የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)
ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡ አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን! ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን! ♻: https://api.whatsapp.com/send?phone=
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official) analitikasi
የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official) (@sultan_54) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 13 493 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 6 561-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 503-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 13 493 obunachiga ega bo‘ldi.
20 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 2 ga, so‘nggi 24 soatda esa -3 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 19.35% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 5.96% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 2 612 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 804 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 34 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡
አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን!
ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን!
♻: https://api.whatsapp.com/send?p...”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 21 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 21 Iyul | 0 | |||
| 20 Iyul | 0 | |||
| 19 Iyul | 0 | |||
| 18 Iyul | +8 | |||
| 17 Iyul | +6 | |||
| 16 Iyul | +3 | |||
| 15 Iyul | +2 | |||
| 14 Iyul | +4 | |||
| 13 Iyul | +1 | |||
| 12 Iyul | +3 | |||
| 11 Iyul | 0 | |||
| 10 Iyul | +1 | |||
| 09 Iyul | +3 | |||
| 08 Iyul | +4 | |||
| 07 Iyul | 0 | |||
| 06 Iyul | +9 | |||
| 05 Iyul | +8 | |||
| 04 Iyul | +4 | |||
| 03 Iyul | +8 | |||
| 02 Iyul | +5 | |||
| 01 Iyul | +6 |
| 2 | ﴿إِنَّ مَعَ الْعُسْرِ يُسْرًا﴾
«በእርግጥ ከችግር ጋር ምቾት አለ።»
ቀናቶች ምንም ያህል ቢጠነክሩብህ ከአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጥ፤ ምክንያቱም ፈረጃው ባሪያው ባላሰበው መንገድ ይመጣል። አላህ በእርሱ ላይ መልካም የጠረጠረውን ሰው መቼም ቢሆን አያሳፍረውም።
