👉ክርስቶስ ተንስአ እም ሙታን
✝️በዐቢይ ሀይል ወስልጣን
👉አሰሮ ለሰይጣን
✝️አግአዞ ለአዳም
👉ሰላም
✝️እምይዝኤሰ
👉ኮነ
✝️ፍሰሃ ወሰላም
#ወደ_አባቴ_አላረኩምና_አትንኪኝ
✍🏾 ማርያም መቅደላዊት ግን ሽቱ ይዛ ጎህ ሳይቀድ ሄደች ሌሎችም ተከትለዋት ከመቃብር በደረሱ ጊዜ የጌታችንን ቅዱስ ሥጋ አጡት ‹‹ወስደውታል›› እያሉ ሲያለቅሱ መልአክ ‹‹ ሕያውን ከሙታን መካከል ለምን ትፈልጉታላችሁ ተነስቷል።
ከዚህ የለም ይልቁኑስ ገና በገሊላ ሳለ ለእናንተ እንደተናገረ አስቡ
ቃሉንም አስቡ ለደቀመዛሙርቱ ንገሯቸው አላቸው ፡፡ ሉቃ 24፡1
👉ሌሎች ሲሔዱ ማርያም መቅደላዊት ግን የደረሰበትን ሳላውቅ አልሄድም ብላ ቆማ ታለቅስ ነበር ጌታችንም ከወደኋላዋ መጥቶ ‹‹ ምን ሆነሽ ታለቅሺያለሽ ›› አላት የአትክልት ጠባቂ መስሏት ‹‹ ጌታዬን አንተ ወስደኸው እንደሆነ ሽቱ እንድቀባው ያደረክበትን አሳየኝ ›› አለቸው
‹‹ ማርያም ›› ብሎ ስሟን ሲጠራት ጌታ መሆኑን አውቃ ‹‹መምህር ሆይ›› ብላ እጅ ልትነሳው ስትቀርብ
‹‹ገና ወደ አባቴ አላረኩምና አትንኪኝ ሄደሽ ለደቀመዛሙርቴ ተነሣ ብለሽ ንገሪያቸው ›› አላት። ዮሐ20፡17
ሄዳ አብስራቸዋለች ጴጥሮስና ዮሐንስ እየሮጡ መጥው መግነዙን እንጂ እሱን አላገኙትም ‹‹ በእውነት ተነስቷል ›› እያሉ ተመለሱ፡፡
👉ሰውን ወዳጅ ኢየሱስ ክርስቶስ መቅደላዊት ማርያምን አትንኪኝ ያላት ጠልቷት ወይም ተጸይፏት አይደለም፡፡
👉ትንሣኤውን ከሰው ልጆች ቀድማ እንድታይ የፈቀደላት ስለወደዳት ነው፡፡
#ታዲያ_ለምን_አትንኪኝ_አላት?
* 3 መዓልት 3 ሌሊት በከርሰ መቃብር አድሬ እነሳለው ብሎ የተናገረውን ስለረሳች ስለ እምነቷ ማነስ ሊገስጻት ፈልጎ ነው።
ለመላእክት ስለምን ታለቅሺያለሽ ሲላት ጌታዬን ወስደውታል አለች እንጂ ‹‹እንደተናገረው ተነስቷል›› አላለችም። ዮሐ 20፡11-13
👉 #አንድም፦ በዛው ወደ ባህሪ አባቱ የሚያርግ መስሏት እግሩን ስማ ልትሰናበተው ነበር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ግን። የማርግበት ጊዜ ገናነውና ለመሰናበት ብለሽ አትንኪኝ ሲላት ነው።
👉#አንድም፦ ሥርዓተ ክህነትን ሲመሰርት ሴቶች ካህን መሆን ሥጋወ ደሙን መፈተት እንደማይችሉ ሥርዓት ሲሰራልን ነው።
ለዚህም ማረጋገጫ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስን ግን እንዲዳስሰው የፈቀደለት ሲሆን መግደላዊት ማርያምን ግን አትንኪኝ ነው ያላት። ዮሐ 20፡26
ወዲያው ጌታ በተዘጋ ቤት እንዳሉ በማይመረመር ጥበብ በመሐከላቸው ቆሞ
‹‹ ሰላም ለክሙ ›› ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው፡፡ ምትሃት መስሏቸው ታወኩ በጦር የተወጋ ጎኑን በችንካር የተቸነከሩ እጆቹን እሮቹን አሳይቷቸው አውቀውታል።
👉መቃብሩን ሲጠብቁ የነበሩ ወታደሮች በክብር ብርሃን ተጎናጽፎ ሲነሣ አይተው ደንግጠው ወደ አይሁድ ዘንድ ሔዱና መነሳቱን የሆነውን ሁሉ ነገሯቸው፡፡ አይሁድም ‹‹ ብዙ ገንዘብ እንሰጣችኋለን ተኝተን ሳለ ደቀመዛሙርቱ ሰረቁት በሉ አሏቸው፡፡
በነግ አይሁድ ጲላጦስ ዘንድ መጥተው ‹‹ ሥጋው
ተሰርቋል ጠባቂዎቹን አስጠርተህ መርምርልን ›› አሉት።
👉 ለየብቻ ከፋፍሎ ሲመረምራቸው ግማሹ ጴጥሮስና ዮሐንስ ሰረቁት ሲሉ ሌሎች ደግሞ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ሰረቁት አሉ።
👉አስራ አንዱም መጥተው ሰረቁት ያሉም ነበሩ፡፡ ጲላጦስም ወደ መቃብሩ ሄዶ ሲያይ መግነዙን አገኘው ‹‹ ደቀመዛሙርቱ ከወሰዱትማ መግነዙንም አብረው ይወስዱት ነበር ›› አለ።
👉በእነዚህ ምክንያቶች ደቀመዛሙርቱ እንዳልወሰዱት አወቀ።
‹‹ ሞትን ያጠፋ ሞትን ድል የነሣ ጌታችን ኢየሱስ ግን አይሁድን ይህን ቀን አነሣዋለሁ እንዳላቸው፡፡ በእውነት በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፡፡
👉አንበሳ ከተኛበት ፈጥኖ እንዲነሣ ወይን ጠጥቶ የሰከረ ኃይለኛ ፈጥኖ እንዲነሣ፡፡ በመንፈስ ቅዱስና በባቱ ኃይል በራሱም ሥልጣን ፈጥኖ ተነሣ የሞት ቁራኝነትንም አጠፋ፤ ሞት ሊያዘው አይችልምና፡፡
👉የተገነዘበትንም ልብስ ትቶ ልብሰ መንግሥቱን ለብሶ ተነሣ፡፡ በተወለደም ጊዜ የናቱን ማኅተመ ድንግልና እንዳለወጠ፡፡
👉በትንሣኤውም የመቃብሩን ቁልፍ አልከፈተም፡፡ በተገነዘበትም ልብስ የመቶ አለቃውን ዐይን አዳነ፡፡ የሞተውንም ሰው አስነሣ፡፡ በመቃብርም ጲላጦስ በውስጡ በቀበረው ጊዜ ፊያታዊ ዘየማንን አስነሳው፡፡
👉እሁድ ማታም ጌታችን ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ አይሁድን ስለፈሩ ተሰብስበው ወዳሉበት ከዝግ ቤት ገባ ያረጋጋቸውና ደስም ያሰኛቸው ዘንድ፡፡
👉ጌታችን ኢየሱስም ቸር አላቸውን አትፍሩ አትደንግጡ እኔ ነኝ አላቸው፡፡ እነሱ ግን ምትሐት የታያቸው መስሏቸው ፈጽመው ፈሩ፡፡
👉ጌታችን ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱን ምን ያስደነግጣችኋል እንደዚህ ያለ ሐሳብ በልቡናችሁ ለምን ያድራል አላቸው፡፡ እጄንም እግሬንም ዳሳችሁ እዩ፡፡
👉ለምትሐት በኔ እንደምታዩት ሥጋ ዐጥንት የለውምና፡፡ ይህን ብሎ የተወጋ ጎኑን የተቸነከሩ እጆቹንና እግሮቹ አሳያቸው ደቀመዛሙርቱም ጌታችንን ባዩት ጊዜ ደስ አላቸው፡፡››
#ቻናሉን_ይቀላቀሉ?
☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv