ru
Feedback
የደጉ ሳምራዊ መልካምነት®

የደጉ ሳምራዊ መልካምነት®

Открыть в Telegram

ይህ ትክክለኛ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት የቴሌግራም ቻናል ነው:: /በመምህር ሲራክ ሰሎሞን/ በዚህ የቴሌግራም ቻናል:- ➮አስተማሪ እና መንፈሳዊ ፅሁፎችን ➮የቅዱሳን ገድላት ➮ መዝሙሮችን ➮መንፈሳዊ ትምህሮቶችን ያገኛሉ። የመወያያ ግሩፕ: https://t.me/+QKiTJYGJvYpmNWM0 የዚህ ግሩፕ ዓላማ ለበጎ ምግባር ቃለ እግዚአብሔርን መማማር ነዉ::

Больше
1 127
Подписчики
+424 часа
+67 дней
+1730 день

Загрузка данных...

Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
июль '26
июль '26
+40
в 0 каналах
июнь '26
+60
в 0 каналах
Get PRO
май '26
+45
в 0 каналах
Get PRO
апрель '26
+42
в 0 каналах
Get PRO
март '26
+48
в 0 каналах
Get PRO
февраль '26
+59
в 0 каналах
Get PRO
январь '26
+28
в 1 каналах
Get PRO
декабрь '25
+63
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '25
+63
в 2 каналах
Get PRO
октябрь '25
+41
в 1 каналах
Get PRO
сентябрь '25
+22
в 1 каналах
Get PRO
август '25
+40
в 0 каналах
Get PRO
июль '25
+24
в 0 каналах
Get PRO
июнь '25
+31
в 0 каналах
Get PRO
май '25
+14
в 0 каналах
Get PRO
апрель '25
+44
в 0 каналах
Get PRO
март '25
+27
в 0 каналах
Get PRO
февраль '25
+28
в 1 каналах
Get PRO
январь '25
+20
в 1 каналах
Get PRO
декабрь '24
+28
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '24
+51
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '24
+33
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '24
+36
в 0 каналах
Get PRO
август '24
+63
в 0 каналах
Get PRO
июль '24
+25
в 0 каналах
Get PRO
июнь '24
+25
в 1 каналах
Get PRO
май '24
+16
в 0 каналах
Get PRO
апрель '24
+11
в 0 каналах
Get PRO
март '24
+15
в 0 каналах
Get PRO
февраль '24
+17
в 0 каналах
Get PRO
январь '24
+33
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '23
+14
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '23
+23
в 2 каналах
Get PRO
октябрь '23
+15
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '23
+28
в 0 каналах
Get PRO
август '23
+33
в 0 каналах
Get PRO
июль '23
+18
в 0 каналах
Get PRO
июнь '23
+28
в 0 каналах
Get PRO
май '23
+18
в 0 каналах
Get PRO
апрель '23
+32
в 0 каналах
Get PRO
март '23
+20
в 0 каналах
Get PRO
февраль '23
+46
в 0 каналах
Get PRO
январь '23
+38
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '22
+43
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '22
+31
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '22
+33
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '22
+29
в 0 каналах
Get PRO
август '22
+60
в 0 каналах
Get PRO
июль '22
+33
в 0 каналах
Get PRO
июнь '22
+18
в 0 каналах
Get PRO
май '22
+23
в 0 каналах
Get PRO
апрель '22
+58
в 0 каналах
Get PRO
март '22
+38
в 0 каналах
Get PRO
февраль '22
+33
в 0 каналах
Get PRO
январь '22
+30
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '21
+23
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '21
+30
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '21
+51
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '21
+103
в 0 каналах
Get PRO
август '21
+90
в 0 каналах
Get PRO
июль '21
+51
в 0 каналах
Get PRO
июнь '21
+13
в 0 каналах
Get PRO
май '21
+32
в 0 каналах
Get PRO
апрель '21
+362
в 0 каналах
Дата
Привлечение подписчиков
Упоминания
Каналы
22 июля+2
21 июля+4
20 июля+1
19 июля0
18 июля+4
17 июля+3
16 июля+3
15 июля+2
14 июля+3
13 июля0
12 июля+7
11 июля+1
10 июля+1
09 июля0
08 июля+2
07 июля+1
06 июля+1
05 июля+1
04 июля+2
03 июля0
02 июля+2
01 июля0
Посты канала
#ንስሐ ​"የሰው አይን ሊያይህ ይችላል፣ የሰውም አንደበት ሊወቅስህ ይችላል፤ ነገር ግን ከገዛ ሕሊናህ የምታመልጥበት ምንም ስፍራ የለም። ንስሐ ማለት የሕሊናህን ዳኝነት በእግዚአብሔር ምሕረት መፍታት
#ንስሐ ​"የሰው አይን ሊያይህ ይችላል፣ የሰውም አንደበት ሊወቅስህ ይችላል፤ ነገር ግን ከገዛ ሕሊናህ የምታመልጥበት ምንም ስፍራ የለም። ንስሐ ማለት የሕሊናህን ዳኝነት በእግዚአብሔር ምሕረት መፍታት እንጂ የኃጢአትህን እዳ በራስህ ላይ መደርደር አይደለም።" #ቅዱስ_አምብሮስ የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