አላህ ልባችሁን ደስታን እንዲሞላው፣ ነገሮቻችሁን እንዲያገራልችሁ እና ቁርአንን የልባችሁ ብርሃን እንዲያደርግላችሁ እለምነዋለሁ። | 974 |
| 3 | የሸይኽ ዐብዱረዛቅ ኢብኑ ዐብዲልሙሕሲን አል-ዐባድ አል-በድር (አላህ ይጠብቃቸው) የሕይወት ታሪክ
ታላቁ ዓሊም፣ ወሪዕ(ጥንቁቁ ፈቂህ)፣ የመልካም ስብዕና እና የከፍተኛ ስነ-ምግባር ባለቤት የሆኑት ሸይኽ ዐብዱረዛቅ ኢብኑ ዐብዲልሙሕሲን አል-ዐባድ አል-በድር (አላህ ይጠብቃቸው)።
እሳቸው ጥልቅ እውቀትን፣ መልካም ስነ-ምግባርን፣ ከፍተኛ ትጋትን እንዲሁም በማስተማርና በዳዕዋ ስራ ላይ ዘወትር በማስተማር በአንድ ላይ ካዋሃዱ ታላላቅ ዑለማኦች (ሊቃውንት) አንዱ ናቸው። በለስላሳነታቸውና በርህራሄያቸው የሚታወቁ ሲሆን፣ ከጭቅጭቅ የራቁና ሰዎችን ከማንቋሸሽና ሁከት ከመፍጠር የጠሩ ናቸው። ስለ ማንም ሰው መጥፎ ሲናገሩ አይሰማም፤ ይልቁንም መመሪያቸው ስህተትን መሸፈን፣ መምከርና በትክክለኛው መንገድ መምራት ነው።
የዒልም እድገታቸውና መሻይኾቻቸው፦
እሳቸው (አላህ ይጠብቃቸው) ያደጉት በዒልም እና በዲን በታነጸ ቤት ውስጥ ሲሆን፣ በታላቁ የመዲና የሐዲሥ ሊቅ በሆኑት በአባታቸው በሸይኽ ዐብደልሙሕሲን አል-ዐባድ ጥላ ስር ነው ያደጉት። ይህም ለስብዕናቸው መገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ነበረው። በመቀጠልም የዘመኑ ታላላቅ ዑለማኦች እውቀትን ቀስመዋል፤ ከእነዚህም መካከል፦
ሸይኽ ዐብደልዐዚዝ ኢብን ባዝ
ሸይኽ ሙሐመድ ኢብን ሷሊሕ አል-ዑሠይሚን
ሸይኽ ዐብደላህ አል-ጉደያን
ሸይኽ ዐብደላህ አል-ጉነይማን
ሸይኽ ዐሊ ናሲር ፈቂሂ እና ሌሎችም።
በዚህም የኢስላሚክ ዩኒቨርሲቲ (መዲና) እውቅ መምህር እና በመዲና መስጂደ ነበዊ ከሚያቀሩ ታዋቂ የዲን ሊቃውንት አንዱ ለመሆን በቅተዋል።
የቅርብም የሩቅም ሰው ለመልካም ስነ-ምግባራቸው፣ በማስተማር ክህሎትና ብቃታቸውና ንግግራቸው ግልጽነት መስክሮላቸዋል። እንዲያውም ሸይኽ ሷሊሕ አስ-ሱሐይሚ ስለ እሳቸው ሲናገሩ፦
"ዐብዱረዛቅ አል-በድር አባቱ ሸይኼ ነው፣ እሱ ደግሞ ተማሪዬ ነው፤ ዛሬ ግን እሱ ከእኔ ይበልጣል" ብለዋል።
የሕይወት ታሪካቸውንና ትምህርቶቻቸውን ያስተዋለ ሰው አላህ የሰጣቸውን የብስለት አእምሮ፣ ጥበብና ቀጥተኛ አካሄድ በግልጽ ይመለከታል። እውቀትን ከተግባር፣ ዐቂዳን ደግሞ ነፍስን ከማጥራት(ተዝኪየቱ አን ነፍስ) ጋር ለማገናኘት ያላቸው ልዩ ትኩረት ይታያል፤ በዚህም የተነሳ የትምህርት መጃሊሶቻቸው በትህትና እና በሰኪና (በመረጋጋት) የተሞሉ ናቸው። በዒልማቸው በሳዑዲ ዓረቢያ ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ በርካታ ሕዝብ ተጠቃሚ ሆኗል።
ታዋቂ ማብራሪያዎቻቸውና ትምህርቶቻቸው (ሸርሆች)
ሸርሕ አል-ቀዋዒድ አል-ሙሥላ (شرح القواعد المثلى)
ሸርሕ አል-ከሊም አጥ-ጦይብ (شرح الكلم الطيب)
ሸርሕ ቀዋዒድ አል-አስማእ አል-ሑስና (شرح قواعد الأسماء الحسنى)
ሸርሕ ሐሺየት ኢብን አቢ ዳውድ (شرح حاشية ابن أبي داود)
የዋሲጢያህ፣ የሉምዐቱል ኢዕቲቃድ፣ የመሳኢል አል-ጃሂሊያህ እና የሌሎች ሰለፎች የዐቂዳ ኪታቦች ማብራሪያ።
የሪያዱ አስ-ሷሊሒን፣ የተጅሪድ አስ-ሶሪሕ፣ የሙኽተሰር ሶሒሕ ሙስሊም እና የአርበዒን አል-ነወዊያህ ማብራሪያ።
በስነ-ምግባርና በባህሪ ዙሪያ ጠቃሚ ትምህርቶች አሏቸው፤ ከእነዚህም፦ የአድ– ዳእ ወድ-ደዋእ ፣ የአኽላቅ ሐመለቲል ቁርዓን እና የዋቢል አስ-ሰዪብ ማብራሪያዎች።
ታዋቂ መጽሐፎቻቸው ፦
ፊቅህ አል-አድዒያህ ወል-አዝካር (فقه الأدعية والأذكار)
አል-ሐጅ ወተህዚብ አን-ኑፉስ (الحج وتهذيب النفوس)
ተዝኪረቱል ሙእተሲ ሸርሕ ዐቂዳህ ዐብደልገኒ አል-መቅዲሲ (تذكرة المؤتسي)
ዲራሰቱ አሠር አል-ኢማም ማሊክ ፊ ባብ አል-ኢስቲዋእ (دراسة أثر الإمام مالك)
ተዕዚም አስ-ሶላት (تعظيم الصلاة)
በሐዲስ፣ በፊቅህ፣ በዐቂዳና በስነ-ምግባር ዙሪያ የተሰሩ ምርምሮችና ጥናቶች።
ፊቅህ አል-አስማእ አል-ሑስና (فقه الأسماء الحسنى)
እነዚህና ሌሎች ጠቃሚ መጽሐፎች ያሏቸው ሲሆን፣ በቅርቡ መጽሐፎቻቸውና መልዕክቶቻቸው በሙሉ በአንድ ጠቃሚ ጥራዝ ተሰብስበው ታትመዋል።
ማጠቃለያ፦ እሳቸው አላህ እውቀትንና ተግባርን፣ ማስረጃንና ርህራሄን፣ ሱናንና መልካም ስነ-ምግባርን በአንድ ላይ የሰበሰበላቸው ሸይኽ ናቸው። በመሆኑም ለአስተማሪ ዳዒና መካሪ ዓሊም ምርጥ ምሳሌ ናቸው። የእውቀት ፈላጊዎች ወደ መጽሐፎቻቸው እንዲዞሩ፣ ትምህርቶቻቸውን እንዲያዳምጡ እና ዐቂዳን በማረጋገጥ፣ ነፍስን በማጥራትና በመልካም አስተዳደግ ረገድ ካላቸው ጠንካራ አካሄድ እንዲጠቀሙ እንመክራለን።
አላህ ሸይኹን ይጠብቃቸው፣ በእድሜያቸውና በእውቀታቸው ላይ በረከትን ያድርግላቸው፣ እስልምናንና ሙስሊሞችንም በእሳቸው ይጠቅም ዘንድ እንለምነዋለን። | 1 508 |
| 4 | Matn yo'q... | 1 149 |
| 5 | ፈትዋ
ጥያቄ፦ ነጋዴው የዚህ ዕቃ ዋጋ በጥሬ ገንዘብ (ካሽ) ከተከፈለ 100 ዲናር ነው፤ በየወሩ እየተከፋፈለ በክሬዲት (በተቅሲጥ) ከሆነ ግን 150 ዲናር ነው ይላል። ታዲያ የዚህ ብይን ምንድን ነው? አላህ ምንዳዎን ይክፈልዎና።
መልስ (በሸይኽ ኢብኑ ዑሰይሚን)፦ ይህ አሰራር ይፈቀዳል፣ ምንም ችግር የለውም። አላህ በትዕዛዙ በጥቅሉ እንዲህ ስላለ፦
"አላህ መሸጥን ፈቀደ፤ ወለድን ግን እርም አደረገ።" (አል-በቀራህ፡ 275)
እንዲሁም አላህ እንዲህ ብሏል፦
"እናንተ ያመናችሁ ሆይ! እስከ ታወቀ ጊዜ ድረስ ባለ እዳ በተዋዋላችሁ ጊዜ ጻፉት።" (አል-በቀራህ፡ 282)
ይህ ገዥ ዕቃው በሁለት የተለያየ ዋጋ ቀረበለት ማለት ነው፤ በጥሬ ገንዘብ (በካሽ) የሚከፈል ዋጋ እና በጊዜ ገደብ (በክሬዲት) የሚከፈል ዋጋ። ለምሳሌ የጥሬ ገንዘቡ ዋጋ 100 ነው እንበል፤ የጭልፊቱ ዋጋ ደግሞ 150 ነው፤ እሱም በዚያው በተቀመጡበት መጅሊስ ከቦታው ሳይበተኑ የክሬዲቱነረ (የ150ውን) መረጠ። ከዚያም ዕቃውን ይዞ ሄደ። በዚህ ጊዜ በእሱ እዳ ላይ 150 ዲናር በትክክልና በግልጽ ተቀምጦ ጸና።
ይህ ዓይነቱ ሽያጭ ምንም ችግር የሌለበት ትክክለኛ ሽያጭ ነው። ምክንያቱም ገዢው በዚህ ወይም በዚያኛው ዋጋ ለመግዛት ምርጫ ተሰጥቶታል።
ይህ ደግሞ በምንም መልኩ ከወለድ (ሪባ) ጋር አይገናኝም። ምክንያቱም ወለድ ማለት "ብርን በብር" (ገንዘብን በገንዘብ) ላይ ጨምሮ መሸጥ ማለት ነው። እዚህ ጋር ግን እየተሸጠ ያለው ዕቃ ነው፤ ዕቃን ደግሞ በጥሬ ገንዘብ ሲሆን በዚህ ዋጋ፣ በጊዜ ገደብ ሲሆን ደግሞ በዚያ ዋጋ መሸጥ ሙሉ በሙሉ የተፈቀደ ነው።
እንዲሁም ይህ ሽያጭ ነቢዩ (ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም) ከከለከሉት "በአንድ ሽያጭ ውስጥ ሁለት ሽያጭ ማድረግ" (بيعتين في بيعة) ከሚለው ክልከላ ውስጥ አይገባም። ምክንያቱም እዚህ ጋር የተፈጸመው አንድ ሽያጭ ብቻ ነው። ሰውየው በሁለት አማራጮች መካከል ምርጫ ተሰጥቶት አንደኛውን መርጦ በአንዱ ላይ ብቻ ተስማምቶ ወጥቷልና። | 1 413 |
