2 106
Підписники
+224 години
-17 днів
-530 день
Архів дописів
2 106
ቀን:- 03/10/2018 ዓ.ም
ለ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ
ነገ ሐሙስ ሰኔ 04 ቀን በትግል ለነፃነት ትምህርት ቤት በሚሰጠው ክልላዊ ፈተና ዙሪያ ወሳኝ የኦረንቴሽን (የማስተዋወቂያ) መርሃ-ግብር ተዘጋጅቷል። በመሆኑም ሁላችሁም የትምህርት ቤቱን ደንብ ልብስ በመልበስ ከጠዋቱ 1:30 ላይ በለምለም ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ እንድትገኙ እናሳውቃለን።
የኦረንቴሽን ሰዓት፦
📌ለ6ኛ ክፍል፦ ከጠዋቱ 1:30 እስከ 5:00 ሰዓት
📌 ለ8ኛ ክፍል፦ ከጠዋቱ 1:30 እስከ 7:00 ሰዓት
⚠️ ማሳሰቢያ፦
በዕለቱ ምንም ዓይነት የመማሪያ ቁሳቁስም ሆነ ምሳ ይዞ መምጣት አይፈቀድም።
2 106
ቀን፦02/10/2018 ዓ.ም
አስቸኳይ ማሳሰቢያ ለተማሪ ወላጆች/አሳዳጊዎች በሙሉ
በቅድሚያ የተከበረ ሰላምታችንን እያቀረብን፤ እንደማንኛውም የትምህርት ዘመን የሰኔ ወር የበጀት መዝጊያ በመሆኑ ተቋማዊ ስራዎቻችንን በወቅቱ ማጠናቀቅ ይኖርብናል።
በመሆኑም፦
✅ ክፍያ ላጠናቀቃችሁ፦የተማሪዎችን የትምህርት ክፍያ እስከ ሰኔ ወር ድረስ ቀድማችሁ ላጠናቀቃችሁ ወላጆች በሙሉ የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
📌 ውዝፍ ክፍያ ላለባችሁ፦እስካሁን የተማሪዎች ክፍያ ውዝፍ ያለባችሁ ወላጆች፣ የበጀት ዓመቱ ከመዘጋቱ በፊት እስከ ሰኔ 10/2018 ዓ.ም ድረስ ሂሳባችሁን እንድታወራርዱ እናሳስባለን።
ይህንን በማድረግ ስራችን የተሳለጠ እና የተቀላጠፈ እንዲሆን ከጎናችን እንድትሆኑ ከወዲሁ በትህትና እንጠይቃለን።
ከአክብሮት ሰላምታ ጋር፤ትምህርት ቤቱ
2 106
ቀን:- 21/09/18
ለወላጆች በሙሉ
ከት/ት ፅህፈት ቤት በደረሰን መረጃ መሰረት
✅ሰኞ ግንቦት 24/2018 ብሔራዊ ምርጫ ስለሆነ ት/ት የለም!!
✅ከማክሰኞ -ረዕቡ(ግንቦት 25 እና 26) የፈተና የቅድመ ዝግጅት ስራ ስለሚሰራ ት/ት አይኖርም!
✅ሐሙስ ግንቦት 27/2018 መደበኛ ት/ት ይኖራል!
2 106
+1
ቀን:-13/09/18
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡
✅ በዚህ መሰረትም ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ሰኔ 8 ፣ 9 እና 10/2018 ዓ.ም
✅ እንዲሁም የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚሰጥ ይሆናል፡፡
2 106
+1
✔️በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ እና የ6ኛ ክፍል የሁለተኛ ሴሚስተር ከተማ አቀፍ ሞዴል ፈተና መስጫ ጊዜ ሰሌዳ
2 106
ቀን፦ 04/09/2018 ዓ.ም
ለ6ኛ ክፍል ተማሪዎች እና ወላጆች በሙሉ
የ6ኛ ክፍል የክልል ፈተና አድሚሽን ካርድ (Admission Card) ተዘጋጅቶ መጠናቀቁን እንገልጻለን። በመሆኑም በካርዱ ላይ (ከታች የተቀመጠውን መረጃ በመክፈት ) ማንኛውም ዓይነት የፊደል ግድፈትም ሆነ የመረጃ ስህተት ያለባችሁ ተማሪዎች፣ ረቡዕ 05/09/2018 ዓ.ም እስከ ቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ ከወላጅ ጋር በመምጣት እንድታስተካክሉ እናሳስባለን።
ማሳሰቢያ፦
📌 የእድሜ ስህተት ያለባችሁ ተማሪዎች የልደት ሰርተፍኬት ይዛችሁ መምጣት ይኖርባችኋል።
📌 ከተጠቀሰው ቀን እና ሰዓት በኋላ ለሚመጡ ተማሪዎች ትምህርት ቤቱ ኃላፊነት የማይወስድ መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን።
ከአክብሮት ሰላምታ ጋር!
2 106
ቀን:-02/09/18
እናት በፈተናዎች መካከል ለልጆቿ ተስፋ የምትሆን፣ በትጋቷም ቤትን የምታቆም ብርቱ ኃይል ናት።
ለአገር ሰላም፣ ለቤተሰብ ደስታና ለትውልድ ዕድገት ሌት ተቀን ለሚደክሙ እናቶች ሁሉ ያለንን ጥልቅ አክብሮትና ምስጋና እንገልጻለን። እናቶች የሕይወት ብርሃን፣ የልባችን ሰላም ናቸው።
ዛሬም ሆነ ሁሌም እናቶችን እናከብራለን!
መልካም የእናቶች ቀን!
2 106
የእገዛ ጥሪ ከለምለም ትምህርት ቤት ለመቄዶንያ!
ቀን፦ ሚያዝያ 30፣ 2018 ዓ.ም
ዛሬ ምሽት 12፡00 ጀምሮ ከለምለም ትምህርት ቤት የሚተላለፈውን ልዩ ዝግጅት በመቄዶንያ ዩትዩብ (Macedonia YouTube) ገጽ ላይ በቀጥታ ይከታተሉ።
ምን ማድረግ ይጠበቅብዎታል?
ሰብስክራይብ ያድርጉ፦ ይህንን ሊንክ www.youtube.com/@Mekedonia በመጫን የዩትዩብ ቻናሉን ሰብስክራይብ (Subscribe) ያድርጉ።
ላይክ ያድርጉ፦ ቪዲዮውን ላይክ (Like) በማድረግ ተደራሽነቱን ያግዙ።
አስተያየት ይጻፉ፦ በኮሜንት መስጫው ላይ ስማችሁንና ክፍላችሁን በመጥቀስ፣ ለመቄዶንያ ያላችሁን ድጋፍ ግለጹ።
የልገሳ መረጃ
ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር ድጋፍ ለማድረግ በለምለም ትምህርት ቤት ስም የተከፈተ የባንክ ሂሳብ ቁጥር፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
የሂሳብ ቁጥር፦ 1000750458557
(በአቶ መስፍን ደስታ እና በአቶ ሙሉሰው ሙንዬ ስም የተከፈተ)
"አሁኑኑ በመርዳት የክፉ ቀን ደራሽ እንሁን!"
በነዚህ ስልክ ቁጥሮች ይደውሉ፦
📞 0989898989
📞 0979797979
ለምለም ትምህርት ቤት!
2 106
ቀን፡- 30/08/2018 ዓ.ም
ለተማሪዎችና ለወላጆች በሙሉ
ጉዳዩ፡- የመቄዶንያ የኦንላይን መርሃ-ግብር መራዘምን ስለማሳወቅ
ነገ ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው የመቄዶንያ የኦንላይን ገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ሚቀጥለው ሳምንት የተዛወረ መሆኑን በአክብሮት እንገልጻለን።
መርሃ-ግብሩ የተላለፈባቸው ዋና ዋና ምክንያቶች፦
✅ ጥራትን ለማረጋገጥ፡- ለፕሮግራሙ ይበልጥ የተሻለና የተሟላ ዝግጅት በማድረግ ስራውን ውጤታማ ለማድረግ፤
✅ የወላጅንና የተማሪዎችን ጥያቄ በማክበር፡- ከበርካታ ተማሪዎች የቀረበውን “የዝግጅት ጊዜ ይራዘምልን” የሚል ጥያቄ ተቀባይነት በማግኘቱ ነው።
በመሆኑም፣ ከነገ ጀምሮ ፕሮግራሙ ዓላማውን ከግብ እንዲያደርስና ይበልጥ የተዋጣለት እንዲሆን አስፈላጊውን ቅድመ-ዝግጅት አጠናክረን የምንቀጥል መሆኑን እናሳውቃለን።
ትክክለኛውን ቀንና ሰዓት በቅርቡ የምናሳውቅ መሆኑን እየገለጽን፣ ላጋጠመው የጊዜ ለውጥ ይቅርታ እንጠይቃለን።
ከልባዊ ሰላምታ ጋር!
2 106
ቀን፡- 27/08/2018 ዓ. ም
🏠 ለለምለም ከ1ኛ - 3ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች
📝 አርብ ሚያዝያ 30/2018 ዓ.ም እና ሰኞ ግንቦት 03/2018 ዓ.ም ከ1ኛ - 3ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የሁለተኛው መንፈቅ ዓመት ሁለተኛ ሙከራ ስለሚሰጥ በቤት ውስጥ እገዛ እንድታደርጉላቸው በአክብሮት እናሳውቃለን።
📌 አርብ 30/09/18
✅ አማርኛ
✅ ሒሳብ
✅ አካባቢ ሳይንስ
✅ አፋን ኦሮሞ ( ለ3ኛ ክፍል)
📌 ሰኞ 03/09/18
✅ English
✅ ክ.እ.ጥ
✅ ግብረ - ገብ
✅ ጤ.ሴ.ማ
👉 ማሳሰቢያ :- ሙከራው የሚሰጠው ለሙሉቀን በት/ት ሰአት ይሆናል።
ት/ት ቤቱ
2 106
እንኳን ለ85ኛው የዐርበኞች የድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ ደምና አጥንት ነፃነቷን አስከብራ የኖረች ኩሩ ሀገር ናት። ይህ የድል ቀን የታሪካችን አሻራ፣ የነፃነታችን ምስክር ነው።
ክብር ለሀገር መስዋዕት ለሆኑ አርበኞቻችን!
2 106
ቀን:- 24/08/18
የቅንነትና የበጎ ተግባር ጥሪ!
ለለምለም ትምህርት ቤት ወላጆች በሙሉ
የመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከልን ለመርዳትና ለመደገፍ ትምህርት ቤታችን ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አዘጋጅቷል።
የእርዳታ እጃችንን በመዘርጋት የአረጋውያኑን እንባ የምናብስበት ይህ የልዩ የበጎ አድራጎት የቀጥታ ስርጭት (Online Stream) http://www.youtube.com/@Mekedonia Live በመግባትና Subscrib በማድረግ እንዲሁም በቀጥታ ስርጭቱ ላይ ስልክ በመደወል መሳተፍ ይቻላል።
መርሃ ግብር የሚካሄድበት ቀን እና ሰዓት፦
📌ቀን፦ ዓርብ፣ ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም.
📌ሰዓት፦ ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ
📌አድራሻ፦ በዩቲዩብ (YouTube) ቀጥታ ስርጭት
✅ እንዴት መሳተፍና መርዳት ይቻላል?
በቀጥታ ስርጭቱ ላይ ስልክ በመደወል የሚከተሉትን አማራጮች በመጠቀም ድጋፍ ማድረግ ይችላሉ፦
1. በልጅዎ፣ በእህትዎ ወይም በወንድምዎ ስም ቃል በመግባት፤
2. በራስዎ ስም ፤
3.በትምህርት ቤታችን ስም፤ ወይም
4. በሚወዱት ሰው ( መምህር) ስም የቻሉትን ያህል የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ ይችላሉ።
✅ ቀጥታ የባንክ ድጋፍ ለማድረግ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000750458557
(ለምለም ት/ት ቤት በመቄዶንያ ስም የተከፈተ የባንክ ሂሳብ)
☎️ ለመደወል፦
0979797979 / 0989898989 / 0949494949
"ርህራሄ ለሌላው የሚሰጥ ትልቁ ስጦታ ነው!"
አብረን በመሆን የአረጋውያንን ህይወት
እናድስ። የእርስዎ ትንሽ እርዳታ ለሌሎች ትልቅ ተስፋ ነው!
ለምለም ትምህርት ቤት
ለላቀ የትምህርት ጥራት እንተጋለን!
2 106
ቀን፡ 23/08/2018 ዓ.ም
"ሥራ የሰው ልጅ መለያ፣ የእድገትም መሠረት ነው። የትምህርት ቤታችንን ራዕይ ለማሳካት ሌት ተቀን ለምትደክሙ የትምህርት ቤታችን ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ለዓለም አቀፍ የሰራተኞች ቀን በሰላም አደረሳችሁ እያልን፤ ለምታደርጉት ጥረት ምስጋናችንን እናቀርባለን።"
2 106
ቀን፦ 10/08/2018 ዓ.ም
ለለምለም አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ወላጆች በሙሉ፤
የ2018 ዓ.ም የሁለተኛው መንፈቅ ዓመት የአጋማሽ - 2 (Mid-Exam - 2) ፈተና ከሰኞ ሚያዝያ 12/2018 ዓ.ም እስከ ረቡዕ ሚያዝያ 14/2018 ዓ.ም ድረስ የሚሰጥ መሆኑን እናሳውቃለን።
⏰ የትምህርት ቤት መግቢያና መውጫ ሰዓት፦
* የጠዋት ፈረቃ፦ መግቢያ ከጠዋቱ 1:30 – 2:00 ሰዓት
መውጫ - 4:30
* የከሰዓት ፈረቃ፦መግቢያ ከቀኑ 6:30 – 6:45 ሰዓት
መውጫ - 9:00
✅ ከተማሪዎች የሚጠበቁ ነገሮች፦
* ለፈተና የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን (እስኪብርቶ፣ እርሳስ፣ ማጥፊያ እና መቅረጫ) ማሟላት።
* የትምህርት ቤቱን ዩኒፎርም በአግባቡ ለብሶ መገኘት።
❌ ይዞ መግባት በጥብቅ የተከለከሉ ነገሮች፦
* ማንኛውም ዓይነት ደብተር፣ መጽሐፍ፣ ወረቀት እና ሌሎች ተያያዥ ቁሳቁሶች።
‼️ ለአፈታተን ሥርዓቱ የወጡ ጥብቅ ማሳሰቢያዎች
* የመግቢያ ሰዓት፦ ፈተና ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በኋላ ወደ መፈተኛ ክፍል መግባት አይፈቀድም።
* የግቢ ደንብ፦ ከላይ ከተጠቀሰው የመግቢያ ሰዓት ቀድሞ መገኘትም ሆነ ፈተና እንደተጠናቀቀ በትምህርት ቤቱ ግቢ ውስጥም ሆነ በበሩ አካባቢ መቆየት ፈጽሞ የተከለከለ ነው።
* የሥነ-ምግባር መመሪያ፦ መኮረጅ፣ ማስኮረጅ ወይም የፈተናውን ሂደት ማወክ ካስመዘገቡት ውጤት ላይ ከፍተኛ ቅጣት የሚያስከትል ይሆናል።
* የፈተና ጊዜ አጠቃቀም፦ የተሰጠውን የፈተና ሰዓት በአግባቡ ሳይጠቀሙ ከፈተና ክፍል ቀድሞ መውጣት አይቻልም።
📅 የፈተና መጀመሪያ ሰዓት፦
* የጠዋት ፈተና (ከጠዋቱ 2:30 ሰዓት)፦ ለክፍል 4፣ 5 እና 7 ተማሪዎች።
* የከሰዓት ፈተና (ከቀኑ 7:00 ሰዓት)፦ ለክፍል 6 እና 8 ተማሪዎች።
መልካም የፈተና ጊዜ ይሁንላችሁ!
ትምህርት ቤቱ
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
