2 255
Obunachilar
+624 soatlar
+307 kunlar
+3730 kunlar
Postlar arxiv
2 256
ቀን:-09/11/18
👉 ለነባር ተማሪ ወላጆች በሙሉ
ነገ ማለትም አርብ ሐምሌ 10/18 በ12ኛ ክፍሎች ፈተና ምክንያት ምዝገባ የማይኖር መሆኑን እየገለጽን ሰኞ ግን ምዝገባው የሚቀጥል መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።
2 256
የምዝገባ ጥሪ ማስታወቂያ
ቀን፦ 08/11/2018 ዓ.ም
ለለምለም አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ወላጆች/አሳዳጊዎች በሙሉ፤
ትምህርት ቤታችን ለ2019 የትምህርት ዘመን የአዲስና የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ነገ ሐምሌ 09 ቀን 2018 ዓ.ም መጀመሩን እያበሰረ፣ ወላጆች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች በማሟላት በተጠቀሰው ጊዜ እንድትመዘግቡ በአክብሮት ያሳስባል።
✅ 1. ለአዲስ ተመዝጋቢ ተማሪዎች የሚፈለጉ ሰነዶች፦
📌 የክትባት የምስክር ወረቀት (ኮፒ)
📌 የመሸኛ/የመልቀቂያ ደብዳቤ (ከተማሩበት የቀድሞ ትምህርት ቤት)
📌 የልደት የምስክር ወረቀት (ኮፒ)
📌 የተማሪው የውጤት መግለጫ (ሪፖርት ካርድ) (ኮፒ)
ማሳሰቢያ፦ ከ6ኛ ክፍል ወደ 7ኛ ክፍል ለሚዘዋወሩ ተማሪዎች የክልላዊ ፈተና (ሚኒስትሪ) ውጤት መግለጫ ካርድ ኮፒ መያዝ ግዴታ ነው።
📌 ሁለት (2) ባለ 3 በ 4 መጠን የተማሪው ወቅታዊ ፎቶግራፍ
📌 አንድ (1) ባለ 3 በ4 መጠን የወላጅ/የአሳዳጊ ፎቶግራፍ
📌 አንድ (1) ክላሰር (ሰነድ መያዣ)
✅ 2. ለነባር ተማሪዎች የሚፈለጉ ሰነዶች፦
👉 የ2018 ዓ.ም የውጤት መግለጫ (ሪፖርት ካርድ)
👉አንድ (1) ባለ 3 በ 4 መጠን የተማሪው ወቅታዊ ፎቶግራፍ
‼️ መመዝገቢያ ቦታ :- በአንደኛ ደረጃ ት/ት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ
⏰ መመዝገቢያ ሰዓት :- ከጠዋቱ 2:30 - ቀኑ 10:00