| 6 | የአላህ መልእክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
«የጠራችሁን ሰው ጥሪ ተቀበሉ (እሺ በሉ)፣ ስጦታን አትመልሱ፣ ሙስሊሞችንም አትምቱ።»
(አህመድ ዘግበውታል፣ አልባኒም ሰሂህ ነው ብለውታል)
የሐዲሱ ማብራሪያ (የግርጌ ማስተዋሻ)
«የጠራችሁን ሰው ጥሪ ተቀበሉ»፦ ይህ የሰርግ ድግስም ይሁን ሌላ ማንኛውም ዓይነት ምግብ ላይ እንዲገኝ የጠራውን ሰው ጥሪ ምላሽ እንዲሰጥ የታዘዘበት ነው።
«ስጦታን አትመልሱ»፦ ይህ ደግሞ ሁለተኛው ትዕዛዝ ሲሆን፣ የቀረበን ስጦታ ባለመመለስ መካከል ላይ ፍቅርና መተሳሰር እንዲኖር ያደርጋል።
«ሙስሊሞችንም አትምቱ»፦ ይህ ሦስተኛው ትዕዛዝ ሲሆን፣ ያለ ምንም (ሸሪዓዊ ቅጣት) ወይም ያለ አግባብ ሙስሊሞችን ከመምታትና ከመበደል መቆጠብን ያዛል። መሠረቱ ግን ከእነሱ ጋር በቃልም ሆነ በተግባር በደግነትና በለስላሳነት መኖር ነው። | 1 899 |
| 7 | • ኢብኑ ዑሰይሚን (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ ብለዋል፦
"ሰዎች ከሸሪዓዊ አውራዶች (የጠዋትና የማታ ዚክሮች) በዘነጉ ጊዜ፤ በእነሱ ላይ ጅን በዛባቸው፣ ተጫወተባቸውም (አላገጠባቸውም)።"
• ሊቃኡል ባቢል መፍቱህ (197) | 2 070 |
| 8 | በአላህ ላይ ሙሉ እርግጠኝነት (የቂን)" የሚባል ተአምራዊ ኃይል አለ፤ በእሱም ቀውሶቻችንን እንሻገራለን። ሁሉም በሮች ተዘግተው፣ ሁኔታዎች ባይመቻቹና ነገሮች ሁሉ እኛ ከምንመኘው ተቃራኒ ቢሆኑም እንኳ ዱዓ ማድረጋችንን እንቀጥላለን። ምክንያቱም አላህ ሁሉንም ነገር በትክክለኛው ጊዜ እንደሚያስተካክለው ሙሉ እርግጠኞች ነን። በአላህና በእሱ እቅድ (አስተናባሪነት) ስለምናምን፤ አላህ ሆይ! በችሎታህ ከሚያምኑና በአንተ ጉርብትና ከሚረኩት አድርገን። | 2 093 |
| 9 | "ስንት የተቸገረ እያለ፣ ሐጅና ዑምራን አታብዛ!"
ይህን ንግግር ከዚህ በፊት ሰምተሃል አይደል?
ነገር ግን በእርግጥ የአላህ መልእክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ወደዚህ ነው ያመለከቱን?
የአላህ መልእክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦ «በሐጅና በዑምራ መካከል (አንዱን ከሌላው በማስከተል) አከታትሉ፤ እነሱ ድህነትንና ወንጀልን ያስወግዳሉና።»
ስለዚህ አላህ (ሱብሃነሁ ወተዓላ) በድጋሚ የመመለስን አቅም ከሰጠህ፣ የሰዎች ወሬ እንዳይከለክልህ። | 2 369 |
| 10 | አብሽር! ... የአላህ ፍቃድ በሆነው ልክ ሐዘን በአንተ ውስጥ እንዲኖር ፍቀድለት፤ ይህ ሁሉ በከንቱ የሚጠፋ አይምሰልህ። ይልቁንም ለእያንዳንዱ ትንፋሽ እና እንጉርጉሮ ታላቅ ምንዳ አለው፤ ለእያንዳንዱ ስቅስቅታና የእንባ ጠብታም ታላቅ ዋጋ አለ። ስለዚህ አትበሳጭ፣ አላህ ካለቀስክባት ምሽት ወይም ከተሰማህ የሕመም ትንፋሽ እንደሚዘነጋህ አታስብ። በትዕግስት መራራነት ውስጥ በሐዘን እሾህ መካከል እየኖርክ መታገስህንና ለመታገስ መጣርህን እንደማያይ አትገምት። ሐዘን በአንተ ውስጥ ለዘላለም እንደሚኖር አድርገህ ፈጽሞ አታስብ... | 2 089 |
| 11 | የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፦
"ሁለት ጸጋዎች አሉ፤ ከሰዎች አብዛኛዎቹ በእነሱ (በአጠቃቀማቸው) ይሸወዳሉ ፦ እነሱም ጤና እና ትርፍ ጊዜ ናቸው።"
(ቡኻሪ ዘግበውታል) | 2 583 |
| 12 | 🔴 የማንቂያ ደውል!