2
#ራስህን_ጠይቅ ቤትህ ውስጥ ከፍተህ የረሳኸው ባንቧ ቢኖርና ድንገት ሌሊት ከእንቅልፍህ ስትነቃ መሬቱ እንዳለ በውኃ ተጥለቅልቆ ብታገኝ በቅድሚያ ምን ታደርጋለህ? የፈሰሰውን ውኃ ለመጥረግ ወይስ የሚፈሰውን ቧንቧ ለመዝጋት ነው የምትቸኩለው? ቧንቧውን ሳትዘጋ መሬት ላይ ያለውን ውኃ ለማፈስ ብትሞክር ትርፉ ድካም ነው። ቀኑን ሙሉ ስትዝቅ ብትውል ቤትህ የሞላውን ውኃ አታጎድልም። እናስ? ቧንቧውን ዝጋዋ! በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ መፍትሔ በማታገኝበት ነገር ላይ ጊዜህን አታባክን። ለዚህ የሚዳርገኝ መነሻው ምክንያት ምንድን ነው? ብለህ ራስህን ጠይቅ። አእምሮህ ውስጥ የሞሉትን ክፋቶች ከመቁጠር በላይ እነዚያ ክፋቶች የገቡበትን አንድ ቀዳዳ ወይም ሽንቁር ለማወቅ ጣር። እርሱን ያወቅኸው ቀን ለችግርህ ትልቁን መፍትሔ አብረህ ታገኛለህ። ያን ቀዳዳ ከዘጋህ ወይም ምንጩን ካደረቅኸው የቀረው ቀስ እያለ ተኖ መጥፋቱ አይቀርም። ከመውደቅህ በላይ የውድቀትህ ምክንያት ያስጨንቅህ። ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇🏽👇👇🏽       •➢ ሼር // SHARE Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
129
3
#ሰድበውኛልና_ልበቀላቸው_አትበል አንድ ሐኪም አእምሯቸውን የሳቱ ሰዎች ቢሰድቡት፥ ስድባቸውን ከቁም ነገር አይቆጥረውም፡፡ እንዲህ አእምሯቸውን እንዲስቱ ያደረጋቸውን ምክንያት ያስወግድላቸው ዘንድ ይተጋል እንጂ፡፡ ''ሰድበውኛል'' ብሎ የራሱን ጥቅም አያይም፤ የሕሙማኑን እንጂ፡፡ በጥቂቱም ቢኾን ሻል ካላቸውና ራሳቸውን መግዛት የሚችሉ ከኾነም እጅግ ደስ ይሰኝባቸዋል፡፡ ውስጡ በፍጹም ሐሴት ይሞላል፡፡ መድኃኒት መስጠቱን በፊት ከሚያደርግላቸው ይልቅ ተግቶ ይሰጣቸዋል፡፡ ''ከዚህ በፊት ሰድበውኛልና ልበቀላቸው'' ብሎ በፍጹም አያስብም፡፡ ይበልጥ እንዲጠቀሙና ወደ ቀድሞ ጤናቸው ይመለሱ ዘንድ ተግቶ ይሠራል እንጂ፡፡ "እግዚአብሔርም እንደዚህ ነው፡፡ ምንም እንኳን እጅግ ጥልቅ በኾነ ኃጢአት ውስጥ ብንወድቅም፥ ኹሉንም ነገር የሚያደርገው እኛን ከመቅጣት አንጻር አይደለም፤ የሚቀጣን ስለ ሠራነው የኃጢአት ዓይነት አይደለም፡፡ ከዚህ ሕመማችን እንድንፈወስ ብሎ ነው እንጂ፤ በዚሁ መንገድ ሊመለሱ ይችላሉ ብሎ በማሰብ ነው እንጂ፡፡" የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇👇🏽👇 ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
238
4
#እኔ_የምፈልገው_የቅርጫት_ውሃ_ነው፡፡ ✍🏽👉🏼በአንድ ተራራማ ስፍራ እርሻ በማረስ ከልጅ ልጁ ጋር የሚኖር አንድ ሽማግሌ ነበር፡፡ ይህ ሽማግሌ ዘወትር ፀሐይ ብርሃኗን ስትፈነጥቅ እየተነሳ መጽሐፍ ቅዱስን ያነባል፡፡ የልጅ ልጁ የአያቱን ተግባር ይከታተል ስለነበር እሱም ያያቱን ፈለግ በመከተል ጠዋት ጠዋት እየተነሳ መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ጀመረ፡፡ አንደ ቀን ታድያ አያቱን “አባባ መጽሐፍ ቅዱስን ለማንበብ እየሞከርኩ ነበር፡፡ ነገር ግን ልረዳው አልቻልኩም ደግሞም አንብቤ እንደጨረስኩ ወዲያውኑ እረሳዋለሁ እናም እንድረዳውና እንዳልረሳው ምን ማደረግ አለብኝ?” ሲል ጠየቀ፡፡ ሽማግሌው ምንም ድምጽ ሳያሰሙ “ከሰሉን ወደ ምድጃው ጨመሩና እንካ ይሄን የከሰል ቅርጫት ይዘህ ወንዝ ውረድና ውሃ ይዘህልኝ ተመለስ” አሉት፡፡ ልጁ ትዛዙን ለመፈጸም ወደወንዝ ወርዶ ውሃውን ይዞ ሊመለስ ቢመክርም ቅርጫቱ ውሃውን እያንጠባጠበ ቤት ከመድረሱ በፊት ፈሶ አለቀበት፡፡ ሽማግሌው የልጁን ሁኔታ እያስተዋሉ “አሁን ለሁለተኛ ጊዜ ይዘህ ስትመጣ ግን ፈጠን ፈጠን ብለህ ተመለስ ብለው” ድጋሜ ላኩት፡፡ አሁንም ልጁ እንደተነገረው በፍጥነት ውሃውን ቀድቶ ሊመለስ ቢሞክርም ቤቱ ሳይደርስ ውሃው ፈሶ አለቀበት፡፡ አያቱንም “በቅርጫት ውሃ ማምጣት ስለማይቻል ሌላ መያዥ ይስጡኝና ላምጣ” ሲል ጠየቀ፡፡ ሽማግሌ አያቱም “እኔ የምፈልገው የቅርጫት ውሃ ነው፡፡ ጠንክረህ ባለመሞከርህ ነው ፈሶ ያለቀብህ” በማለት እንደገና ላኩት፡፡ በዚህ ጊዜ ልጁ በቅርጫት ውሃን ማምጣት እንደማይቻል ቢያውቅም ለአያቱ ታዛዥነቱን ለማሳየት ከበፊቱ ፈጥኖ ለማምጣት ሲሞክር ውሃው ፈሶ ስላለቀበት ባዶውን ቅርጫት እያሳየ “ተመልከት አባባ! እዲሁ ነው የምደክመው እንጅ እኮ ጥቅም የለውም” አለ፡፡ ከዚህ ጊዜ ምልልስ በኋላ ሽማግሌው “እስኪ ቅርጫቱን ተመልከተው” አሉት፡፡ ልጁ ቅርጫቱን ሲመለከት ከዚህ በፊት የማያውቀው ቅርጫት ይመስል ቅርጫቱ የተለየ ሆነበት የከሰል መያዣ እያለ በጅጉ የቆሸሸ ነበር፡፡ አሁን ግን ሙልጭ ብሎ ጸድቷል፡፡ ውስጡን ሲመለከተው ከመንጻቱ የተነሳ የበፊቱ ቅርጫት አልመስለው አለ፡፡ ስለዚህ ልጄ መጽሐፍ ቅዱስን ስታነብ የሚሆነው እደሱ ነው፡፡ ላትረዳው ትችል ይሆናል ወይም ደግሞ ያነበብከውን ሁሉንም ነገር ላታስታውሰው ትችል ይሆናል ዳሩ ግን ባነበብክ ቁጥር ለውጨኛው የሚተርፍ ውስጣዊ ንጽህና እያመጣህ መሆኑን አትዘንጋ የመንፈስ ሥራ እንደዚህ ነው በማለት አስተማሩት፡፡ የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇👇🏽👇 ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
317
5
እንኳን ለአጋእዝተ ዓለም #ሥላሴ እና ለቅዱሳን አበው [#አብርሃም_#ይስሐቅ_#ያዕቆብ] #አባ_ሲኖዳ እና #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። #ሥሉስ_ቅዱስ =>በአንድነቱ ምንታዌ (ሁለትነት): በሦስትነቱ ርባዔ (አራትነት) የሌለበት የዘለዓለም አምላክ: የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ #እግዚአብሔር ነው:: #አብ : #ወልድ : #መንፈስ_ቅዱስ በስም: በአካል: በግብር ሦስትነት: በባሕርይ: በሕልውናና በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው:: በዚህ ጊዜ ተገኙ: በዚህ ጊዜ ያልፋሉ አይባሉም:: መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና:: ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት " #ቅድስት_ሥላሴ " እንላቸዋለን:: የሚጠላቸው (የማያምንባቸውን) አይጠሉም:: የሚወዳቸውን ግን እጽፍ ድርብ ይወዱታል:: በቤቱም መጥተው ያድራሉ:: ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም:: አባታችን #ቅዱስ_አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና በኬብሮን በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል:: ሥላሴ አኀዜ ዓለም (ዓለምን በእጁ የያዘ) ነው:: ነገር ግን በፍቅር ለሚሻው በፍቅር ይመጣል:: አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ: እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ ሥላሴን በድንኩዋናቸው አስተናገዱ:: አብርሃም እግራቸውን አጠበ:: (ወይ መታደል!) በጀርባውም አዘላቸው:: (ድንቅ አባት!) ምሳቸውንም አቀረበላቸው:: እንደሚበሉ ሆኑለት:: በዚያው ዕለትም የይስሐቅን መወለድ አበሠሩት:: #ቅድስት_ሣራ ሳቀች:: እንደ ዘንድሮ ወገኖቻችን የማሾፍ አይደለም:: ደስታና ጉጉት የፈጠረው እንጂ:: ሥላሴ "ምንት አስሐቃ ለሣራ በባሕቲታ" ብለው ነበርና በዚህም ምክንያት ነው " #ይስሐቅ" የተባለው:: ሥላሴን ያስተናገደች ድንኩዋን (ሐይመት) የድንግል እመቤታችን ማርያም ምሳሌ ናት:: በድንግል ላይ #አብ ለአጽንኦ: #መንፈስ_ቅዱስ ለአንጽሖ: #ወልድ በተለየ አካሉ ለሥጋዌ በእርሷ ላይ አርፈዋል / አድረዋልና:: እግዚአብሔርም ለአብርሃም ተስፋ በሰጠው ጊዜ:- 'በእውነት እየባረክሁ እባርክሃለሁ:: እያበዛሁም አበዛሃለሁ' ብሎ ከእርሱ በሚበልጥ በማንም ሊምል ስላልቻለ በራሱ ማለ:: እንዲሁም እርሱ ከታገሠ በሁዋላ ተስፋውን አገኘ:: (ዕብ. 6:13) => የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ: የእግዚአብሔርም ፍቅር: የመንፈስ ቅዱስም ሕብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን:: አሜን:: (ቆሮ. 13:14) Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
176
6
እንኳን ለአጋእዝተ ዓለም #ሥላሴ እና ለቅዱሳን አበው [#አብርሃም_#ይስሐቅ_#ያዕቆብ] #አባ_ሲኖዳ እና #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ✝️ሥላሴን ያስተናገደች
እንኳን ለአጋእዝተ ዓለም #ሥላሴ እና ለቅዱሳን አበው [#አብርሃም_#ይስሐቅ_#ያዕቆብ] #አባ_ሲኖዳ እና #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ✝️ሥላሴን ያስተናገደች ድንኩዋን (ሐይመት) የድንግል እመቤታችን ማርያም ምሳሌ ናት:: በድንግል ላይ #አብ ለአጽንኦ: #መንፈስ_ቅዱስ ለአንጽሖ: #ወልድ በተለየ አካሉ ለሥጋዌ በእርሷ ላይ አርፈዋል / አድረዋልና:: እግዚአብሔርም ለአብርሃም ተስፋ በሰጠው ጊዜ:- 'በእውነት እየባረክሁ እባርክሃለሁ:: እያበዛሁም አበዛሃለሁ' ብሎ ከእርሱ በሚበልጥ በማንም ሊምል ስላልቻለ በራሱ ማለ:: እንዲሁም እርሱ ከታገሠ በሁዋላ ተስፋውን አገኘ:: (ዕብ. 6:13) => የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ: የእግዚአብሔርም ፍቅር: የመንፈስ ቅዱስም ሕብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን:: አሜን:: (ቆሮ. 13:14) የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ: ለጓደኛዎ እንዲሁም ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇🏽👇👇🏽       •➢ ሼር // SHARE Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
391
7
እንኳን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን #ዼጥሮስ #ወዻውሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። =>ፍጡር ቢከብር ከእመ ብርሃን ቀጥሎ የእነዚህን ቅዱሳን ያህል የሚከብር አይኖርም:: ለቤተ ክርስቲያን ያልሆኑላት ምንም ነገር የለምና እርሷም "ብርሃኖቼ: ዐይኖቼ: ዕንቁዎቼ" ብላ ትጠራቸዋለች:: ✝️#ቅዱስ_ዼጥሮስ_ሊቀ_ሐዋርያት✝️ ✍️=>የዮና ልጅ ስምዖን ዼጥሮስ (ኬፋ) የተባለው በጌታችን ንጹሕ አንደበት ነው:: ይሔውም ዓለት (መሰረት) እንደ ማለት ነው:: ¤በቤተ ሳይዳ ከወንድሙ እንድርያስ ጋር ዓሳ በማጥመድ አድጐ ¤ሚስት አግብቶ ዕድሜው 56 ሲደርስ ነበር ጌታችን የተቀበለው:: በዕድሜውም ሆነ በቅንዐቱ: በአስተዋይነቱም መሠረተ ቤተ ክርስቲያን ተብሏል:: ለሐዋርያትም አለቃቸው ሆኗል:: (ማቴ. 16:17, ዮሐ. 21:15) 👉🏻ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተያዘባት ሌሊት ለሰራው ስሕተት ንስሃ ገብቶ ምሳሌም ሆኗል:: ቅዱስ ዼጥሮስ እንደ እረኝነቱ ሐዋርያትን ጠብቆ ለጸጋ መንፈስ ቅዱስ ሲያበቃ ከበዓለ ሃምሳ በሁዋላም ለሁሉም ሃገረ ስብከት አካፍሏል:: ምንም የርሱ ክፍል ሮሜ ብትሆንም አርድእትን ስለ ማጽናት በሁሉም አሕጉራት ዙሯል:: 👉🏻በስተእርጅናው ብዙ መከራዎችን ተቀብሏል:: አሕዛብ ግብራቸው እንደ እንስሳ ነውና በአባታችን ላይ ቀልደዋል:: እርሱ ግን ሁሉንም ታግሷል:: የቅዱሱን ታሪክ ለመናገር ከመብዛቱ የተነሳ ይከብዳልና ልቡና ያለው ሰው ሊቃውንትን ሊጠይቅ እንደሚገባ እመክራለሁ:: 👉🏻ቅዱስ ዼጥሮስ መልካሙን ገድል ተጋድሎ በ66 ዓ/ም የኔሮን ቄሳር ወታደሮች ሲሰቅሉት ለመናቸው:: "እባካችሁን? እኔ እንደ ጌታየ ሆኜ መሰቀል አይገባኝም" አላቸው:: እነሱም ዘቅዝቀው ሰቅለው ገድለውታል:: በበጐ እረኝነቱም የማታልፈውን ርስት ከነመክፈቻዋ ተቀብሏል:: በሰማዕትነት ሲያርፍም ዕድሜው ወደ 88 አካባብ ደርሶ ነበር:: ✝️=>#የቅዱስ_ዼጥሮስ መጠሪያዎች✝️ 1. ሊቀ ሐዋርያት 2. ሊቀ ኖሎት (የእረኞች / ሐዋርያት አለቃ) 3. መሠረተ ቤተ ክርስቲያን 4. ኰኩሐ ሃይማኖት (የሃይማኖት ዐለት) 5. አርሳይሮስ (የዓለም ሁሉ ፓትርያርክ) ✝️ #ቅዱስ_ዻውሎስ_ሐዋርያ ✝️ ✍️=>የቤተ ክርስቲያን መብራቷ ቅዱስ ዻውሎስን እንደ ምን ባለ ዐማርኛ እንገልጠዋለን? ¤ስለ እርሱ መናገርና መጻፍ የሚችልስ እንደ ምን ያለ ሰው ነው? ¤የዓለምን ነገር ሲጽፍ በኖረ እጄስ እንደ ምን እጽፈዋለሁ? ¤ይልቁኑስ የርሱን 14ቱን መልዕክታትና ግብረ ሐዋርያትን መመልከቱ ሳይሻል አይቀርም:: 👉🏻#ቅዱስ_ዻውሎስ ከነገደ ብንያም #ሳውል የሚባል የጠርሴስ ሰው ሲሆን ምሑረ ኦሪት: ቀናተኛና ፈሪሳዊ ነበር:: ጌታ በደማስቆ ጐዳና ጠርቶ በ3 ቀናት ልዩነት ምርጥ ዕቃ አደረገው:: ይህ የሆነው በ42 ዓ/ም: ጌታ ባረገ በ8ኛው ዓመት ነበር:: ከዚያማ ብርሃን ሆኖ አበራ:: ጨው ሆኖ አጣፈጠ:: 👉🏻ከኢየሩሳሌም እስከ ሮም: ከእንግሊዝ እስከ እልዋሪቆን (የዓለም መጨረሻ) ወንጌልን