en
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 322 subscribers, ranking 6 154 in the Religion & Spirituality category and 2 360 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 322 subscribers.

According to the latest data from 22 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 507 over the last 30 days and by 11 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 49.23%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 13.09% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 1 875 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 23 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

14 322
Subscribers
+1124 hours
+1077 days
+50730 days
Posts Archive
ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ። 12/01/2018 ዓ.ም (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ከሙከራ ትግ
+3
ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ። 12/01/2018 ዓ.ም (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ከሙከራ ትግበራ ጀምሮ ትምህርታቸውን ለተከታተሉ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችና የዕውቅና መርሐ ግብር ተከናወነ። የዕውቅና መርሐ ግብሩ የተከናወነው በ2015 ዓ.ም የዐሥረኛ ክፍል ምዘናን በሀገረ ስብከት ደረጃ ወስደው ለዘንድሮ የዐሥራ ኹለተኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ምዘና ለወሰዱ በአዲስ አበባና በሸገር ሀገረ ስብከት የሚገኙ አጥቢያ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ነው። ይህ የዕውቅና መርሐ ግብር በትላንትናው ዕለት በጠቅላይ ቤተክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ሲከናወን ለሦስተኛ ጊዜ ነው።በመርሐ ግብሩ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ የሆኑት መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የእንኳን ደስ አላቹ  መልዕክታቸውን ያስተላለፉ ሲሆን በጉባኤው የተገኙት ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የማዕከላዊ ጎንደር ሊቀ ጳጳስ "ይህ የትምህርት መጨረሻ እንዳልሆነ እና የተማረ ትውልድ ለቅድስት ቤተክርስቲያን እንደሚያስፈልጋት" ተናግረው አባታዊ መልዕክት እና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል። በመጨረሻም ተመራቂ ተማሪዎች የምሥክር ወረቀት እንዲሁም ለደረጃ ተማሪዎች የማበረታቻ ሽልማት በመስጠት የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል። የሰዋሰው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ሰ/ት/ቤት ከሌሎች ተፈታኝ ሰ/ት/ቦእቶች የላቀ ውጤት በማስመዝገቡ የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶለታል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

ቅዱስነታቸው በተገኙበት የተቀጸል ጽጌ በዓል በድምቀት ተከበረ !!! #የተቀጸል ጽጌ በየዓመቱ መስከረም 10 ቀን የሚከበር ሃይማኖታዊ መሠረት ያለው በዓል ነው !!! #በዓሉ የመስቀልን በዓል ከምስጋና
+3
ቅዱስነታቸው በተገኙበት የተቀጸል ጽጌ በዓል በድምቀት ተከበረ !!! #የተቀጸል ጽጌ በየዓመቱ መስከረም 10 ቀን የሚከበር ሃይማኖታዊ መሠረት ያለው በዓል ነው !!! #በዓሉ የመስቀልን በዓል ከምስጋና ና ከደስታ ጋር የሚያገናኝ ሲሆን፣ በተጨማሪም ክረምት አብቅቶ የመጸው (የአበባ) ወቅት መግባትን የሚያመለክት ነው። #በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በተከበረው በዚህ በዓል ላይ #ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ #ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ ና የቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ የበላይ ኀላፊ #ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ፣የሐዲያና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ #ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያውና የየድርጅት ኃላፊዎች #የአዲስ አበባ ሀገረስብከት የሥራ ኀላፊዎች፣ የአድባራት ና ገዳማት አስተዳዳሪዎች #ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ማህበረ ካህናት ወጣት የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎችና ምዕመናን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሯል ። #በበዓሉ ልዩልዩ መንፈሳዊ ፕሮግራሞች ቀርበዋል። #ስለ በዓሉ አመጣጥና አጠቃላይ ይዘት ትምህርተ ወንጌል ከተሰጠ በኃላ በቅዱስነታቸው አባታዊ ቡራኬ በጸሎት ተፈጽሟል !! መረጃው የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

እንኳን ደስ አላችሁ! ሦስተኛ ዙር የ፲፪ኛ ክፍል የምርቃት መርሐ ግብር በ2017 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ፲፪ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ምዘና የተመዘኑ ተማሪዎች ምረቃ
እንኳን ደስ አላችሁ! ሦስተኛ ዙር የ፲፪ኛ ክፍል የምርቃት መርሐ ግብር በ2017 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ፲፪ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ምዘና የተመዘኑ ተማሪዎች ምረቃ ዕለተ እሑድ መስከረም ፲፩ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ከቀኑ ፯ ጀምሮ (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በቢኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአሶሳ ከተማ የመንበረ ጵጵስና ገዳማትና አድባራት የሰ/ት/ቤቶች የሥርዓተ ትምህርት አተገባበር የመምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና መርሐ ግብር ተከናወነ። በመር
+5
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በቢኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአሶሳ ከተማ የመንበረ ጵጵስና ገዳማትና አድባራት የሰ/ት/ቤቶች የሥርዓተ ትምህርት አተገባበር የመምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና መርሐ ግብር ተከናወነ። በመርሐ ግብሩ መክፈቻ ላይ የሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መልአከ ፀሐይ ቆሞስ አባ ዘካርያስ ፀጋው፤ የሀ/ስብከቱ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ልሳናት ትሕትና አበበ የሀ/ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዘሪሁን ጣፋ ተገኝተዋል። ሀ/ስብከቱ በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የተቀረጸውን ሥርዓተ ትምሕርት ሙሉ በሙሉ ለመተግበር የትኩረት አቅጣጫ አስቀምጧል። ሥልጠናውንም ቁጥራቸው ከ40 በላይ የሚ ሆኑ የአብነት መምህራን ፣ የስብከተ ወንጌል መምህርና ከሰንበት ትምህር ቤቶች የተውጣጡ የሰንበት ትምርህት ቤቶች መምህራ ወስደዋል። መረጃው ያደረሰን የሀገረ ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ነው። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ
+5
ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ እንኳን ለ2018 ዓ.ም በሰላም አደረሰዎ መርሐ ግብር እየተከናወነ ይገኛል ። በዕለቱም ብፅዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የደቡብ ምዕራብ እና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የምሥራቅ ደቡብ ትግራይ እና የራያ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ በመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ልዩ ልዩ ኃላፊዎች፣ የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ እና ሰንበት ተማሪዎች ተገኝተዋል። መረጃው የኢ/ኦ/ተ/ቤ መገናኛ ብዙኀን ነው። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

እንኳን ለዘመነ ማርቆስ ፳፻፲፰ ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ! "በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ" መዝ ፷፭ (፷፮) ፡ ፲፩ ዘመኑ የፍስሐ የስኬት የንስሐ እና የቅድስና ይሁንልን! መልካም አዲስ ዓመት! (
እንኳን ለዘመነ ማርቆስ ፳፻፲፰ ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ! "በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ" መዝ ፷፭ (፷፮) ፡ ፲፩ ዘመኑ የፍስሐ የስኬት የንስሐ እና የቅድስና ይሁንልን! መልካም አዲስ ዓመት! (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website