አንተ ውድቅ (ፋሺል) ሰው አይደለህም... አእምሮህ በማይመለከቱህ ነገሮች የተበታተነ ነው እንጂ!
አእምሮህ ሁልጊዜም በነገሮች ተወጥሯል... በችግሮች፣ በዜናዎች፣ ራስን ከሌሎች ጋር በማወዳደር፣ በስሜቶች እና ማለቂያ በሌላቸው የሶሻል ሚዲያ ይዘቶች!
አንተ ግን ጥቂት ቆም ማለት ያስፈልግሃል! ረጋ በል... ቅድሚያ የምትሰጣቸውን ነገሮች በጥንቃቄ መርምር... እናም ማንነትህን በትክክለኛ መንገድ መልሰህ ገንባ።
የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ምንም በማይጠቅም ወሬ እዚያው ባለህበት እንድትሽከረከር በማድረግ ዓመታትን ወስደውብሃል። አሁን ግን ጊዜህን ጠብቅ፤ ራስህን ለማበልጸግና ለማሳደግ ዛሬውኑ መስራት ጀምር። | 2 154 |
| 13 | በኢስላም አስተምህሮ ውስጥ የቃላት አጠቃቀምና የንግግር ግልጽነት ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነው። መልዕክትን በግልጽ፣ ያለ ጥርጥርና ለአላስፈላጊ ትርጉም በር በማይከፍት መልኩ መግለጽ ከእምነቱ መርሆዎች አንዱ ነው።
ይህንን አስመልክቶ በሱረቱል በቀራህ ላይ የተጠቀሰው «ላ ተቁሉ ራዒና ወቁሉ አንዙርና»
(لَا تَقُولُوا رَاعِنَا وَقُولُوا انْظُرْنَا)
የሚለው መለኮታዊ ትዕዛዝ፣ በንግግር ውስጥ አሻሚነትንና የተደበቁ መጥፎ ትርጉሞችን ማስወገድ እንደሚገባ ያስተምረናል። | 1 869 |
| 14 | ዑምራ በጊዜ ወይም በገንዘብ (ብቻ) የሚሆን አይደለም፤ ይልቁንም ጥንታዊ ቤቱን (ካዕባን) እንድትጎበኝ ከአል-ራህማን (ከአላህ) የሚቀርብ ጥሪ ነው።
አላህ ቤቱን እንድትጎበኝ ከጠራህ፣ እርሱ ራሱ ላንተ፣ ለጉዞህ ዋስትና ይሆንልሃል፤ እንዲሁም ባላሰብከው መንገድ ጉዞውን ያቃልልሃል።
ቸር የሆነውን አላህ መካንና መዲናን ከምትወዷቸው ሰዎች ጋር እንድትጎበኙ እንዲወፍቃችሁ እለምነዋለሁ።
ወሰላሙ አለይኩም። | 2 403 |
| 15 | የውዷ (የነቢዩ) ሀገር ልትወደድ ይገባታል፣
በደስታ ትዝታዋ ሁሌም ይናፈቃል፤
እንደ መዲና ያለ መኖሪያ የት አለ?
ሙሐመድ በመግባትዋ ክብሯ እኮ ላቀ። | 2 658 |
| 16 | ለእኔ ከሁሉ በላይ የተወደድሽው ሆይ፤ የአንቺ ናፍቆት እያዳከመኝ (ሊገለኝ) እንደሆነ እወቂ!
አላህ ወደ አንቺ መመለስን ከወሰነልኝ፣ በሕይወት እስካለሁ ድረስ መለያየትን ዳግመኛ አላነሳውም። የመለያየቱ ትኩሳት አካሌን አክስቶታል፣ ልቤንም አቃጥሎታል...
