Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community
Відкрити в Telegram
1 781
Підписники
+824 години
+167 днів
+3630 день
Архів дописів
Repost from Addis Ababa Education Bureau
ፈተናው በ6 ዙር እንደሚሰጥና በማህበራዊ ሳይንስ በሶስት ዙር በተመሳሳይ በተፈጥሮ ሳይንስ ደግሞ በሶስት ዙር በመሆኑ አንድ ኮምፒዩተር ስድስት ተማሪን ያስተናግዳል ነው ያሉት።
ተማሪዎች የፈተና ስርዓቱን እንዲለማመዱና ትምህርት ቤቶች እና ወላጆች ለተፈታኝ ተማሪዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉም አስገንዝበዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በ667 የፈተና ማዕከላት እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጻል፡፡
(ግንቦት 11/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና በ667 የፈተና ማዕከላት ላይ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አሳውቋል፡፡
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) እንደገለጹት የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናን በ97 ዩኒቨርሲቲዎች እና በ570 የክልልና የከተማ አስተዳደሮች ማዕከላት ላይ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ፈተና መደበኛ ተማሪዎችን ጨምሮ በሁሉም ፕሮግራሞች በተፈጥሮ ሳይንስ 306 ሺህ 964 እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ 257 ሺህ 255 በድምሩ 564 ሺህ 219 ተማሪዎች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡
ፈተናውን በሙሉ አቅም በበይነ መረብ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ፤ በተለያዩ ምክንያቶች ቁጥራቸው አነስተኛ የሆኑ በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎች እንደሚኖሩም ጠቁመዋል።
በየክልሎች ፣ በከተማ አስተዳደሮች እና የፈተና ማዕከላት ያለው አቅም የተለያየ ቢሆንም በርካታ ኮምፒዩተሮች ለፈተና ዝግጁ እየተደረጉ እንደሚገኙ አመልክተዋል።
ከባለፈው አርብ ጀምሮ ለተፈታኞች የበይነ መረብ የሙከራ ፈተና መሰጠት መጀመሩን አንስተዋል።
Repost from Kolfe education official channel🇪🇹
ለ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና የኦንላይን ልምምድ ያድርጉ!
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ተፈታኞች ፈተና የሚለማመዱበት አድራሻ ይፋ አድርጓል።
ተፈታኞች በተደለደሉበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር ትይዩ ያለውን ሊንክ በመጠቀም፣ User Name በሚለው ላይ የፈተና አዳራሽ መግቢያ ካርድ ላይ ያለውን አድሚሽን ቁጥር በማስገባት እና Password በሚለው ላይ 1234 በማስገባት በዴስክቶፕ ኮምፒውተር፣ በላፕቶፕ፣ በታብሌት፣ በስልክ እና በመሰል የኤልክትሮኒክስ መሳሪያዎች ማንኛውንም አይነት የኢንተርኔት አማራጭ በመጠቀም ከነገ ግንቦት 07/2018 ዓ.ም ጠዋት 3፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከፈተናው ድረስ መለማመመድ እንደሚችሉ ተገልጿል።
@tikvahuniversity
ግንቦት 6/2018 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2018 የትምህርት ዘመን ለ12ኛ የሁለተኛ ሴሚስተር ከተማ አቀፍ ሞዴል ፈተና መስጫ ጊዜ ሰሌዳ ከዚህ በፊት ከግንቦት 10/2018 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሠጥ ተገልፆ የነበረ ቢሆንም በዛሬው ዕለት ፈተናው የሚሠጥበት ቀን ተቀይሮ ፈተናው ከረቡዕ ግንቦት 12/2018 ዓ.ም እስከ አርብ ግንቦት 14/2018 ዓ.ም እንደሚሠጥ እንገልፃለን።
ት/ቤቱ
ALPHA KERANYO SECONDARY SCHOOL_Geography Handhout 2nd.pdf1.35 MB
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓ.ም
@tikvahethiopia
Grade 11 Mathematics work sheet for mid exam 2018 E.C
Mathematis Second Semester Work sheet for mid exam 2018.docx0.32 KB
አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት
ለመላው የት/ቤታችን የክርስትና እምነት ተከታይ
መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣
የተማሪ ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ
ውድ የክርስትና እምነት ተከታይ የሆናችሁ የት/ቤታችን መምህራን፣ የአስተዳደር ሠራተኞች፣ የተማሪ ወላጆች፣ ተማሪዎች እንዲሁም የትምህርት ቤታችን ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ለትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ እያልን በዓሉ የሰላም፣ የጤናና የመተሳሳብ እንዲሆን እንመኛለን።
መልካም በዓል
ት/ቤቱ
Repost from Tikvah-University
#ጥቆማ
በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ እየተዘጋጁ ነው?
በትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጁ አጋዥ የትምህርት ይዘቶች እና የመለማመጃ ጥያቄዎችን የያዙ ቪዲዮዎች በድረ-ገፅ ያገኛሉ።
ይለማመዱ 👇
https://examinfo.moe.gov.et/guides
የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
@tikvahuniversity
Repost from Addis Ababa Education Bureau
12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅባቸው የትምህርት ዓይነቶችና የክፍል ደረጃዎችን ይፋ ሆኑ።
(መጋቢት 24/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅባቸውን የትምህርት ዓይነቶችና የክፍል ደረጃዎችን ይፋ አድርጓል።
በዚሁ መሠረት ፈተና የሚሰጥባቸው የትምህርት አይነቶች በተፈጥሮ ሳይንስ እንግሊዝኛ ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪና ፊዝክስ መሆናቸውን ገልጿል፡፡
በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ እንግሊዝኛ ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው።
ፈተናው በየትምህርት ዓይነቱ ከ9ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች የሚሸፍን ይሆናል።
የዝግጅት አግባቡም 9ኛ ክፍል ላይ የቀድሞውና የአዲሱ ስርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘት ላይ ያተኩራል።
ከ10ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ያለው በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ላይ የተመሠረተ ይሆናል።
የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት ሆኖ ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን የሚሸፍን መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
