cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

+251113498906

Більше
Рекламні дописи
1 154
Підписники
+124 години
+197 днів
+6430 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት      የተማሪዎች ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የነባር እና አዲስ ተማሪዎችን ምዝገባ ከሐምሌ 01/2016 ዓ.ም ጀምሮ እንደ ጀመርን ይታወቃል። በመሆኑም ምዝገባው የሚቆየው እስከ ሐምሌ 15/2016 ዓ.ም  ብቻ ስለሆነ ልጆቻችሁን ያላስመዘገባችሁ ወላጆች የምዝገባው ጊዜ ሳያልፍባችሁ እንድታስመዘግቡ ስንል በአክብሮት እንገልፃለን።                                                          ት/ቤቱ
Показати все...
አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት                 ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት   የተማሪዎች ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ                         ማስታወቂያ እንደሚታወቀው የ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ተጠናቆ ተማሪዎችም የማጠቃለያ ፈተና ወስደው ውጤታቸውንም ተመልክተው ለሚቀጥለው የትምህርት ዘመን እየተዘጋጁ እንደሆነ ይታወቃል። በ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎችም  የበለጠ ጠንክረው እንዲሠሩ በሌሎች ተማሪዎች ላይም  መነሳሳትን እንዲፈጥር ትምህርት ቤታችንም ለተማሪዎቹ ለሚቀጥለው የትምህርት ዘመን ከነፃ የትምህርት ዕድል ከመስጠት  አንስቶ እንደ የደረጃቸው የተለያዩ  የማበረታቻ ሽልማቶችን ያበረከተ ሲሆን ከፍተኛ ውጤት ያመጡ የተወሰኑትን ተማሪዎችንም በምስል (በፎቶ) እንደሚከተለው አያይዘን አቅርበናል።                                                                ት/ቤቱ
Показати все...
አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት                 ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት   የተማሪዎች ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ                         ማስታወቂያ እንደሚታወቀው የ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ተጠናቆ ተማሪዎችም የማጠቃለያ ፈተና ወስደው ውጤታቸውንም ተመልክተው ለሚቀጥለው የትምህርት ዘመን እየተዘጋጁ እንደሆነ ይታወቃል። በ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎችም  የበለጠ ጠንክረው እንዲሠሩ በሌሎች ተማሪዎች ላይም  መነሳሳትን እንዲፈጥር ትምህርት ቤታችንም ለተማሪዎቹ ለሚቀጥለው የትምህርት ዘመን ከነፃ የትምህርት ዕድል ከመስጠት  አንስቶ እንደ የደረጃቸው የተለያዩ  የማበረታቻ ሽልማቶችን ያበረከተ ሲሆን ከፍተኛ ውጤት ያመጡ የተወሰኑትን ተማሪዎችንም በምስል (በፎቶ) እንደሚከተለው አያይዘን አቅርበናል።                                                                ት/ቤቱ
Показати все...
አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት                 ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ (Social Science) የተማሪዎች ወላጆች  በሙሉ                                ማስታወቂያ የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ሀገር አቀፍ ፈተና ዛሬ የሚጠናቀቅ ሲሆን ተማሪዎችም በዛሬው ዕለት ወደ ቤት የሚመለሱ ይሆናል። በመሆኑም ወላጆች ከምሽቱ 12:30 ጀምሮ በትምህርት ቤታችን ግቢ በመገኘት ልጆቻችንን መውሰድ እንደምትችሉ በአክብሮት እንገልፃለን።                                                                ት/ቤቱ
Показати все...
አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት                 ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ (Social Science) የተማሪዎች ወላጆች በሙሉ                                ማስታወቂያ የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ሀገር አቀፍ ፈተና ከማክሰኞ ሐምሌ 09/2016 ዓ.ም እስከ ሐሙስ 11/2016  ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል። በመሆኑም የትምህርት ቤታችን የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት   ተፈታኞች እሁድ  ማለትም  07/11/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ሠዓት ወደ  ተመደባቹበት  የፈተና ጣቢያ    ማለትም  ወደ አዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ  ዋና ግቢ ጉዞ የሚደረግ በመሆኑ ተማሪዎች  በተጠቀሰው ሠዓት እንድትገኙ እናሳስባለን። ማሳሰቢያየትምህርት ቤቱን የደንብ ልብስ (Uniform) መልበስ   ይኖርባችኋል። ፨ አድሚሽን ካርድ እና የትምህርት ቤቱን መታወቂያ መያዝ ይኖርባችኋል። ፨ በዕለቱ በማርፈድ ወይም በመቅረት ለሚፈጠረው ክፍተት  ትምህርት ቤቱ ኃላፊነት አይወስድም።                                                                ት/ቤቱ
Показати все...
አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት                 ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ (Natural Science) የተማሪዎች ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ ማስታወቂያ የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ሀገር አቀፍ ፈተና ከማክሰኞ ሐምሌ 09/2016 ዓ.ም እስከ ሐሙስ 11/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል። በመሆኑም የትምህርት ቤታችን የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት   ተፈታኞች እሁድ  ማለትም 07/11/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ሠዓት ወደ ተመደባቹበት  የፈተና ጣቢያ    ማለትም  ወደ አዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ  ዋና ግቢ ጉዞ የሚደረግ በመሆኑ ተማሪዎች በተጠቀሰው ሠዓት እንድትገኙ እናሳስባለን። ማሳሰቢያ በዕለቱ በማርፈድ ወይም በመቅረት ለሚፈጠረው ክፍተት ትምህርት ቤቱ ኃላፊነት አይወስድም። ት/ቤቱ
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት  ለመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪ ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ የ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ትምህርት ተጠናቆ የማጠቃለያ ፈተና መሠጠቱ ይታወቃል።  በመሆኑም የተማሪዎች የውጤት መግለጫ ሪፖርት ካርድ የሚሠጠው ነገ እሁድ ማለትም በቀን 30/10/2016 ዓ.ም ስለሆነ የተከበራችሁ የተማሪ ወላጆች እንዲሁም ህጋዊ አሳዳጊዎች በዕለቱ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በትምህርት ቤቱ አዳራሽ በመገኘት የልጆቻችሁን የትምህርት ውጤት መግለጫ ሪፖርት ካርድ እንድትወስዱ በአክብሮት እንጋብዛለን።                                                                ት/ቤቱ
Показати все...
አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት                     ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል የተማሪዎች ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ ነገ አርብ እና ከነገ ወዲያ ቅዳሜ ማለትም በቀን 28/10/2016 ዓ.ም እና በ29/10/2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና በኦን ላይን የሚሠጥ በመሆኑ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በዕለቱ በመገኘት ፈተናውን እንድትወስዱ እንገልፃለን። የሞዴል ፈተናው ፕሮግራም እንደሚከተለው ይሆናል፡፡ ፨ ማህበራዊ ሳይንስ (Social Science) ጠዋት      2፡30  - 5፡30 ፨ አርብ         እንግሊዘኛ          ፨ ቅዳሜ       ሒሳብ ፨ የተፈጥሮ ሳይንስ (Natural Science)  ከሰዓት     7፡00 እስከ 10፡00  ይሆናል። ፨ አርብ         እንግሊዘኛ ፨ ቅዳሜ       ሒሳብ ማሳሰቢያ በዕለቱ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ስትመጡ: - ፨ የትምህርት ቤቱን ሙሉ የደንብ ልብስ (ዩኒፎርም) ብቻ አድርጋችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን። ፨ የትምህርት ቤቱን መታወቂያ እንዲሁም አድሚሽን ካርድ መያዝ እንደሚኖርባችሁ እናሳስባለን። ፨ የትምህርት ቤቱን የደንብ ልብስ  (ዩኒፎርም) ሳይለብስ እንዲሁም የትምህርት ቤቱን መታወቂያ እና አድሚሽን ካርድ ያልያዘ ተማሪ ወደ ትምህርት ቤቱ ግቢ እንደማይገባ እንገልፃለን።                                                                ት/ቤቱ
Показати все...
አልፋ ቀራንዮ አፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት                     ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል የተማሪዎች ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ ነገ ማለትም በቀን 25/10/2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና በኦን ላይን የሚሠጥ በመሆኑ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በዕለቱ በመገኘት ፈተናውን እንድትወስዱ እንገልፃለን። የሞዴል ፈተናው ፕሮግራም እንደሚከተለው ይሆናል፡፡ ፨ ማህበራዊ ሳይንስ (Social Science) ጠዋት 2፡30  - 5፡30 ፨ የተፈጥሮ ሳይንስ (Natural Science)  ከሰዓት 7፡00 እስከ 10፡00 ይሆናል። ማሳሰቢያ በዕለቱ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ስትመጡ: - ፨ የትምህርት ቤቱን ሙሉ የደንብ ልብስ (ዩኒፎርም) ብቻ አድርጋችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን። ፨ የትምህርት ቤቱን መታወቂያም እንዲሁም አድሚሽን ካርድ መያዝ እንደሚኖርባችሁ እናሳስባለን። ፨ የትምህርት ቤቱን የደንብ ልብስ  (ዩኒፎርም) ሳይለብስ እንዲሁም የትምህርት ቤቱን መታወቂያ እና አድሚሽን ካርድ ያልያዘ ተማሪ ወደ ትምህርት ቤቱ ግቢ እንደማይገባ እንገልፃለን።                                                                ት/ቤቱ
Показати все...
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.