#መዲነተ_ሙነወራህ | 2 442 |
| 17 | - @ccdbot. | 3 282 |
| 18 | > በዚህ በዕለተ ጁምዓ፦ *ኢላሂ! በልባችን ውስጥ ያለን ማንኛውንም ሐዘን በደስታ የቀየርክልን ቢሆን እንጂ አትተውልን።*
>
> በዚህ እለተ ጁምዓ፦ * ኢላሂ! ሲሳያችንን (ሪዝቃችንን) አስፋልን፤ በልባችን ውስጥ ያሉትንና ከአንተ በቀር ማንም የማያውቃቸውን ፍላጎቶቻችንን በሙሉ ስጠን።*
> | 3 055 |
| 19 | አላህ )ሱብሃነሁ ወተዓላ የሚክስህ፤ በሱ ሀቅ ላይ፣ እሱን በማመስገንህ ላይ ጉድለት እንዳለብህ እስኪሰማህ ድረስ ነው።
እስክትደነቅ ድረስ ይተካሃል።
“በፊት ባጣሁትና ባላገኘሁት ነገር ላይ እንዴት አዝኜ ነበር?” ብለህ እስክታስብ ድረስ!
በፊትህ ላይ የተዘጉት በሮች በሙሉ፤ ከነሱ የተሻሉና እጅግ በጣም በላጭ የሆኑ በሮች ላንተ እንዲከፈቱልህ ተብሎ እንደተዘጉ ትረዳለህ።
የተከለከልከው ነገር በሙሉ ከክፉው እንደተጠበቅክበት፣ ያላገኘኸው ነገር ሁሉ አላህ ከዚያ የተሻለ መልካም ነገር እንደተካህልህ ትገነዘባለህ።
የአላህ ምትክ(መካስ) ሲመጣ ያጣኸውን ነገር ሁሉ ያስረሳሃል። | 3 343 |
| 20 | አላህ ዘንድ መለኪያዎች በቁጥር (በብዛት) አይደሉም።"
"ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ *'በቂያማ ቀን ትልቅና ወፍራም ሰው ይመጣል'* — እዚህ ጋ ወፍራም ሲል የግድ በሰውነት መወፈር ብቻ ሳይሆን በሰዎች ዘንድ ትልቅ ቦታና ክብር ያለውንም ያጠቃልላል — ነገር ግን አላህ ዘንድ የትንኝ ክንፍ ያህል ክብደት አይኖረውም'* አሉ።"
.. ያ ሁሉ ክብር፣ ያ ሁሉ ሀብት፣ ያ ሁሉ ማዕረግና በክብር ስፍራዎች ላይ መቀመጥ እያለው!"
አላህ ዘንድ ዜሮ ነው!
በሌላ በኩል ደግሞ፦ *'ስንት ጸጉሩ የተንጨባረረ፣ ትቢያ የለበሰ ከደጃፍ የሚገፈተር (ምስኪን) ሰው አለ፤ አላህን በውስጡ ቢማጸነው ኖሮ አላህ ልመናውን በእርግጥ የሚቀበለው' ስንትና ስንት ሰው አለ!* ይላል።
መለኪያው ይህ ነው። ለምሳሌ ኢብኑ መስዑድን ብንወስድ፤ እሱ እረኛ ነበረ፣ አጭርና በጣም ቀጭን ሰውነቱ ነበረው። እንዲያውም ከሰውነቱ ማነስ የተነሳ እሱ ቆሞ ሰሃባዎች ተቀምጠው ሳለ እኩል ጭንቅላታቸው ጋ ይደርስ ነበር ይባላል።"
ከአጭርነቱ የተነሳ። ይህ ሆኖ ሳለ ግን አንድ ቀን ዛፍ ላይ ሲወጣ ነፋስ መጣና ቀጫጭን ባቶቹ ተርገበገቡ፣ ሰሃባዎች ይህን በተመለከቱ ግዜ ሳቁ፣ እንዲህ ያለ አጋጣሚ ሲፈጠር ሳያውቁት መሳቃቸው ተፈጥሯዊ ነው። ነቢዩም ﷺ ይህንን ባዩ ጊዜ ምን አሏቸው? "'በሁለቱ እግሮቹ ቅጥነት ትደነቃላችሁን? ነፍሴ በእጁ በሆነችው አምላክ እምላለሁ፤ አላህ ዘንድ ከኡሁድ ተራራ በላይ ይከብዳሉ'* አሏቸው። | 3 484 |
