መቻል የዩኒቨርሲቲው አስተዋጽዖ እንዳለ ሆኖ የአከባቢው ህዝብና አመራሮችም ትጋት ያለበት እንደሆነ አንስተው፣ ለዚህም ከፍተኛ ክብር እንዳላቸው ጠቁመዋል።
አከባቢውን በቡና ምርት ብቻ ሳይሆን በጥራት እና በምርታማነት ተምሳሌት ቦታ ለማድረግ እና መልካም ተሞክሮዎችን የበለጠ ለማሳደግ ዩኒቨርሲቲውም በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ጠቁመዋል።
ዩኒቨርሲቲው በአከባቢው ላይ ያለውን ሀብት የበለጠ ለማሳወቅ እና እሴት ለመጨመር ከሚሰራቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት ጎን ለጎን ሌሎች ባለድርሻ አካላትን የማሰባሰብ ስራ እንደሚሰራ ዶ/ር ቶሎሳ ገልፀዋል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#universityofthegreenland | 1 066 |
| 13 | بدون متن... | 1 160 |
| 14 | በፍስሃገነት የስልጠና ማዕከል ላይ ጉብኝት ተደረገ
==========***********=========
ዲዩ: ሰኔ 06/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
በዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶላሳ ዳዲ (ዶ/ር) የተመራ የዩኒቨርሲቲው የማኔጅመንት ልዑክ ቡድን በኮቾረ ወረዳ በፍስሀገነት የሚገኘውን የስልጠና ማዕከል ጎብኝቷል።
በፍስሃገነት በሚገኘው የስልጠና ማዕከል ላይ እየተሰሩ ያሉ ተግባራትን በተመለከተ የዩኒቨርሲቲው የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም አለሙ ደሳ (ዶ/ር) ለልዑክ ቡድኑ ገለፃ አድርገዋል።
የስልጠና ማዕከሉ ከዚህ በፊት በወርልድ ቪዥን ስር የነበረ ሲሆን፣ አሁን ላይ ለተማሪዎች ብሎም ለመምህራን እንደ ስልጠናና ስብሰባ ማዕከልነት እያገለገለ እንደሚገኝ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በማዕከሉ የሚገኙ የማደሪያ ክፍሎች፣ የስብሰባ አዳራሾች፣ የምግብ ማብሰያ ስፍራዎች እና የቡና ስልጠና ቦታ ላይ ምልከታ ተደርጓል። በማዕከሉ ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ በቡድን የሚሰሩ ስራዎችን ለመስራት የሚገለገልበት እንደሆነ ተነስቷል።
የጤና ተማሪዎችም በቦታው ላይ የTTP ፕሮጀክቶችን ለመስራት እንደ ማደሪያነት እንደሚጠቀሙት እንዲሁም መምህራንም የጋራ ስራዎችን ለመስራት ሲፈልጉ እንድያርፉበት አስፈላጊ ግብአቶች እንደተሟሉለት ተነስቷል። እስካሁን ግን ወደ ማዕከሉ ሰልጣኞች አለመግባታቸውን እና በቅርቡም ቀሪ ስራዎችን በማጠናቀቅ ወደ ስራ ለማስገባት እንደሚሰራ ተጠቁሟል።
የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም ዳይሬክተር ዶ/ር አለሙ ደሳ፣ በስልጠና ማዕከሉ አንዳንድ የግብአት እጥረትን ማሟላት እንደሚያስፈልግ አንስተው፣ መጠነኛ የእድሳት ስራ እንዲሰራለትም ጠይቀዋል።
ማዕከሉን ለብዙ ዓላማዎች ለመጠቀም ያለበትን ይዞታ ማስፋት እንደሚጠበቅ ያነሱት ደግሞ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ሀላፊ ዶ/ር አለማዬሁ አካሉ ናቸው፣
የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ሀብታሙ ተመስገን (ዶ/ር) ዲላ ዩኒቨርሲቲ በቡና መደበኛ ስርዓተ ትምህርት በማዘጋጀት ዘርፉ ላይ ግንባር ቀደም ሆኖ እየሰራ እንደሚገኝ አውስተው፣ በተለያዩ ጊዜያቶችም ላይ ዩኒቨርሲቲው የቡና ሲምፖዚዬምን በማዘጋጀት ባለድርሻ አካላትን ማሰባሰብ መቻሉን ጠቁመዋል።
በይርጋጨፌ ላይ የቡና ምርምር ኢንስቲትዩት ለማቋቋም ዩኒቨርሲቲው በማቀድ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች ስያደርግ እንደነበር ያወሱት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፣ አሁንም ባለድርሻ አካላት፣ የቡና ላኪዎች፣ በኢንዱስትሪው ውስጥ ያሉ ባለድርሻ አካላት ርብርብ እንድያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ቶላሳ ዳዲ በበኩላቸው፣ በማዕከሉ ላይ ባዩት ነገር መደሰታቸውን ጠቁመው፣ በአከባቢው ካለው የመሬት ጥበት አንፃር ያለውን ሀብት በአግባቡ መጠቀም ያስፈልጋል ብለዋል። ነገር ግን የማስፋፊያ ስራውን ካሁኑ ማሰብ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋልል። በማዕከሉ አስፈላጊ የሆኑ የእድሳት ስራዎችን መስራት እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል።
ማዕከሉን የምርምር ተቋም ለማድረግ አስፈላጊ የሆኑ የማስተርፕላን ስራዎችን መስራት እንደሚገባ የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ፣ በእራስ አቅም ለመጀመር የሚጠበቅብንን የቤት ስራዎች ቀድሞ መጨረስ ያስፈልጋል ብለዋል።
በአከባቢው ላይ በስፋት በሚታወቀው የቡና ምርምር ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሰራል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ በዚህ ጉዳይ ከአከባቢው አመራሮች እና ማህበረሰቦች ጋር በመነጋገር እና በመቀናጀት መስራት ያስፈልጋልም ነው ያሉት።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#universityofthegreenland | 1 159 |
| 15 | بدون متن... | 1 290 |
| 16 | بدون متن... | 1 |
| 17 | በኮቾረ ወረዳ የቡና ምርምርና ሰርቶ ማሳያ ማዕከል ላይ ጉብኝት ተደረገ
===========***********===========
ዲዩ: ሰኔ 06/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
በዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶላሳ ዳዲ (ዶ/ር) የተመራ የማኔጅመንት ልዑክ ቡድን በዞኑ በተለያዩ አከባቢዎች ላይ በሚገኙ የዩኒቨርሲቲው የምርምር ማዕከሎች ላይ ጉብኝት እያደረገ ይገኛል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ቶላሳ ዳዲ (ዶ/ር) የመጀመሪያ የመስክ ምልከታቸውን በማድረግ ላይ የሚገኙ ሲሆን፣ በዩኒቨርሲቲው ስር የሚገኙ የምርምር ማዕከላት ያሉበትን ደረጃ ለማወቅ እንደሆነ ተገልጿል።
የኮቾሬ ወረዳ የብልጽግና ደፓርቲ ፅ/ቤት ሀላፊ እና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ዘርሁን አለሙ፣ ልዑኩን እንኳን በሰላም መጥታችሁ በማለት ተቀብለዋቸዋል።
የወረዳው አብዛኛው መሬት በቡና የተሸፈነ መሆኑን ያነሱት ሀላፊው፣ ያለው የቡና ዝርያ ግን የምርታማነት ችግር እንደነበረበት አንስተዋል። ዩኒቨርሲቲው በጥናት የተደገፉ ምርታማነታቸው የተረጋገጡ የቡና ዝርያዎችን ከማከፋፈል ጀምረሮ የተለያዩ ሰርቶ ማሳያ ቦታዎች ላይ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ጠቁመው፣ ለዚህም የዩኒቨርሲቲው አሻራ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል።
በዞኑ በኮቾሬ ወረዳ ላይ የሚገኘውን የቡና ምርምርና ሰርቶ ማሳያ ማዕከልን የጎበኙ ሲሆን፣ በማዕከሉ ላይ ስላለው አጠቃላይ መረጃን በተመለከተ የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም ዳይሬክተር ዶ/ር አለሙ ደሳ ለልዑኩ ገለፃ አድርገዋል።
ዶ/ር አለሙ በንግግራቸው፣ ዞኑ በከፍተኛ የቡና ምርት የሚታወቅ ቢሆንም ያሉ ዝርያዎች ያረጁ፣ ዝቅተኛ ምርት የሚሰጡ መሆናቸውን ጠቁመው፣ ዩኒቨርሲቲው ይህንን እንደ ክፍተት በመለየት በርካታ የምርምር ስራዎችን ስለመስራቱ አውስተዋል። ዩኒቨርሲቲው የአየር ንብረቱን መቋቋም የሚችሉ ዝርያዎችን በማምጣት ምርታማነትን ለመጨመር ከፍተኛ ስራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
ዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ጋር የምርምር ስራዎችን በቅንጅት በመስራት ላይ እንደሚገኝ አንስተው፣ በኮቾረ የሰርቶ ማሳያ የቡና ማሳ ላይም ለተሞክሮ የሚሆኑ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ሀብታሙ ተመስገን (ዶ/ር)፣ በወረዳው በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቁመው፣ በሰርቶ ማሳያ ሳይቱም ላይ ላለፉት ዓመታት የአከባቢውን አርሶአደር ኑሮ ለማሻሻል በቡና ዘርፍ ላይ የተሰራው ስራ አበረታች መሆኑን ጠቁመዋል።
ዩኒቨርሲቲው በቡና ዘርፍ ላይ የልህቀት ማዕከል ለመሆን በተለያዩ ሳይቶች ላይ ከሚሰራቸው የምርምር ስራዎች ጎን ለጎንም በስልጠና ዘርፉ ላለፉት በርካታ ዓመታት በርካታ ሰልጣኞችን በቡና ስልጠና ማብቃቱን የጠቆሙት ዶ/ር ሀብታሙ፣ ይህም ዩኒቨርሲቲው በዘርፉ ላይ መሪ ተዋናይ ለመሆን እያደረገ ላለው ስራ አንዱ ማሳያ መሆኑን ጠቁመዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ቶሎሳ ዳዲ በጉብኝቱ ወቅት እንደተናገሩት፣ እንዲህ ዓይነት ተግባራት ከዩኒቨርሲቲዎች የሚጠበቅ ስራ መሆኑን ጠቁመው፣ ቡና ትልቁ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንትና አረንጓዴ ወርቅ ከሚባሉ ሀብቶች መካከል አንዱ በመሆኑ በዘርፉ ላይ የተቻለንን ሁሉ ማድረግ ይገባል ብለዋል። ቡና የውጭ ምንዛሬን በማምጣት ረገድም ከፍተኛ ሚና ያለው ሀብት በመሆኑ የበለጠ ልንመራመር ይገባል ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ።
የቡና ምርታማነት እንድያድግ እና የሀገርን ኢኮኖሚ እንድያግዝ የተሰራው ስራ እጅግ የሚያኮራ መሆኑን እና ዩኒቨርሲቲው በሳይቱ ላይ የሰራውን ስራ ያደነቁት ፕሬዝዳንቱ፣ ከሁሉ በላይ ደግሞ የአከባቢው ማህበረሰብ እና የዩኒቨርሲቲው ቅንጅት ለዚህ ስራ ትልቅ አስተዋጽዖ ማድረጉን አንስተዋል።
የቡና ምርት ሰባት እና ከዚያ ዓመት በላይ ሳይጠበቅ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለፍሬ እንዲበቃ የተሰራው ፕሮጀክት የሚያኮራ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ በዚህ ስራ ውስጥ አስተዋጽዖ የነበራቸው ሁሉም አካላትን አመስግነዋል። ስራውን የበለጠ ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
በጉብኝቱ ላይ የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት አባላት እና ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የወረዳው የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#universityofthegreenland | 1 828 |
| 18 | بدون متن... | 1 754 |
| 19 | ዲላ ዩኒቨርሲቲ በ4ኛው ዙር ያሰለጠናቸውን የግል የቡና ሰልጣኞችን አስመርቀ
===========*************============
ዲ.ዩ: ሰኔ 05/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
የዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም በ4ኛው ዙር የግል የቡና ስልጠና የወሰዱ 15 ሰልጣኞችን አስመርቋል።
የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ሀብታሙ ተመስገን (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት ሰልጣኞችን እንኳን አደረሳችሁ በማለት፣ በዩኒቨርሲቲው ቡና በካሪኩለም መመራት ከጀመረ ሰባት ስምንት አመታት መሻገሩን ጠቁመዋል። ጂ.አይ.ዘድ ተቋምም ከተለያዩ ቦታዎች የሚመጡ ሰልጣኞችን በመደገፍ እና በማምጣት ከዩኒቨርሲቲው ጋር ሲሰራ መቆየቱን አውስተው፣ አሁን ላይ ግን ዩኒቨርሲቲው በዘርፉ የልህቀት ማዕከል እየሆነ እንደሚገኝ አንስተዋል።
በመጪው ጊዜ ላይም የበይነ መረብ የቡና ትምህርትን ለማስጀመርና በርቀት ያሉ የቡና ዘርፍ ወዳድ ሰዎችን ለማሳተፍ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ስለመሆናቸው አንስተዋል ዶ/ር ሀብታሙ።
ኢንዱስትሪዎች የቡናውን ዘርፍ ለማዘመን በሚደረገው ርብርብ የእራሳቸውን አሻራ ማሳረፍ ከቻሉ ዘርፉን ማሳደግ እንደሚቻል የተናገሩት ዶ/ር ሀብታሙ፣ ይህንን እውን ለማድረግ የባለድርሻ አካላትን ትስስር መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
ሰልጣኞች "በሰለጠናችሁት እውቀት ከእራሳችሁ አልፋችሁ ሀገርን የሚያሻግር ስራ የምትሰሩበት ይሁንላችሁ" በማለት የደስታ መልዕክታቸውንም አስተላልፈዋል ዶ/ር ሀብታሙ።
የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም ዳይረክተር አለሙ ደሳ (ዶ/ር)፣ ተቋሙ ባለፉት አምስት ዓመታት ከ360 በላይ ሰልጣኞችን ማስመረቁን ገልፀው፣ በዚህኛው ዙር የተሳተፉ ሰልጣኞችም ብርቱ ትግል አድርገው በፅናት የሚሰጠውን የንድፈ ሀሳብና የተግባር ትምህርት መከታተላቸውን አንስተዋል።
እስካሁን የአሁኖቹን ተመራቂዎች ጨምሮ 131 የሚሆኑ የግል ሰልጣኞች በቡና ስልጠና ላይ በመሳተፍ የተመረቁ መሆናቸውንም ዶ/ር አለሙ ገልፀዋል።
የምርምር ስነ ምግባር፣ ህትመት እና ስርፀት ዳይሬክቶሬት ምስጋኑ ለገሰ (ዶ/ር) ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልዕክት፣ "እናንተ ገበያውን የምትቀላቀሉ፣ ለብዙዎች ስራ የምትፈጥሩ፣ ዘርፉን በሳይንስ የምትመሩ" ስለሆናችሁ የሚጠበቅባችሁን ሀላፊነት እንድትወጡ አደራ ማለት እፈልጋለው ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲው በሁሉም ዘርፍ በጥራት የማይታማ ስለመሆኑ ያነሱት ዶ/ር ምስጋኑ፣ የዩኒቨርሲቲው አምባሳደር በመሆን በሄዳችሁበት ቦታ ሁሉ የተሻለ አበርክቶ እንዲኖራችሁ ጠንክራችሁ ልትሰሩ ይገባል በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።
ስልጠናውን በብቃት ላጠናቀቁ ሰልጣኞች ሰርተፊከት የተበረከተ ሲሆን፣ ከሰልጣኞቹ መካከል ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ሰልጣኞች ልዩ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ሰልጣኞች ባገኙት እውቀት በዘርፉ የተሻለ ስራ ለመስራት እና የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት እንደሚተጉ ገልፀውልናል።
በ4ኛው ዙር ለ45 ቀናት በዘለቀው ስልጠና 15 ሰልጣኞች ከንድፈ ሀሳብ ጀምሮ እስከ ተግባር ስልጠና ድረስ ብቁ በሆኑ በዘርፉ ባለሙያዎች መሰልጠናቸው በመድረኩ ተገልጿል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#universityofthegreenland | 1 957 |
| 20 | بدون متن... | 1 998 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
