የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)
ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡ አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን! ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን! ♻: https://api.whatsapp.com/send?phone=
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)
تُعد قناة የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official) (@sultan_54) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 13 430 مشتركاً، محتلاً المرتبة 6 480 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 553 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 13 430 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 03 سبتمبر, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -23، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 6، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 19.20%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 7.65% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 0 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 027 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 0.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡
አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን!
ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን!
♻: https://api.whatsapp.com/send?p...”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 04 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 04 سبتمبر | 0 | |||
| 03 سبتمبر | +6 | |||
| 02 سبتمبر | 0 | |||
| 01 سبتمبر | +6 |
| 2 | በመጀለት አድ-ደዕዋ (ቁጥር 1591፣ በ9/1/1418 ሂ) ላይ «ፊ ዚላሊል ቁርኣን» በተሰኘው መጽሐፍ ዙሪያ ለቀረበላቸው ጥያቄ ኢማም ኢብኑ ዑሠይሚን -ረሒመሁልላህ- ሲመልሱ እንዲህ ብለዋል፦
«ለሱረቱል ኢኽላስ የሰጡትን ተፍሲር አንብቤአለሁ፤ በእሷም ውስጥ ከአህሉሱና ወልጀማዐህ እምነት ያፈነገጠ ታላቅ (አደገኛ) ንግግር ተናግረዋል። ተፍሲራቸው የሚያመላክተው "ወሕደቱል ውጁድ" (ፍጡርና ፈጣሪ አንድ ናቸው) የሚለውን እምነት እንደሚቀበሉ ነው። እንዲሁም "ኢስቲዋእ" የሚለውን የኣላህ መገለጫ "በስልጣኑ ተቆጥጥረና በስልጣን የበላይነት" (ሀይመናህ ወሰይጠራህ) ብለው ፈስረውታል።» | 1 660 |
| 3 | ፊትን መሸፈን(ኒቃብ) ጉዳይን በተመለከተ፡ ዑለሞች ከሴት ልጅ ፊትና ሁለት መዳፎች ውጭ ያሉትን የሰውነት ክፍሎች ሙሉ በሙሉ መሸፈን ግዴታ (ዋጅብ) መሆኑ ላይ በጋራ ተስማምተዋል (ኢጅማዕ አድርገዋል)። ማለትም፡ ሁለት እግሮቿን፣ እጅን እስከ ክርን ቢሆን ማሳየት ይፈቀዳል የሚል አንድም የለም።
ሁለተኛ፡ ዑለሞች ፊትንና ሁለት እጆችን መሸፈን ትልቅ ደረጃ ያለው፣ (በላጭ ነው) የታዘዘበት እና የተወደደ (ሙስተሃብ) ተግባር መሆኑ ላይ ተስማምተዋል። ፊትን ማሳየት ይፈቀዳል የሚሉት እንኳ መሸፈኑ የተወደደ ነው ይላሉ፤ ምክንያቱም እጅግ ዝቅተኛው ጥቅም እንኳ ከልዩነት (ኺላፍ) ለመውጣት ይረዳልና።
ሦስተኛ፡ በውበቷ ምክንያት ፈተና ይፈጠራል ተብሎ የሚሰጋባት ቆንጆ ሴት ፊቷንና ሁለት እጆቿን መሸፈን ግዴታ (ዋጅብ) ይሆንባታል በሚለው ላይ ተስማምተዋል። እንዲሁም ማሳየት ይፈቀዳል የተባለው ፊት ምንም ዓይነት ሜካፕ (የፊት መኳኳያ) የሌለበት መሆን አለበት በሚለው ላይም ተስማምተዋል። | 1 490 |
| 4 | ዲንን ማቃለል እና በ«ዑለሞች መካከል ልዩነት/ኺላፍ አለ» በሚል ሽፋን ስሜትን መከተል
በዑለሞች መካከል ኺላፍ አለባቸው በሚል ምክንያት በርካታ ዲናዊ ጉዳዮችን ለማቃለል (ለማለስለስ) መሞከር፤ በልዩነቱም በመመካት ደካማ የአቋም ብያኔዎችን ለመከተል ሰበብ መፈለግ፤ እንዲሁም የተገለሉና አሻሚ አቅዋሎችን ማስተዋወቅ፣ ማሰራጨት እና በህዝቡ መካከል ማስፋፋት ሰዎች የተሳሳቱና አሻሚ አቋሞችን እንዲይዙ ማድረግ እጅግ አደገኛ መርዝ ነው።
ይህ ድርጊት ያለ ምንም ጥርጥር ዲንን ከማበላሸት የሚቆጠር ሲሆን፣ መጥፎ አላማ ላላቸውና በሽታ ያለባቸው ደካማ ነፍስ ለአስከፊ ተግባራቸው እንዲሁም ሸይጣኖቻቸው በዓለም ላይ እንዲያሰራጩ የሚጎተጉቷቸውን መጥፎ ሃሳቦች ለመተግበር በሩን ይከፍትላቸዋል።
ቃዲ አቡ በክር እብኑል አረቢ እንዲህ ብለዋል፡-
«የሚከሰቱትን ኺላፎች በሙሉ የምንከተልና የምንጠብቅ ቢሆን ኖሮ፣ ዲን በማንኛውም መሰረት ላይ ሊረጋገጥና ሊፀና ባልቻለ ነበር።» | 1 398 |
| 5 | በአንዳንድ ወጣቶች አእምሮ ውስጥ፣ አንዳንድ ጊዜ ከመጠን በላይ በሆነ እራስን የመተማመን ስሜት የታጀበ፣ ለስላሳ እና ሮማንቲክ የሆነ አስተሳሰብ ይሰረጻል፤ ይህም አንዳንዶቹ፡ «ዲኗን ያልጠበቀች ወይም የላቀ በጎ ምግባር የሌላትን ሴት አግብቼ በራሴ እጅ አርማታለሁ፤ ወይም እቀይራታለሁ ፣ ወደ ቅን መንገድም እመራታለሁ» ብለው እንዲያስቡ ያደርጋቸዋል። ይህንንም የሚያስቡት በጥበባቸው፣ በጠንካራ ስብዕናቸው እና በሰዎች ላይ ባላቸው የማነፅ አቅም በመተማመን ነው።
ይህ አስተሳሰብ፣ ውጫዊ ገጽታው በመልካም እሴት የተሸፈነ ቢመስልም፣ በውስጡ ግን ትልቅ ስህተትን እና ፍጹም ተገቢ ያልሆነ ዓይነ-ሥውር የሆነ በራስ የመተማመን ጥግ ነው።
نعوذ بالله من الحور بعد الكور! | 1 328 |
| 6 | "ዋናው ቁምነገር ሰው ማግባቱ ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም ትልቁ ቁልፉ ነጥብ፤ ማንኛዋን ያገባል?? የሚለው ነው።
የዲን ባለቤት የሆነችዋን አግኝተህ ፤ ፈጥነህ አግባ፣ ይህን ካደረግህ (ዲነኛዋን ካገባህ) ታላቅ ሀብትን/ከንዝን አግኝተህ አሸንፈሃል፤ በረካም ተጎናጽፈሃል።
አሊያ ግን እጆችህ አፈር ይፈርሱ (የያዘከው ሀብት አይባረክ!)"
ከታላቁ ዓሊም ሸይኽ ሷሊሕ አል-ፈውዛን (አላህ ይጠብቋቸው) | 1 274 |
| 7 | «ስለ ፂም መላጨት ከተነሳ፤ በአላህ ይሁንብኝ! በራሴ ላይ መጥፎ ድርጊትንና መጥፎ ንግግርን አላጣምርም። እኔ በተግባር የጣስኩት ቢሆንም እንኳ እውነትን አልሸሽግም። በአላህም ሆነ በሰዎች ላይ አልዋሽም። በዚህ ድርጊቴ ላይ ተሳስቼ የተገኘሁ መሆኔንም በራሴ ላይ አመምናለሁ።
ይህን ስህተት ለመተው ደጋግሜ ሞክሬ ነበር፤ ነገር ግን የነፍስ ፍላጎትና የልማድ ኃይል አሸነፈችኝ።
ፂሜን እስክለቅ ድረስ አላህ በነፍሴ ላይ እንዲረዳኝ እጠይቀዋለሁ፤ እናንተም ይህንኑ አላህን እንዲለምንልኝ እጠይቃለሁ፤ የኢማን ወንድም ለወንድሙ በሩቅ የሚያደርገው ዱዓ በአላህ ፈቃድ ተቀባይነት አለው።»
✍ሸይኽ አሊ አጥ-ጠንጣዊ | 1 583 |
| 8 | በሁኔታዎችህ (በስራህ) ምክንያት ከቁርኣን እንዳትራራቅ ተጠንቀቅ! በአላህ እምላለሁ! እነዚያን ሁኔታዎችህን እንድትወጣ ከቁርኣን ቲላዋ በረካ ውጭ ምንም የሚያግዝህ የለምና ..»
ቃሪእ ሸዕባን ፋይዝ | 1 797 |
| 9 | አንድ ወጣት እንዲህ ይላል፦
"አንድ ቀን እኔና ጓደኛዬ የገንዘብ ቦርሳችንን (ዋሌታችንን) ተለዋወጥን። እኔ የእሱን ቦርሳ ስፈትሽ፣ እሱ ደግሞ የእኔን ቦርሳ ይፈትሽ ነበር። ቦርሳው ውስጥ የነበሩትን በርካታ የወረቀት ቁርጥራጮች እያነበብኩ ነበር። በአንዱ ወረቀት ላይ የተጻፈውን አነበብኩ ፊቴ በደስታና በግርምት ተሞላ።
'ይህ ምንድን ነው?' ብዬ ጠየቅኩት፤ – በስሜ የተቆረጠ የበጎ አድራጎት ድርጅት ደረሰኝ ነበር –
እሱም፡ 'የአንድ አባት የሌለው ልጅ (የየቲም) እርዳታ/ድጋፍ ነው' አለኝ።
እኔም፡ 'ግን ለምን በኔ ስም ሆነ!?' አልኩት።
እሱም፡ 'በአንተ ስም ነው የቲሙን የደገፍኩት' አለኝ።
እኔም፡ 'ከመቼ ጀምሮ ነው?' አልኩት።
እሱም፡ 'ከሁለት ዓመት በፊት ጀምሮ' አለኝ።
እኔም፡ 'ለምን ይህንን አደረግክ!' ብዬ ጠየቅኩት።
እሱም፡ 'እሳት (ጀሃነም) እንዳይነካህ ስለፈራሁልህ ነው' ሲል መለሰልኝ።”
አላህ ሆይ! መልካም እና ደግ ጓደኛን ወፍቀን! 🥺 | 3 890 |
| 10 | اللهم مع شروق هذا اليوم، نسألك خيراً في كل أمر، ونوراً في كل درب، وراحة في البال، وتوفيقاً يرافق خطواتنا. | 3 227 |
| 11 | لا يوجد نص... | 3 345 |
| 12 | ነገሮች ሲዘበራረቁ ቦታቸውን እያየዙ ሊሆን ይችላል፤ ተስፋ አትቁረጥ!
በአንድ ጉዳይ ላይ ወደ አላህ አብዝተህና አጥብቀህ ዱዓ አድርገህ ... ከዚያ በኋላ ግን ሁሉም ነገር ወደ ተቃራኒው ሲቀየር ብታይ፣ ዱአዬ አልተቀበለኝም ብለህ እንዳታስብ! አላህ መልካሙን ነገር አንተ ልትረዳው በማትችለው መንገድ እየመራው ይሆናል፤ በክስተቶችም የምስክርነትህንና የእምነትህን ጥንካሬ ይፈትናል። የእምነትህ ፅናት ሳይናወጥ የጸና ሆኖ ካገኘው ደግሞ ባልጠበቅኸው ስጦታ ያስገርምሃል.. አላህ በእርሱ በሚተማመኑት ባሮቹ ጥርጣሬና ግምት ልክ ነው!♥️ | 3 418 |
| 13 | በአቅራቢያዋ ሰላምና ስክነት አለ…🕊️
በአላህ መልእክተኛ ﷺ መስጂድ ቅጽር ግቢ ውስጥ ደግሞ ከምንም ነገር ጋር የማይመሳሰል የልብ እርጋታና እረፍት ይገኛል። 💚 | 2 751 |
| 14 | «ደካማ የሆነ ምላሽ(ረድ) ከሚሰጠው ጥቅም ይልቅ የሚያደርሰው ጉዳት ያመዝናል!
