uk
Feedback
NGCS PARENTS GRADE 1-8

NGCS PARENTS GRADE 1-8

Відкрити в Telegram

Показати більше
4 483
Підписники
+824 години
+397 днів
+21130 день
Архів дописів
ሐሙስ ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም አስቸኳይ ማሣሠቢያ በመጪው አዲስ ዓመት 2019ዓ.ም ልጆቻችሁን የ 12 ኛ ክፍል (የ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና(ማትሪክ) ለምታስፈትኑ ወላጆች እንዲሁም አሳዳጊዎች በሙሉ። በዚህ እያገባደድን ባለው 2018ዓ.ም ጀምሮ ከትምህርት ሚኒስቴር በተዋረድም ከ ትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች በወረደው መመሪያ መሠረት 12ኛ ብሔራዊ ፈተና ለመውሰድ የሚመጡ ተመዝጋቢ ተማሪዎች በሙሉ የብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ይዘው መቅረብ እንዳለባቸው ስለተደነገገ እስከ አሁን ፋይዳ መታወቂያ ያላወጣችሁ ትምህርት ቤት ሳይከፈት በዚህ በቀረው ጊዜ ለልጆቻችሁ ፋይዳ መታወቂያ አውጥታችሁ ዝግጁ አድርጋችሁ እንድትጠብቁ እያሳሰብን ትምህርት ቤቱ በሚከፈትበት ጊዜ ፎቶ ኮፒውን ከየክፍላቸው እየዞርን የምንሰበስብ መሆኑን እየገለፅን በ ፋይዳ መታወቂያው ላይ የሚሰፍሩት የልጆቻችሁ መረጃዎች ስም፣የአባት ስም፣ የአያት ስም (ስፔሊንግ) የትውልድ ዘመን፣ፃታ ወ.ዘ.ተ በትክክል መስፈራቸውን አረጋግጣችሁ እንድትቀበሉ እናሳስባለን። ከዚህ በተጨማሪ የ 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለመፈተን የ 8ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ፈተና ውጤት እና ከ 9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የነበራችሁን አጠቃላይ የትምህርት አቀባበላችሁን የሚያሳይ ትራንስክሪፕት ማቅረብ ስላለባችሁ በተለይ ከሌላ ትምህርት ቤት ወደ ልደታ ማርያም ልጃገረዶች ትምህርት የመጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ ከላይ የተጠየቁትን የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን በሙሉ ከነበራችሁበት ትምህርት ቤት ተቀብላችሁ ለቢሮ ገቢ እንድታደርጉ እናሳስባለን ። ይህ የ2019 ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ በምንጀምርበት ጊዜ ከተመዝጋቢ ተማሪዎች መረጃ አለመሟላት ጋር በተያያዘ ከሚገጥሙን ችግሮች እንደሚያላቅቀን በማሰብ ስለሆነ ይህንን ዛሬ ነገ ሳትሉ ተግባራዊ እንድታደርጉ አበክረን እናሳስባለን ።

ሐሙስ ሐምሌ 16/2016ዓ.ም አስቸኳይ ማሣሠቢያ በ መጪው አዲስ ዓመት 2019 ዓ.ም ልጆቻችሁን የ 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና (ሚኒስትሪ) ለምታስፈትኑ ወላጆች እንዲሁም አሳዳጊዎች በሙሉ። በዚህ እያገባደድነው ባለው 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከትምህርት ሚኒስቴር በተዋረድም ከአዲስ አበባ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በወረደው መመሪያ መሠረት ክልላዊ (ሚኒስትሪ) ፈተና ለመውሰድ የሚመጡ ተመዝጋቢ ተማሪዎች በሙሉ የ ብሔራዊ መታወቂያ ( ፋይዳ ) ይዘው መቅረብ እንዳለባቸው ስለተደነገገ እስከ አሁን ፋይዳ መታወቂያ ያላወጣችሁ ትምህርት ቤት ሳይከፈት በዚህ በቀረው ጊዜ ለልጆቻችሁ ፋይዳ መታወቂያ አውጥታችሁ ዝግጁ ሆናችሁ እንድትጠብቁ እያሳሰብን ትምህርት ቤቱ በሚከፈትበት ጊዜ ፎቶ ኮፒውን ከየክፍላቸው እየዞርን የምንሰበስብ መሆኑን እንገልፃለን ። በ ፋይዳ መታወቂያው ላይ የሚሰፍሩት የልጆቻችሁ መረጃዎች በሙሉ ስም፣ የአባት ስም፣ የአያት ስም፣ የትውልድ ዘመን፣ ፃታ ወ.ዘ.ተ በትክክል መስፈራቸውን አረጋግጣችሁ እንድትቀበሉ እናሳስባለን ። ይህ የ 2019ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ በምንጀምርበት ጊዜ ከተመዝጋቢ ተማሪዎች መረጃ አለመስተካከል ጋር በተያያዘ ከሚገጥሙን ችግሮች እንዲያላቅቀን በማሰብ ስለሆነ ይህንን ዛሬ ነገ ሳትሉ ተግባራዊ እንድታደርጉ አበክረን እናሳስባለን ። ትምህርት ቤቱ ትምህርት ቤቱ

