cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

የደጉ ሳምራዊ መልካምነት®

ይህ ትክክለኛ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት የቴሌግራም ቻናል ነው:: (በመ/ር ሲራክ ሰሎሞን) በዚህ የቴሌግራም ቻናል:- ➮አስተማሪ እና መንፈሳዊ ፅሁፎችን ➮የቅዱሳን ገድላት ➮ መዝሙሮችን ➮መንፈሳዊ ትምህሮቶችን ያገኛሉ። የመወያያ ግሩፕ: https://t.me/+QKiTJYGJvYpmNWM0 የዚህ ግሩፕ ዓላማ ለበጎ ምግባር ቃለ እግዚአብሔርን መማማር ነዉ::

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
720
Obunachilar
-224 soatlar
-57 kunlar
-130 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

👉ክርስቶስ ተንስአ እም ሙታን                  ✝️በዐቢይ ሀይል ወስልጣን 👉አሰሮ ለሰይጣን                   ✝️አግአዞ ለአዳም 👉ሰላም                  ✝️እምይዝኤሰ 👉ኮነ                  ✝️ፍሰሃ ወሰላም #ወደ_አባቴ_አላረኩምና_አትንኪኝ ✍🏾 ማርያም መቅደላዊት ግን ሽቱ ይዛ ጎህ ሳይቀድ ሄደች ሌሎችም ተከትለዋት ከመቃብር በደረሱ ጊዜ የጌታችንን ቅዱስ ሥጋ አጡት ‹‹ወስደውታል›› እያሉ ሲያለቅሱ መልአክ ‹‹ ሕያውን ከሙታን መካከል ለምን ትፈልጉታላችሁ ተነስቷል። ከዚህ የለም ይልቁኑስ ገና በገሊላ ሳለ ለእናንተ እንደተናገረ አስቡ ቃሉንም አስቡ ለደቀመዛሙርቱ ንገሯቸው አላቸው ፡፡ ሉቃ 24፡1 👉ሌሎች ሲሔዱ ማርያም መቅደላዊት ግን የደረሰበትን ሳላውቅ አልሄድም ብላ ቆማ ታለቅስ ነበር ጌታችንም ከወደኋላዋ መጥቶ ‹‹ ምን ሆነሽ ታለቅሺያለሽ ›› አላት የአትክልት ጠባቂ መስሏት ‹‹ ጌታዬን አንተ ወስደኸው እንደሆነ ሽቱ እንድቀባው ያደረክበትን አሳየኝ ›› አለቸው ‹‹ ማርያም ›› ብሎ ስሟን ሲጠራት ጌታ መሆኑን አውቃ ‹‹መምህር ሆይ›› ብላ እጅ ልትነሳው ስትቀርብ ‹‹ገና ወደ አባቴ አላረኩምና አትንኪኝ ሄደሽ ለደቀመዛሙርቴ ተነሣ ብለሽ ንገሪያቸው ›› አላት። ዮሐ20፡17 ሄዳ አብስራቸዋለች ጴጥሮስና ዮሐንስ እየሮጡ መጥው መግነዙን እንጂ እሱን አላገኙትም ‹‹ በእውነት ተነስቷል ›› እያሉ ተመለሱ፡፡ 👉ሰውን ወዳጅ ኢየሱስ ክርስቶስ መቅደላዊት ማርያምን አትንኪኝ ያላት ጠልቷት ወይም ተጸይፏት አይደለም፡፡ 👉ትንሣኤውን ከሰው ልጆች ቀድማ እንድታይ የፈቀደላት ስለወደዳት ነው፡፡ #ታዲያ_ለምን_አትንኪኝ_አላት? * 3 መዓልት 3 ሌሊት በከርሰ መቃብር አድሬ እነሳለው ብሎ የተናገረውን ስለረሳች ስለ እምነቷ ማነስ ሊገስጻት ፈልጎ ነው። ለመላእክት ስለምን ታለቅሺያለሽ ሲላት ጌታዬን ወስደውታል አለች እንጂ ‹‹እንደተናገረው ተነስቷል›› አላለችም። ዮሐ 20፡11-13 👉 #አንድምበዛው ወደ ባህሪ አባቱ የሚያርግ መስሏት እግሩን ስማ ልትሰናበተው ነበር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ግን። የማርግበት ጊዜ ገናነውና ለመሰናበት ብለሽ አትንኪኝ ሲላት ነው። 👉#አንድምሥርዓተ ክህነትን ሲመሰርት ሴቶች ካህን መሆን ሥጋወ ደሙን መፈተት እንደማይችሉ ሥርዓት ሲሰራልን ነው። ለዚህም ማረጋገጫ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስን ግን እንዲዳስሰው የፈቀደለት ሲሆን መግደላዊት ማርያምን ግን አትንኪኝ ነው ያላት። ዮሐ 20፡26 ወዲያው ጌታ በተዘጋ ቤት እንዳሉ በማይመረመር ጥበብ በመሐከላቸው ቆሞ ‹‹ ሰላም ለክሙ ›› ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው፡፡ ምትሃት መስሏቸው ታወኩ በጦር የተወጋ ጎኑን በችንካር የተቸነከሩ እጆቹን እሮቹን አሳይቷቸው አውቀውታል። 👉መቃብሩን ሲጠብቁ የነበሩ ወታደሮች በክብር ብርሃን ተጎናጽፎ ሲነሣ አይተው ደንግጠው ወደ አይሁድ ዘንድ ሔዱና መነሳቱን የሆነውን ሁሉ ነገሯቸው፡፡ አይሁድም ‹‹ ብዙ ገንዘብ እንሰጣችኋለን ተኝተን ሳለ ደቀመዛሙርቱ ሰረቁት በሉ አሏቸው፡፡ በነግ አይሁድ ጲላጦስ ዘንድ መጥተው ‹‹ ሥጋው ተሰርቋል ጠባቂዎቹን አስጠርተህ መርምርልን ›› አሉት። 👉 ለየብቻ ከፋፍሎ ሲመረምራቸው ግማሹ ጴጥሮስና ዮሐንስ ሰረቁት ሲሉ ሌሎች ደግሞ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ሰረቁት አሉ። 👉አስራ አንዱም መጥተው ሰረቁት ያሉም ነበሩ፡፡ ጲላጦስም ወደ መቃብሩ ሄዶ ሲያይ መግነዙን አገኘው ‹‹ ደቀመዛሙርቱ ከወሰዱትማ መግነዙንም አብረው ይወስዱት ነበር ›› አለ። 👉በእነዚህ ምክንያቶች ደቀመዛሙርቱ እንዳልወሰዱት አወቀ። ‹‹ ሞትን ያጠፋ ሞትን ድል የነሣ ጌታችን ኢየሱስ ግን አይሁድን ይህን ቀን አነሣዋለሁ እንዳላቸው፡፡ በእውነት በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፡፡ 👉አንበሳ ከተኛበት ፈጥኖ እንዲነሣ ወይን ጠጥቶ የሰከረ ኃይለኛ ፈጥኖ እንዲነሣ፡፡ በመንፈስ ቅዱስና በባቱ ኃይል በራሱም ሥልጣን ፈጥኖ ተነሣ የሞት ቁራኝነትንም አጠፋ፤ ሞት ሊያዘው አይችልምና፡፡ 👉የተገነዘበትንም ልብስ ትቶ ልብሰ መንግሥቱን ለብሶ ተነሣ፡፡ በተወለደም ጊዜ የናቱን ማኅተመ ድንግልና እንዳለወጠ፡፡ 👉በትንሣኤውም የመቃብሩን ቁልፍ አልከፈተም፡፡ በተገነዘበትም ልብስ የመቶ አለቃውን ዐይን አዳነ፡፡ የሞተውንም ሰው አስነሣ፡፡ በመቃብርም ጲላጦስ በውስጡ በቀበረው ጊዜ ፊያታዊ ዘየማንን አስነሳው፡፡ 👉እሁድ ማታም ጌታችን ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ አይሁድን ስለፈሩ ተሰብስበው ወዳሉበት ከዝግ ቤት ገባ ያረጋጋቸውና ደስም ያሰኛቸው ዘንድ፡፡ 👉ጌታችን ኢየሱስም ቸር አላቸውን አትፍሩ አትደንግጡ እኔ ነኝ አላቸው፡፡ እነሱ ግን ምትሐት የታያቸው መስሏቸው ፈጽመው ፈሩ፡፡ 👉ጌታችን ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱን ምን ያስደነግጣችኋል እንደዚህ ያለ ሐሳብ በልቡናችሁ ለምን ያድራል አላቸው፡፡ እጄንም እግሬንም ዳሳችሁ እዩ፡፡ 👉ለምትሐት በኔ እንደምታዩት ሥጋ ዐጥንት የለውምና፡፡ ይህን ብሎ የተወጋ ጎኑን የተቸነከሩ እጆቹንና እግሮቹ አሳያቸው ደቀመዛሙርቱም ጌታችንን ባዩት ጊዜ ደስ አላቸው፡፡›› #ቻናሉን_ይቀላቀሉ? https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
Hammasini ko'rsatish...
የደጉ ሳምራዊ መልካምነት®

ይህ ትክክለኛ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት የቴሌግራም ቻናል ነው:: (በመ/ር ሲራክ ሰሎሞን) በዚህ የቴሌግራም ቻናል:- ➮አስተማሪ እና መንፈሳዊ ፅሁፎችን ➮የቅዱሳን ገድላት ➮ መዝሙሮችን ➮መንፈሳዊ ትምህሮቶችን ያገኛሉ። የመወያያ ግሩፕ:

https://t.me/+QKiTJYGJvYpmNWM0

የዚህ ግሩፕ ዓላማ ለበጎ ምግባር ቃለ እግዚአብሔርን መማማር ነዉ::

Photo unavailableShow in Telegram
👉ክርስቶስ ተንስአ እም ሙታን                  ✝️በዐቢይ ሀይል ወስልጣን 👉አሰሮ ለሰይጣን                   ✝️አግአዞ ለአዳም 👉ሰላም                  ✝️እምይዝኤሰ 👉ኮነ                  ✝️ፍሰሃ ወሰላም #ወደ_አባቴ_አላረኩምና_አትንኪኝ ጌታችንም ‹‹ ማርያም ›› ብሎ ስሟን ሲጠራት ጌታ መሆኑን አውቃ ‹‹መምህር ሆይ›› ብላ እጅ ልትነሳው ስትቀርብ ‹‹ገና ወደ አባቴ አላረኩምና አትንኪኝ ሄደሽ ለደቀመዛሙርቴ ተነሣ ብለሽ ንገሪያቸው ›› አላት። ዮሐ20፡17 #ቻናሉን_ይቀላቀሉ? https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
Hammasini ko'rsatish...
ወደ ኖኅ መርከብ ለመጨረሻ ጊዜ የገባችው እንስሳ የኖኅ መርከብ ጉዳይ በጣም አስገራሚ ከሚሆኑብኝ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች አንዱ ነው:: በዓለማችን አሁን ያሉ እንስሳት ሁሉ "ከነ ባለቤትዎ" እንዲገኙልን እንደሚባልበት ሰርግ ጥንድ ጥንድ ሆነው የገቡባት ትልቅ መርከብ ታሪክ : ዳግም ለሰው ልጆች ወላጆች ለመሆን የተመረጡ አራት ወንዶችና አራት ሴቶች ብቻ የተሳፈሩባት ትልቅ መርከብ ሁኔታ ትኩር ብሎ ላየው አስገራሚ እውነቶችን ያዘለ ነው:: ከሁሉም በላይ ግን መርከቢቱ የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ መሆንዋ ብዙ ነገር እንድናስብ ያግዘናል:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ "ወደ ኖኅ መርከብ ተኩላ ገብቶ ሲወጣም ተኩላ ሆኖ ይወጣል:: ወደ ቤተክርስቲያን ግን ተኩላ ሆነው ገብተው በግ ሆነው የወጡ ብዙዎች ናቸው" ብሎአል:: እውነትም ቤተ ክርስቲያን ወደ እርስዋ የገቡትን መለወጥ የምትችል መርከብ ናት:: ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደ ጅብ ሆዳም ሆነው ገብተው ጾመኞች ሆነው የወጡ አሉ:: እንደ የሌሊት ወፍ በቀን መኖር አቅቶአቸው ሌሊቱን የልባቸው ዓይን ታውሮ በኃጢአት ጨለማ ሲደናበሩ የኖሩ ሰዎች ወደ መርከቢቱ ገብተው እንደ ንስር አርቀው አጥርተው ቀኑን የሚያዩ ሆነዋል:: ቤተ ክርስቲያን ወደ እርስዋ የገቡትን የምትለውጥ መርከብ ናት:: ውኃ ወደ እርስዋ ሲገባ ጠበል ይሆናል:: አፈር ወደ እርስዋ ሲገባ እምነት (እመት) ይሆናል:: ዘይት ወደ እርስዋ ሲገባ ቅዱስ ቅባት ይሆናል:: ኅብስትና ወይን ወደ እርስዋ ሲገባ ወደ ቅዱስ ቁርባን ይለወጣል:: ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ያልተለወጠ ሰው ግን ሲገባም ጅብ ሲወጣም ጅብ ሆኖአል:: ኖኅ ከመርከብ መልእክት ልኮት የቀረው የቁራ ነገርስ? ከቤተ ክርስቲያን ወጥተው ስንቶች በዚያው ቀርተዋል? ለዓለም ጨው እንዲሆኑ ተልከው በዚያው ሟሙተው የቀሩ ስንት አሉ:: ርግብ ግን ማረፊያ ስታጣ ተመልሳ ነበር:: ከመርከቢቱ የራቅን ሁላችን "ልባችን በእግዚአብሔር እስካላረፈ ድረስ ዕረፍት የለውም" እንዳለ ሊቁ ወደ መርከቢቱ ፈጥነን መመለስ አለብን:: ሰሞኑን ደግሞ አንድ ጥያቄ በአእምሮዬ ተመላለሰብኝ:: "ወደ ኖኅ መርከብ ለመጨረሻ ጊዜ የገባው እንስሳ ማን ሊሆን ይችላል?" የሚል:: ይህን ጥያቄ በግልም በጉባኤ ላይም ሰዎችን ጠይቄ ነበር:: መቼም ለዚህ ጥቅስ አያስፈልገውም:: ኖኅ ቆሞ እንስሳቱ እስኪገቡ ድረስ እንደጠበቀና ማንንም እንስሳ ጥሎ እንዳልገባ የታወቀ ነው:: በዚህ ምክንያት እንስሳቱ ወደ መርከቢቱ የሚገቡት እንደደረሱበት ቅደም ተከተል ነው:: ክንፍ ያላቸው በርረው ቀድመው ይገባሉ:: እንደ ጥንቸል እንደ ካንጋሮ እንደ ሚዳቁዋ ያሉትም እየዘለሉ ፈጥነው ይገባሉ:: ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ነፍሳቸውን ለማዳን ፈጥነው በርረው የገቡ እንደ ሚዳቋ ዘልለው የደረሱ ብርቱዎች አሉ:: እንደ ፒኮክ ያሉ ባለ ውብ ክንፎች : እንደ ቀጭኔ ያሉ ባለ ረዥም አንገቶች እንደ ጃርት ያሉ ሌላው ላይ የሚሰኩት እሾኽ የለበሱ እንስሳት ወደ መርከብዋ ገብተዋል:: በቤተክርስቲያን እንደ ፒኮክ አምሮ መታየት መዘባነን የሚወዱ ለታይታ የሚገዙ ብዙዎች ገብተዋል:: እንደ ቀጭኔ አንገታቸውን ከፍ አድርገው ሰውን ቁልቁል የሚመለከቱና "አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ የዕብራውያን ሴቶች" ዓይነት ሕይወት ያላቸውም ገብተዋል:: እንደ ጃርት በክፉ ንግግር የሰው ልብ ላይ የሚሰኩት ጥላቻ የተላበሱ ሰዎችም ገብተዋል:: የኖኅ መርከብ ያልያዘችው እንስሳ እንደሌለ ቤተ ክርስቲያንም ያልተሸከመችው ዓይነት ሰው የለም:: ወደ ጥያቄው ስመለስ በእኔ ግምት ወደ መርከቡ በጣም ዘግይታ የገባችው ኤሊ ነበረች:: በላይዋ ድንጋይ የተጫናት እጅግ ቀርፋፋዋ ኤሊን የማይቀድም እንስሳ መቼም አይኖርም:: ምንም ብትዘገይም ኖኅ እስከመጨረሻው ጠብቆ አስገብቶ ለዘር አትርፎአታል:: የኤሊ ዘሮችም "ኖኅ ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ዳይኖሰር በጠፋን ነበር" ብለው ኖኅን ማመስገናቸው አይቀርም:: እግዚአብሔር ምንም ብትዘገይ ኤሊ ሳትገባ መርከቡን አልዘጋውም:: የኤሊ በመርከቡ መትረፍ በቤተ ክርስቲያን ልንተርፍ ተስፋ ለምናደርግ ለእኛ ትልቅ መጽናኛችን ነው:: ወዳጄ ወደ ቤተ ክርስቲያን ለመምጣት እንደ ወፍ ትበርራለህ? እንደ ሚዳቋ ትዘልላለህ? ወይንስ እንደ ኤሊ ትጎተታለህ? እግሮችህ ለመንፈሳዊ ነገር ሲሆን አቅም እያጡ አልተቸገርህም? ልብህ ቢፈልግም እንደ ኤሊዋ የተጫነህ የኃጢአት ድንጋይ አላንቀሳቅስ ብሎህ አልዘገየህም? እንዲህ ከሆነ አትጨነቅ መርከብዋ ቤተ ክርስቲያን አንተን ሳትይዝ ጥላህ ወዴትም አትሔድም:: ጉዞህን እስካላቆምህ ድረስ ትጠብቅሃለች:: እየተጎተትህም እየተሳብህም ቢሆን አንተ ብቻ ወደ ደጁ ገስግስ:: አንተ ብቻ መንገድ ጀምር እንጂ ፈጣሪ በሩን የሚዘጋው አንተ እስክትገባ ጠብቆ ነው:: ከቅዱስ ኤፍሬም ጋር እንዲህ ብለህ ለምነው :- "ብበድልህም እንኳን አሁንም በርህን እያንኳኳሁ ነው:: እየተጎተትሁም ቢሆን አሁንም የምጉዋዘው ወደ አንተ ለመምጣት ነው" የቴሌግራም #ቻናሉን_ይቀላቀሉ ቤተሰብ ይሁኑን! 👇 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
Hammasini ko'rsatish...
የደጉ ሳምራዊ መልካምነት®

ይህ ትክክለኛ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት የቴሌግራም ቻናል ነው:: (በመ/ር ሲራክ ሰሎሞን) በዚህ የቴሌግራም ቻናል:- ➮አስተማሪ እና መንፈሳዊ ፅሁፎችን ➮የቅዱሳን ገድላት ➮ መዝሙሮችን ➮መንፈሳዊ ትምህሮቶችን ያገኛሉ። የመወያያ ግሩፕ:

https://t.me/+QKiTJYGJvYpmNWM0

የዚህ ግሩፕ ዓላማ ለበጎ ምግባር ቃለ እግዚአብሔርን መማማር ነዉ::

Photo unavailableShow in Telegram
የሶርያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ሞር አግናጥዮስ ኤፍሬም ዳግማዊ በካይሮ የሚገኘውን የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ የባሕል ማዕከል ጎበኙ ! የሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ሞር አግናጥዮስ ኤፍሬም ዳግማዊ በግብፅ ካይሮ የሚገኘውን የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ የባሕል ማዕከል ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ወቅት ከቅዱስነታቸው በተጨማሪ ብፁዓን ሊቃነ የተገኙ ሲሆን ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የኮፕቲክ ባሕል ማዕከል እና የሚ ሳት ቴቪ የበላይ ጠባቂ ሊቀ ጳጳስ ቅዱስነታቸውንና ልዑካቸውን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት በማዕከሉ ቅጥር ግቢ በመገኘታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል። የቴሌግራም #ቻናሉን_ይቀላቀሉ ቤተሰብ ይሁኑን! 👇 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
Hammasini ko'rsatish...
✝ዳግም ትንሳኤ✝ 👉ክርስቶስ ተንስአ እም ሙታን                  ✝️በዐቢይ ሀይል ወስልጣን 👉አሰሮ ለሰይጣን                   ✝️አግአዞ ለአዳም 👉ሰላም                  ✝️እምይዝኤሰ 👉ኮነ                  ✝️ፍሰሃ ወሰላም ዳግም ትንሣኤ የተባለበት ምክንያት፡- በኣከባበር፥ በሥርዓት የመጀመሪውን ትንሣኤ ስለሚመስል ነው፡፡ የትንሣኤ ዕለት የሚባለው ቃለ እግዚአብሔር ሳይለወጥ፤ በሙሉ በዚህ ቀን ይደገማል፡፡ ከዚህም ሌላ ሁለት መጠሪያ ስሞች አሉት፡፡ እነዚህም “ፈጸምነ አና አግብዖተ ግብር” ይባላሉ፡፡ “ፈጸምነ” የተባለበትም፤ የሰሙነ ትንሣኤን በዓል አክብረን ፈጸምን ማለት ነው፡፡ “አግብዖተ ግብር ” የተባለበትም፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “አባ ወአቡየ ግብር ዘወሀብከኒ ፈጸምኩ... እኔ ልሠራው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር ላይ አከበርሁህ” ያለውን ከቅዳሴ በኋላ ሊቃውንት በዚህ ቀን ስለሚዘምሩት ነው፡፡ ዮሐንስ ፲፯፥፬ በተጨማሪም የሐዋርያው ቶማስ ምስክርነት የሚታሰብበት ነው፡፡ ዳግመኛ ከስምንት ቀን በኋላ ደቀ መዛሙርቱ በዝግ ቤት ሳሉ፥ ቶማስም ከእነርሱ ጋር ሳለ ደጁም ተዘግቶ ሳለ፥ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጥቶ በመካከላቸው ቁሞ እንዴት ሰነበታችሁ! አስታረቅኋችሁ” አላቸው፡፡ ሁለት ሰዓት አሳልፎ ስለመጣ “እምድኅረ ሰሙን” አለ እንጅ፥ በስምንተኛ ቀን ሲል ነው፡፡ በመጀመሪያው መገለጡ ያልተገኘው ሐዋርያው ቶማስ ትንሣኤውን አላመነም ነበርና፤ “ጣትህን ወደዚህ አምጣ እጆቼንም እይ፤ እመን እንጅ ተጠራጣሪ አትሁን” አለው፡፡ ቶማስም መለሰ “ጌታዬ አምላኬ ሆይ ” አለ፡፡ መዳሰሱን ሲያይ “ጌታዬ”፤ ማቃጠሉን ሲያይ “አምላኬ” አለ፡፡ ገቦ መለኮቱን የዳሰሰች እጁ ሕያዊት ሁና፤ ( በሕይወት ትኖራለች ) በሕንድ አገር ከታቦት ጋር በመንበሩ ላይ ያስቀምጧታል፡፡ በዓመት በዓመት በእመቤታችን በዓል በአሰተርእዮ ሊያጥኑ ሲገቡ፥ የሚሾመውን ወጥታ ቀኝ እጁን ትይዘዋለች፤ ዓመት አገልግሎ ያረፋል፤ እንዲሁ በዓመቱ የሚሾመውን ተራምዳ ትይዘዋለች፤ እንዲህ እያለች ትኖራለች፡፡ ይህም የሚያስተምረን የጌታን ተአምራት፤ የሐዋርያውን ሥልጣንና ብቃት ነው፡፡ጌታም ቶማስ ሆይ ! ብታየኝ አመንክን ? ሳያዩኝ የሚያምኑብኝ ብፁዓን ናቸው አለው፡፡ ዮሐ ፳፩፥፳፬ -፳፱ ለብርሃነ ትንሣኤው ያደረሰን አምላካችን፥ እስከ ፍጻሜ ሕይወታችን በሃይማኖት የቀናን፤ በምግባር የጸናን ያድርገን! አሜን፡፡ የቴሌግራም #ቻናሉን_ይቀላቀሉ ቤተሰብ ይሁኑን! 👇 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv                
Hammasini ko'rsatish...
የደጉ ሳምራዊ መልካምነት®

ይህ ትክክለኛ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት የቴሌግራም ቻናል ነው:: (በመ/ር ሲራክ ሰሎሞን) በዚህ የቴሌግራም ቻናል:- ➮አስተማሪ እና መንፈሳዊ ፅሁፎችን ➮የቅዱሳን ገድላት ➮ መዝሙሮችን ➮መንፈሳዊ ትምህሮቶችን ያገኛሉ። የመወያያ ግሩፕ:

https://t.me/+QKiTJYGJvYpmNWM0

የዚህ ግሩፕ ዓላማ ለበጎ ምግባር ቃለ እግዚአብሔርን መማማር ነዉ::

Repost from Mahibere Kidusan
Hammasini ko'rsatish...
ዝማሜ ትንሣኤ || በሲያትል ግቢ ጉባኤ እና ተተኪ ትውልድ ክፍል ተማሪዎች

እንኳን ለዳግማይ ትንሣኤ አደረሰንዜማ ወጥበብን ያጋሩ ቤተሰብ ይሁኑhttp://www.youtube.com/@-zemawetibebzmk7905

እንኳን ለዳግማ ትንሳኤ በሰላም በጤና በፍቅር አደረሰን አደረሳችሁ። መልካም በዓል
Hammasini ko'rsatish...
Hammasini ko'rsatish...
♦️ዳግም ትንሣኤ ማለት እንዴት ?

የጌታ ዳግመኛ መነሳት ( ዳግማይ ትንሣኤ)

እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን:: "...ሞቱን በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን..."  ሮሜ ፮÷፭ ክርስቶስ ተንስአ እም ሙታን                   በዐቢይ ሀይል ወስልጣን አሰሮ ለሰይጣን                   አግአዞ ለአዳም ሰላም                   እምይዝኤሰ ኮነ                   ፍሰሃ ወሰላም #ከትንሣኤ_እሁድ_በኋላ_ያሉ_ዕለታት_ስያሜ፡- ✝ቅዳሜ ቅዱሳን አንስት ይባላል:- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡ [   ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል !  ] " በሰንበትም መጨረሻ መጀመሪያው ቀን ሲነጋ መግደላዊት ማርያምና ሁለተኛይቱ ማርያም መቃብሩን ሊያዩ መጡ። ... መልአኩም መልሶ ሴቶቹን አላቸው። እናንተስ አትፍሩ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንድትሹ አውቃለሁና ፤ እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም ፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ። ኸ ፈጥናችሁም ሂዱና። ከሙታን ተነሣ ፥ እነሆም ፥ ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል በዚያም ታዩታላችሁ ብላችሁ ለደቀ መዛሙርቱ ንገሩአቸው። " [ማቴ.፳፰፥፩ ] የቴሌግራም #ቻናሉን_ይቀላቀሉ ቤተሰብ ይሁኑን! 👇 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
Hammasini ko'rsatish...
የደጉ ሳምራዊ መልካምነት®

ይህ ትክክለኛ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት የቴሌግራም ቻናል ነው:: (በመ/ር ሲራክ ሰሎሞን) በዚህ የቴሌግራም ቻናል:- ➮አስተማሪ እና መንፈሳዊ ፅሁፎችን ➮የቅዱሳን ገድላት ➮ መዝሙሮችን ➮መንፈሳዊ ትምህሮቶችን ያገኛሉ። የመወያያ ግሩፕ:

https://t.me/+QKiTJYGJvYpmNWM0

የዚህ ግሩፕ ዓላማ ለበጎ ምግባር ቃለ እግዚአብሔርን መማማር ነዉ::

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጓዙ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ጆሐንስበርግ መንበረ ጵጵስና ጽርሐ ጽዮን መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የተመሠረተበት ፳፭ኛ ዓመት በዓል ላይ ለመገኘት፣ቅዳሴ ቤቱን ለማክበርና በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናትን ለመባረክ እንዲሁም ምዕመናንን ለማስተማር ዛሬ ማለዳ ግንቦት 02 ቀን 2016 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጓዙ። ቅዱስነታቸው ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት፣ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የዳውሮ-ኮንታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያ ኃላፊዎችን ያካተተ ልዑካንን በመምራት ወደ ደቡብ አፍሪካ የተጓዙ ሲሆን ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ክቡር ሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅና ከቡር መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ኃይለገብርኤል ነጋሽ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በመገኘት አሸኛኘት አድርገውላቸዋል። በቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራው የልዑካን ቡድን ደቡብ አፍሪካ ጆሐንስበርግ ኦሊቨር ታምቦ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በሚደርሱበት ጊዜ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የከምባታና ሀላባ፣ ሀዲያና ስልጤ ደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች፣ካህናትና ምዕመናን ደማቅ አቀባበል ያሚያደርጉላቸው ይሆናል። Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
Hammasini ko'rsatish...