es
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

El canal የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 292 suscriptores, ocupando la posición 6 183 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 365 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 292 suscriptores.

Según los últimos datos del 20 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 492, y en las últimas 24 horas de 16, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 52.64%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 13.12% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 7 523 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 875 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 29.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 21 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

14 292
Suscriptores
+1624 horas
+1157 días
+49230 días
Archivo de publicaciones
ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ። 12/01/2018 ዓ.ም (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ከሙከራ ትግ
+3
ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ። 12/01/2018 ዓ.ም (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ከሙከራ ትግበራ ጀምሮ ትምህርታቸውን ለተከታተሉ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችና የዕውቅና መርሐ ግብር ተከናወነ። የዕውቅና መርሐ ግብሩ የተከናወነው በ2015 ዓ.ም የዐሥረኛ ክፍል ምዘናን በሀገረ ስብከት ደረጃ ወስደው ለዘንድሮ የዐሥራ ኹለተኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ምዘና ለወሰዱ በአዲስ አበባና በሸገር ሀገረ ስብከት የሚገኙ አጥቢያ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ነው። ይህ የዕውቅና መርሐ ግብር በትላንትናው ዕለት በጠቅላይ ቤተክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ሲከናወን ለሦስተኛ ጊዜ ነው።በመርሐ ግብሩ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ የሆኑት መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የእንኳን ደስ አላቹ  መልዕክታቸውን ያስተላለፉ ሲሆን በጉባኤው የተገኙት ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የማዕከላዊ ጎንደር ሊቀ ጳጳስ "ይህ የትምህርት መጨረሻ እንዳልሆነ እና የተማረ ትውልድ ለቅድስት ቤተክርስቲያን እንደሚያስፈልጋት" ተናግረው አባታዊ መልዕክት እና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል። በመጨረሻም ተመራቂ ተማሪዎች የምሥክር ወረቀት እንዲሁም ለደረጃ ተማሪዎች የማበረታቻ ሽልማት በመስጠት የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል። የሰዋሰው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ሰ/ት/ቤት ከሌሎች ተፈታኝ ሰ/ት/ቦእቶች የላቀ ውጤት በማስመዝገቡ የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶለታል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

ቅዱስነታቸው በተገኙበት የተቀጸል ጽጌ በዓል በድምቀት ተከበረ !!! #የተቀጸል ጽጌ በየዓመቱ መስከረም 10 ቀን የሚከበር ሃይማኖታዊ መሠረት ያለው በዓል ነው !!! #በዓሉ የመስቀልን በዓል ከምስጋና
+3
ቅዱስነታቸው በተገኙበት የተቀጸል ጽጌ በዓል በድምቀት ተከበረ !!! #የተቀጸል ጽጌ በየዓመቱ መስከረም 10 ቀን የሚከበር ሃይማኖታዊ መሠረት ያለው በዓል ነው !!! #በዓሉ የመስቀልን በዓል ከምስጋና ና ከደስታ ጋር የሚያገናኝ ሲሆን፣ በተጨማሪም ክረምት አብቅቶ የመጸው (የአበባ) ወቅት መግባትን የሚያመለክት ነው። #በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በተከበረው በዚህ በዓል ላይ #ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ #ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ ና የቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ የበላይ ኀላፊ #ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ፣የሐዲያና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ #ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያውና የየድርጅት ኃላፊዎች #የአዲስ አበባ ሀገረስብከት የሥራ ኀላፊዎች፣ የአድባራት ና ገዳማት አስተዳዳሪዎች #ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ማህበረ ካህናት ወጣት የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎችና ምዕመናን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሯል ። #በበዓሉ ልዩልዩ መንፈሳዊ ፕሮግራሞች ቀርበዋል። #ስለ በዓሉ አመጣጥና አጠቃላይ ይዘት ትምህርተ ወንጌል ከተሰጠ በኃላ በቅዱስነታቸው አባታዊ ቡራኬ በጸሎት ተፈጽሟል !! መረጃው የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

እንኳን ደስ አላችሁ! ሦስተኛ ዙር የ፲፪ኛ ክፍል የምርቃት መርሐ ግብር በ2017 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ፲፪ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ምዘና የተመዘኑ ተማሪዎች ምረቃ
እንኳን ደስ አላችሁ! ሦስተኛ ዙር የ፲፪ኛ ክፍል የምርቃት መርሐ ግብር በ2017 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ፲፪ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ምዘና የተመዘኑ ተማሪዎች ምረቃ ዕለተ እሑድ መስከረም ፲፩ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ከቀኑ ፯ ጀምሮ (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በቢኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአሶሳ ከተማ የመንበረ ጵጵስና ገዳማትና አድባራት የሰ/ት/ቤቶች የሥርዓተ ትምህርት አተገባበር የመምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና መርሐ ግብር ተከናወነ። በመር
+5
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በቢኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአሶሳ ከተማ የመንበረ ጵጵስና ገዳማትና አድባራት የሰ/ት/ቤቶች የሥርዓተ ትምህርት አተገባበር የመምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና መርሐ ግብር ተከናወነ። በመርሐ ግብሩ መክፈቻ ላይ የሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መልአከ ፀሐይ ቆሞስ አባ ዘካርያስ ፀጋው፤ የሀ/ስብከቱ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ልሳናት ትሕትና አበበ የሀ/ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዘሪሁን ጣፋ ተገኝተዋል። ሀ/ስብከቱ በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የተቀረጸውን ሥርዓተ ትምሕርት ሙሉ በሙሉ ለመተግበር የትኩረት አቅጣጫ አስቀምጧል። ሥልጠናውንም ቁጥራቸው ከ40 በላይ የሚ ሆኑ የአብነት መምህራን ፣ የስብከተ ወንጌል መምህርና ከሰንበት ትምህር ቤቶች የተውጣጡ የሰንበት ትምርህት ቤቶች መምህራ ወስደዋል። መረጃው ያደረሰን የሀገረ ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ነው። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ
+5
ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ እንኳን ለ2018 ዓ.ም በሰላም አደረሰዎ መርሐ ግብር እየተከናወነ ይገኛል ። በዕለቱም ብፅዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የደቡብ ምዕራብ እና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የምሥራቅ ደቡብ ትግራይ እና የራያ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ በመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ልዩ ልዩ ኃላፊዎች፣ የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ እና ሰንበት ተማሪዎች ተገኝተዋል። መረጃው የኢ/ኦ/ተ/ቤ መገናኛ ብዙኀን ነው። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

እንኳን ለዘመነ ማርቆስ ፳፻፲፰ ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ! "በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ" መዝ ፷፭ (፷፮) ፡ ፲፩ ዘመኑ የፍስሐ የስኬት የንስሐ እና የቅድስና ይሁንልን! መልካም አዲስ ዓመት! (
እንኳን ለዘመነ ማርቆስ ፳፻፲፰ ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ! "በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ" መዝ ፷፭ (፷፮) ፡ ፲፩ ዘመኑ የፍስሐ የስኬት የንስሐ እና የቅድስና ይሁንልን! መልካም አዲስ ዓመት! (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website