uz
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Kanalga Telegram’da o‘tish

📈 Telegram kanali የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU analitikasi

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 14 292 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 6 183-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 365-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 14 292 obunachiga ega bo‘ldi.

20 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 492 ga, so‘nggi 24 soatda esa 16 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 52.64% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 13.12% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 7 523 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 875 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 29 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Kanal uchun tavsif kiritilmagan.

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 21 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

14 292
Obunachilar
+1624 soatlar
+1157 kunlar
+49230 kunlar
Postlar arxiv
ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ። 12/01/2018 ዓ.ም (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ከሙከራ ትግ
+3
ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ። 12/01/2018 ዓ.ም (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ከሙከራ ትግበራ ጀምሮ ትምህርታቸውን ለተከታተሉ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችና የዕውቅና መርሐ ግብር ተከናወነ። የዕውቅና መርሐ ግብሩ የተከናወነው በ2015 ዓ.ም የዐሥረኛ ክፍል ምዘናን በሀገረ ስብከት ደረጃ ወስደው ለዘንድሮ የዐሥራ ኹለተኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ምዘና ለወሰዱ በአዲስ አበባና በሸገር ሀገረ ስብከት የሚገኙ አጥቢያ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ነው። ይህ የዕውቅና መርሐ ግብር በትላንትናው ዕለት በጠቅላይ ቤተክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ሲከናወን ለሦስተኛ ጊዜ ነው።በመርሐ ግብሩ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ የሆኑት መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የእንኳን ደስ አላቹ  መልዕክታቸውን ያስተላለፉ ሲሆን በጉባኤው የተገኙት ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የማዕከላዊ ጎንደር ሊቀ ጳጳስ "ይህ የትምህርት መጨረሻ እንዳልሆነ እና የተማረ ትውልድ ለቅድስት ቤተክርስቲያን እንደሚያስፈልጋት" ተናግረው አባታዊ መልዕክት እና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል። በመጨረሻም ተመራቂ ተማሪዎች የምሥክር ወረቀት እንዲሁም ለደረጃ ተማሪዎች የማበረታቻ ሽልማት በመስጠት የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል። የሰዋሰው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ሰ/ት/ቤት ከሌሎች ተፈታኝ ሰ/ት/ቦእቶች የላቀ ውጤት በማስመዝገቡ የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶለታል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

ቅዱስነታቸው በተገኙበት የተቀጸል ጽጌ በዓል በድምቀት ተከበረ !!! #የተቀጸል ጽጌ በየዓመቱ መስከረም 10 ቀን የሚከበር ሃይማኖታዊ መሠረት ያለው በዓል ነው !!! #በዓሉ የመስቀልን በዓል ከምስጋና
+3
ቅዱስነታቸው በተገኙበት የተቀጸል ጽጌ በዓል በድምቀት ተከበረ !!! #የተቀጸል ጽጌ በየዓመቱ መስከረም 10 ቀን የሚከበር ሃይማኖታዊ መሠረት ያለው በዓል ነው !!! #በዓሉ የመስቀልን በዓል ከምስጋና ና ከደስታ ጋር የሚያገናኝ ሲሆን፣ በተጨማሪም ክረምት አብቅቶ የመጸው (የአበባ) ወቅት መግባትን የሚያመለክት ነው። #በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በተከበረው በዚህ በዓል ላይ #ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ #ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ ና የቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ የበላይ ኀላፊ #ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ፣የሐዲያና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ #ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያውና የየድርጅት ኃላፊዎች #የአዲስ አበባ ሀገረስብከት የሥራ ኀላፊዎች፣ የአድባራት ና ገዳማት አስተዳዳሪዎች #ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ማህበረ ካህናት ወጣት የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎችና ምዕመናን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሯል ። #በበዓሉ ልዩልዩ መንፈሳዊ ፕሮግራሞች ቀርበዋል። #ስለ በዓሉ አመጣጥና አጠቃላይ ይዘት ትምህርተ ወንጌል ከተሰጠ በኃላ በቅዱስነታቸው አባታዊ ቡራኬ በጸሎት ተፈጽሟል !! መረጃው የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

እንኳን ደስ አላችሁ! ሦስተኛ ዙር የ፲፪ኛ ክፍል የምርቃት መርሐ ግብር በ2017 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ፲፪ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ምዘና የተመዘኑ ተማሪዎች ምረቃ
እንኳን ደስ አላችሁ! ሦስተኛ ዙር የ፲፪ኛ ክፍል የምርቃት መርሐ ግብር በ2017 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ፲፪ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ምዘና የተመዘኑ ተማሪዎች ምረቃ ዕለተ እሑድ መስከረም ፲፩ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ከቀኑ ፯ ጀምሮ (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በቢኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአሶሳ ከተማ የመንበረ ጵጵስና ገዳማትና አድባራት የሰ/ት/ቤቶች የሥርዓተ ትምህርት አተገባበር የመምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና መርሐ ግብር ተከናወነ። በመር
+5
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በቢኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአሶሳ ከተማ የመንበረ ጵጵስና ገዳማትና አድባራት የሰ/ት/ቤቶች የሥርዓተ ትምህርት አተገባበር የመምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና መርሐ ግብር ተከናወነ። በመርሐ ግብሩ መክፈቻ ላይ የሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መልአከ ፀሐይ ቆሞስ አባ ዘካርያስ ፀጋው፤ የሀ/ስብከቱ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ልሳናት ትሕትና አበበ የሀ/ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዘሪሁን ጣፋ ተገኝተዋል። ሀ/ስብከቱ በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የተቀረጸውን ሥርዓተ ትምሕርት ሙሉ በሙሉ ለመተግበር የትኩረት አቅጣጫ አስቀምጧል። ሥልጠናውንም ቁጥራቸው ከ40 በላይ የሚ ሆኑ የአብነት መምህራን ፣ የስብከተ ወንጌል መምህርና ከሰንበት ትምህር ቤቶች የተውጣጡ የሰንበት ትምርህት ቤቶች መምህራ ወስደዋል። መረጃው ያደረሰን የሀገረ ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ነው። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ
+5
ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ እንኳን ለ2018 ዓ.ም በሰላም አደረሰዎ መርሐ ግብር እየተከናወነ ይገኛል ። በዕለቱም ብፅዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የደቡብ ምዕራብ እና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የምሥራቅ ደቡብ ትግራይ እና የራያ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ በመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ልዩ ልዩ ኃላፊዎች፣ የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ እና ሰንበት ተማሪዎች ተገኝተዋል። መረጃው የኢ/ኦ/ተ/ቤ መገናኛ ብዙኀን ነው። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

እንኳን ለዘመነ ማርቆስ ፳፻፲፰ ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ! "በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ" መዝ ፷፭ (፷፮) ፡ ፲፩ ዘመኑ የፍስሐ የስኬት የንስሐ እና የቅድስና ይሁንልን! መልካም አዲስ ዓመት! (
እንኳን ለዘመነ ማርቆስ ፳፻፲፰ ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ! "በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ" መዝ ፷፭ (፷፮) ፡ ፲፩ ዘመኑ የፍስሐ የስኬት የንስሐ እና የቅድስና ይሁንልን! መልካም አዲስ ዓመት! (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website