የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
📈 Telegram kanali የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU analitikasi
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 14 516 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 6 021-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 332-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 14 516 obunachiga ega bo‘ldi.
02 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 504 ga, so‘nggi 24 soatda esa 15 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 43.66% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 10.19% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 6 330 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 477 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 33 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Kanal uchun tavsif kiritilmagan.
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 03 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 03 Iyul | +17 | |||
| 02 Iyul | +16 | |||
| 01 Iyul | +7 |
ይህ መልእክት ለኦርቶዶክሳውያን ሁሉ እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግ ክርስቲያናዊ ኃላፊነትዎን ይወጡ።
| 2 | በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነተ በሀገረ ስብከቱ ሥር ለሚገኙ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ4ተኛ እና የ8ተኛ ክፍል የሚኒስትሪ ፈተና ተሰጠ።
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ምዘናው በጭሮ በአራቱ አድባራት ተማሪዎች የፈተናውን አሰጣጥ ሊቀ ኅሩያን ቆሞስ አባ ፍቅረ ዮሐንስ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ከማደራጃው ኃላፊ መጋቤ ሥርዓት ዘነበ ብርሐኑ እንዲሁም የአንድነቱ ተቀዳሚ ሰብሳቢ መ/ር መኮንን አብዩ ሌሎቹችም የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አማራር በመገኘት የሀገረ ስብከቱ ስራ አስኪያጅ ቡራኬና ጸሎት ሰጥተው ፈተናውን አስጀምረዋል።
ፈተናውም በሀገረ ስብከቱ አዳራሽ እንዲሁም በአቡነ ጎርጎሪዎስ ትምህርት ቤት ተሰጥቷል። በተጨማሪም በወረዳ ላሉት የሰንበት ትምህርት ቤት ተፈተኞች
1. በጡሎ ዶባ ወረዳ በሂርና ሁለቱ አድባራት ና በዶባ ቅ/ሚካኤል ቤተክርስቲያን
2.በቦኬ ኦዳ ቡልቱም ወረዳ በበዴሳ ሁለቱ አድባራት ና በመካኒሳ ቅ/ገብርኤል ቤተክርስቲያን
3. በዳሮ ለቡ ወረዳ መቻራ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን
4. በሀብሮ ወረዳ ገለምሶ ሁለቱ አድባራት እና በልበሊቲ ቅ/ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን
5. በገመቺስ ወረዳ በቁኒ ሁለቱም አድባራት ፈተናው መስጠት ተችሏል።
ይህ የስርዓተ ትምህርት የምዘና ስራ አምና በአንድ ወረዳ ብቻ ተሰጥቶ ቢሆንም ዘንድሮ በ5 ወረዳ እና ከ16 ለሚበልጡ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ፈተናው ተዘጋጅቶ መበተን ተችሏል። በርዕሰ ከተማው ለሚገኙ ተፈታኞችም የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ አቡነ እንጦንስ በፈተናው ማብቂያ ላይ በመገኘት ልጆቻቸውን ሲያበረቱ ምክር ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬን በመስጠ በጸሎት ማጠቃለያ ማድረግ ተችሏል። የሰንበት ትምህርት ቤቱ ማደራጃ እና የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን በ9 ወረዳዎች ተዳራሽ ለማድረግ ስራዎችን ከወዲሁ እየሰራ ይገኛል። የረዳን እግዚአብሔር ይመስገን።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website | 4 035 |
| 3 | Matn yo'q... | 3 381 |
| 4 | በምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት የ2018 ዓ.ም ሀገረ ስብከት አቀፍ የ4ኛ ፣ 8ኛ እና 10ኛ ክፍል የሞዴል ፈተናዎች ሰጠ፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ስር የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የ2018 ዓ.ም ሀገረ ስብከት አቀፍ የሞዴል ተሰጠ። በሀገረ ስብከቱ በሚገኙ 6 ወረዳ ቤተ ክህነት መንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ አዳማ ፣ቢሾፍቱና አካባቢው፤ ሉሜ ፣አዳሚ ቱሉ፤ዱግዳ ፣እና በቦሰት ወርዳ ቤተ ክህነት በስሮቻቸው ባሉ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርቱን ሲከታተሉ ለቆዩት 3000 ተማሪዎች የ2018 ዓ.ም ሞዴል ፈተና በቀን 07/09/2018 ዓ.ም ተሰጥቷል፡፡ የሞዴል ፈተናው ስድስት የትምህርት አይነቶችን ለየብቻቸው ተዘጋጅቶ ተሰጥቷል።
የተሰጠው ፈተና መሠረተ ሃይማኖት፤ ክርስቲያናዊ ሥነ-ምግባር ፤ልሳነ ግዕዝ ፤የቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት፤ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ እና ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ለእያንዳንዱ ትምህርቶችን 50 ጥያቄዎችን ያከተተ ሲሆን በሀገረ ስብከቱ አንድነት የሚዘጋጀው የ4ተኛ 8ተኛ እና 10ኛ ክፍል ሀገረ ስብከት አእቀፍ የሚኒስትሪ ፈተና በወጣይ ወር በሁሉም ወረዳዎች ባሉ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ይሰጣል።
መረጃው የምሥራቅ ሸዋ ሀገረስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ነው።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website | 7 011 |
| 5 | "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫
እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!
የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በጋራ ጉባኤ በአንድነት ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሚመክሩበት፣ የትውልዱን መጻኢ ጉዞ የሚተልሙበት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለነገው ትውልድ ሊያሻግሩ የሚችሉ ዐውደ ሐሳቦች ለውይይት የሚቀርቡበት ታላቅ በዓል ነው። ይህ በቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና ተሰጥቶት በየዓመቱ እየተከናወነ የሚገኘው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ዘንድሮ በሀገራዊ ጉዳይ ምክንያት በመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ደረጃ ጠቅላላ ጉባኤውን በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማከናወን ባይችልም በሁሉም አህጉረ ስብከት፣ በየወረዳው እና በየአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ዕለቱ በደማቅ ሁኔታ "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫ በሚል መሪ ቃል ተከብሮ ይውላል።
ቅዱስ ጳውሎስ "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ብቻ አይደለም ያለን ይህንንም የመንፈስ አንድነት እንዴት መጠበቅ እንዳለብን በመንገርም ጭምር ነው እንጂ። ይኸውም በፍጹም የዋሕነት፤ ራሳችሁን ዝቅ አድርጋችሁ፣ እየታገሣችሁ፣ ለወንድሞቻችሁም እሺ እያላችሁ፣ በፍቅር እየተጋችሁና እየተባበራችሁ በማለት ነው። የአንድነታችንንም ዓላማ እንዳንዘነጋ ሲገልጽልን “ለአንዱ ተስፋችሁ እንደመጠራታችሁ” ይለናል። እኛም የ15ኛ ዓመት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ቀንን ስናከብር ከወትሮ በላቀ የመንፈስ አንድነታችንን ለመጠበቅ መትጋት እንዲገባን ይህን የቅዱስ ጳውሎስን ምክር መርሐችን አድርገናል። ከሁል ጊዜው በላይ ዓለምም ሆነ ሀገራችን እየተጓዘችበት ካለው አስፈሪ የጥፋት ጉዞ ትውልዱን መጠበቅ፣ ማዳንና ማሰማራት የሚቻለው የመንፈስ አንድነታችንን ለመጠበቅ ስንተጋ ብቻ ነው።
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ትውልዱን በቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር ለመጠብቅ የመንፈስን አንድነት መርሕ ይዞ የሚጓዝ መዋቅር ነው። ታዲያ ይህንን አንድነታችንን ከውስጥም ከውጭም ፈተናዎች ለመጠበቅ እየታየ ያለውን በጎ ፍሬ ለማስቀጠል ትጋትን ገንዘብ ልናደርግ ይገባናል እንላለን። ምን እንኳን በበዓለ ጰራቅሊጦስ የዘንድሮውን ዓለም አቀፋዊ ጠቅላላ ጉባኤያችንን ማከናወን ባንችልም በያለንበት መዋቅር ዕለቱን ልንዘክረው ይገባናል። በመጨረሻም የዘንድሮውን ዓለም ዓቀፍዊ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የሚከናወንበትን ዕለት በቅርቡ የምናሳውቅ መሆኑን እየገለጽን እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ እንላለን።
የመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
ግንቦት 22/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website | 10 967 |
| 6 | Matn yo'q... | 6 193 |
| 7 | በዓለ ጰራቅሊጦስ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን መሪ ቃል:-
"የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website | 10 055 |
| 8 | የ2018ዓ.ም የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት የ12ኛ ክፍል የናሙና ምዘና ተሰጠ።
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ግንቦት 17 2018ዓ.ም
በመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አዘጋጅነት እየተተገበረ በሚገኘው ሥርዓተ ትምህርት ተምረው ለሀገር አቀፍ ለሙከራ የናሙና ምዘና የደረሱ ተማሪዎችን ለ4ኛ ጊዜ አስፈተነ።
ለዚህ የናሙና ምዘና የደረሱ በአዲስ አበባና በሸገር ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኙ አጥቢያዎች ሲሆኑ ምዘናውንም ግንቦት 16 ቀን ወስደዋል። በመቀጠልም በወርሐ ሰኔ መጨረሻ የማጠቃለያ ምዘና እንደሚወስዱ ይጠበቃል።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) | 7 907 |
| 9 | ለሁሉም የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዋቅር:- የሰንበት ትምህርት ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ ሰነድ በዚህ ሊንክ በተያያዘው ሰነድ መሠረት ተልኳል። https://eotc-gssu.org/a/የሰንበት-ት-ቤቶች-የሥራ-አመራር-ምርጫ-ማስ/
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website | 9 120 |
| 10 | ለሁሉም የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዋቅር:- የሰንበት ትምህርት ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ ሰነድ በዚህ ሊንክ በተያያዘው ሰነድ መሠረት ተልኳል። https://eotc-gssu.org/a/የሰንበት-ት-ቤቶች-የሥራ-አመራር-ምርጫ-ማስ/ | 0 |
| 11 | ስቅለት!
እንኳን አደረሳችሁ!
“ሕመማችንንም ተሸክሞአል” ኢሳ 53፡4
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website | 0 |
| 12 | https://youtube.com/live/7NXwJ7bgm_s | 0 |
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
