en
Feedback
የደጉ ሳምራዊ መልካምነት®

የደጉ ሳምራዊ መልካምነት®

Open in Telegram

ይህ ትክክለኛ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት የቴሌግራም ቻናል ነው:: /በመምህር ሲራክ ሰሎሞን/ በዚህ የቴሌግራም ቻናል:- ➮አስተማሪ እና መንፈሳዊ ፅሁፎችን ➮የቅዱሳን ገድላት ➮ መዝሙሮችን ➮መንፈሳዊ ትምህሮቶችን ያገኛሉ። የመወያያ ግሩፕ: https://t.me/+QKiTJYGJvYpmNWM0 የዚህ ግሩፕ ዓላማ ለበጎ ምግባር ቃለ እግዚአብሔርን መማማር ነዉ::

Show more
1 187
Subscribers
+124 hours
+37 days
+3730 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+11
in 0 channels
August '26
+80
in 0 channels
Get PRO
July '26
+64
in 0 channels
Get PRO
June '26
+60
in 0 channels
Get PRO
May '26
+45
in 0 channels
Get PRO
April '26
+42
in 0 channels
Get PRO
March '26
+48
in 0 channels
Get PRO
February '26
+59
in 0 channels
Get PRO
January '26
+28
in 1 channels
Get PRO
December '25
+63
in 0 channels
Get PRO
November '25
+63
in 2 channels
Get PRO
October '25
+41
in 1 channels
Get PRO
September '25
+22
in 1 channels
Get PRO
August '25
+40
in 0 channels
Get PRO
July '25
+24
in 0 channels
Get PRO
June '25
+31
in 0 channels
Get PRO
May '25
+14
in 0 channels
Get PRO
April '25
+44
in 0 channels
Get PRO
March '25
+27
in 0 channels
Get PRO
February '25
+28
in 1 channels
Get PRO
January '25
+20
in 1 channels
Get PRO
December '24
+28
in 0 channels
Get PRO
November '24
+51
in 0 channels
Get PRO
October '24
+33
in 0 channels
Get PRO
September '24
+36
in 0 channels
Get PRO
August '24
+63
in 0 channels
Get PRO
July '24
+25
in 0 channels
Get PRO
June '24
+25
in 1 channels
Get PRO
May '24
+16
in 0 channels
Get PRO
April '24
+11
in 0 channels
Get PRO
March '24
+15
in 0 channels
Get PRO
February '24
+17
in 0 channels
Get PRO
January '24
+33
in 0 channels
Get PRO
December '23
+14
in 0 channels
Get PRO
November '23
+23
in 2 channels
Get PRO
October '23
+15
in 0 channels
Get PRO
September '23
+28
in 0 channels
Get PRO
August '23
+33
in 0 channels
Get PRO
July '23
+18
in 0 channels
Get PRO
June '23
+28
in 0 channels
Get PRO
May '23
+18
in 0 channels
Get PRO
April '23
+32
in 0 channels
Get PRO
March '23
+20
in 0 channels
Get PRO
February '23
+46
in 0 channels
Get PRO
January '23
+38
in 0 channels
Get PRO
December '22
+43
in 0 channels
Get PRO
November '22
+31
in 0 channels
Get PRO
October '22
+33
in 0 channels
Get PRO
September '22
+29
in 0 channels
Get PRO
August '22
+60
in 0 channels
Get PRO
July '22
+33
in 0 channels
Get PRO
June '22
+18
in 0 channels
Get PRO
May '22
+23
in 0 channels
Get PRO
April '22
+58
in 0 channels
Get PRO
March '22
+38
in 0 channels
Get PRO
February '22
+33
in 0 channels
Get PRO
January '22
+30
in 0 channels
Get PRO
December '21
+23
in 0 channels
Get PRO
November '21
+30
in 0 channels
Get PRO
October '21
+51
in 0 channels
Get PRO
September '21
+103
in 0 channels
Get PRO
August '21
+90
in 0 channels
Get PRO
July '21
+51
in 0 channels
Get PRO
June '21
+13
in 0 channels
Get PRO
May '21
+32
in 0 channels
Get PRO
April '21
+362
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
06 September0
05 September+2
04 September+3
03 September+3
02 September+1
01 September+2
Channel Posts
#በወርሃ_#ጳጉሜን_ዙሪያ_ከምዕመናን_የተጠየቁ_ጥያቄዎች??? #የቅዱስ_ሩፋኤልን_ዓመታዊው_ክብረ_በዓል_ለምን_እናከብራለን? ✍🏽በየአመቱ ጳጉሜ ሶስት ቀን ሊቀ መላእክት የቅዱስ ሩፋኤል አመታዊ ክብረበአል እናከብራለን ይህ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ከከበሩት ቅዱሳን መላእክት ሶስተኛው ነው ። ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ ጦቢት 12፥15 ፦መላእክት ሲፈጠሩ የማይሞቱ የማይራቡ ፆታ የሌላቸው ዝንተ አለም በቅድስና ፀንተው እንዲያገለግሉ ፈፃምያነ ፈቃድ እንዲሆኑ ነው መላእክት የተፈጠሩት ከእሳት ከንፋስ ከውኃ ነው በዚህ አገልግሎታቸውም የእግዚአብሔር ና የሰውን በጎ ፈቃድ ሲፈፅሙ ይኖራሉ። :-ቅዱስ ሩፋኤል የሰላምና የጤና መልአክ ይባላል እንደ ቤተክርስቲያን አስተምህሮት በቅዱስ ሩፋኤል እላት ሰማያት የሚከፈቱበት መሆኑን በማመን ምእመናን በጳጉሜ ቀናት በሚዘንበው ዝናብ በመጠመቅ በረከትን ይሻሉ ይመኛሉ። ፦ሩፋኤል የሚለው የስሙ ትርጓሜ፦ደስ የሚያሰኝ ፣ መሀሪ፣ የዋህ፣ ቅን ቸር ማለት ነው በሰውነታችን ላይ የሚመጣውን ደዌ ሆነ ይፈውስ ዘንድ ከአምላካችን ከእግዚአብሔር ስልጣን ተሰጥቶታል በሰው ቁስል ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፍኤል ነው መ. ሔኖክ 6፥3 ለማህፀን ችግር ለሴቶች እረዳታቸው ሴት በፀነሰችበት ወቅት ቅዱስ ሩፋኤል አይለያትም ፦ቅዱስ ሩፉኤል በሰውነት ያለን ረቂቅ ርኩስ መንፈስ ያውቃል አስማንጽዮስ የተባለ ጋኔን በወለተ ራጉኤል ጭን ላይ አድሮ ባሎቿን እየገደለ ሲያሰቃያት ቅዱስ ሩፋኤል ጋኔኑን አስጨንቆ አስወጥቶላታል ጦቢት 3፥8-17 ፦እግዚአብሔር ለሩፋኤል አዛዝኤልን እጁን እግሩን አስረህ በጭለማ ውስጥ ጣለው አለው መ.ሄኖክ 3፥5-7 የቃየን ልጆች ሰይፍና ሾተል መስራትን የመንዝራ ጌጥ መቀንደብን ያስተማረ አዛዝኤል የተባለውን ጋኔን በእሳት ሰይፍ የቀጣው አስሮ ወደ ጥልቁ የጣለው ቅዱስ ሩፋኤል ነው ሄኖክ 2፥18 ፦የሰው ልጅ ከተያዘበት የኃጥያት ይፈወስ ዘንድ በአማላጅነቱና በፀሎቱ የማይለይ መላእክ ቅዱስ ሩፋኤል ነው በበሽታ ሁሉ ላይ በሰው ልጆችም ቁስል ላይ የተሾመው ቅዱስ ሩፋኤል ነው መ.ሄኖክ 10፥13 ፦የቅዱሳንን ፀሎት ከሚያሳርጉ ወደ ከበረ ወደ ገነት ወደ እግዚአብሔር ጌትነትም ከሚያገቡ ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ ጦቢት 12፥15 ፦የቅዱስ ሩፋኤል በአል የሚከበርባቸው ምክንያቶች ሁለት ናቸው እነርሱም አንደኛው በአለ ሢመቱን ምክንያት በማድረግ ሲሆን ሁለተኛው የቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት ስለሆነ ነው ይኸውም በመፃፈ በስንክሳር ስንመለከት ከእስክንድርያ አቅራቢያ በምትገኝ በደሴት የታነፀች የቤተክርስቲያኑ በከበረ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎፍሎስ ዘመን በውስጧ ተአምር የተገለፀበት የከበረችበት ነው። ለተጠየቁት ጥያቄዎች ከበቂ ማብራሪያ ጋር መልስ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv

2
እንኳን "ለወርሃ #ጳጉሜን"በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን:: #በወርሃ_#ጳጉሜን_ዙሪያ_ከምዕመናን_የተጠየቁ_ጥያቄዎች??? #በጳጉሜን_ለምን_5ቱንም_ቀን_እንጠመቃለን? ✍🏽እንደሚታወቀው ብዙዎቻችን ወርኃ ጳጉሜን እንጠመቃለን፣ ጳጉሜን የምንጠመቅበት ዋናው ምክንያት ከሊቀ መልአኩ ከቅዱስ ሩፋኤል ጋር የተያያዘ ነው፣በዚህ በጳጉሜ ወር በዓለም ላይ ያሉ ውቅያኖሶች፣ ባህሮች፣ ወንዞች፣ ኩሬዎች ጸበሎች በአጠቃላይ ሰማይ ተከፍቶ ውኃዎች በመላክእት የሚባረኩበት ስለሆነ፣ ጳጉሜን የቻልን ጸበል ቦታ ሄደን፣ ወይም በአከባቢያችን ጸበል ካለ እዛም ሄደን፣ መሄድ ባይመቸን፣ ቤታችን ውስጥ ባለው ውኃ ብንጠመቅ እንባረክበታለን ከበሽታችንም እንድንበታለን፡፡ በጳጉሜ ጸበል፣ እንኳን የሰው በሽታ፤ በሽታ ያለው እህል፣ በሽታው ይለቀዋል፣ ገበሬው ከጳጉሜ ወዲያ ነው የሚጠፋውንና የማይጠፋውን እህል የሚለየው፣ በተለይም ጳጉሜ ሦስት፣ የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በአሉ ስለሆነ፣ በዚህ ቀን ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ውኃችን የሚባርክበትና ለሰው ልጆች በፈጣሪው ፀጋ፣ ድኅነትና ፈውስ የሚያሰጥበት ቀን ስለሆነ ብንጠመቅ ከበሽታችን እንድናለን፡፡ በመፅሐፍ ቅዱስ በዮሐንስ ወንጌል በምዕ. 5:4 ላይ "አንዳንድ ጊዜ የጌታ መልአክ ወደ መጠመቂያይቱ ወርዶ፣ ውኃውን ያናውጥ ነበርና፤ እንግዲህ ከውኃው መናወጥ በኃላ በመጀመሪያ የገባ ከማናቸውም ካለበት ደዌ ጤናማ ይሆን ነበር" ይላል፣ የጌታ መልአክ "ውኃውን ያናውጥ ነበር" የተባለው ከሰማይ ወርዶ ውኃውን ይባርከው ነበር ለማለት ነው፣ ውኃውም የሚናወጠው የእግዚአብሔር መልአክ ውኃውን ሲባርከውና እና በመጠመቂያው፣ ለፈውስ ደጅ የሚጠኑት፣ ህሙማን ውኃው በመልአኩ መባረኩን የሚያውቁት ውኃው ሲናወጥ ነው፡፡ ዛሬም ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል በዓለም ላይ ያሉትን ውሃዎች ሁሉ ስለሚባርካቸው፣ ብንጠመቅባቸው እንፈወሳለን፣ ቅዱስ ሩፋኤል ብቻ ሳይሆን ሌሎች ቅዱሳን መላእክትም ውኃውን ይባርኩታል ጳጉሜ ሦስት ይህ ብቻ አይደለም ሊቀ መልአኩ ያስለመደን ነገር አለ፣ ሁል ጊዜ ጳጉሜ ሦስት ሌሊት፣ ጠዋት፣ ከሰዓት ወይም ምሽት ላይ ይዘንባል፣ ይህ ከሰማይ የሆነ የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሩፋኤል ጸበል ነው፡፡ ጳጉሜ ሦስት በዘነበው ውኃ መጠመቅ ትልቅ መታደል እና ፈውስ ነው፣ በደዌ ይሰቃይ የነበረው ኢዮብም በዚህ ሳምንት ነው ተጠምቆ ነው የዳነው፡፡ የቅዱስ ሩፋኤል እለት የዘነው ዝናብ በዕቃ ይቀዳና ይቀመጣል፣ በተቀዳው ጸበል በውኃው እህሉ ይቦካበታል፣ ቤቱ ደጁ ይረጭበታል፣ ይህም የሚሆነው የቅዱስ ሩፋኤል እለት የዘነበው ውኃ እርኩሳን መናፍስትን ስለሚያርቅ ነው፣ በጸበሉ በረከት እህሉን ያበረክትልናል፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት ሦስተኛው ነው፣ በመጀመሪያዋ እለተ ፍጥረት እግዚአብሔር መቶ ነገደ መላእክት ፈጥሮ በአሥር ከተማ ሲያኖራቸው ቅዱስ ሩፋኤል ራማ ላይ ነው ከነ ሠራዊቱ ያረፈው፣ በራማም መናብርት ተብለው ለሚጠሩት አሥሩ ነገድ አለቃ ወይም መሪ ሆኖ በእግዚአብሔር ተሹሟል፣ በኋላም መጋብያን በሚባሉ በሃያ ሦስቱ ነገድ ላይ ተሹሟል፡፡ ስለዚህ ጳጉሜ ሦስት የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ በዓሉ ነው፣ ይህንንም እራሱ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል በመጽሐፈ ጦቢት ምዕራፍ 12 ቁጥር 15 ላይ "ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ" በማለት ተናግሯል፣ የስሙንም ትርጉም ስንመለከት ሩፋኤል ማለት የእግዚአብሔር ሐኪም ማለት ነው፣ ቅዱስ ሩፋኤል "ፈታሔ ማህፀን" ስለሆነ እርጉዝ የሆኑ ሴቶችም ፀበሉን በመጠጣት፣ በሰላም ይገላገላሉ፣ በሰላም ይወልዳሉ ማለት ነው። 👉የጳጉሜ ወር ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበትም ወር ነው። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዳግም ምጽአት እንዴት እንደሚመጣ፣ እንዴት እንደሚገለጥና እንዴት ፍርድ እንደሚሰጥ የሚጠበቀውን ቀንና የዘመን መጨረሻ ዳግም ምጽአቱ የሚነገርበት ሳምንት ስለሆነ ነው። በወርሃ ጳጉሜ እለታት በቤተክርስቲያን የሚዘመረው ዝማሬ የሚቀርበው ስብሃተ እግዚአብሔር ሁሉ ስለነገረ ምጽአቱ ይናገራል። ጳጉሜ የወሮቹ መጨሻ፣ የሚመጣው አዲስ ዘመን ዋዜማ እግዚአብሔርም በዚህ ዘመን ይመጣል ተብሎ ከሚነገርባቸው ቀናት እና ዘመናት ወርሃ ጳጉሜ አንዷ እንደሆነች ቅዱሳት መፅሐፍት እና የቤተክርስቲያናችን ሊቃውንት ያስተምራሉ። ለተጠየቁት ጥያቄዎች ከበቂ ማብራሪያ ጋር መልስ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
33
3
እንኳን "ለወርሃ #ጳጉሜን"በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን:: #በወርሃ_#ጳጉሜን_ዙሪያ_ከምዕመናን_የተጠየቁ_ጥያቄዎች??? #በጳጉሜን_ጾም_ይጾማልን? #በጳጉሜን_ለምን_እንጾማለን? የጳጉሜ ወር በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ኃይማኖት የዓለም ፍጻሜ መታሰቢያ ወር ተደርጋ ትታሰባለች፣ ጳጉሜ የዓመታት መሸጋገሪያ፤ ጨለማው የክረምት ወቅት ወደ ማብቂያው እና የሚያልፍበት እንደ ሆነ ሁሉ ዳግም ምጽዓትም ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ፣ ከጊዜያው ወደ ዘላዓለማዊ መሻጋገሪያ ስለሆነ ነው ጳጉሜ የእለተ ምጽአት ምሳሌ የሆነችው፡፡ በዚህም ምክንያት የኦርቶዶክስ አማኞች የጳጉሜን ወር በሱባኤ፣ በጾም፣ በጸሎት ያሳልፋሉ በገዳም ያሉ አባቶች ጳጉሜን በዝግ ሱባኤ ያሳልፋሉ በእርግጥ ጳጉሜ ከሰባቱ አጽዋማት ውስጥ ባትካተትም፤ ጳጉሜን በግዴታ ሳይሆን በውዴታ ብንጾም የበረታን፣ ሱባኤ ብንይዝባት፣ የቻልን በተዐቅቦ ብናሳልፋት ትልቅ ጥቅም እናገኝበታለን። አንደኛ በፈቃዳችን በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት፣ በሱባኤ ብናሳልፍ ፀጋና በረከት ያሰጠናል፣ ሁለተኛው ጳጉሜ የአዲስ ዓመት መቀበያ የዋዜማ ቀናት በመሆኗ አዲሱን ዓመት በጾም፣ በጸሎት በሱባኤ ብንቀበል አዲሱ ዓመት የበረከት፣ የረድኤት ይሆንልናል ማለት ነው፡፡ አዲሱን ዓመት በተለይም በዋዜማው በጸሎት ብንቀበል አዲሱ ዓመት የበረከት ዓመት፣ ያሰብነውን ያቀድነውን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሚሳካበት ይሆንልናል፣ የገዳም አባቶቻችን የጳጉሜን ወር መንፈሳዊ ጥቅም ስለሚያውቁ በፈቃዳቸው በታላቅ ሱባኤ ሆነው ስለ አገር፣ ስለ መጪው አዲስ ዓመት መልካምነት ፈጣሪን ይማጸኑበታል፣ እኛ የአባቶቻችን ልጆች ነንና እነሱ የሄዱበትን መንገድ ተከትለን እንደ እነሱ ልንጠቀም ያስፈልጋልና ወርሐ ጳጉሜን በጾም፣ በጸሎትና ፣ በሱባኤ ብናሳልፍ እንጠቀማለን፡፡ እግዚአብሔር እንዲታረቀን፣ ምሕረቱን እንዲመልስልን፣ ወረርሽኙን እንዲያጠፋልን፣ ለቅድስት ቤተ ክርስትያናችንና ለአገራችን ሰላም እና አንድነት እንዲሰጥልን ወርሐ ጳጉሜን እንደ በፊቱ በመብላት በመጠጣት ሳይሆን በጾም በጸሎት ብናሳልፍ ጥቅሙ ለእኛው ነው፡፡ ለተጠየቁት ጥያቄዎች ከበቂ ማብራሪያ ጋር መልስ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
22
4
እንኳን "ለወርሃ #ጳጉሜን"በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን:: ❗️#በወርሃ_#ጳጉሜን_ዙሪያ_ከምዕመናን_የተጠየቁ_ጥያቄዎች??? #ወርሃ_ጳጉሜን_ለምን_በኢትዮጵያ_ብቻ_ኖረች? ✍🏽በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከነሐሴ በኋላ 13ኛ ወር የአመቱ መጨረሻና ለአዲስ አመት መሸጋገርያ ወር ጳጉሜን የምትባል #አምስት ወይም #ስድስት ቀን ከስድስት መቶ አመት/600/ አንድ ጊዜ ደግሞ #ሰባት ቀን የምትሆን ግን እንደ አንድ ወር ተብላ ትቆጠራለች፡፡ ጳጉሜ የሚለው ስያሜዋ ግን “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ መሆኑ በአበው ቃል ተነግሯል፡፡ “ኤፓጉሜኔ” ማለት ጭማሪ ማለት ነው ፡፡ በግእዝ ቋንቋችን ተውሳክ ማለት ነው፡፡ ተውሳክ ማለት ተጨማሪ ማለት ነው፡፡ “ወሰከ - ጨመረ” ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ነው፡፡አመቱንም በአራቱ ወንጌላውያን በዘመነ ማቲዎስ ፣ በዘመነ ማርቆስ ፣ በዘመነ ሉቃስ እና በዘመነ ዮሐንስ በማለት ዘመናትን በመከፋፈል ትሰይማለች። ዘንድሮ ከዘመነ ማርቆስ ወደ ዘመነ ሉቃስ መሸጋገርያ ጳጉሜ ወር ላይ እንገኛለን ። የአውሮፓውያን ወይም በጎርጎርዮስ አቆጣጠር 13ኛ ወር ወይም ጳጉሜ የሚባል ወር የላቸውም:: ነገር ግን ጳጉሜን የወር ተጨማሪ በማድረግ እኛ የወርን ቁጥር ሠላሳ ስናደርግ እነርሱ ግን ሠላሳ አንድ ብለው የሚቆጥሩት ወር አላቸው፡፡ ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ሊቃውንት ጳጉሜን የወር ተጨማሪ ሳያደርጉ የዓመት ተጨማሪ አድርገዋታል፡፡ የዓመቱንም ቀን ቁጥር ሦስት መቶ ስድሳ አምስት ቀን ከ1/4ኛ ከነሱ ብለው ደምረውታል፡፡ ሌላው ዓለም ወሮችን በ31 ፣ በ30 እና በ29 (በ28) እያደረገ ሲጠቀም እኛ ግን እንደ ኖኅ (ዘፍ. 8:1-15) አቆጣጠር ወሮችን በ30 ቀናት ወስነን: ዻጉሜንን ለብቻዋ እናስቀምጣለን:: ዻጉሜን 'ኤዻጉሚኖስ' 'ትርፍ: ጭማሪ' እንደ ማለት ስለሆነ ነው:: በቤተ-ክርስቲያናችን የጳጉሜ ወር የተለያዩ ስርዓት የሚፈፀም ሲሆን ስለ እግዚአብሔር ክብር ሊሆን እንደሚገባቸው ተረድተው ሕይወታቸውን ሙሉ ሲያለቅሱና ሲጸልዩ የነበሩ ቅዱሳን አባቶቻችን እነ ቅዱስ ዮሐንስን የምንዘክርበት ሳምንት ነው ። የጳጉሜ ወር ለንስሀ የተጨመረችልን ዕድሜ ትመስላለች ተረፈ አመት ናትና ። እግዚአብሔር የፈቀደላቸው የተዋህዶ ቤተሰቦች ጸበል በመጠመቅ እንዲሁን ጾምና ጸሎት ሱባዔም በመያዝ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ይሰነብታሉ ለፍርድ በምትመጣበት በዚያች አስፈሪ ቀን በክብር ለመቆም አብቃን እያሉ ይማጸናሉም የጳጉሜን ወር የጌታ ምጽአት መምጫ ናት ተብሎ ይጠበቃልና ። ጳጉሜ ወር በስፋት ስለ ዳግም ምጽዓት ይታሠባል:: ጳጉሜ በገባ በሦስተኛው ቀን( ጳጉሜ 3 ) " የማቴዎስ ወንጌል ምራ . 24 " ሙሉውን ይነበባል የነገረ ምጽአት ታሪክን የሚያስረዳ ነውና ይሰበካል ። ምጽአት ማለት የጌታን መምጣት የሚያረዳ በመሆኑም ቤተ ክርስቲያን የጌታን ምጽአት ከዓመት ሁለት ግዜ ታስታውሳለች ይህዉም በጳጉሜና ወርና በጌታ በጾሙ እኩሌታ (ለደብረ ዘይት )ነው ። መዝሙረ ዳዊት 49 ፣ 2-4 ስለ ነገረ ምጽአት ይነግረናል:: ☞እግዚአብሔር አዝማናትን የፈጠራቸው ለሰው ልጆች ጥቅም መሆኑ ይታወቃል:: እርሱ ባወቀ: በረቂቅ ሥልጣኑ ዓለምን ፈጥሮ: ጊዜያትን እንዲከፍሉ ብርሃናትን (ፀሐይ: ጨረቃ: ከዋክብትን) ፈጥሮልናል:: ☞ጊዜያትንም በደቂቃ: በሰዓት: በቀን: በሳምንት: በወር: በዓመታት: በኢዮቤልዩ: በክፍላተ ዘመናት እንድንቆጥር ያስማረንም እርሱ ነው:: የሰከንድ 540,000 ክፋይ ከሆነችው 'ሳድሲት' እስከ ትልቁ ቀመር (532 ዓመት) ድረስ እርሱ ለወደዳቸው እንዲያስተውሉት ገልጧል:: ☞በየዘመኑም በቅዱስ ድሜጥሮስ: በቅዱስ ዮሐንስ_ዘደማስቆ: በቅዱስ አቡሻኽር እና በሌሎቹም አድሮ መልካሙን አቆጣጠር አስተምሯል:: ሃገራችን ኢትዮዽያ ደግሞ የ13 ወራት የፀሐይ ጸጋ (thirteen months sun shine) ያላት: 4ቱ ወቅቶች የተስማሙላት ናት:: ለተጠየቁት ጥያቄዎች ከበቂ ማብራሪያ ጋር መልስ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
27
5
እንኳን ከዘመነ ማርቆስ (2018 ዓ.ም) ወደ ዘመነ ሉቃስ (2019 ዓ.ም) አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። በጳጉሜን_ዙሪያ_ከምዕመናን_ለተጠየቁ_ጥያቄዎች_የተሰጠ_መልስ!!! ❇️#ጳጉሜን_ማለት_ምን_ማለት_ነው? በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ከነሐሴ በኋላ ጳጉሜን አምስት /ስድስት/ ቀን አለች። ይኸውም ዐሥራ ሦስተኛ ወር ያሰኛታል። ጳጉሜን የሚለው ስያሜ "ኤጳጉሜን" ከሚለው የግረክ ቃል የወጣ ሲሆን "ኤጳጉሜን " ማለት ጭማሪ ማለት ነው። በግእዝ ተውሳክ ማለት ነው። ተውሳክ ማለትም ጨመረ ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ነው። በሌላ አገላለጽ ጳጉሜን፦ ዓመቱ በዕለት ሲለካ የተረሳ: የተረፈ ማለት ነው፡፡ #ጳጉሜ ማለት ጭማሪ ማለት ነው። ይህም የሆነበት ምክንያት በየዓመቱ መጨረሻ ላይ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር 13 ወር ተብላ ተጨምራለች ። በ3ቱ ዘመናት ማለትም በዘመነ ማቴዎስ፣ በዘመነ ማርቆስ እና በዘመነ ሉቃስ መግቢያ ላይ 5 ቀን ስትሆን በዘመነ ዮሐንስ መጀመሪያ ላይ ማለትም በ4ቱ ዘመናት ውስጥ በ 1 ዘመን ብቻ 6 ቀን ሆና ትቆጠራለች። በየአራት አመቱ ጳጉሜ ስድስት ቀን ትሆናለች! ይህ ማለት በዘንድሮ ከ2018 ዓ.ም ወደ 2019 ዓ.ም የመሸጋገሪያ ዓመት አምስት ቀን ሆናለች:: ከ#ዘመነ_ማርቆስ_ወደ_ዘመነ_ሉቃስ_ ልንሸጋገር ዋዜማው ላይ እንገኛለን ማለትም ዘንድሮ ጳጉሜ አምስት ቀናትን ታስቆጥራለች ማለት ነው። ጳጉሜ የወር ስም ሆኖ በነሐሴ እና በመስከረም ወራት መኻል የሚገኝ ከአስራ ሦስቱ ኢትዮጵያ የወራት አቆጣጠር ውስጥ የመጨረሻው እና አሥራ ሦስተኛው (፲፫ ኛው) የወር ስም ነው። ከላይ እንዳየነው «ጳጉሜ» የሚለው ስም ምንጩ ከግሪክ ቋንቋ ሲሆን ቀሪ ዕለታት ማለት ነው። ኢትዮጵያ ሀገራችንም በዓለም ብቸኛዋ የ13 ወራት ጸጋ ባለቤት ናት። ይህን የፓጉሜን ወር በኢትዮጵያውያን ዘንድ የምህረት ወር ተብሎ ይታመናል። ወደ አዲስ ዓመት መግቢያ (መሸጋገርያ) ወርም ነው። ጳጉሜ የክረምቱ ማብቂያ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም በመጨረሻው ዘመን መከራ የሚበዛበት የዚህ ዓለም ማብቂያ ናት፡፡ ወርኃ ጳጉሜ አዲሱን ዓመት ለመቀበል የዝግጅት ጊዜ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ጻድቃን አዲሲቷን ምድር (መንግስ ሰማያትን) ለመውረስ ተዘጋጅተው ”ኑ የአባቴ ብሩካን ዓለም ሳይፈጠር የተዘጋጀላችሁን መንግስት ውረሱ” የሚባሉባት ናት፡፡ በዚህም የተነሣ ብዙ ምእመናን በጾምና በጸሎት (በሱባዔ) ያሳልፏታል፡፡ በተለይም በቅዱስ ሩፋኤል ዕለት ሰማያት የሚከፈቱበት (ርኅዎተ ሰማይ) መኾኑን በማመን ምእመናን የጸሎታቸውን ማረጊያ (ማሳረጊያ) መሆኑን በማመን ከምንጊዜውም በበለጠ በእምነት ይጸልያሉ፡፡ ለተጠየቁት ጥያቄዎች ከበቂ ማብራሪያ ጋር መልስ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
29
6
እንኳን ለኢትዮጵያዊያን 13ኛ ወር "ወርሃ #ጳጉሜን" በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን:: ወርሃ_#ጳጉሜን_ዙሪያ_ከምዕመናን_የተጠየቁ_ጥያቄዎች??? 1. #ጳጉሜን_ማለት_ምን_ማለት_ነው? 2. #ወ+2
እንኳን ለኢትዮጵያዊያን 13ኛ ወር "ወርሃ #ጳጉሜን" በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን:: ወርሃ_#ጳጉሜን_ዙሪያ_ከምዕመናን_የተጠየቁ_ጥያቄዎች??? 1. #ጳጉሜን_ማለት_ምን_ማለት_ነው? 2. #ወርሃ_ጳጉሜን_ለምን_በኢትዮጵያ_ብቻ_ኖረች? 3. #በጳጉሜን_ጾም_ይጾማልን? #በጳጉሜን_ለምን_እንጾማለን? 4. #በጳጉሜን_ለምን_5ቱንም_ቀን_እንጠመቃለን? 5. #የቅዱስ_ሩፋኤልን_ዓመታዊው_ክብረ_በዓል_ለምን_እናከብራለን? ለተጠየቁት ጥያቄዎች ከበቂ ማብራሪያ ጋር መልስ ለማግኘት እንዲሁም የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
201
7
እንኳን ለኢትዮጵያዊያን 13ኛ ወር "ወርሃ #ጳጉሜን" በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን:: ወርሃ_#ጳጉሜን_ዙሪያ_ከምዕመናን_የተጠየቁ_ጥያቄዎች??? 1. #ጳጉሜን_ማለት_ምን_ማለት_ነው? 2. #ወ+1
እንኳን ለኢትዮጵያዊያን 13ኛ ወር "ወርሃ #ጳጉሜን" በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን:: ወርሃ_#ጳጉሜን_ዙሪያ_ከምዕመናን_የተጠየቁ_ጥያቄዎች??? 1. #ጳጉሜን_ማለት_ምን_ማለት_ነው? 2. #ወርሃ_ጳጉሜን_ለምን_በኢትዮጵያ_ብቻ_ኖረች? 3. #በጳጉሜን_ጾም_ይጾማልን? #በጳጉሜን_ለምን_እንጾማለን? 4. #በጳጉሜን_ለምን_5ቱንም_ቀን_እንጠመቃለን? 5. #የቅዱስ_ሩፋኤልን_ዓመታዊው_ክብረ_በዓል_ለምን_እናከብራለን? ለተጠየቁት ጥያቄዎች ከበቂ ማብራሪያ ጋር መልስ ለማግኘት እንዲሁም የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
1
8
#ይህ_እኔን_አይመለከተኝም_አትበሉ #ወንድሞቼ ከእናንተ መካከል አንድ አይነ ሥውር ሰው ወደ ጉድጓድ ገብቶ ሊወድቅ ሲል እጁን ዘርግቶ የማይደግፈው ማን ነው? ታድያ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በልቡናቸው ታውረው ወደ ሲዖል ጉድጓድ ለዘለዓለም ሲወድቁ እንደ ምን እጃችንን የበለጠ አይዘረጋም? #ወገኖቼ በነፍስም በሥጋም የታመመ ሰውን ስታዩ "ይህ የእኔ ሥራ አይደለም የቀሳውስትና የመነኮሳት ሥራ እንጂ፤ ምክንያቱም ሚስት አለችኝ ልጆችንም አሳድጋለሁ" አትበሉ፡፡ እስኪ ምሳሌ መስዬ ልጠይቃችሁ እናንተም መልሱልኝ፡፡ አንድ ትልቅ በወርቅ የተሞላ ሳጥን ወድቆ ብታዩ "ይህ እኔን አይመለከተኝም ሌሎች መጥተው ያንሡት እንጂ" ትላላችሁን? ግራ ቀኛችሁን አይታችሁ በፍጥነት የምታነሡት አይደለምን? ይህ ወደ ዘለዓለም ጉድጓድ እየወደቀ ያለው ወንድማችሁም ከዚያ ወርቅ በላይ ውድ የእግዚአብሔር ሀብት ነውና አንሡት እንጂ የበለጠ እንዲወድቅ አትግፋት። እግዚአብሔር ይህን በተመለከተ በአፈ ያዕቆብ እንዲህ ብሏልና፡- "ወንድሞቻችን ሆይ ከእናንተ ወገን ከጽድቅ ወጥቶ የበደለ ቢኖር መክሮ አስተምሮ ከበደሉ የመለሰው ቢኖር ራሱን አንድም ወንድሙን ከሞት እንዳዳነ ይወቅ፡፡ የራሱን አንድም የወንድሙን ብዙ ኃጢአቱን እንዳስተሠረየ ይወቅ፡፡ አንድም የወንድሙን ነፍስ እንዳዳነ ይወቅ።" (ያዕ. 5፥19-20) የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
221
9
#ጥንቁቅ_ሁን ✍🏽ከሰይጣን በቀር ምንም ጠላት አይኑርህ፡፡ የሰዎችን ስህተት አትመራመር፤ የባልንጀራህ ኃጢአት አትግለጥ፡፡ የባልጀራህ ውድቀት ደጋግመህ አታውራ፡፡ በራስህ ኃጢአት ላይ ፍረድ እንጂ በ
#ጥንቁቅ_ሁን ✍🏽ከሰይጣን በቀር ምንም ጠላት አይኑርህ፡፡ የሰዎችን ስህተት አትመራመር፤ የባልንጀራህ ኃጢአት አትግለጥ፡፡ የባልጀራህ ውድቀት ደጋግመህ አታውራ፡፡ በራስህ ኃጢአት ላይ ፍረድ እንጂ በሌሎች ላይ አትፍረድ ገዢያቸው አይደለህምና፡፡ ኃጢአትን በፈጸመ ሰው ላይ ወቀሳ አታብዛ አንተም ትበድላለህና፡፡ ነገር ግን ከኃጢአቱ ይመለስ ዘንድ ረዳትና መካሪ ሁነው፡፡ ከወደቀበትም የስህተት ሥራ እንዲወጣ አበርታው፡፡ ተስፋውን በእግዚአብሔር ላይ ቢያደርግ ኃጢአቱን ልክ በእሳት ፊት እንደወደቀ ገለባ ፈጥኖ እንደሚወገድለት ንገረው፡፡ ቅዱስ፣ ጥንቁቅ፣ ግልጽና ብልህ ሁን፡፡ እርጋታን የተላበሰ ሰብእና ይኑርህ፡፡ ደስተኛ ሁን፤ ሰላምታህ በፈገግታ የታጀበ ንጹህ ይሁን፡፡ ንግግርህ የታረመ አጭርና በጨው እንደተቀመመ ጣፋጭ ይሁን፡፡ ቃላቶችህ የተመጠኑ እና ጤናሞች ሁሉም የሚረዳቸው ይሁኑ፡፡ የጓደኛህን ምስጢር አትግለጥ፤ ለሚወዱህ ሁሉ የታመንክ ሁን፡፡ ወደ ጭቅጭቅ እና ንትርክ ከመግባት ራህን ጠብቅ፡፡ የሚሰሙህ ሁሉ እንዳይጠሉህ ወደ ጠብ አትግባ፡፡ የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
252
10
#ማንነትህን_ማወቅ ተወዳጁ ወንድሜ ሆይ! ኃይለኛ ነኝ ብለህ ታስባለህን? ካሰብህ ይህን ኃይልህን ከየት አመጣኸው? አንተ አመድና ትቢያ ጎስቋላና ምስኪን ስለሆንህ ይህ ኃይል የአንተ አይደለም። ይህ ኃይል ከሌላ ሰው ያገኘኸውም አይደለም ከእግዚአብሔር እንጂ። ክብርና ምሥጋና ለእርሱ ይሁንና ኃያል እርሱ ብቻ ነው፡ ኃይልም ሁሉ የሚገኘው ከእርሱ ብቻ ነው። ያንተስ ኃይል ከእግዚአብሔር አይደለምን? ከሆነ ለምን ትታበያለህ? ለምንስ ትኩራራለህ? የእግዚአብሔርንስ ኃይል እርሱን ለማገልገል ካልሆነ ለሌላ ለምን ታውለዋለህ? ስለዚህ ሊከበር የሚፈልግ ቢኖር በእግዚአብሔር ይክበር። እርሱ ከክብር ሁሉ በላይ የሆነና ለምንከብርበት ነገር ሁሉ ምንጩ ነውና። በእግዚአብሔር ኃይለኛ ሆነህ በተፈጥሮህ ደካማ ብትሆን ከሐዋርያው ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር እንዲህ በል። "እንግዲህ የክርስቶስ ኃይል ያድርብኝ ዘንድ በብዙ ደስታ በድካሜ ልመካ እወዳለሁ። ስለዚህ ስለ ክርስቶስ በድካም በመንገላታትም በችግርም በስደትም በጭንቀትም ደስ ይለኛል፤ ስደክም ያን ጊዜ ኃይለኛ ነኝና።" 2ኛ ቆሮ 12:9-10 ✍🏽#ብፁዕ_ወቅዱስ_አቡነ_ሺኖዳ የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
177
11
እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት(ቅዱስ): ለቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ እና ለቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን: አደረሳችሁ:: ✝️ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ሐዋርያዊ ✝️ *ልደት* =>መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ: ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው:: እርሱ በክህነቱ: እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል:: +በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ ሚካኤል: ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል:: በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል:: +ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24 ቀን በ1206 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታሕሳስ24 ቀን በ1207 ዓ/ም ነው:: በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል:: ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል:: *ዕድገት* =>የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል:: ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁናም ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል:: *መጠራት* =>አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮስ ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ:: የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ:: +የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ:: "ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን:: ከዚህ በሁዋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ ሰዓትን አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ:: *አገልግሎት* =>ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ:: ያን ጊዜ ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት:: +1ኛ ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል: ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል:: +2ኛው ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር:: +ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ:: ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል:: *ገዳማዊ ሕይወት* =>ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል:: +እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት: በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26 ዓመታት አገልግለዋል:: +በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል:: *ስድስት ክንፍ* =>ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ እሥራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር:: +የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በሁዋላ ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር:: +ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ:- -በቤተ መቅደስ ብስራቱን -በቤተ ልሔም ልደቱን -በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን -በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን -በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር:: +የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ:: በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው:: +በዚያም:- -የብርሃን ዐይን ተቀብለው -6 ክንፍ አብቅለው -የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው -ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው -ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው -ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው -"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል:: *ተአምራት* =>የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው:: *ሙት አንስተዋል *ድውያንን ፈውሰዋል *አጋንንትን አሳደዋል *እሳትን ጨብጠዋል *በክንፍ በረዋል *ደመናን ዙፋን አድርገዋል:: +ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና:: *ዕረፍት* =>ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል:: Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
132
12
እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት(ቅዱስ): ለቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ እና ለቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን: አደረሳችሁ::+2
እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት(ቅዱስ): ለቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ እና ለቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን: አደረሳችሁ::
90
13
#ከሁሉ_በላይ_ትሆናለህ "ከዕለት ጉርስኽ የተረፈኽ ቢኖር ለደኻ ስጠው። . . . ክብር ይግባውና ወደ ፈጣሪ ለመቅረብ እንደ ምጽዋት ክሂል የሚሰጥ የለም። ከሥራም ወገን ወድዶ ሰጥቶ እንደመቸገር በልቡና ኅድዓት (ፀጥታ ፣ ዕረፍት ፣ ሠላም) የሚያደርግ የለም። ሰጥተኽ መጽውተኽ አጥተኽ 'አላዋቂ' ቢሉኽ ይሻልኻል። ጨብጠኽ ይዘኽ አስተዳደር ዐዋቂ ከሚሉኽ።. . . ኅብስቱን ከውሃ ጣለው ብሎ ተናግሯልና። ከውሃ የጣሉት እንዳይመለስ ፣ 'ይ 'ሰጠኛል' ብለኽ አትስጥ ሲል ነው። አንድም ኀብስቱን ከእግዚአብሔር ፊት አኑረው ሲል ነው። በፍጻሜ ዘመንኽ ዋጋኽን ታገኛለኽ። ባለጸጋውን ለይተኽ ለድኻ አትስጥ። 'ይኽ ይገባዋል ይኽ አይገባውም' አትበል። አላ ኩሉ ሰብእ ይኩኑ ዕሩያነ በኅቤከ -በምትመጸውትበት ጊዜ አስተካክለኽ መጽውት እንጂ! አስተካክለኽ በመስጠትኽ ወደ በጎ ሥራ ለማቅረብ ትችላለኽ። ምንም የበቁ ባይኾኑ ነፍስ በመብል በመጠጥ ምክንያት ወደ ክቡር እግዚአብሔር ትሳባለችና! በምጽዋት ጊዜ 'ይኽ አይሁዲዊ ነው። ይኽ ከሀዲ ነው' አትበል። 'ይኽ ነፍሰ ገዳይ ነው' አትበል። ይልቁንስ ብታስታውለው ወንድምኽ ነው እንጂ። አእምሮ አጥቶ ከሃይማኖት ተለየ እንጂ።ከበጎው ነገር ወገን ለሰው ያደረግኽ እንደኾነ መክፈልን አትውደድ።. . . መጽውተኽ ብትቸገር ክብር ይግባውና በእግዚአብሔር ቸርነት ከትካዝ ሥጋዊ ትድናለኽ! ከኹሉ በላይ ትኾናለኽ! ሰው ኹሉ ለገንዘቡ ሲገዛ እሱ ለእግዚአብሔር ይገዛልና። . . . 'በዝናም ያበቀለው በፀሓይ ያበሰለው የእግዚአብሔር ገንዘብ ነው' ብለኽ ምጽዋትኽን በትሕትና መጽውት። ጻድቃን በሚከብሩበት ጊዜ ይቅርታን ታገኛለኽ" የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
191
14
#ኃጢአት_ሰርተሃልን? በቤትህ ያለው ዳቦ ለተራበው ሰው የሚውል(ንብረቱ) ነው፥ በልብስ ማስቀመጫህ ውስጥ ያለው የማትጠቀመው ኮት የችግረኛው ገንዘቡ ነው፥ በጫማ ማስቀመጫህ ውስጥ አልፈልገውም ብለህ ሊበላሽብህ የሆነው ጫማ የደሃው ጫማ (ጫማ ለሌለው ገንዘቡ) ነው ፥ ያከማቸኸው ገንዘብ ለድሃው የሚገባው ነው.... ዛፍ በፍሬው ይታወቃል፥ ሰውም በድርጊቱ፡፡ መልካም ስራ መቼም አይጠፋም፡፡ መልካም እርዳታን የሚዘራ፥ ወዳጅነትን ያጭዳል፡፡ ደግነትን የሚተክል ፍቅርን ይሰበስባል፡፡ "ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ብቻ የለብንም፥ ነገር ግን ካነበብነው ተምረን ማደግ አለብን፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ምንም የማይጠቅም ነገር እንዳልተጻፈ ተገንዘብ፡፡ አሁንም ለጥንካሬ፣ ለመታገስ፣ለመዳን፣ለመለወጥ ጊዜ አለህ! ተኝተሃልን? ንቃ! ኃጢአት ሰርተሃልን? እንግዲያውስ  መስራቱን አቁም፡፡ ✍️ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
260
15
#ዘወትር_እግዚአብሔርን_አመስግን "መንፈሳዊ ጥበብን የምትወድ ነፍስ ዘወትር እግዚአብሔርን ታመሰግናለች፡፡ ሰው ሆይ! ሰዎች ክፉ ነገር ሲያደርሱብህ እግዚአብሔርን አመስግን፤ ያን ጊዜም ክፉው መልካም
#ዘወትር_እግዚአብሔርን_አመስግን "መንፈሳዊ ጥበብን የምትወድ ነፍስ ዘወትር እግዚአብሔርን ታመሰግናለች፡፡ ሰው ሆይ! ሰዎች ክፉ ነገር ሲያደርሱብህ እግዚአብሔርን አመስግን፤ ያን ጊዜም ክፉው መልካም ይኾንልሃል፡፡ "እንዴት?" ብለህ የጠየቅኸኝ እንደኾነም፦ "በደል የሚፈፅመው ክፉ ነገር የሚቀበለው ሳይኾን ክፉ ነገር የሚያደርሰው ሰው ነውና" ብዬ በእውነት ያለ ሐሰት እመልስልሃለሁ፡፡ ስለዚህ ዘወትር እግዚአብሔርን አመስግን፡፡ ብትታመምም እግዚአብሔርን አመስግን፤ ሀብት ንብረት ብታጣም አመስግን፤ በሐሰት ቢከሱህም አመስግን፡፡ እንደ ነገርኩህ ተጎጂዎቹ ክፉ ተቀባዮች ሳይኾኑ ክፉ አድራሾች ናቸውና፡፡" የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
501
16
እንኳን አምላክን በድንግልና ለወለደች ለእናታችን ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። #ድንግል_ማርያም_በሰማይ_የታየች_ታላቅ_ምልክት! =>በሰማይ ያለችውን ድን
እንኳን አምላክን በድንግልና ለወለደች ለእናታችን ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። #ድንግል_ማርያም_በሰማይ_የታየች_ታላቅ_ምልክት! =>በሰማይ ያለችውን ድንግል ማርያምን ቅዱስ ዮሐንስ ታላቅ ምልክት በሰማይ ዐየሁ በማለት ይገልጻታል። "ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ፤ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራሷም ላይ የዐሥራ ኹለት ከዋክብት አክሊል የተቀዳጀች አንዲት ሴት ነበረች።" ራዕይ ፲፪: ፩። ነቢየ ልዑል ኢሳይያስ በትንቢት "ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅንም ትወልዳለች፤ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች" ብሎ የተናገረላት ድንግል ማርያም ናት። ኢሳ ፯:፲፬። የነቢዩን ቃል የተረጎመው ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ ያየውን ጽፏል። ምልክት ብቻ ሳይኾን ታላቅ ይላታል። የማይታይ ምልክት የለምና የታየችውን ታላቅ ምልክት በመጽሐፍ ቅዱስ ዐይንነት ለእኛም አሳይቶናል። በሰማይ የታየችው ከሞት ስለተነሣች ነው። ትንሣኤዋ በመጽሐፍ አልተጻፈም ለሚሉ ይድረስ። ያውም ፀሐይን የምታክል ኃያል ፍጥረት እንደ ተራ ሸማ ተጎናጽፋ። ይኽም ክብሯና ንጽሕናዋ ነው። አባቷ ቅዱስ ዳዊት የወርቅ በመጎናጸፊያ ተሸፋፍና በቀኙ ቆማ ያያት ንግሥት እርሷ ናት። ወርቅ የተባለ ንጽሕና ቅድስናዋ ነው። በሰማይ ያልታየቻችሁ ቅዱስ ዮሐንስን ጠይቁት። ዛሬም በሕያው ቃሉ ጣት እየጠቆመ ወደ ሰማይ ያሳያችኋል። ድንግል ማርያምን በሰማይ አለማየት ፀሐይን አትታየኝም ከማለት በላይ ነው። ካልታየቻችሁ ድክመቱ የእናንተ ነውና ፀሐይዋ የለችም አትበሉ። ወይ በሙቀቷ ብሰሉ ወይም ዐይናችሁን ተኳሉ። Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
310
17
#ዐረገች_በስብሐት ዐረገች በስብሐት ዐረገች በእልልታ በስብሐት በእልልታ ዐረገች ዐረገች በእልልታ የጻድቃን እመቤት የኃጥአን ተስፋ ዐረገች ዐረገች በእልልታ የማይታበለው እንዲፈጸም ቃሉ ብታርፍም እመ አምላክ ቤዛዊተ ኩሉ ዐረገች ተነስታ ድንግል የእኛ እናት እልል በሉላት እልል በሉላት አዝ= = = = ሰማያት ተደንቀው በአዲሲቷ ሰማይ ያልቻሉትን ጌታ ወስናው ብትታይ ሊቀበሏት ወጡ በሐሴት በሙሉ ንዒ ንዒ እያሉ ንዒ ንዒ እያሉ አዝ= = = = = ዘመኗን በሙሉ ስለ ልጇ አልቅሳ የመከራ ሰይፍን አሳልፋ ነፍሷ በቀኙ ልትቆም ንግሥት እየተባለች ይኸው ዐርጋለች ይኸው ዐርጋለች አዝ= = = = በሐዋርያት አበው ትምሕርት የጸናችሁ የልጇ ምሥክር ከዘሯ የቀራችሁ ከሞት ተነሥታለች ቅድስት እናታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አላችሁ አዝ= = = = = እጅሽ በዳሰሰው በነካው ሰበን እንደ ባረክሻቸው ሐዋርያቱን ማርያም ማርያም ስንል ደጅሽ ላይ ቆመን እኛንም ባርኪን እኛንም ባርኪን መዝሙር ዲያቆን አማን ኡርጌሳ "በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች።" መዝ ፵፬፥፱ Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
151
18
#ማርያም_አርጋለች ማርያም አርጋለች ወደ ገነት(፪) የሰማይ መላእክት እያረጋጓት እርሷም እንደ ልጇ ተነስታለች የአባቷን ዳዊት ትንቢት ልትፈፅም ወርቁን ተጎናፅፋ በቀኙ ልትቆም ወደ አምላክ ማደሪያ ወደ ሰማያት አረገለች በእልልታ ድንግል የእኛ እናት አርጋለች ማርያም ተነስታለች አዝ= = = = = ሰማያት ይከፈት ደመናም ይዘርጋ ዝምታም አይኖርም እመ አምላክ አርጋ አንደበት ይከፈት ማርያምን ያመስግን ከዘላለም ጥፋት በምልጃዋ እንድንድን አርጋለች ማርያም ተነስታለች አዝ= = = = = የአምላክ ማደሪያ ቅዱስ ስጋሽ አምላክን ያቀፉት እነዚያ እጆችሽ ሙስና መቃብር ይዞ አላስቀራቸው ተነስተዋል በክብር በእምነት አየናቸው አርጋለች ማርያም ተነስታለች አዝ= = = = = ሐዋርያት አበው እንኳን ደስ አላችሁ በክብር አረገች ማርያም ሞገሳችሁ ወደ ዓለምም ውጡ ሰበኑዋን ይዛችሁ የድንግል እርገቷን ንገሩ ተግታችሁ አርጋለች ማርያም ተነስታለች ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ "በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች።" መዝ ፵፬፥፱ Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
125
19
“#ሰላም_ለፍልሰተ_ሥጋኪ” ✍🏽ፍልሰታ የሚለውን ቃል አለቃ አያሌው ታምሩ "የእመቤታችን ሥጋ ከጌቴሴማኒ ወደ ገነት መፍለሱን ኋላም በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር ከነበረበት መነሣቱን ለሜመልከት የሚነገር ቃል ነው " በማለት ያብራራሉ። ስለ እመቤታችን ፍልሰት ነቢያት በትንቢት አስቀድመው ተናግረዋል ። "አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት(መዝ” 131÷8)። ነቢዩ ዳዊት " አንተና የመቅደስህ ታቦት ተነሥ" ሲል የተናገረው "አንተ " የተባለው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን "ታቦት " የተባለችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መሆኗን መተርጕማነ መጻሕፍት ያስረዳልሉ።"ተንሥኢ ወንዒ ቅርብትየ፣እንቲአየ ሠናይት ርግብየ፣ውስተ ጽላሎተ ኰኵሕ ቅሩበ ጥቅም፣ አቅራቢያዬ መልካሟ ርግቤ ተነሽ ነዬ ፣በግንቡ አጠገብ ወዳለው ዋሻው ጥላ" (መኃ ፪÷፲-፲፬) የሚለው ነው። ሐዋርያት ከድንግል ማርያም በመለያየታቸው ሲያዘኑ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ እመቤታችን በገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር እንዳለች ነገራቸው። እንዴት ዮሐንስ ዓይቶ እኛ ሳናይ እንቀራለን ብለው ነሐሴ አንድ ቀን  ቀኖና ገቡ። ያን ጊዜ ነሐሴ ጥር በባተበት ሰኞ ይብታል። ከሰኞ እስከ ሰኞ ስምንት፣ ከሰኞ እስከ ሰኞ አሥራ አምስት አንዱን ቀንሶ በአሥራ አራት እሑድ ሥጋዋን  አምጥቶ ሰጥቷቸው ቀብረዋት ዕለቱን ተነሥታለች። ያን ጊዜ ቅዱስ ቶማስ በቦታው አልነበረም። በሀገረ ስብከቱ ሕንድ ሲያስተምር ኖሮ በደመና  ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲሔድ እመቤታችን ወደ ሰማይ ስታርግ አጅበዋት የነበሩ ቅዱሳን መላእክት እመቤታችን ናት ስገድላት አሉት። እሱም ትንሣኤዋን ሳላይ የቀረሁ መስሎት ከደመናው ወልቆ ሊወድቅ ሲል እመቤታችን ትንሣኤዋን እሱ እንጂ ሌሎች ሐዋርያት እንዳላዩ ነገረችና የተገነዘችበትን ሰበን ሰጠችው። ቶማስ ከሐዋርያት ሲገናኝ ምሥጢሩን ነገራቸው። እነሱም በዓመቱ ቶማስ እንዳየ እናያለን ብለው ነሐሴ አንድ ቀን ሱባኤ ገቡ። ነሐሴ ማክሰኞ ይብታል። ከማክሰኞ እስከ ማክሰኞ ስምንት፣ ከማክሰኞ እስከ ማክሰኞ አሥራ አምስት  አንድ ቀን ጨምሮ ረቡዕ ነሐኤ አሥራ ስድስት ጌታ ሠራዒ ካህን፣ ጴጥሮስን ተራዳኢ ቄስ፣ እስጢፋኖስን ሠራዒ ዲያቆን አድርጎ ቀድሶ ቈርቦ አቍርቧቸዋል። የመልክአ ማርያም ደራሲ" ሰላም ለግንዘተ ሥጋኪ በእደ ሐዋርያት አርጋብ በአፈወ ዕፍረት ቅድው ዘሐሳበ ሤጡ ዕፁብ ማርያም ድንግል ወለተ ኅሩያን ሕዝብ ረሰይኩኪ እግዝእትየ ህየንተ እም ወአብ ይሕፅነኒ ከመ ጥብ ፍቅርኪ ሐሊብ፣ እመቤቴ ማርያም ሆይ! ዋጋው እጅግ ውድ በሆነና መዓዛው በሚጣፍጥ ሽቱ በሐዋርያት እጅግ ለተገነዘው ንጹሕ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል።ድንግል ሆይ ! የተመረጡና የተባረኩ ወገኖችሽ የሆኑ ቡርክት ልጅ ነሽ። እመቤቴ ሆይ! ቸርነትሽ እንደ ጡት ሁኖ ያሳድገኝ ዘንድ አንቺን እናት አባት አድርጌሻለሁ"ይላታል። "ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ደባትረ ብርሃን ኅበ ተተክሉ። ለገነተ ጽባሕ በማእከሉ ውድስት አንቲ ወስብሕት በአፈ ኵሉ ።እምነ ጻድቃን ዘታሕቱ ወእምትጉሃን ዘላዕሉ ።ማርያም ለኪ ስብሐተ አደሉ፣ እመቤቴ ማርያም ሆይ! በምሥራቅ ተክል በበዛበት በገነት መካከል የብርሃን ድንኳኖች ወደ ተተከሉበት ላረገ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል። ድንግል ሆይ! በሁሉ አንደበት መመስገን የተገባሽ ስለሆነ በሰማይ ካሉ መላእክትና በምድር ከሚኖሩ ደቂቀ አዳም ሁል ጊዜ ምስጋና ይቀርብልሻል” በማለት ያደንቃል።ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን የድንግል ማርያም ፍልሰተ ሥጋ እና ንሣኤ ከትንሣኤ ዘጉባኤ በኋላ የምንኖረውን ዘለዓለማዊ ሕይወት አመላካች መሆኑን  ታምናለች፣ታሳምናለች። ይኸውም ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ " በጌታ የሚሞቱ. ብፁዓን ናቸው።ከድካማቸው ያርፉ ዘንድ ሥራቸውም ይከተላቸዋል (ራእ፲፬÷፲፫) በማለትበ የገለጠው ነው። ቤተ ክርስቲያናችን ፍልሰታን በውዳሴ፣ በቅዳሴ፣ በጾም በጸሎት ታከብራለች። “ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ” (ዮሐ 11÷25)  በማለት የተናገረውን የሕይወትን እናት ሞት ይዞ ማስቀረት አይቻለውም። ቅዱስ ያሬድ “ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአፅብ ለኲሉ፣ የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል”  ያለውም ለዚህ ነው። ቅዱስ አግናጥዮስ “ከተቻለ በኢየሩሳሌም የሚኖረውን የአማኞች ጉባኤ ለማየት ለመካፈል እመጣለሁ፡፡ በተለይም የኢየሱስን እናት ለማየት፡ እርሷ የተከበረች፣ትሑት፣ በሁሉም አስደናቂበመሆኗ እርሷን ለማየት የማይሻ የለም፡፡ እርሷ የእግዚአብሔር እናት ሁላችንን ትባርካለች፤•••፡፡ያያት ሁሉ ይደነቃል፤ይደሰታል” በማለት መስክሯል፡፡ ቅዱስ ያሬድ " የሰው እጅ ያልሰራት ድንኳን ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ የተናገረላት እመቤታችን አባቷ ዳዊት በመሰንቆው እያመሰገናት ከሚያልፈው ዓለም ወደማያልፈው ዓለም ሔደች" በማለት አመስግኗታል። እኛም ክርስቲያኖች ቅዱሳን አባቶቻችንን  አብነት አድርገን በጾም፣ በጸሎት፣ በማሕሌት እና በቅዳሴ እናመሰግናታለን። ከትንሣኤዋ በረከት ያድለን። አሜን! Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
136
20
ጌታን ሲያርግ ዐይተው የነገሩን ቅዱሳን ሐዋርያት ናቸው። ድንግልም ስታርግ ዐይተው የነገሩን ራሳቸው ቅዱሳን ሐዋርያት ናቸው። ስለ ጌታ ዕርገት የነገሩንን አምነን ስለ እመቤታችን ዕርገት ሲነግሩን አና
ጌታን ሲያርግ ዐይተው የነገሩን ቅዱሳን ሐዋርያት ናቸው። ድንግልም ስታርግ ዐይተው የነገሩን ራሳቸው ቅዱሳን ሐዋርያት ናቸው። ስለ ጌታ ዕርገት የነገሩንን አምነን ስለ እመቤታችን ዕርገት ሲነግሩን አናምንም ማለት አይቻልም። ሐዋርያት ያልነገሯቸው ስለማይገባቸው ነውና ሊያውቁት አይችሉም። የዓለም ብርሃን የተባሉት የነገሩንን ትተን የጨለማ ልጆች የሚሉንን አንከተልም። በእነርሱ ዐይን ያየናቸውን ዕርገቶች ስናከብራቸው እንኖራለን። የበለጠ መረጃ እንዲደርሶ የደጉ ሳምራዊ መልካምነት ቴሌግራም ቻናላችንን ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅ ዘመድዎ እንዲሁም ለጓደኛዎ ያጋሩ:👇🏽 Telegram: ☞ https://t.me/+S3QVyScP7Saom-Lv
145