ሰበከ:: ስለ ወንጌል ተደበደበ: ታሠረ: በእሳት ተቃጠለ:: በድንጋይ ተወገረ: በጦር ተወጋ:: ባፍም በመጣፍም ብሎ አገለገለ:: በየቦታውም ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ሠራ:: ለ25 ዓመታት ቀንና ሌሊት ያለ መታከት ወንጌልን ሰበከ:: 👉🏻እርሱን የመሰሉ: እርሱንም ያከሉ ብዙ አርድእትን አፍርቶ: በ67 ዓ/ም በኔሮን ቄሳር ትእዛዝ አንገቱ ተቆርጧል:: ከ14ቱ መልዕክታቱ ባሻገር ቅዱስ ሉቃስ ወንጌልን ሲጽፍ አግዞታል:: ልክ ቅዱስ ዼጥሮስ ማርቆስን እንዳገዘው ማለት ነው:: ✝️=>የቅዱስ ዻውሎስ መጠሪያዎች✝️ 1. ሳውል (ከእግዚአብሔር የተሰጠ) 2. #ልሳነ_ዕፍረት (አንደበቱ እንደ ሽቱ የሚጣፍጥ) 3. #ልሳነ_ክርስቶስ (የክርስቶስ አንደበቱ) 4. #ብርሃነ_ዓለም 5. #ማኅቶተ_ቤተ_ክርስቲያን (የቤተ ክርስቲያን መቅረዝ) 6. #የአሕዛብ_መምሕር 7. #መራሒ (ወደ መንግስተ ሰማያት የሚመራ) 8. #አእኩዋቲ (በምስጋና የተሞላ) 9. #ንዋይ_ኅሩይ (ምርጥ ዕቃ) 10. #መዶሻ (ለአጋንንትና መናፍቃን) 11. #መርስ (ወደብ) 12. #ዛኅን (ጸጥታ) 13. #ነቅዐ_ሕይወት (የሕይወት ትምሕርትን ከአንደበቱ ያፈለቀ) 14. #ዐዘቅተ_ጥበብ (የጥበብ ምንጭ / ባሕር) 15. #ፈዋሴ_ዱያን (ድውያንን የፈወሰ) . . . =>ጌታችን እግዚአብሔር የአባቶቻችንን ብርሃን ያብራልን:: ከበረከታቸውም ያድለን:: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
201
8
እንኳን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን #ዼጥሮስ #ወዻውሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን:: የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለ+4
እንኳን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን #ዼጥሮስ #ወዻውሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን:: የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
468
9
#ሰውን_የሚጥለው_መመካቱ_ነው ✍ወንድሜ ሆይ በሥራህ ሁሉ የታመንህ ሁን አገልጋይ ባልንጅሮችህን ውደዳቸው። ንጹሑን አረጋዊ መቼም መች አክብረው። ወንድሜ ሆይ በታላላቆች መሃል አትቀመጥ። ተቀመጥ እስኪሉህ ድረስ ቁም እንጅ በሽማግሌዎች መካከል አትቀመጥ፤ በዝቀተኛው ማዕርግ ተቀመጥ እንጅ። ወንድሜ ሆይ ቁጡ ወይም አንጎራጓሪ አትሁን፤ በጸሎት ጊዜ ሐኬተኛ አትሁን፤ በጸሎት ጊዜ ምንም ተግባር ለመፈጸም ወዲያና ወዲህ አትናወጽ። እንዳትዋረድ በሊቅ በአዋቂ መሃል አትናገር። ልጄ ሆይ በጽድቅህ አትመካ፤ ራስህን አታመስግን፤ ሰይጣን ትምክሕትን እንዳያመጣብህ ራስህን በፈቃድህ አዋርድ እንጅ። በትዕቢትና ትምክሕት ሰዶምና ገሞራ ወደቁ። ከእግዚአብሔር መንገድም ተሰናከሉ። ትምክሕተኛውን መነኩሴ ፈተና ያገኘዋል፤ መንፈስ ቅዱስም ይለየዋል፤ የዲያብሎስ መንፈስም ያድርበታል። በሥራችሁ ሁሉ አትመኩ፤ ሁሉም ሰው እግዚአብሔር የሰጠውን ይሠራል እንጅ ከራሱ የሆነ ምንም የለምና። ነቢይ የተናገረውን አልሰማችሁምን? ፈጽማችሁ አትመኩ ታላላቅ ነገርንም አትናገሩ፤ ክፉ ነገርም ከአንደበታችሁ አይውጣ!!! የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ: ለጓደኛዎ እንዲሁም ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇🏽👇👇🏽                 •➢ ሼር // SHARE Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
444
10
Нет текста...
206
11
እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን:: ✍🏽=>ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነዘካርያስን ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ መናገሩ ይከብዳል:: ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል አጽፎታል:: "ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6) የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ መኖር ምን ይረቅ? ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል! እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90 የዘካርያስ 100 ደግሞ ደርሶ ነበር:: ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ: ትንቢት ለብቻው የተነገረለት (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው:: ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች:: በ6ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ በተጸነሰ ጊዜ የአርያም ንግሥት ድንግል እመቤታችን ደጋ ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት የእህትማማች ልጆች ናቸው:: የአምላክ እናቱ ስትደርስና "ሰላም" ስትላቸው መንፈስ ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ በሁዋላ በዚህች ቀን (ሰኔ 30) ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ "ዮሐንስ" ሲለው አንደበቱ ተፈትቶለታል:: =>መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ 👉የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ 👉በማሕጸን ሳለ መንፈስ ቅዱስ የሞላበት 👉በበርኀ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ 👉እሥራኤልን ለንስሃ ያጠመቀ 👉የጌታችንን መንገድ የጠረገ 👉ጌታውን ያጠመቀና 👉ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ሰው ነው:: ስለዚሕም ቤተ ክርስቲያን ነቢይ: ሐዋርያ: ሰማዕት: ጻድቅ: ገዳማዊ: መጥምቀ መለኮት: ጸያሔ ፍኖት: ቃለ ዐዋዲ ብላ ታከብረዋለች:: => ደግሞም አንተ ሕጻን ሆይ የልዑል ነቢይ ትባላለህ:: መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሔዳለህና:: እንደዚህም የኃጢአታቸው ስርየት የሆነውን የመዳን እውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ:: ይሕም ከላይ የመጣ ብርሃን በጐበኘበት በአምላካችን ምሕረትና ርኅራኄ ምክንያት ነው:: (ሉቃ. 1:76) << ወስብሐት ለእግዚአብሔር >> Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
440
12
#እግዚአብሔርማ_አልረሳኝም በጸሎት ኃይል የሚያምን አንድ ጽኑዕ ክርስቲያን ነበር፡፡ ይህም ክርስቲያን ጥሪት የሌለው ደሃ፣ የሚበላ የሚቸግረው ረሃብተኛ፣ ልብሱ በላዩ ላይ አልቆ የታረዘ ምስኪን ነው፡፡ ከእለታት አንድ ቀን በጸሎት ሕይወቱ የነበረውን ትጋት በቅርበት ያውቅ የነበረው አንድ ወዳጁ እየተቆጣ 'ቢያንስ ለረሃብህ ማስታገሻ ቁራሽ ዳቦ እንኳን ማሰጠት ካልቻለ የአንተ ጸሎት ፋይዳው ምንድር ነው? ይቅርብህ በቃ! ፈጣሪህ አይሰማህም ማለት ነው' ሲል ተስፋ በሚያስቆርጥ ቃል ተናገረው፡፡ ያም ምስኪን ክርስቲያን እንዲህ ሲል መለሰለት፦ 'እግዚአብሔርማ አልረሳኝም። ለአንዱ ሰው ከዕለት እንጀራው የበለጠ አትርፎ በመስጠት ለእኔ እንዲያካፍለኝ መልእክተኛ አድርጎት ነበር፡፡ ነገር ግን ይህን አደራ የተቀበለው ሰው ዘነጋኝ፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ሳይሆን አድራሹ ሰው ረስቶኛል!' መጻሕፍት እንደሚያስተምሩን "የዕለት እንጀራችንን ስጠን" የሚለው ጸሎት ለመነኮሳት ሲሆን "ለዕለት"፣ በዓለም ለሚኖሩ ሰዎች ሲሆን ደግሞ "ለዓመት" የሚሆን እንጀራ ስጠን ማለት ነው። ታዲያ ለምን አንዳንዶች ከዓመት የሚተርፍ ብዙ እንጀራ ሲያገኙ፣ ሌሎች ደግሞ ለዕለት እንኳን የሚሆን ቁራሽ ያጣሉ ? መቼም 'ለሰው ፊት የማያዳላ' እግዚአብሔር "አድልዎ ቢኖርበት ነው" ብለን የድፍረት ቃል በእርሱ ላይ አንናገርም። (ሐዋ 10፥34) ይህ የሆነው እንደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርት አትርፈው ያገኙ ሰዎች ምንም የሌላቸውን እንዲረዱ እና መግቦት የባሕርይው የሆነውን አምላካቸውን በጸጋ እንዲመስሉት ነው። በዚሁም ላይ በፈጠራቸው ሰዎች መካከል ያለውን የመተዛዘንና የፍቅር ትስስር የበለጠ ለማጠናከር ነው፡፡ 'የዕለት እንጀራችንን ስጠን ለዛሬ' ብለን የለመንነው አምላክ ከዓመት እንጀራችን በላይ አትርፎ የሚሰጠን፣ የሚበቃንን ያህል ተመግበን በቀረው ለሌሎች አድራሽ መልእክተኞች እንድንሆን ነው። ስለዚህ ይህን የተጣለብንን አምላካዊ አደራ ባለመወጣት ድሆችን አንበድል፤ ተማርረው ከፈጣሪያቸውም ጋር እንዲጣሉ አናድርጋቸው። የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽 ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
366
13
«ወደ_ቤታችን_ስንመለስ» ሉቃ ፩፭ ፥ ፲፩- ፳፬ ✍🏽አንድ ሰው ሁለት ልጆች ነበሩት። ከእነርሱም ታናሹ አባቱን "አባቴ ሆይ ከገንዘብህ የሚደርሰኝን ክፍል ስጠኝ" አለው። ገንዘቡንም አካፈላቸው። ከጥቂት ቀንም በኋላ ታናሹ ልጅ ገንዘቡን ሁሉ ሰብስቦ ወደ ሩቅ አገር ሄደ። ከዚያም እያባከነ ገንዘቡንም በተነ። ሁሉንም ከከሰረ በኋላ በዚያች አገር ጽኑ ራብ ሆነ እርሱም ይጨነቅ ጀመር። ሄዶም ከዚያች አገር ሰዎች ከአንዱ ጋር ተዳበለ እርሱም እሪያ (አሳማ) ሊያሰማራ ወደ ሜዳ ሰደደው። እሪያዎችም ከሚበሉት አሰር ሊጠግብ ይመኝ ነበር የሚሰጠውም አልነበረም። ወደ ልቡም ተመልሶ እንዲህ አለ "እንጀራ የሚተርፋቸው የአባቴ ሞያተኞች ስንት ናቸው? እኔ ግን ከዚህ በራብ እጠፋለሁ። ተነሥቼም ወደ አባቴ እሄዳለሁና፤ አባቴ ሆይ በሰማይና በፊትህ በደልሁ ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም ከሞያተኞችህ እንደ አንዱ አድርገኝ " እለዋለሁ አለ። ተነሥቶም ወደ አባቱ መጣ። እርሱም ገና ሩቅ ሳለ አባቱ አየውና አዘነለት ሮጦም አንገቱን አቀፈውና ሳመው። ልጁም " አባቴ ሆይ በሰማይና በፊትህ በደልሁ ወፈ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም" አለው። አባቱ ግን ባሪያዎቹን አለ "ፈጥናችሁ ከሁሉ የተሻለ ልብስ አምጡና አልብሱት ለእጁ ቀለበት ለእግሩም ጫማ ስጡ የሰባውንም ፊሪዳ አምጥታችሁ እረዱት እንብላም ደስ ይበለን ይህ ልጄ ሞቶ ነበርና ደግሞም ሕያው ሆኖአል ጠፍቶም ነበር ተገኝቶአልም። ልጁ በመመለሱ በአባቱ ጥልቅ ደስታ ሆነ። #አባት የተባለው ስለእኛ ብሎ ፍቅር አሸንፎት ወደ ምድር የመጣው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው #የጠፋው_ልጅ የተባለው እኛ ሰዎች ነን ከሞቀው ቤታችን ፍቅር ሰላም ረድኤት በረከት ከሞላበት ከአባትችን እቅፍ ከቅድስት ቤተክርስቲያን እርቀን በዚች ከንቱ ዓለም ስንባዝን ዓለም እንደ ሸንኮራ አገዳ መጣ ስጥለን አንድ ቀን መባዘናችን፣ ሀጢያት መስራታችን እና መበደላችን ታውቆን ወደ አባታችን ቤት ስንመለስ የቀድሞ ክፋታችንን የቀድሞ ሀጢያታችን የቀድሞ በደላችንን አያይም፤ እንዲህ አድርገሀል እንዲህ ሰርተሀል አይለንም። መድኃኒዓለም ደስ የሚለው ወደ ቤቱ መመለሳችን ነው። በንስሀ ሳሙና ታጥበን ፍቅር እና ሰላም ወደ አለበት ወደ ቤታችን ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን ስንመለስ በመንግስተ ሰማያት በእግዚአብሔር እና በመላእክት ዘንድ ትልቅ ደስታ ነው። በድያለው ኃጢአት ሰርቻለሁ እንዴት ትችው ወደ ወጣሁት ቤት እመለሳለሁ አንበል። ልዑል እግዚአብሔር ያለፈውን በደላችንን ያለፈውን ክፋታችንን ያለፈውን ሀጢያታችንን አይመለከትም ያለፈውን አይቆጥርብንም ገብቶን መመለሳችን ብቻ ነው የምያው አቅፎ ስሞ ይቀበለናል የቀድሞውን ማንነታችን ቀይሮ አዲስ ሰው ያደርገናል የፍቅር አምላክ ስለሆነ። ስለዚህ ዛሬ ነገ ሳንል "ንስሀ" እንገባ መቼ እንደምናልፍ አናውቀውም። የመዳን ቀን አሁን ነው እንደሚል ቅድስ መፅሐፍ ንስሀ እንገባ። ነፍስ አባት የሌለን ነፍስ አባት እንያዝ። ለንስሀ የተዘጋጀ ልቦና ለሁላችንም እንደ ቸርነቱ ያድለን። ንስሀ ገብተን ክቡር ደሙን ቅዱስ ስጋውን ተቀብለን ተስፋ የምናደርጋትን እርስት መንግስተ ሰማያትን እንድንወረስ የአምላካችን ቅዱስ ፍቃድ እንደ ቸርነቱ ይሁንልን። የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽 ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
498
14
#ተጠንቅቀህ_ታውቃለህን? ✍🏽አንድ በጣም ትልቅ ቆሻሻ የጫነ ጋሪ የሚገፋ ሰው ወደ ቤትህ መጥቶ "እባክህ በርህን ክፈትልኝና ይህን ቆሻሻ አንተ ቤት ላራግፈው?" ቢልህ፣ "ውይ የሚጥልበት ቢያጣ ነው። ባይቸገር ወደ እኔ አይመጣም ነበር" ብለህ ደጅህን ከፍተህ ታስገባዋለህ? በፍጹም፤ እንደውም "እንዴት ብታስበኝ ነው? ምነው ስታየው ቤት አልመሰለህም? እንዴት ሰው በሚኖርበት ቤት ቆሻሻ ካልደፋሁ ትላለህ? ስትል ለጠብ ትጋበዛለህ። መደፈርህ እያንገበገበህ "እምቢ!" ብለህ ትቆጣለህ። በእርግጥም ያስቆጣል። ግን ሌላ የሚከፋ ሽታ ያለው ቆሻሻን ጭኖ ለመጣ ባላጋራ እኮ በፈቃድህ የከፈትከው ቤት አለ። "የምን ቤት?" ብለህ ብትጠይቀኝ "ልብህ ነዋ" ብዬ እመልስልሃለሁ፤ "ማን ይኖርበታል?" ካልኸኝም "እግዚአብሔር ነዋ" እልሃለሁ። አንተ ለመኖሪያ ቤትህ ጽዳት የምትጠነቀቀውን ያህል የያዕቆብ አምላክ ለሚያርፍበት ኅሊናህ ተጠንቅቀህ ታውቃለህ? ሰይጣን ጭኖ የሚያመጣውን የኃጢአት ቆሻሻ ሁሉ እሺ ብለህ ወደ ልብህ በማስገባት የፈጣሪህን መቅደስ ለምን ታቆሽሻለህ? ንጹሑ እግዚአብሔር የሚያድርበትን ቤት ሊያቆሽሽ በመጣ ሰይጣን ላይ እንዴት አልተቆጣህም? ድፍረቱ ለምን አላብከነከነህም? እግዚአብሔር አንተ ልትኖርበት ከምትፈልገው ንጹሕ ቤት የበለጠ ጽዱ መቅደስ የማይፈልግ ይመስልሃል? የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽 ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
546
15
ተወዳጁ ልጅሽ እንዲመግበኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እማጸንሻለሁ እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የመድኃኒት እናት ሆይ በመዓልትም በሌሊትም አማላጅ ትሆኝኝ ዘንድ እሰግድልሻለሁ። እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ ከእርሱ የሚገኘውን ኃይልን ይሰጠኝ ዘንድ ከአንቺ ወደ ተወለደው ልጂሽ እንድትለምኝልኝ እማጸናለሁ። በመወለዱ ድኅነት የተገባሽ ሆነሻልና። በሔዋን ውድቀት ሆነ። አብ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ገብርኤል አማካኝነት ሰላምን የላከልሽ እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ሰላምታን ሰጠሽ ሰገደልሽም። ጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ሰላምታ ይገባሻል። እነሆ ትጸንሻለሽ ልጅም ትወልጃለሽ፣ ስሙንም አማኑኤል ትይዋለሽ። የልዑል ኃይል ይጸልልሻል፤ ከአንቺ የሚወለደውም ቅዱስ ነው፤ እርሱም የልዑል ልጅ ይባላል አለሽ። በተቀደሰው ስሙ ኅሊናዬን ልቡናዬን እንዲቀድስ ትለምኝው ዘንድ እማጸንሻለሁ። ንጽሕት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የሕይወት ቃል ከአንቺ ሰው ይሆን ዘንድ በሥጋ ከአንቺ ይወለድ ዘንድ የተገባሽ የመድኃኒት እናት እመቤታችን ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ከአንቺ በመዋሐዱም እኛ ዳንን። እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። በእናታቸው ማሕፀን ሕፃናትን የሚስላቸው ከአባቱ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋርም ሁሉን የፈጠረው በማሕፀንሽ የተቀረጸብሽ የብርሃን እናት ሆይ እሰግድልሻለሁ። ረቂቅ ድንቅ ምሥጢርን ዓለምንም ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣውን እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እለምንሻለሁ። በመንፈሳዊ ልደት ይወልደኝ ዘንድ ወደ እርሱ ዓለምና አዳኝ ወደ ሆነች ዕውቀት ከፍ ያደርገኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እለምንሻለሁ፣ አማጸንሻለሁ። የሕይወት መገኛ የነገሥታት ንጉሥ የባለሥልጣናቱ ባለሥልጣን የአምላኮችን አምላክ በበረት ያስተኛሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። አዳኝ ስለሆነው ስለስምሽ እንዲረዳኝ ትለምኝልኝ ዘንድም ወደ አንቺ እለምናለሁ፤ እማልዳለሁም። በማየቱ አዳምንና ከእርሱ ጋር ያሉትን ሁሉ ነጻ ያወጣውን በክንድሽ የታቀፍሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። በረቂቅ መመልከቱ እንዲመግበኝ ከሰይጣን መሰናክልም እንዲያድነኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እለምንሻለሁ፤ እማጸንሽማለሁ። ዓለማትን ሁሉ ለሚመግበው ጡትሽን ያጠባሽው የመድኃኒት እናት እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ፤ የሰማይ ኃይላት የሚመገቡትም ከእርሱ ነው። ነፍሴን በፈቃዱ ከጸጋው ይመግባት ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ። እመቤቴ ድግል ማርያም ሆይ ተወዳጁ ልጅሽ እንደ ፍጹም ፈቃዱ እንዲመግበኝ በየጊዜው በየሰዐቱ አማላጅ ሁኚኝ። ይህችም ወደ እርሱ የምትለምኝውን ልመና የተመላች መጽሐፍ ናት ። የለመንሁትን ሁሉ እርሱ ያደርግልሻልና። ኃጢአቴን ይቅር ይለኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ። ሰላምን ስለሰጠሽ ስለ አብ ከአንቺ ስለተወለደው አንቺንም ስለተዋሐደው ከአንቺም ሰው ስለሆነው ስለወልድ ፣ ስለቀደሰሽ፣ ከሦስቱ ቅዱስ ለአንዱ ማደሪያ ለመሆን እስከሚገባሽ ድረስ ስላነጻሽ ስለመንፈስቅዱስም እለምንሻለሁ። አገልጋይሽን ተወዳጁ ልጅሽ እንዲመግበኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እማጸንሻለሁ። ለዘለዓለሙ አሜን። #ቅዱስ_ባስልዮስ_ዘቂሳርያ የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
345
16
#ልጅህን_ጾምና_ጸሎት_አስለምደዉ => ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ መጽሐፍ ከገጽ 122 እስከ 124 በተጻፈዉ ምንባብ ላይ ልጅህን ጾምና ጸሎት አስለምደዉ ይላል! ሁልጊዜ ሳይሆን በሳምንት ሁለት ቀን ይኸውም ረቡዕ እና ዓርብ መጾምን እና ጸሎት ማድረስን አስለምደው፡፡ ቤተ ክርስቲያን እንዲሳለምም አድርገው፡፡ ተውኔት በሚያልቅበት በማታው ክፍለ ጊዜም ልጅህን ከተውኔት ቤት የሚወጡ ሰዎችን አሳየው፡፡ ትልልቅ ሰዎች እንደ ምን በዋዛና በፈዛዛ እንደ ተጠመዱ፣ ወጣቶችም እንደ ምን በምኞት ተቃጥለው እየወጡ እንደ ኾነ አሳየው፡፡ ልጅህንም እንዲህ ብለህ ጠይቀዉ፡- "እነዚህ ሰዎች ተዉኔት በማየታቸዉ ምን ጥቅም አገኙ? ከሐፍረት፣ ከሕሊና ወቀሳና ኵነኔ ውጭ ምንም አላገኙም፡፡" ከእንደዚህ ዓይነት ትርኢቶችና ጭፈራዎች መራቅና ራስን መጠበቅ በጎ ምኞት ብሎም ሌላ በጎ ምግባር እንዲኖር የሚያደርጉት አስተዋጽኦ እንዲሁ ቀላል እንዳልኾነ ንገረው፡፡ ዳግመኛም ከፍ ባለ ፍርሐት እና መንቀጥቀጥ መጸለይን አስተምረዉ፡፡ እንዲህ እንድታደርግ ስነግርህም ልጅ እንደዚህ ማድረግ እንደማይችል በፍጹም አትንገረኝ፡፡ ልጅ አስተዋይና ንቁ ከሆነ እነዚህን በእውነት ያለ ሐሰት ያደርጋቸዋልና፡፡ እንደ እነ ዳንኤልና ዮሴፍ የመሳሰሉ ለዚህ ማሳያ የሚሆኑን የጥንት ሰዎችም አሉ፡፡ ከዚያ በፊት ከሌሎች ከታላላቅ ወንድሞቹ ይልቅ በአባቱ ዘንድ ተወዳጅ ያደረገው ምን እንደ ሆነ አስብ፤ አሰላስልም እንጂ ዮሴፍ ዐሥራ ሰባት ዓመቱ እንደ ነበረ አትንገረኝ፡፡ “ዮሴፍ እንዲህ ያደረገው በዐሥራ ሰባት ዓመቱ ስለ ኾነ ትልቅ ነው” ብለህ ካልከኝም እኔም እንዲህ ብዬ እጠይቅሃለሁ፡- ያዕቆብ ከእርሱ ያነሰ አልነበረምን? ኤርምያስስ? ዳንኤልስ ቢኾን [ በባዕድ አገር ሆኖ ፊቱን ወደ ኢየሩሳሌም አዙሮ ሲጸልይ ] ገና ዐሥራ ኹለት ዓመቱ አልነበረምን? ሰሎሞንስ፡- “እርሱ በፊትህ በእዉነት እና በጽድቅ፣ በልብም ቅንነት ከአንተ ጋር እንደ ሄደ፤ ከአባቴ ከባርያህ ከዳዊት ጋር ታላቅ ቸርነትን አድርገሃል፡፡ ዛሬ እንደ ሆነም በዙፋኑ ላይ የሚቀመጥ ልጅ ሰጥተህ ታላቁን ቸርነትህን አቆይተህለታል፡፡ አሁንም አቤቱ አምላኬ ሆይ! እኔን ባሪያህን በአባቴ በዳዊት ፋንታ አንግሠኸኛል፡፡ እኔም መውጫዬንና መግቢያዬን የማላውቅ ታናሽ ብላቴና ነኝ፡፡ ባሪያህም ያለው አንተ በመረጥኸው ሕዝብህ ስለ ብዛቱም ይቈጠር ዘንድ በማይቻል በታላቅ ሕዝብ መካከል ነው፡፡ ስለዚህም ሰምቶ በሕዝብ ላይ መፍረድ ይችል ዘንድ መልካሙንና ክፉውንም ይለይ ዘንድ ለባሪያህ አስተዋይ ልቡና ስጠው፤ አለዚያ’ማ በዚህ በታላቅ ሕዝብ ላይ ይፈርድ ዘንድ ማን ይችላል?” በማለት ዕፁብ ድንቅ የኾነ ጸሎትን የጸለየው በዐሥራ ሁለት ዓመቱ አይደለምን? (1ኛ ነገ.3፡6-9)፡፡ ሳሙኤልስ የገዛ መምህሩን ራእይ በማየት የነገረው ገና በሕፃንነቱ ሳለ አይደለምን? (1ኛ ሳሙ.3፡17)፡፡ ስለዚህ “ልጅ ስለሆነ መጸለይ አይችልም” አትበል፡፡ በነፍሱ ሕፃን የሆነ ሰው አድጎም ቢሆን እነዚህን ነገሮች አያደርጋቸውምና፡፡ በመሆኑም ልጃችን በታላቅ ፍርሐት እና መንቀጥቀጥ ሆኖ መጸለይን ይልመድ፡፡ የቅድስና አኗኗር በሁለንተናው ላይ ይታተምበት፡፡ ከመሐላ፣ ከሚሰድቡት ሰዎች፣ የሌሎችን ስም ከማጥፋትና ከጥላቻ ከራቀ፣ ጎን ለጎንም ጾምንና ጸሎትን ገንዘብ ካደረገ እነዚህ ሁሉ ወደ ምግባር ወደ ትሩፋት ያደርሱት ዘንድ በቂ ናቸው፡፡ #በቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1 123
17
የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVy
የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
255
18
✥••●◉ #ክፉ_ሃሳብን_እንዴት_እናሸንፍ ◉●••✥ 💠 ክፉ ሀሳብ የሚባሉት ለምሳሌ የዝሙት ሀሳቦች፣ የሰውን መጥፎነት ማሰብ፣ ትንኮል እና ክፋትን ማሰብ፣ የቂምና በቀል ሀሳቦች፣ አሁን አሁን ደሞ የአብዛኛው ችግር እየሆነ የመጣው የሌሉ ነገሮችን እየፈጣጠሩ ዝምብሎ እያለሙ መደሰት (የቀን ቅዥት) ፣ የበዛ ሀዘን፣... ወዘት 💠 በአእምሮአችን የሚመላለሱ ክፉ ሀሳቦች ወደ ድርጊት ሳይደርሱ በፊት ማቆም ይገባል፤ ምናልባት ከሀሳብም አልፈን በድርጊት ለምናከናውናቸው ኃጢአቶችም እታች ያሉትን መንገዶች መከተል መፍትሄዎች ናቸው። 💠 ሰው ልተወው አልቻልኩም ይሄን ሀጥያት የሚለውን ሀጥያት በእነዚህ መንገድ መንገድ መተው ይችላል። ➊ ክፉ ሃሳብን በመልካም መተካት 🎚 ክፉ ሃሳብ ከኛ ዘንድ መጥተው እስኪያስጨንቁን እስኪያደክሙን መቆየት አይገባም አስቀድሞ ከእኛም ዘንድ እንዳይደርሱ እድል አለመስጠት ዋነኛ ማራቂያ መንገድ ነው፡፡ 🎚 ይህውም በትርፍ ጊዜ ስራ ፈቶ እግር ዘርግቶ ከመቀመጥ ይልቅ መልካም በሆኑና ለነፍሳችን ሐሴት የሚሰጡ ነገሮችን በመስራት ማሳለፍ ያስፈልጋል፡፡ 🎚 አእምሮን ዘወትር መልካም በሆኑ ተግባራት በሞላነው ቁጥር ጠላት ሰይጣን እኛን ለመጣል ሲመጣ አእምሮዋችን በመልካም ነገሮች ተይዞአልና ሊፈትነን አይቀርብም፡፡ 🎚 ሰይጣን በከፉ ሃሳብ ሊጥለን ሲያደባ ክፍት ሆኖ ሲያገኘው የሰይጣንን ሃሳብ ለመቀበል የተመቸ ይሆናል፡፡ 🎚 ክፉ ሃሳብ በአእምሮዋች ተፈጥሮም ከሆነ መልካም ነገሮችን በማሰብ መተካት ያስፈልጋል፤ አእምሮዋችን በአንድ ጊዜ ሁለት ነገሮች አእምሮዋችንበተመሳሳይ ተመስጦ (ጥልቀት) ሊያስብ አይችልም፡፡ 🎚 ስለዚህም በክፉ ሃሳብ ፈንታ የምናስበው ሃሳብ ክፉውን ሃሳብ ለማጥፋት ይችል ዘንድ ጥልቅ ሊሆን ይገባዋል፡፡ 🔘ለምሳሌ 🎚 በስራ ሊጠምዱ የሚችሉ የሚያመራምሩ ጥያቄዎች የሃይማኖት ጥያቄዎችና ትምህርቶች የቀደሙ መልካም ገጠመኞችን በማሰብ መመሰጥ የመሳሰሉት ጠቃሚ መንገዶች ናቸው፡፡ ➋ ማንበብ 💠 አንድን ነገር በተመስጦ በምናነብት ጊዜ አእምሮዋችን በንባብ ይያዝና ክፉውን ሃሳብ ይረሳዋል፡፡ 💠 መንፈሳዊ ጥያቄዎችን፣ መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ ያላነበብናቸውን መጻህፍት ለምሳሌ፦ ልብወለድ የታሪክ መጻህፍት... ማንበብ ጠቃሚ ናቸው፡፡ 💠 ከዚሁ ጋር በተያያዘም አንዳንዶቻችን ሰነፎች ነን እና ለማንበብ ስብከቶችን፣ ትምህርቶችን ማዳመጥ። ➌ በጸሎትና በስግደት 🎚 እግዚአብሔርን ክፉ ሃሳብን እንዲያርቅልን በመማጸን በፊት በመንበርከክ ስግደትን በማቅረብ መማጸን ያስፈልጋል፡፡ 🎚 ጌታ በወንጌል ✍️"እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ ወደ እኔ ኑ እኔም አሳርፋችኀለሁ" ብሎናልና ችግራችንን በጸሎት በልመና መጠየቅ አለብን፡፡ 📖ማቴ 11፥28 🎚 ዳግመኛም ቅዱስ ጳውሎስ ✍️"በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ" ተብሏልና ሁሉ ወደ ሚቻለው ጌታ ጸሎት ምልጃን ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡ 📖ፊልጵ 4፥6 ➍ በስራዎች በመጠመድ 💠 በስራዎች መጠመድ የሰውን ትኩረት ወደ አንድ በመወሰን ሃሳቡ ወደ ሌላ እንዳይሄድ ያደርጋል፤ ምንም ሳይሰሩ ተዘልሎ መቀመጥ ግን በክፉ ሃሳብ ለመውደቅ ክፍት ይሆናል፡፡ 💠 ለዚህም ነው አበው "ሰው ስራ ሲሰራ አንድ ሰይጣን ይፈትነዋል፤ ሳይሰራ ተዘልሎ ሲቀመጥ ግን በብዙ ሰይጣናት ይፈተናል" የሚሉት፡፡ 💠 በገዳም ያሉ አባቶችም ስራን በመስራት ከኃጢአት ለመራቅ ይጠቀማሉ "ስራ ያጣ መነኩሴ ቆቡን ቀዶ ይሰፋል" የሚለውም ምሳሌያዊ አነጋገር የገደማውያ አበውን በስራ መጠመድ ህይወት ያሳያል፡፡ ➎ ከሰው ጋር በማውራት 🎚 ክፉ ሃሳብ ባስጨነቁን ጊዜ ከወዳጆቻችን ጋር ስለ ልዩ ልዩ ጉዳዮች በማውራት ክፉውን ሃሳብ መርሳት ይቻላል፤ እያወሩ ማሰብ አይቻልምና፤ ራስን በማዝናናት በመጻፍ በማንበብ ክፉ ሃሳብን መርሳት ይቻላል፡፡ በሕይወታች የሚመጡብን ክፋ ሃሳቦች አምላከ ቅዱሳን ያርቅልን፤ የእናቱ ምልጃና ጸሎት ይጠብቀን:: ወስብሐት ለእግዚአብሔር ይቆየን! Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
567
19
ድኻ ነኝ የምትለኝ ለምንድን ነው? ሌሎች ሰዎችን ከማያድን ክርስቲያን በላይ የከፋ ምንም የለም፡፡ አንተ ሰው! ድኻ ነኝ የምትለኝ ለምንድን ነው? ኹለት ዲናር የጣለችዋ ሴት ትፋረድባሃለች፡፡ ከምናምንቴ ቤተሰብ እንደ ተወለድክ የምትነግረኝስ ለምንድን ነው? ሐዋርያትም ምናምንቴዎች ነበሩ፤ ነገር ግን ታላላቅ መኾን ተችሏቸዋል፡፡ አለመማርህን ሰበብ አድርገህ አትንገረኝ፤ ሐዋርያትም ያልተማሩ ነበሩና፡፡ ባሪያ ብትኾንም እንኳ፣ ስደተኛ ብትኾንም እንኳ ሥራህን መሥራት ይቻልሃል፤ ሌሎችን መርዳት ይቻልሃል፤ ሰዎችን ማዳን ይቻልሃል፥ አናሲሞስም እንደ አንተ ዓይነት ሰው ነበርና (ፊልሞ.1፥10-11)፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ምን ወዳለ ማዕረግ ከፍ እንዳደረገውና ምን ብሎ እንደ ጠራው አድምጥ፡- “በእስራቴ ስለ ወለድሁት፡፡” ወዳጄ ሆይ! እኔ እንኳን ሕመምተኛ ነኝ ብለህ አትንገረኝ፤ ጢሞቴዎስም እንደ አንተ ዘወትር ይታመም ነበር፡፡ ፍሬ የማያፈሩ ዛፎች እንደ ምን ብርቱዎችና ተወዳጆች፣ ግዙፋንና ሐመልማላውያን እንደዚሁም ረጃጅም እንደ ኾኑ አላየህምን? የፍራፍሬ ቦታ ቢኖረን ግን ፍሬ የሚያፈሩት ሮማንንና ወይራን እንተክላለን እንጂ እነዚህ ፍሬ የማይሰጡንን ዛፎች አንተክልም፡፡ ምክንያቱም እንዲሁ ለዓይን ማረፊያ ለማየት ካልኾነ በስተቀር ሌላ ጥቅም የላቸውምና፡፡ የራሳቸውን ጥቅም ብቻ የሚመለከቱ፣ ሌሎች ሰዎችንም የማይረዱ ክርስቲያኖችም እንደ እነዚህ ዛፎች ናቸው፡፡ እንዲያውም ከእነዚህ ዛፎችም የባሱ ናቸው፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ሰዎች የሚቆረጡት ለእሳተ ገሃነም ነው፡፡ ዛፎቹ ግን ቢያንስ ቢያንስ ጠረጴዛም ወንበርም ለመሥራት ይጠቅማሉ፡፡ ለቤት መሥሪያ ይጠቅማሉ፡፡ አጥር ቅጥር ኾነው ያገለግላሉ፡፡ እነዚያ አምስቱ ደናግል እንደዚህ ነበሩ (ማቴ.25፥1)፡፡ ርግጥ ነው ንጽህናቸውን የጠበቁ ነበሩ፡፡ ለሚያያቸው ኹሉ ግሩም የኾነ ጠባይ የነበራቸው ነበሩ፡፡ ሥርዓት ያላቸው ነበሩ፡፡ ይህ ኹሉ ግን ምንም አልጠቀማቸውም፡፡ ወደ እሳተ ገሃነም ከመጣ’ል አልታደጋቸውም፤ ዘይት የተባለው ምጽዋት አልነበራቸው’ማ! ክርስቶስን በነዳያን አማካኝነት የማይመግቡትም ዕጣ ፈንታቸው ጽዋ ተርታቸው ይኸው ነው የሰነፎቹ ደናግል ዕጣ! አንተ ሰው ልብ ብለህ አስተውል! እነዚህ ደናግል በግል ኃጢአታቸው አልተነቀፉም፡፡ በዝሙት ወይም በሐሰት ምስክርነት አልተወቀሱም፡፡ በፍጹም! ይልቁንም የተነቀፉትና የተወቀሱት ሌሎች ሰዎችን ባለመጥቀማቸው ነው፡፡ እንደዚህ ከኾነ ታዲያ ሰዎች ክርስቲያን ተብለው ሊጠሩ የሚችሉት በምን መመዘኛ ነው? እኮ በምን መስፈርት? አንተ ሰው እስኪ ንገረኝ! በሊጥ ውስጥ የተጨመረ እርሾ ሊጡን እንዲቦካ ካላደረገው እንዲሁ እርሾ ተብሎ መጠራት ብቻውን ምን ይረባዋል? ዳግመኛም ወደ እርሱ የቀረቡትን ሰዎች መዓዛው ካልሸተታቸውና ቤቱን ካላወደው በቀር ከርቤ በከርቤነቱ ምን በቁዔት አለው? ሌሎች ሰዎችን መርዳት አይቻለኝም ብለህ አትንገረኝ፡፡ እንዲያውም ልንገርህ፤ አንተም ስማኝ፡- አንተ በእውነት ክርስቲያን ከኾንክ ሌሎች ሰዎችን አለመርዳት የማይቻል ነው፡፡ ዕጣን መዓዛ እንዲኖረው፣ እርሾም ሊጥን እንዲያቦካ ተፈጥሮው እንደ ኾነ ኹሉ፥ አንድ ክርስቲያንም በስም ክርስቲያን ከመባል አልፎ በእውነት ያለ ሐሰት ክርስቲያን ከኾነ ሌሎች ሰዎችን መርዳት መቻሉ፣ ሌሎችን የሚጠቅም ሥራ መሥራቱ ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነው፡፡ ስለዚህ አይኾንልኝም፤ አይቻለኝም በማለት እግዚአብሔርን አታማርር፡፡ ፀሐይ ብርሃኗን በእኔ ላይ ማብራት አይቻላትም ካልክ ፀሐይን እየሰደብካት ነው፡፡ ልክ እንደዚሁ አንድ ክርስቲያንም ሌሎች ሰዎችን ሊጠቅማቸው አይችልም የምትል ከኾነ እግዚአብሔርን እየሰደብክ [ሎቱ ስብሐትና] ሐሰተኛም እያደረግኸው ነው፡፡ ምክንያቱም አንድ ክርስቲያን ሌሎች ሰዎችን ካለመርዳትና ካለመጥቀም ይልቅ ፀሐይ ሙቀትና ብርሃን ባትሰጥ ይቀላል፡፡ እንደዚህ ከሚኾን ብርሃን ወደ ጨለማ መቀየር ይቀላል፡፡ እናስ? እና’ማ አይቻለኝም አትበለኝ፡፡ የማይቻለው መርዳት አለመቻል ነውና፡፡ አይኾንልኝም እያልክ በከንቱ እግዚአብሔርን አታማርር፡፡ ሕይወታችንን በአግባቡና በሥርዓቱ የምንመራ ከኾነ እነዚህን ነገሮች ኹሉ በቀላሉ ማድረግ ይቻለናል፤ እነዚህ ነገሮች ሊደረጉ ግድ ነው፡፡ በመቅረዝ ላይ የተቀመጠ ሻማ ብርሃኑን መደበቅ እንደማይቻለው ኹሉ ክርስቲያንም የእውነት ክርስቲያን ከኾነ ብርሃኑም መሸሸግ አይቻለውም፡፡ ስለዚህ እውነተኞች ክርስቲያኖች ከኾንን ሌሎች ሰዎችን መርዳት መጥቀምም ችላ አንበል፡፡ Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
339
20
#ቅዱስ_ባሕራን_ቀሲስ ✍🏽የደጋግ ክርስቲያኖች ግን የድሆች ልጅ: ¤=> በሕጻንነቱ በግፍ ወደ ባሕር የተጣለ: ¤=> በእግዚአብሔር ጥበብ አድጎ የግፈኛውን ንብረት የወረሰ: ¤=> በመልካም ትዳር በቅ
#ቅዱስ_ባሕራን_ቀሲስ ✍🏽የደጋግ ክርስቲያኖች ግን የድሆች ልጅ: ¤=> በሕጻንነቱ በግፍ ወደ ባሕር የተጣለ: ¤=> በእግዚአብሔር ጥበብ አድጎ የግፈኛውን ንብረት የወረሰ: ¤=> በመልካም ትዳር በቅስና ያገለገለ: ¤=> ምጽዋትን ያዘወተረ: አብያተ ክርስቲያናትን ያሳነጸ ደግ ክርስቲያን ነው:: ¤=> በዚህች ቀን አርፎ ቅዱስ ሚካኤል ወዳጁ በዕረፍተ ገነት አኑሮታል:: "በሰማይም ሰልፍ ሆነ:: ሚካኤልና መላእክቱ ዘንዶውን ተዋጉ:: ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ:: አልቻላቸውምም:: ከዚያም ወዲያ በሰማይ ሥፍራ አልተገኘላቸውም:: ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ወደ ምድር ተጣለ::" (ራዕይ. 12:7) አምላካችን እግዚአብሔር ከቅዱስ ባሕራን ቀሲስ በረከት ይክፈለን:: አሜን:: የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ!ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ: 👇🏽👇🏽👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
296