ጠንካራ ያልሆነ ምላሽ ሊመልሱ ወይም ማስረጃ የማይሆንን ነገር እንደ ማስረጃ ሊያቀርቡ ይችላሉ፤ ከዚያም በህዝቡ መካከል ሲበተኑት፣ በዚህ ጥርጣሬ (ሹብሃ) የተበከለው ሰው ምላሽህ ደካማ መሆኑን ሲያውቅ ያኔ ጥርጣሬው በልቡ ውስጥ የበለጠ ይስፋፋል።
አንተ የአህሉሱና ተወካይ ነህ፤ በዚህ ጃህል እይታ ውስጥ የአንተ ድክመት ማለት የሱና መንገድ (መዝሀብ) ድክመት ተደርጎ ይወሰዳል—ይህ ደግሞ ትልቅ ችግር ነው።
አንዳንዶች ምላሽ ለመስጠት በቅድመ-ግንባር ይሰለፋሉ፤ ነገር ግን ምላሾቻቸው ደካማና ተሰባሪ ናቸው፤ አስፈላጊው ዕውቀት፣ ጥንካሬና ጥልቀት የላቸውም።
በራስህ ውስጥ የዚህ መስክ ባለቤት አለመሆንህን ካወቅህ፣ አላህ ከአቅምህ በላይ አልጫነብህምና ጉዳዩን ለሌሎች ተወው። በህዝቡ መካከል 'ይህ የአህሉሱና መንገድ ነው' ብለህ እያሰራጨህ ምላሽህ ግን ያን ያህል ጠንካራ ካልሆነ፣በጣም አደገኛ ጉዳይ ነው።
ይህም ወደ ሌላ ነባራዊ ሁኔታ ትኩረት እንድስብ ያደርገኛል፤ እርሱም፦ ዛሬ ያሉ ወጣቶች በልቦቻቸው ውስጥ ጥርጣሬዎች ሊፈጠሩ ይችላሉ። ጥርጣሬዎቹ ከቀደር ጋር የተያያዙ፣ ከአንዳንድ ሕግጋት ጋር የተያያዙ፣ ወይም ደግሞ ከፈጣሪ (ሱብሃነሁ ወተዓላ) ማንነት ጋር የተያያዙ ሊሆኑ ይችላሉ።
እንዲሁም የማህበራዊ ሚዲያና የኢንተርኔት መረቦች በዚህ ግልጽ በሆነ የጥመቶች ስብስብ የተሞሉ ናቸው፤ ስለዚህ ከእነዚህ ጥርጣሬዎች መካከል የሆነ ነገር በዚያ ወጣት ልብ ውስጥ ሊያድር ይችላል።
እናም አንተ በትምህርት ቤት ውስጥ ያለህ አስተማሪ፣ በ መስጂድ ውስጥ ያለህ ኢማም፣ ወይም ደግሞ እርሱ እንደ ሸይኽና እንደ ዓሊም (ዕውቀት ያለው ሰው) አድርጎ የሚያይህ ሰው ወደ አንተ መጥቶ ጥያቄውን ሲያቀርብልህ፤ እንዴት ምላሽ መስጠት አለብህ?
በአላህ መልካም ፈቃድ ጥርጣሬውን ከልቡ የሚያስወግድ፣ አጥጋቢና ትክክለኛ የሆነ ምላሽ ካልሰጠኸው፣ ማድረግ የሚገባህን አልሰራህም።
በዚያ ደካማ ምላሽ ምክንያት እርሱ ዝም ሊል ወይም በፊቱ አንገቱን ሊነቀንቅ ይችላል፤ ነገር ግን በእውነቱ በልቡ ውስጥ 'ጉዳዩ በእርግጥም አጠራጣሪ ነው፣ እረ እናንተ ሸይኾች ዘንድ ምንም ምላሽ የላችሁም' ብሎ ያምናል።
ይህንንም ከአንዳንዶቹ ሰምቼዋለሁ፤ ከእነዚህ ወጣቶች አንዱ ስላጋጠመው ጥርጣሬ ሲጠይቅ የተሰጠው ምላሽ፦ 'ይህን ንግግር ተወው!' የሚል ነበር።
'ይህን ንግግር ተወው' የሚለው ምላሽ በልቡ ውስጥ ያለውን ጥርጣሬ ያስወግደዋልን? አያስወግደውም! በተለይም የዛሬ ወጣቶች አሳማኝ ማስረጃ ያስፈልጋቸዋል፤ ልስላሴ ልታሳያቸው፣ በሚረዱትና በሚገባቸው ቋንቋ ልታበራራላቸው ይገባል።
ስለዚህ አንተ በቁጣ፣ ወይም 'ዝም በል' በማለት፣ ወይም ደግሞ በደካማ ምላሽ ካሰናበትከው፣ ጥርጣሬውን በልቡ ውስጥ የበለጠ ታጠናክራለህ።
ስለሆነም፦ ወይም አጥጋቢ ምላሽ ስጠው፣ ወይም ደግሞ መልካም ምላሽ መስጠት ወደሚችልና ወደሚያውቅ ሰው እጁን ይዘህ ውሰደው።"
ፕሮፌሰር ሸይኽ ሷሊሕ አስ–ሲንዲ | 2 793 |
| 15 | 🔴 የጁምዓ ኹጥባ
🎙 خطبة الجمعة
أحوال يوم القيامة (الشفاعة)
✨ የቂያማ ቀን ክስተቶች 2
ሸፋዐ (ምልጃ)
⚠️ሊደመጥ የሚገባ ኹጥባ❗️
🎙በኡስታዝ ሱልጧን ኸድር
💫የአጅሩ ተካፋይ እንድንሆን ሼር!
🕌 ቃሊቲ ሀምዛ መስጂድ
🗓 ሶፈር 25/1448 አ/ሂ
http://t.me/kalityhamzamesjid | 2 437 |
| 16 | «በጀመዓ (በአንድነት) ውስጥ ያለ ችግር፣ በመለያየት ከሚገኝ ምቾት ይበልጣል።»
ሸይኽ ሷሊሕ ኢቢኑ አብደልዐዚዝ ኢቢን ዑሥማን አስ-ሲንዲ (በመዲና ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ የዐቂዳ ፕሮፌሰር) | 2 677 |
| 17 | በሰላቱ ላይ የዘወተረ ሰው፣ በሁለት ሰላቶች መካከል ይሞታል፡ በሰገዳት እና በሚጠብቃት ሰላት መካከል፤» 🥹🌻🌸 አላህ ሆይ! ያማረ መጨረሻንና ከፍተኛዋን ጀነት (ፊርደውስን) እንለምንሃለን። | 2 322 |
| 18 | በሁሉም ነገር ውስጥ የአላህን ቸርነት እና ደግነት መፈለግን ለራሳችሁ ልማድ አድርጉ፤ ግራ በሚያጋቡ አጋጣሚዎች እና በጭንቀት/በመከራ ወቅትም እንኳ ቢሆን። ሁልጊዜም፦ «ምናልባት መልካም ይሆናል፤ ምናልባት አላህ የማላውቀውን ክፉ ነገር ከእኔ አርቆልኝ ይሆናል፤ ምናልባት ከዚህ በኋላ መላቀቅ፣ እረፍት እና ማቃለል ይመጣል» ማለትን ልማድ አድርጉ። ሁልጊዜም በአላህ ውሳኔ የመርካት (ቀደርን የመቀበል) መንፈስ ይኑራችሁ... ከዚያም በኋላ አላህ እንዴት እንደሚያስደስታችሁ እና እንዴት እንደሚበቃችሁ ታያላችሁ። | 3 181 |
| 19 | እውነተኛ ጓደኝነት ለአላህ ብሎ ሲሆን… ✨
በዚህች ምድር ላይ ለአንድ አማኝ ከተሰጡት ትላልቅ ጸጋዎች አንዱ "መልካም ጓደኛ" ነው። ይህ ጓደኛ በገንዘብ፣ በዝና ወይም በጊዜያዊ ጥቅም ሳይሆን፣ ንጹህ በሆነው የአላህ ፍቅር ብቻ የተሳሰራችሁት ነው።
አብዛኛው የሰው ልጅ ግንኙነት በግላዊ ጥቅም ላይ በተመሰረተበት በዚህ ጊዜ፣ ለአላህ ተብሎ የሚመሰረት ውዴታ እጅግ ውድ ነው። ነቢዩ ሰለሏሁ አይሂ ወሰለም አላህ ዘንድ በልዩ ሁኔታ ስለሚጠለሉት ሰዎች ሲናገሩ፦ "ስለ አላህ ብለው የተዋደዱ፣ በእርሱ ላይ የተሰበሰቡና በእርሱ ላይ የተለያዩ..." ብለዋል።
ይህ ማለት ለአላህ ተብሎ የተገነባ የወንድማማችነት ፍቅር በሞት አያበቃም፤ ጠቀሜታውም ሆነ አማላጅነቱ ጀነት ድረስ የሚዘልቅ ዘላለማዊ ትስስር ነው!
🤲 ኢላሂ! ወደ አንተ የሚመሩንን፣ ስንዘናጋ የሚያስታውሱንን እና ትዕዛዝህን በመፈጸም ላይ የሚያግዙንን መልካም ጓደኞች ወፍቀን። ውዴታችንን ላንተ ብሎ ብቻ አድርግልን፤ በቂያማ ቀንም ምንም ጥላ በሌለበት ጊዜ በአርሽህ ጥላ ስር ከሚሰበሰቡት ባሮችህ አድርገን። አሚን! 🤍 | 3 892 |
| 20 | የመልካም ጓደኝነት ውብ ከሆኑ ነገሮች አንዱ፡ በዚህች ዱንያ መጠናቀቅ የማይበቃ መሆኑ ነው፤ ይልቁንም እስከ ቂያማ የሚዘልቅ ሲሆን፣ ከአላህ ጥላ ውጭ ምንም ጥላ በሌለበት ቀን በአላህ ጥላ ስር አብረው ይጠለላሉ። | 2 736 |