photo content

School fee payment for 2019E.C Grade 1st 2nd 3rd 1-6 8674.84 8069.61 8079.61 7-8 9003.43 8375.28 8385.28 9-12 9529.19 8864.36 8874.36     Account Number   CBE 1000235980839   -Nativity Girls school NIB 7000002776222/ 5254   ECS  Nativity Girls school

14/11/2018   ለመደበኛ የልደታ ማርያም ልጃገረዶች  ት/ቤት ተማሪዎች በሙሉ የልደታ ማርያም ልጃገረዶች ት/ቤት የ2019 ዓ.ም. መደበኛ ምዝገባ ከሀምሌ 15-23/2018 ዓ.ም. ባሉት ቀናት ውስጥ ብቻ ልጆቻችሁን እንድታስመዘግቡ እያሳሰብን በእነዚህ ቀናት ውስጥ ያላስመዘገበ ወላጅ በራሱ ፍቃድ እንደለቀቀ ተቆጥሮ በምትኩ ሌላ አዲስ ተማሪ የምንቀበል መሆኑን በቅድሚያ እናሳውቃለን፡፡   ት/ቤቱ

14/11/2018   ማሳሰቢያ ለአዲስ 1ኛ ክፍል ፈተና ተፈትነው አልፈው የትምህርት ቤት ክፍያ ከፍላችሁ የተመዘገባችሁ ነገር ግን የፖሊሲ ቡክ (የት/ቤቱ መመሪያ ደንብ) እና ዩኒፎርም ያልገዛችሁ ወላጆች/አሳዳጊዎች በዚህ በ3 ቀን ውስጥ ገንዘብ በካሽ        በመያዝ መጥታችሁ ከዩኒፎርም ክፍል እና ከመጽሐፍት ቤት ግዥ እንድትፈጽሙ በጥብቅና በትህትና እናሳስባለን፡፡   ት/ቤቱ

ይህ ከላይ ያስቀመጥንላችሁን ማሳሰቢያ የ 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና የተፈተኑ ተማሪ ወላጆች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የተፈታኝ ተማሪዎችን ውጤት ሰርቲፊኬት አትሞ ለማውጣት በዝግጅት ላይ ስለሆነ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የልጆቻችሁ ስም ዕድሜ ፆታ እንዲሁም ፎቶ መቀያየር ( አድሚሽን ካርዱ) ላይ በተቀመጠው መሠረት ምንም ዓይነት ስህተት እንደሌለው እንድታረጋግጡና ስህተትም ያጋጠማችሁ ከሆነ ለትምህርት ቤቱ ቢሮ እጅግ ቢዘገይ እስከ ፊታችን ሰኞ ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም ጠዋት 3:00 ሰዓት ድረስ እንድታሳውቁ እያሣሠብን ከዚያ በኋላ ለሚመጡ ቅሬታዎች ትምህርት ቤቱ ምንም ዓይነት ሃላፊነት እንደማይወስድ አበክረን እናሣሥባለን።

የስም ስህተት ያለባችሁ የ2018 የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል እስከ ሰኞ 13/11/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ በት/ቤቱ ር/መምህር ተፈርሞ ማህተም እንዲላክ እናሳስባለን፡፡

photo content

student-roster-export (1).xlsx0.17 KB

photo content

የ2018_ዓ_ም_የክረምት_ትምህርት_ፕሮግራም.docx0.14 KB

በ 2018 ዓ.ም 6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎቻችን
+9
በ 2018 ዓ.ም 6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎቻችን

Top Scorer
Top Scorer

ለልደታ ማርያም ልጀገረዶች ትምህርት ቤት ከ9-12ኛ ክፍል የክረምት ትምህርት የ   የክረምት ትምህርት ተሳታፊ ተማሪዎች በሙሉ ትምህርቱ ሰኞ ሐምሌ 6/11/2018 ዓ.ም ስለሚጀመር ከ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ ትምህርት ቤት እንድትገኙ እናሳውቃለን የትምህርት ክፍለጊዜው የሚያበቃው 7 ሰዓት ስለሆነ ወላጆች በሰዓታቸው እንድትወስዱ እንጠይቃለን በተለየ የ 12ኛ ክፍል ተማሪ ክረምት መማር ትልቅ ሀላፊነት አለበት የክረምት ትምህርቱ ውጤታማነት የተጠናከረ አቴንዳንስ ስለሚያዝ  ሁሉም ባለድርሻ ከአሁኑ ሀላፊነቱን እንዲወስድ እንጠይቃለን፡፡

photo content

በ 2018 ዓ.ም 6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎቻችን
+9
በ 2018 ዓ.ም 6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎቻችን

Admin - Grade 6Addis Ababa Education Bureau  2018 Back Forward Result/Top Scorers Language Language Gender Gender Sight Sight Program Program Hearing Hearing Education Education Physical Impairment Physical Impairment Nationality Nationality Autism Autism Intellectual Disability Intellectual Disability School Type School Type top Get Top Scorers Clear 1  SchoolNATIVITY GIRLS' SCHOOLWoredaWoreda 1Sub CityArada Female Full Nameአሜን ተገኔ አሰፋ 95.56 Average 99.6 Percentile 573 Total 2  SchoolNATIVITY GIRLS' SCHOOLWoredaWoreda 1Sub CityArada Female Full Nameፌኔት ቦደና ሀይለጊዮርጊስ 94.03 Average 98.9 Percentile 564 Total 2  SchoolNATIVITY GIRLS' SCHOOLWoredaWoreda 1Sub CityArada Female Full Nameሜሮን ገዛኸኝ ሲሳይ 94.03 Average 98.9 Percentile 564 Total 3  SchoolNATIVITY GIRLS' SCHOOLWoredaWoreda 1Sub CityArada Female Full Nameኖሀም ጃፋ በፍቃዱ 93.75 Average 98.8 Percentile 562 Total 4  SchoolNATIVITY GIRLS' SCHOOLWoredaWoreda 1Sub CityArada Female Full Nameወንጌል ነቢያት አድማሱ 93.47 Average 98.5 Percentile 560 Total 4  SchoolNATIVITY GIRLS' SCHOOLWoredaWoreda 1Sub CityArada Female Full Nameናኦሚ ተስፋዬ ጫላ 93.47 Average 98.5 Percentile 560 Total 5  SchoolNATIVITY GIRLS' SCHOOLWoredaWoreda 1Sub CityArada Female Full Nameአብሳላት መኩሪያ ገብሬ 93.33 Average 98.4 Percentile 560 Total 6  SchoolNATIVITY GIRLS' SCHOOLWoredaWoreda 1Sub CityArada Female Full Nameኖላዊት ዮሀንስ ገመቹ 93.2 Average 98.3 Percentile 559 Total 7  SchoolNATIVITY GIRLS' SCHOOLWoredaWoreda 1Sub CityArada Female Full Nameአሜን መስፍን ዘሪሁን 93.06 Average 98.2 Percentile 558 Total 8  SchoolNATIVITY GIRLS' SCHOOLWoredaWoreda 1Sub CityArada Female Full Nameበፀሎት ግርማ ወልቀባ 92.5 Average 97.6 Percentile 555 Total Copyright © 2026 All Rights Reserved - By Qelem Meda Technologies.

በ 2018 ዓ.ም 6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች 1ኛ አሜን ተገኔ አሰፋ Average 95.56 Percentile 99.6 2ኛ ፌኔት ቦደና ሀይለጊዮርጊስ እና ሜሮን ገዛኸኝ ሲሳይ Ave.94.03 Per.98.9 3ኛ ኖሀም ጃፋ በፍቃዱ Ave.93.75 Per.98.8 4ኛ ወንጌል ነቢያት አድማሱ እና ናኦሚ ተስፋዬ ጫላ Ave.93.47 Per.98.5 5ኛ አብሳላት መኩሪያ ገብሬ Ave.93.33 Per.98.4 6ኛ ኖላዊት ዮሀንስ ገመቹ Ave.93.2 Per.98.3 7ኛ አሜን መስፍን ዘሪሁን Ave.93.06 Per.98.2 8ኛ በፀሎት ግርማ ወልቀባ Ave.92.5 Per.97.6

ሰኞ ሰኔ 29/2018ዓ.ም የልደታ ማርያም ልጃገረዶች ትምህርት ቤት ዘንድሮ በ 2018 ዓ.ም ለ 6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ( ሚኒስትሪ) ፈተና ካስፈተናቸው 223 ተማሪዎች 221 ተማሪዎች (99.1%) ተማሪዎቻችን ዛሬ ከረፈደ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በደረሰን መረጃ አረጋግጠናል። ከዚህም በመቀጠል ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ የ 6ኛ ክፍል ተማሪዎቻችንን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን